ru
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

Открыть в Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

Больше
637
Подписчики
Нет данных24 часа
-37 дней
-1230 день
Архив постов
                              ✝ ✝ ✝ 🌹 #ሐዲስ_ቅዱስ_መርቆሬዎስና_ወንድሙ_ቅዱስ_ዮሐንስ፡- እነዚህም ቅዱሳን የደጋግ ክርስቲያን ልጆች ናቸው፡፡ የታላቁ ስም ሙናሂ ነበር ሲመነኩስ ግን መርቆሬዎስ ተባለ፡፡ የታናሹም ስም አቡፈረዥ ነበር እርሱም ሲመነኩስ ዮሐንስ ተባለ፡፡ ሁለቱም ወንድማማቾች ወደ ሊቀ ሠራዊት ቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም ገብተው ጽኑ የሆነ ተጋድሎአቸውን ጀመሩ፡፡ ለመነኰሳቱ ሁሉ የሚላላኩና የሚያገለግሉ ሆኑ፡፡ ጣዕም ካላቸው ምግቦችና መጠጦች እንዲሁም ከእንቅልፍ እርቀው በታላቅ ተጋድሎ ኖሩ፡፡ የሚመገቡትም በሦስት ቀን አንድ ጊዜ ሆነ፡፡ የግብፅንና የሌላውንም ጽሕፈት ተምረው መጻሕፍትን መረመሩ፡፡ እነዚህም ወንድማማቾች አንድ ቀን አብረው ሳሉ የታዘዘ መልአክ ተገለጠላቸውና ወደ ምስክርነት አደባባይ ሄደው ስለጌታችን ስለ ስሙ እንዲመሰክሩና ሰማዕትነታቸውን እንዲፈጽሙ ነገራቸው፡፡ 🌹 እነርሱም እንደታዘዙት በከሃዲው መኰንን ፊት ሄደው ስለ ጌታችን ክብር መሰከሩ፡፡ መኰንኑም የተለያዩ ጽኑ ሥቃዮችን አሠቃያቸው፡፡ ከብዙ ሥቃይም በኋላ በወህኒ ቤት ተጥለው ሳለ ሌላ መኰንን ተሹሞ እርሱም ሊተዋቸው በወደደ ጊዜ የአገሩ ሰዎች "እነርሱን ካልገደልካቸው በንጉሡ ዘንድ እንከስሃለን" አሉት፡፡ ይህም መኰንን ሕዝቡን ከመፍራቱ የተነሣ ፈቃዳቸውን ይፈጽምላቸው ዘንድ አሳልፎ ሰጣቸው፡፡ ሕዝቡም ኅዳር 7 ቀን ሐዲስ የተባለ የቅዱስ መርቆሬዎስንና የወንድሙ የቅዱስ ዮሐንስን ራስ በሰይፍ ከቆረጧቸው በኋላ የሰማዕትነት ፍጻሜአቸው ሆነ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                              ✝ ✝ ✝ 🌹 #ቅድስት_ዘኖብያ እና ልጇ ቅዱስ ዘኖቢስ፡- እነዚህም ቅዱሳን ተበይስ ከምትብል አገር ከታላላቅ ወገኖች የተገኙ ሰማዕታት ናቸው፡፡ እነርሱም ክርስቲያኖች እንደሆኑ በከሃዲው ንጉሥ ዘንድ ዜናቸው ተሰማ፡፡ ንጉሡም ወደ እርሱ ካስመጣቸው በኋላ እምነታቸውን መረመራቸው፡፡ እነርሱም "አገራችን ተበይስ ነው የምናመልከውም የክብርን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ነው" አሉት፡፡ ✝ ከዚህም በኋላ ንጉሡ እናትና ልጅን "ለአማልክት ሠው" አላቸው፡፡ ቅዱሳኑም "እኛስ ለእውነተኛው አምላክ ለክርስቶስ እንሠዋለን እንጂ ለረከሱ ጣዖታት አንሠዋም" አሉት፡፡ ንጉሡም በዚህ ጊዜ እጅግ ተቆጥቶ ቅድስት ዘኖብያንና ልጇን ቅዱስ ዘኖቢስን ጽኑ በሆነ ሥቃይ አሠቃያቸው፡፡ ልብሳቸውን ገፈው በራሳቸው ጸጉር ተቅለው እየደበደቡ እንዲያሠቃዩአቸው አደረገ፡፡ ቅዱሳኑም ወደ እግዚአብሔር በጸለዩ ጊዜ ማሰሪያው በተአምራት ተፈታላቸው፡፡ የብርሃን ልብሶችንም ለብሰው ሕዝቡ ሁሉ አዩአቸው፡፡ ይህንንም ባዩ ጊዜ "የእነዚህ ቀዱሳን አምላካቸው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ይክበር ይመስገን እኛም በአምላካቸው አምነናል" እያሉ ጮኹ፡፡ ንጉሡም በታላቅ ቁጣ ሆኖ እናትና ልጅን እርስ በእርስ እንዲተያዩ አድርጎ በሁለት መስቀሎች ላይ እርቃናቸውን ሰቀላቸው፡፡ በዚያን ጊዜም ደመና መጥታ ሸፈነቻቸው፡፡ በዚህም ጊዜ ብዙዎች በጌታችን አመኑ፡፡ 🌹 ዳግመኛም ንጉሡ ቅድስት ዘኖብያንና ልጇን ቅዱስ ዘኖቢስን በብረት ወንበሮች ላይ አስሮ በማስቀመጥ ከሥር በሚነድ እሳት አቃጠላቸው፡፡ ጌታችንም ከዚህ ሥቃይ አዳናቸው፡፡ በወንበሩም ላይ ሆነው በእሳት እየተቃጠሉ ሳለ ሕዝቡን ያስተምሩ ጀመር፡፡ ንጉሡም ይህንን ባየጊዜ እጅግ ተቆጥቶ ቁመቱና ጎኑ ሃያ ሃያ ክንድ የሆነ ጉድጓድ ቆፍረው በውስጡም እሳትን እንዲያነዱበትና ቅዱሳኑን ከዚያ እንጨምሯቸው አደረገ፡፡ ነገር ግን አሁንም ቅድስት ዘኖብያንና ልጇን ቅዱስ ዘኖቢስን ወደ እግዚአብሔር በጸለዩ ጊዜ እሳቱ ፈጥኖ ጠፋ፡፡ ንጉሡም ከዚህ በኋላ ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ በሰይፍ አንገታቸውን ቆርጠው እንገድሏቸውና እስከ ነገ ድረስ በድናቸውን ጠብቀው በእሳት እንዲያቃጥሉአቸው በነፋስም ውስጥ እንዲበትኑአቸው አዘዘ፡፡ ቅዱሳኑንም በገደሏቸው ጊዜ ነጎድጓድ መብረቅ ንውጽውጽታ ሆነ፣ ዝናብም ዘነበ፡፡ በዚህም ታላቅ ንውጽውጽታ ምክንያት 54 ሰዎች ሞቱ፡፡ በሌሊትም ምእመናን መጥተው የቅሱሳኑን ሥጋ በሥውር ወስደው ቀበሯቸው፡፡ በማግሥቱም ንጉሡ በድናቸውን በፈለገ የሆነውን ሁሉ ተረዳ፡፡ የሆነውን ሁሉ ባስተዋለ ጊዜ ዐይነ ልቡናው በራለትና በጌታችን አምኖ ንስሓ ገብቶ ተጠመቀ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                              ✝ ✝ ✝ 🌹 #ሰማዕቱ_አባ_ናህርው፡- ይኸውም ቅዱስ ከግብጽ አገር ከፍዩም መንደር የተገኘ ታላቅ ሰማዕት ነው፡፡ ይኸውም ቅዱስ ፈሪሃ እግዚአብሔር በእጅጉ ያደረበት ደገኛ ክርስቲያን ነው፡፡ በእስክንድርያ አገር በከሃዲያን መኳንንት የሚሠቃዩትንና የሚሞቱትን የክርስቲያኖቹን ዜና በሰማ ጊዜ ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይሁንና ስለ ጌታችን ስለ ስሙ ሰማዕት ይሆን ዘንድ ተመኘ፣ የሰማዕትነት ክብርንም ይቀዳጅ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፡፡ እግዚአብሔር ጸሎቱን ሰማውና በራእይ ተገልጦለት "ወደ አንጾኪያ አገር ሂድ በዚያ በሰማዕትነት ትሞት ዘንድ አለህ" አለው፡፡  🌹 አባ ናህርው ከዚህ በኋላ ወደዚያ እንዴት መድረስ እችላለሁ ብሎ ሲያስብ እግዚአብሔር ቅዱስ ሚካኤልን ላከለትና መልአኩ ይህንን ቅዱስ በክንፎቹ ተሸክሞ ወደ አንጾኪያ አገር አደረሰው፡፡ አንጾኪያ አገር ላይ ያለው ንጉሥ ደግሞ እጅግ ጨካኝ የሆነው የክርስቲያኖችን ደም በዓለም ዙሪያ ያፈስ የነበረው ዲዮቅልጥያኖስ ነበር፡፡ እናም አባ ናህርው በከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ፊት በደረሰ ጊዜ የእግዚአብሔር ክብር መሰከረ፡፡ ንጉሡም ስሙንና አገሩን ጠየቀው፡፡ እርሱም ከግብጽ አገር እንደሆነ አስረዳው፡፡ ንጉሡም ቃሉን ከሰማ በኋላ ለጣዖታቱ ቢሠዋለት ብዙ ገንዘብና ሥልጣን እንደሚሰጠው ቃል ገባለት፡፡ ነገር ግን አባ ናህርው በጌታችን ታመነ፡፡ ንጉሡም "ትእዛዜን አልሰማም ካልክ አሠቃይቼ ለሞት እዳርግሃለሁ" እያለ በተደጋጋሚ ቢናገረውም አባ ናህርው ግን ከሥቃዩ የተነሣ አልፈራም፡፡ 🌹 ከዚህም በኋላ ንጉሡ ቅዱስ አባ ናህርውን በብዙ ዓይነት ሥቃዮች እንዲያሠቃዩት አደረገው፡፡ በእሳት ውስጥ ቢጨምሩት ረድኤተ እግዚአብሔር ጠብቆት ምንም ሳይቃጠል ቀረ፡፡ ዳግመኛም ለተራቡ አንበሶች ቢሰጡት አንበሶቹም ምንም ሳይነኩት ቀሩ፡፡ በሌላም ጊዜ በትልቅ ወጪት አድርገው በእሳት ቀቀሉት ነገር ግን አሁንም ምንም አልሆነም፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ አባ ናህርውን ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ በዚህች ዕለት አንገቱን በሰይፍ አስቆረጠውና የቅዱስ አባታችን የሰማዕትነት ፍጻሜአቸው ሆነ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።  ምንጭ፦ የኅዳር 7 ስንክሳርና መዝገበ ቅዱሳን።                                                        ✝ ✝ ✝ 🌹 #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "መንክር እግዚአብሔር በላዕለ ቅዱሳኒሁ። አምላከ እስራኤል ውእቱ ይሁብ ኃይለ ወፅንዐ ለሕዝቡ። ወይትባረክ እግዚአብሔር"። መዝ 67፥35 ወይም መዝ 78፥10-11 የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 1 4፥1-15 ወይም ማቴ 10፥16-ፍ.ም።               

🌹 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹           🌹 #ኅዳር ፯ (7) ቀን። 🌹 እንኳን #ለሰማዕታት_አለቃ_ለታላቁ_መስተጋድል #ለቅዱስ_ጊዮርጊስ_በልዳ_አገር (በዓለም ላይ) #ቤተ_ክርስቲያን_ለከበረችበት፤ ጌታችን በውስጧ ላደረገው ድንቅ ተአምር፣ ሰባ ነገሥታት #ከደሃይቱ_መበለት ቤት አስረውት ሳለ #ልጇን_ለፈወሰበት፤ ታስሮ የነበረበትን ደረቅ ምሰሶ ከሃገሪቱ ቅጽር በላይ እንዲታይ #ላለመለመበት፤ #ዲዳ_ደንቆሮ_ዕውርና_አንካሳ የነበረው ልጇን #ለፈወሰበት_ለዓመታዊ_መታሰቢያ_በዓል #ከእስክድርያ_አገር ለሆነ ሰማዕትነት ለተቀበለ #ለቅዱስ_ጊዮርጊስ_ለዕረፍቱ_በዓል፣ ከግብፅ አገር ከፍዩም መንደር ሰማዕትነት ለተቀበለ #ለአባ_ናህርው ለዕረፍት በዓል ከገምኑዲ አውራጃ ከአገረ ተመይ ለሆነ ኤጲስቆጶስ #ለአባ_ሚናስ_ለዕረፍቱ_በዓል መታሰቢያ፣ ተበይስ ከምትባል አገር ከታላላቆች ወገን ለሆኑ ሰማዕትነት ለተቀበሉ #ለቅዱሳን_ዘኖቢስና_ለእናቱ_ዘኖብያና_ለዕረፍታቸው በዓልና #ለቅዱሳን_ሐዲስ_መርቆሬዎስና #ለወንድሙ_ቅዱስ_ዮሐንስ_ለዕረፍታቸው_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                                                                                ✝ ✝ ✝ 🌹 በዚችም ቀን #የልዳ_አገር_የሆነ_የሰማዕታት_አለቃ_የታላቁ_መስተጋድል_የቅዱስ_ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የከበረችበት ነው ዳግመኛም ጌታችን በውስጧ ላደረገው ድንቅ ተአምር መታሰቢያ ሆነ። 🌹 ይህም እንዲህ ነው በውስጧ ድንቆች ተአምራት እንደሚሠሩ ከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስም በሰማ ጊዜ ሊአፈርሳት አሰበ ስሙ አውህዮስ የሚባለውንም መኰንን ከብዙ ሠራዊት ጋር ላከው ያም መኰንን በደረሰ ጊዜ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥዕል ወዳለበት አዳራሽ በትዕቢት ሆኖ ገባ በሥዕሉም ፊት በብርጭቆ መቅረዝ መብራት ነበረ በቤተ ክርስቲዪኒቱና በቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ እየዘበተ በእጁ በያዘው በትር የመብራቱን መቅረዝ መትቶ ሰበረው የመቅረዙም ስባሪ ወደ ከሀዲው ራስ ደረሶ መታው ራሱንም ታመመ ፍርሃትና እንቅጥቅጥም መጣበት ወድቆም ተዘረረ ባልጀሮቹም ወደ አገሩ ሊወስዱት ተሸከሙት በክፉ አሟሟትም ተጎሳቊሎ ሞተ ወስደውም ከባሕር ጣሉት ወገኖቹም ወደ አገራቸው አፍረው ተመለሱ። 🌹 ከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስም ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ በልዳ አገር ያለች ነቅዱስ ጊዮርጊስን ቤተ ክርስቲያን ያፈርሳት ዘንድ ራሱ ተነሥቶ ሔደ በዚያንም ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ መታው ሰባት ዓመት ያህልም ዐይኖቹ ታውረው አእምሮውንም አጥቶ ቁራሽ እንጀራም እየለመነ ኑሮ ሞተ። 🌹 ክብር ይግባውና ጌታችንም የቤተ መንግሥቱን ሰዎች አስነሣበት እርሱን አስወግደው ጻድቅ ሰው ቈስጠንጢኖስን በእግዚአብሔር ፈቃድ አነገሡት እርሱም በአዋጅ የጣዖታትን ቤቶች ዘግቶ አብያተ ክርስቲያናትን ከፈተ ለክርስቲያን ወገኖችም በሁሉ ዓለም ተድላ ደስታ ሆነ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ጊዮርጊስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 7 ስንክሳር።                                                 ✝ ✝ ✝ 🌹 #ሰማዕቱ_ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ዘእስክንድርያ፡- አባቱ በእስክንድርያ አገር በንግድ ሥራ ይተዳደር የነበረ ሲሆን ልጅ ስላልነበረው በልዳው ኮከብ ቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ወደተሠራች አንዲት ቤተ ክርስቲያን ሄዶ በቅዳሴ ቤቱ ክብረ በዓል ቀን ልጅ እንዲሰጠው ሰማዕቱን በስዕለት ጠየቀው፡፡ ስዕለቱም ተሰምቶለት ልጅ ሲወልድ ስሙን በሰማዕቱ ስም ጊዮርጊስ ብሎ ጠራው፡፡ ሚስቱም የእስክንድርያው አስተዳዳሪ የአርማንዮስ እኅት ናት፡፡ ጊዮርጊስ ከተወለደ በኋላ ብዙም ሳይቆዩ እናትና አባቱ ስለሞቱ አስተዳዳሪ አጎቱ ወስዶ አሳደገው፡፡ አጎቱም ጣዖትን የሚያመልክ ነው፡፡ ነገር ግን ጊዮርጊስ እስከ 20 ዓመቱ ድረስ በሃይማኖቱም እጅግ ጠንካራ ሆነ፡፡ በጾም በጸሎት እየተጋ ነዳያንን አብዝቶ ይመግብ ነበር፡፡ የጽድቅ ሥራውንም ሰው አያውቅበትም ነበር፡፡ 🌹 የአስተዳዳሪው ብቸኛ ሴት ልጅ ልዩ ልዩ የተዋቡ ቦታዎችን ትጎበኝ ዘንድ ከቤት ወጥታ ወደ ደብረ ቁስቋም ስትደርስ የቤተ ክርስቲያንን የቅዳሴ ዝማሬ ሰምታ ልቧ እጅግ ደስ ተሰኘ፡፡ የአክስቷ ልጅ የሆነ ጊዮርጊስንም መነኮሳቱ ስለሚያሰሙት ዝማሬ ጠየቀችው፡፡ እርሱም ምንነቱን ካስረዳት በኋላ በዚያውም የሃይማኖትን ነገር በደንብ አስተማራት፡፡ ልጅቱም ወደ ከሃዲው አስተዳዳሪው አባቷ ዘንድ ቀርባ ስለ ጌታችን ክብር ትመሰክር ጀመር፡፡ አባቷም ሊሸነግላት ቢሞክር ነገሩን እንዳልሰማችው ሲያውቅ ብቸኛና አንድያ ልጁን አንገቷን በሰይፍ አስቆረጠው፡፡ ከዚህም በኋላ ልጅህን አስተምሮ ያሳታት የእኅትህ ልጅ የሆነው ጊዮርጊስ ነው" ብለው ለመኰንኑ ነገሩት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስንም ይዞ ጽኑ ሥቃይን ካሠቃየው በኋላ ኅዳር 7 ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆረጠውና ሰማዕትነቱን በድል ፈጸመ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                               ✝ ✝ ✝ 🌹 #አቡነ_ሚናስ_ዘሀገረ_ተመይ፡- ተመይ የምትባለው አገር ኤጲስ ቆጶስ የሆነው የአቡነ ሚናስ ወላጆቹ የመነኮሳትን ሥራ የሚሠሩ ደጋጎች ነበሩ፡፡ የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት እያስተማሩ አሳደጉት፡፡ ሲያድግም ያለፈቃዱ ሚስት አጋቡት፡፡ ወደ ጫጉላ ቤትም በገባ ጊዜ ድንግልናቸውን ይጠብቁ ዘንድ ከሚስቱ ጋር ተማክሮ ሁለቱም በንጽሕናና በድንግልና ሆነው በአንድነት ሊኖሩ ተስማሙ፡፡ ሌሊቱንም ሁሉ ለጸሎት ቆመው ያድሩ ነበር፡፡ እርሱም በዓለም እየኖሩ የምንኩስናን ሥራ ከመሥራት ይልቅ መንኩሶ ገዳም መግባት እንደሚሻል ለሚስቱ ሲነግራት ሸኝታ አሰናበተችው፡፡ አቡነ ሚናስም ወደ አቡነ እንጦንስ ገዳም ገባ ነገር ግን በንጉሡ ትእዛዝ ቤተሰቦቹ ቢያስፈልጉትም ጌታችን ሰውሮታል ሊያገኙት አልቻሉም፡፡ ከዚህም በኋላ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሄደ፡፡ 🌹 በዚያም ሁለቱ ብርሃን ከዋክብት አባ አብርሃምንና አባ ገዐርጊን በማገልገል ልጅ ሆናቸው፡፡ ተጋድሎአቸውንና ትምህርታቸውን በሚገባ ከተማረ በኋላ እርሱም በተጋድሎው አባ አብርሃምና አባ ገዐርጊ እስኪያደንቁትና እስኪገረሙበት ድረስ ከፍ ከፍ አለ፡፡ ከዚህም በኋላ ኤጲስ ቆጶስነት ይሾም ዘንድ ጌታችን መርጦት ለሊቀ ጳጳሳቱ እንዲሾመው ነገረው፡፡ ሊቀ ጳጳሳቱም ጠርተው ሲያስመጡት እምቢ ቢላቸውም የእግዚአብሔር ትእዛዝ መሆኑን ነግረውት ተመይ በሚባል አገር ላይ ሾሙት፡፡ አቡነ ሚናስ ከዚህም በኋላ ሀብተ ፈውስም ተሰጥቶት ብዙ ድውያንን የሚያድናቸው ሆነ፡፡ ሁለተኛም የተሰወረውን የማወቅ ሀብት ተሰጠውና በሰው ልቡና የታሰበውን የሚያውቅ ሆነ፡፡ አቡነ ሚናስ ለአራት ታላላቅ አባቶች አባት ሆኖ እጁን በላያቸው ላይ ጭኖ ሾሟቸዋል፡፡ እነርሱም ለእስክንድርያ አገር ሊቃነ ጳጳሳት የሆኑት አባ እለእስክንድሮስ፣ አባ ቆዝሞስ፣ አባ ቴዎድሮስና አባ ሚካኤል ናቸው፡፡ አባታችን በመጨረሻም ከዚህ ዓለም ድካም የሚያርፍበትን ጊዜ ዐውቆ ካህናቱንና ሕዝቡን ሁሉ ሰብስቦ በቀናች ሃይማኖት ጸንተው እንዲኖሩ ከመከሯቸው በኋላ ኅዳር 7 ቀን በሰላም ዐረፉ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በረከታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹            🌹 #ኅዳር ፮ (6) ቀን። 🌹 እንኳን #ለኢትዮጵያውያኑ_ጻድቃን ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ዳንኤል_ዘገርዓልታ_ለዕፍታቸው መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                              ✝ ✝ ✝ 🌹 #አቡነ_ዳንኤል_ዘገርዓልታ፦ የአባታቸው ስም መልክአ ሥላሴ የእናታቸው ስም ዓመተ ጽዮን ሲባሉ የትውልድ አገራቸው ትግራይ ገርዓልታ ነው። በሰባት ዓመታቸው የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ተምረው አጠናቀው በዓሥራ ሦስት ዓመታቸው መነኰሱ። ሊቃውንቱ "ማኅቶተ ገዳም" እያሉ የሚጠሯቸው ታላቅ ገድለኛ አባት ናቸው። ባለ አራት ዓምዱና አርባ ያሸበረቁ ሥዕላት ያሉት አስደናቂው ገድላቸው የት እንዳለ አይታወቅም፣ እኛ አገር ገድላቸው የለም። 2ኛውን ገድላቸውን ፖርቹጋሎች ከጠባቂው ገዝተው ወስደው አገራቸው አሳትመውታል። ገድሉን የሸጠው ጠባቂም ሆዱ ተነፍቶ በስብሶ ተልቶ ከቤተ ክርስቲያኑ በራፍ ላይ ወድቆ ሞቷል። የጻድቁ የዕረፍታቸው ዕለት ኅዳር 6 ቀን ትግራይ ገርዓልታ በሚገኝ ገዳማቸው በደማቅ ሁኔታ የከበራል። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።                 

🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹            🌹 #ኅዳር ፮ (6) ቀን። 🌹 እንኳን #ክብር_ይግባውና_ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ #ከእመቤታችን_ከቅድስት_ድንግል_ማርያም #ከአረጋዊ_ዮሴፍና_ከሰሎሜ ጋር ከስደት በሚመለሱ ጊዜ ወደ #ደብረ_ቊስቋም ገብተው በመንገድ ጒዞ ካገኛቸውም ድካም #ላአረፉበት_ዓመታዊ_መታሰቢያ በዓል፣ #ለሮሜ_አገር_ሊቀ_ጳጳሳት ለቅዱስ አባት #ለአባ_ፊልክስ_ለዕረፍት መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከአባ_ፍሞስ_ከቅዱሳን_ለንዲዎስ_ከይላጥስ፣ #ከማርትሮስ_ከኢላስዎስ_ከቆርናልዮስ_ከሱኪሮስ #ከናውኔኖስ_ከሊባዲቆ_ከሲላስዮስና #ከሰማዕት_ኤስድሮስ_ማኅበር ከሆኑ #ከሁለት_መቶ_ሰባ_ሰማዕታት ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                                                    ✝ ✝ ✝ 🌹 #በዚች_ቀን_ክብርግባውና_ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ከእመቤታችን_ከቅድስት_ድንግል_ማርያም_ከአረጋዊው_ዮሴፍና_ከሰሎሜ ጋር በስደት በሚመለሱ ጊዜ #ወደ_ደብረ_ቊስቋም ገባ በመንገድ ጒዞ ካገኛቸው ድካም ዐረፉ። 🌹 ዳግመኛም በኋላ ዘመን በዚህ ደብረ ቊስቋም ቅዱሳን ሐዋርያቶቹን ሰበሰባቸው ታቦትንና ቤተ ክርስቲያንንም አክብሮ የቊርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋውንና ክብር ደሙን ለወገኖቹ ሰጣቸው። ለዚህም የእስክንድርያ አገር ሊቃነ ጳጳሳት ቅዱሳን አባቶቻችን ቄርሎስና ቴዎፍሎስ ምስክሮችን ሆኑ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አምላክን የወለደች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷ ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።                                                                                  ✝ ✝ ✝ 🌹 #የሮሜ_አገር_ሊቀ_ጳጳሳት_አባ_ፊልክስ፦ የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ ክርስቲያኖች ናቸው የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት አስተማሩት የሮሜ ሊቀ ጳጳሳት አንስጣስዮስም ዲቁና ሾመው ደግሞ የሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ዮስጦስም ጠባዩን የጽድቁንና የትሩፋቱን ደግነት አይቶ ቅስና ሾመው። 🌹 ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ዲዮናስዮስ በዐረፈ ጊዜ ይህን አባት ፊልክስን መረጡት በእግዚአብሔርም ፈቃድ በሮሜ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት የክርስቶስንም መንጋዎች በመልካም አጠባበቅ ጠበቀ። 🌹 ትሩስ ቄሣርም ከሞተ በኋላ ቴዎድሮስ ቄሣር ነገሠ። እርሱም በምዕመናን ላይ ታላቅ መከራ አምጥቶ ጭንቅ በሆኑ ሥቃዮች አሠቃያቸው። ብዙዎችም  በእርሱ እጅ በሰማዕትነት ሞቱ። ይህም አባት ከዚህ ከሀዲ ታላቅ መከራና ኀዘን ደረሰበት። ስርሱም ወደ እግዚአብሔር ማለደ ክብር ይግባውና ጌታችንም ልመናውን ተቀብሎ ይህንን ከሀዲ በሁለተኛ ዘመነ መንግሥቱ አጠፋው። 🌹 ከዚህም በኋላ ከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስም በነገሠ ጊዜ ክርስቲያኖችን አብዝቶ ማሠቃየትን ጀመረ ይህም አባት ፊልክስ የክርስቲያኖችን ሥቃይ እንዳያይ ክብር ይግባውና ወደ እግዚአብሔር ጸለየ በዲዮቅልጥያኖስም በመጀመሪያው ዘመነ መንግሥት ኅዳር 6 ቀን ዐረፈ። 🌹 ይህም አባት ብዙዎች ድርሳናትንና ተግሣጾችን ደርሶአል ከእርሳቸውም ስለ ውግዘትና ስለ ቀናች ሃይማኖት የተመላለሰብት አለ እሊህም ለክርስቲያን ወገን እጅግ የሚጠቅሙ በጎዎች ናቸው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ፊልክስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር  6 ስንክሳር።                                                                                ✝ ✝ ✝ 🌹 #የዕለቱ_የማኅሌቱ_ምስባክ፦ "ዖፍኒ ረከበት ላቲ ቤተ። ወማዕነቅኒ ኀበ ታነብር ዕጐሊሃ። ምሥዋዒከ እግዚኦ እግዚአ ኃያላን"። መዝ 83፥3 የሚነበበው ወንጌል ሉቃ22፥14-24።                             ✝ ✝ ✝ 🌹 #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ርኢክዎ ለኃጥእ ዐብየ ወተለዐለ ከመ አርዘ ሊባኖስ። ወሶበ እገብእ ኀጣእክዎ። ኀሠሥኩ ወኢረከብኩ መካኖ"። መዝ 36፥35። የሚበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 8፥1-16፣ 2ኛ ዮሐ 1፥9-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 1፥12-15። ማቴ 2፥19-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም የቊስቋም ማርያም በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።                   

🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹             🌹 #ኅዳር ፭ (5) ቀን። 🌹 እንኳን ክብር ይግባውና #ጌታችን_በዕጨት_መስቀል ላይ ተሰቅሎ ሳለ ጐኑን ለወጋው #ለቅዱስ_ለጊኖስ_ራሱ_ለታየችበት፣ ለሠራዊት አለቃ #ለቅዱስ_ቴዎድሮስም ከአገረ ሰጥብ ወደ አገረ አስዩጥ #ሥጋው_ለፈለሰበትና #ቤተ_ክርስቲያኑ_ለከበረችበት_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ #ከሰማዕት_ቅዱስ_ጢሞቴዎስ ከመታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                                                   ✝ ✝ ✝ 🌹 በዚች ቀን ክብር ይግባውና #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_በዕንጨት_መስቀል ላይ ተሰቅሎ ሳለ ጐኑን የወጋ #የቅዱስ_ለንጊኖስ_ራሱ የታየችበት ነው፦ ይህም ቅዱስ በጌታችን ከአመነ በኋላ በቀጰዶቅያ አገር ወንጌልን የሚሰብክ ሆነ ከሀድያን አይሁድም በላዩ ተነሡበት በመኳንንት ዘንድ በሐሰት ወንጅለው በቀጰዶቅያ አገር ራሱን አስቆረጡት ራሱንም ብቻዋን ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱዋት። በኢየሩሳሌም የሚኖሩም አይሁድ በአዩዋት ጊዜ እጅግ ደስ አላቸው ከዚህም በኋላ ከኢየሩሳሌም ከተማ ውጭ በአንድ ኮረብታ ላይ ቀበሩዋት። 🌹 ከብዙ ቀኖችም በኋላ እንዲህ ሆነ በቅዱስ ለንጊኖስ ስብከት ያመነች አንዲት ሴት በቀጰዶቅያ አገር ነበረች ራሱን ከቆረጡት ጊዜ ጀምራ በተቆረጠበት ቦታ በመቆም ስለርሱ ታለቅስ ነበር ክብር ይግባውና በእግዚአብሔርም ፈቃድ የዚያች ሴት ዐይኖቿ ታወሩ። 🌹 ከዚህም በኋላ ምናልባት ዐይኖቿ ቢገለጡላት በማሰብ ከከበሩ ቦታዎችና ክብር ይግባውና ከጌታችን መቃብር ለመባረክና ለመለመን ተነሥታ ልጅዋን ይዛ ወደ ኢየሩሳሌም ሔደች። ወደ ኢየሩሳሌምም በደረሰች ጊዜ በዚያ ልጅዋ ሞተ ኀዘንም ተጨመረባት ወደ አገርዋም መርቶ የሚያደርሳት አጣች ስለዚህም  የመረረ ልቅሶን አለቀሰች ከኀዘኗምብዛት የተነሣ ተኛች። 🌹 ከዚህም በኋላ ቅዱስ ለንጊኖስን ከሞተው ልጅዋ ጋር በሕልሟ አየችው። "ዕገሌ ከሚባልም ቦታ ሒደሽ ራሴን ከዚያ ውሰጂ" አላት። ከእንቅልፍዋም በነቃች ጊዜ ስለዚህ ቦታ ጠየቀች ሰዎችም ወደርሱ አደረሱዋት። ያንንም ቦታ በቆፈረች ጊዜ መዓዛው እጅግ ጣፋጭ የሆነ የሽቱ መዓዛ ወጣ። ራሱ ወደአለችበት ስትደርስ ታላቅ ብርሃን ተገለጠላትና ዐይኖቿም በዚያን ጊዜ ተገለጡላት እግዚአብሔርንም አመሰገነች። 🌹 ከዚህም በኋላ ከልጅዋ ሥጋ ጋር የቅዱስ ለንጊኖስን ራስ ወደ አገርዋ ወሰደቻት። በታላቅ ክብርም በአማረ ቦታ አኖረቻት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ለጊኖስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 5 ስንክሳር።                              ✝ ✝ ✝ 🌹 "#ሰላም_ለከ_ጢሞቴዎስ_ቡሩክ። ሰማዕተ አምላክ። ብእሲ ሰማያዊ ወምድራዊ መልአክ። ኅብአኒ በክነፊከ በዕለተ ምንዳቤ ወሀውክ። እምነ ልሳን ምዑክ ወእምዐይን ድሩክ"። #ሊቁ _አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የኅዳር_5።                              ✝ ✝ ✝ 🌹 #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ኃጢአትየ ዘበንስየእ ወዕበድየ ኢትዝክር ሊተ። ወበከመ ሣህልከ ተወከረኒ። በእንተምሕረትከ እግዚኦ"። መዝ 24፥7። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 5፥8-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 2፥9-13 እና የሐዋ ሥራ 26፥12-19። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 19፥31-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የአባ ዮሐኒ ከሞት የተሰወሩበት (የስዋሬ) በዓል፣ የአባ አሞኒ የዕረፍት በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።        

አውሎግሶን" አለች፡፡ ሰይጣን ይህን ስም ሲሰማ 40 ክንድ ይርቃል፡፡ የደብረ ዳሞ መነኰሳት እንደ ሰላምታ መለዋወጫ ይጠቀሙበታል፡፡ አባ ዮሐኒም ይህን ድምጽ ከውጭ በሰሙ ጊዜ "አንተ ማነህ?" አሉ፡፡ እርሷም "ዓመተ መንፈስ ቅዱስ ነኝ" አለቻቸው፡፡ አባታችንም አንድም ድምፁዋ ወትሮ ከሚያውቁት ድምፅ ስተለየባቸው ደግሞም ትዝ ሲላቸው እነዚያ እንስራ አዝለው ደረታቸው ላይ ቀንድ ያላቸው ሆነው ውኃ ቀድተው ሲሄዱ በመነገድ ያዩአቸው ሴቶች ድምፅ ሆነባቸው፡፡ ደግሞም "ወልደ እከሌ፣ ክንፈ እከሌ" ሲባል እንጂ "ዓመተ፣ ወለተ" ሲባል ሰምተው አያውቁም ነበርና አባታቸው አባ አሞኒ የነገሯቸው ትዝ አላቸው፡፡ በዚያውም ቅጽበት የሚጽፉባትን ብዕር ጆሮአቸው ላይ እንደሰኩ 500 ሜትር ርዝመት ካለው ትልቅ ተራራ ላይ ራሳቸውን ቁልቁል ወረወሩ፡፡ ነገር ግን መሬት ሳይደርሱ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በአየር ላይ እንዳሉ ተቀበላቸው፡፡ ብዕራቸው ግን መሬት ላይ ወድቃ ሸምበቆ ሆነች፡፡ ወዲያውም አባ ዮሐኒ ክንፍ አውጥተው ከቅዱስ ገብርኤል ጋር ጎን ለጎን ሆነው በዛሬው ዕለት ኅዳር 5 ቀን ወደ ብሔረ ሕያዋን ይዟቸው ገባ፡፡ 🌹 ብሔረ ሕያዋን ያሉ እነ ሄኖክና ኤልያስም "ሰው ከሚሞትበት ሀገር ሞት ወደሌለበት አገር ማን አመጣው?" አሉ፡፡ መልአኩም በዚህ ጊዜ "እግዚአብሔር ባዘዘኝ ጊዜ እኔ ገብርኤል ነኝ ያመጣሁት" አላቸው፡፡ ቀጥሎም መልአኩ "አንተ ሄኖክ ምንም ንጹሕ ብትሆን በሥርዓተ ሥጋ ተወልደህ በሥርዓተ ሥጋ አድገህ ሚስት አግብተህ ወልደሃል፣ እግዚአብሔርም እዚህ ያደረሰህ በንፅህናህ ነው፤ አንተም ኤልያስ ምንም ድንግል ብትሆን በሥርዓተ ሥጋ ተወልደህ በሥርዓተ ሥጋ አድገህ ከዚህ ደርሰሃል፤ ይህ አባ ዮሐኒ ግን ከተወለደ ጀምሮ የእናቱን ጡት አልቀመሰም፣ ቀን ቀን ሰሳ እያጠባችው ሌሊት ሌሊት ንስር አሞራ በክንፎቹ እያለበሰው አድጓል እንጂ" ብሎ ነገራቸው፡፡ ቀጥሎም መልአኩ የአባ ዮሐኒን ገድል ዘርዝሮ ከነገራቸው በኋላ ሊሞት ያለበትንም የአሟሟቱን ነገር ከነገራቸው በኋላ "ታዲያስ እንዲህ ያለውን አምጥቼ ከብሔር ሕያዋን ባስገባው ፍርዴ እውነት አይደለምን" አላቸው፡፡ ሄኖክና ኤልያስም ይህን ጊዜ "ይገባዋል" ብለው አባ ዮሐኒን በምስጋና ተቀበሉት፡፡   🌹 ከዚህም በኋላ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ወደ ደብረ ዓሣ ተመልሶ መጥቶ ለአባ አበይዶ ተገለጠላቸውና አባ ዮሐኒን ብሔረ ሕያዋን እንዳስገባው ነገራቸው፡፡ በመጀመሪያ ሄኖክና ኤልያስ አላስገባ ብለው እንደነበርና በኋላም መልአኩ ራሱ የአባ ዮሐኒን ገድላቸውን ከነገራቸው በኋላ በምስጋና እንደተቀበሉት ለአባ አበይዶ ነገራቸው፡፡ ቀጥሎም መልአኩ የአባ ዮሐኒን ገድላቸውን እንዲጽፉትና እንዲያስተምሩበት ለአባ አበይዶ አዘዛቸውና ዐረገ፡፡ አባ አበይዶም አባ ዮሐኒ ከገደሉ ተወርውረው ሲወደቁ አንድ ደስ የሚል ወንድ ሲቀበለው አይተው ነበርና አሁን መልአኩ ሲነግራቸው እጅግ ደስ አላቸው፡፡ አባ አበይዶም በታዘዙት መሠረት የአባ ዮሐኒን ገድል ጻፉት፡፡ እርሳቸውም ትናንት ኅዳር 4 ቀን በሰላም ዐረፉ፡፡        🌹 በፎቶው ላይ እንደምታዩት ተንቤን የሚገኘው የአባ ዮሐኒ ቤተ ክርስቲያን አቀማመጡ እጅግ አስደናቂ ነው፡፡ ተራራው መሀል ላይ ወደሚገኘው ቤተ ክርስቲያኑ ለመውጣት 150 ሜትር ተራራውን መውጣት ይጠይቃል፡፡ ሽቅብ ከተወጣ በኋላ አፈ ጽዮንን ትገኛለች፡፡ ከአፈ ጽዮን በኋላ ከድንጋይ የተፈለፈለ 12 መድረክ ያለው የውስጥ ለውስጥ የጨለማ መንገድ አለ፡፡ በመጨረሻ ብርሃን ወዳለብ ስፍራ ሲወጣ በስተግራ በኩል 12 ሜትር ርቀት ላይ ቤተ መቅዱሱ ይገኛል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ 13 ጉልላቶች አሉት፡፡ ገዳሙ ጥንት 58 ዓምደ ወርቅ ነበረው፡፡ በአንድ ወቅት በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት 22ቱ ሲሰባበሩ አሁን ያሉት 36ቱ ብቻ ናቸው፡፡ ገዳሙ ውስጥ ሦስት ቤተ መቅደሶች ያሉ ሲሆን አንዱን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ይቀድሱበት የነበረው ነው፡፡ ገዳሙ ደብረ ዓሣ እየተባለ ይጠራል፡፡ ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያኑ በመሬት መንቀጥቀጥ ከመፍረሱ በፊት ጣራው የዓሣ አንበሪ ቅርጽ ነበረው፡፡ ዐፄ ገብረ መስቀልም በወቅቱ በዚህ ዓሣ ምስል ያሠሩት ቅዱስ መስቀል በገዳሙ ውስጥ ይገኛል፡፡ አንድም ደግሞ በመጀመሪያ ዐፄ ገብረ መስቀል እና ሌሎቹም ቅዱሳን አበው በገዳሙ ውስጥ ሱባኤ ገብተው ሳለ ቅዱሳን በዓሣ ተመስለው ሲወጡና ሲገቡ በማየታቸው ነው ገዳሙ "ደብረ ዓሣ አባ ዮሐኑ" የተባለው፡፡ 🌹 ሌላው በተፈጥሮአዊ አቀማመጡ እጅግ ድንቅ በሆነው በዚህ ገዳም ውስጥ አስገራሚ የመቃብር ጉድጓዶች አሉት፡፡ መቃብሮቹ የተፈለፈሉ ዋሻዎች ናቸው፡፡ አንዱ ዋሻ በአንድ ጊዜ ከ6 ሰዎችን ጎን ለጎን አስተኝቶ መያዝ አይችልም ነገር ግን በጣም የሚገርመው የመቃብር ጉድጓዶቹ እስከዛሬም ድረስ አልሞሉም፡፡ አንድ ሰው ከተቀበረ ከዓመት በኋላ አስክሬኑ ይጠፋል፣ አጥንቱም አይገኝም፡፡ ሰሌኑ ግን እስከ ሁለት ዓመት ይቀመጣል፡፡ ለአባ ዮሐኒ ለዚህ ገደማቸው ዕጣን ጧፍ ዘቢብ የሰጠ ሰው ቢኖር ስጦታውን እንደ አቤል መሥዋዕት አድርጎ ጌታችን እንደሚቀበልለት ለጻድቁ ቃልኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡  ከአባቶቻችን ከአባ አሞኒ ከአባ ዮሐኒና ከአባ አበይዶ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን፣ በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳንና ከገድላት አንደበት።             

🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹             🌹 #ኅዳር ፭ (5) ቀን። 🌹 እንኳን #ለኢትዮጵያውያኑ_ጻድቃን ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ዮሐኒ_እንደ_መላእክት_ክንፍ_አብቅለው (ተሰቷቸው) ወደ ብሔረ ሕያዋን በመግባት #ከሞት_ለተሰወሩበት ለመታሰቢያ በዓላቸውና #አባ_ዮሐኒን_ላሳደጉ_ላስተምረው ለታላቁ አባት #ለአቡነ_አሞኒ_ለዕረፍት_በዓል መታሰቢያ እግዚአብሔር በሰላምና በጤና አደረሰን።                                           ✝ ✝ ✝ 🌹 #አቡነ_አሞኒና_ልጃቸው_አቡነ_ዮሐኒ ደቀ መዝሙራቸው #አባ_አበይዶ፡- የአባ ዮሐኒ አባታቸውን መጽሐፍ ዘስዩመ ተንቤን እሁሁ ይላቸዋል፡፡ እናታቸው ደግሞ ዓመተ መንፈስ ቅዱስ የሚባሉ ደገኛ ምግብራቸው ያማሩ ሀገር ወዳድ ናቸው፡፡ አቡነ አሞኒ የካቲት 5 ቀን አክሱም ውስጥ ሲወለዱ ሰይጣናት የወላጆቻቸውን ቤት ከበው በማየታቸው እንደተወለዱ በእጃቸው ቢያመለክቱ በአንድ ጊዜ 60 ሰይጣናት ተሸንፈው እንደጢስ በነው ጠፍተዋል፡፡ አሞኒ ማለት አሸናፊ ማለት ነው፡፡ 🌹 አባ አሞኒ የራስ ፀጉራቸው ልብስ መጎናጸፊያ ሆኖላቸው የኖሩ ታላቅና ቀደምት አባት ናቸው፡፡ በደመና ተጭነው ደብረ ዘይት ድረስ በመሄድ ከአባ እብሎይ ጋር ተገናኝተው ብዙ ምሥጢርን አውርተዋል፡፡ አባ ዮሐኒን ያሳደጉት አስተምረው ያሳደጓቸው አባ አሞኒ ናቸው፡፡ የእናቱን ጡት ፈጽሞ ጠብቶ የማያውቀውን የመንፈስ ቅዱስ ልጃቸውን አባ ዮሐኒን እሳቸው እያጫወቱት የታዘዘ አሞራ በክንፎቹ እያለበሰው ቶራ (ሰሳ) እያጠባችው ነው ያደገው፡፡ መነሻ ታሪኩም እንዲህ ነው፦ የተንቤን አውራጃ ገዥ የነበረው ሰው በዘመኑ ዐፄ ካሌብ የነበሩበት ዘመን ነበርና አብሯቸው ወደ ምድረ ኖባ ሄደው ሰባት ዓመታትን የፈጀ የጦር ዘመቻ ክርስያኖችን በሚያሠቃዩ ነገሥታት ላይ አዳሄዱ፡፡ የተንቤኑ አውራጃ ገዥም ወደ ዘመቻው ከሄደ ቆይቶ ነበርና ታናሽ ወንድሙ የገዥውን ሚስት "ወንድሜ የቀረው ሞቶ ነው እንደ ኦሪቱ ሕግ እኔው ላግበሽና ልጆቹን ላሳድግ" አላት፡፡ እርሷም "ባሌ ቢሞት ይነገረኝ ነበረ ዘመቻ የሄደው ሁሉ አልተመሰም" ብላ እምቢ ብትለው በግድ ተገናኛት፡፡ በዚህም ጊዜ አባ ዮሐኒ ተፀነሱ፡፡ በሚያዝያ 5 ቀንም ተወለዱ፡፡ 🌹 ከዘጠኝ ወር በኋላ ባሏ ከዘመቻ መጣና ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡ የአካባቢውም ሰው ወጥቶ በክብር ሲቀበለው ሚስቱ ግን ምጥ ተይዛ ታማ ስለነበር ወጥታ አልተቀበለችውም፡፡ "የት ሄደች? ምንስ ሆነች?" ብሎ ሲጠይቅ ልጅ አይደብቅምና አንድ ሕፃን "አርግዛ ልትወልድ በምጥ ላይ ትገኛለች" አለው፡፡ የአውራጃውም ገዥ ያለችበት ድረስ ሄዶ ቢያያት ያማረ ወንድ ልጅ ታቅፋ አገኛት፡፡ ከዚህም በኋላ ከቤቱ ምሰሶ ጋር ጥፍንግ አድርግ አስሮ እየገረፋትና እያስጨነቃት ከማን እንዳረገዘች ጠየቃት፡፡ እርሷም የወንድሙን ምሥጢር ለመጠበቅና ወንድማማቾቹን ላለማጣላት ሥቃዩን ታግሳ ዝም አለች፡፡ በዚህ ቅጽበት የራማው ልዑል ቅዱስ ገብርኤል 40 ዓመት ሙሉ ዘግተው በበረሃ ለሚኖሩት ለአባ አሞኒ ተገለጠላቸው እንደ አውሎ ነፋስ አምዘግዝጎ ወስዶ አውራጃ አገረ ገዥው ቤት አደረሳቸው፡፡ 🌹 እንደደረሱ ዓመተ መንፈስ ቅዱስ በጽኑ ድብደባና ግርፋት እየተሠቃየች እያለ አባ አሞኒ የጸጉራቸውን አጽፍ ለብሰው ራቁታቸውን ደጇ ላይ ቆመው አየቻቸው፡፡ በዚህም ጊዜ ለባሏ "ያውና ከዚህ መነኲሴ ነው የወለድኩት" አለቸው፡፡ የተንቤኑ አውራጃ አገረ ገዥውም አባ አሞኒን ይዞ ጽኑውን ግርፋት በወታደሮቹ አስገረፋቸው፡፡ በመቀጠልም ገና የእናቱን ወተት እንኳን ያልቀመሰውን ጨቅላ ሕፃን አንሥቶ "እንካ ልጅህን ይዘህ ጥፋ ከዚህ" ብሎ ሰጣቸው፡፡ አባ አሞኒም በዚህ ጊዜ "ዮ ሀበኒ ዮ ሀበኒ" አሉ፡፡ በትግርኛ እሽ ስጠኝ ማለት ነው፡፡ ከዚህ በመነሳት ነው ሕፃኑ በኋላ ላይ "አባ ዮሐኒ" የተባሉት፡፡ አባ አሞኒም ሕፃኑን ተረክበው ወደ ደብረ ዓሣ ተራራ ሥር ሄደው ልጁን ከወይራ ዛፍ ሥር አስተኝተው "አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ኃጢአቴን ተመራምረህ ይህንን ሕፃን የሰጠኸኝ አላጠባው ጡት የለኝ አላበላው እህል የለኝ" ብለው የጨቅላው ሕፃን ነገር እጅግ ቢያስጨንቃቸው ምርር ብለው አለቀሱ፡፡ ጸሎታቸውንም እንደጨረሱ ተራራውን በመስቀል ምልክት ቢባርኩት በተራራው መሐል ላይ እንደመደብ ያለ አልጋ በተአምራት ተሠርቶ አገኙት፡፡ ሕፃኑንም ከዚያ አስተኝተው ድጋሚ ጸሎት ሲጀምሩ ቶራ (ሰሳ) መጥታ እግርና እግሯን አንፈራጣ ሕፃኑን አጠባችውና ሄደች፡፡ 🌹 አባ አሞኒም በዚህ ደስ ተሰኝተው ሕፃኑን "የምግብህ ነገር ከተያዘ ግዴለም" ብለው ሌሊቱን ሙሉ ሲጸልዩ አድረው መለስ ቢሉ ዳግመኛም ሕፃኑን የታዘዘ ንስር አሞራ በክንፎቹ ጋርዶ አልብሶትና አቅፎት እንዳደረ ተመለከቱ፡፡ አባታችንም እጅግ ደስ ተኝተው እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡ እንደዚሁ ሁሉ ቀን ቀን ቶራዋ እያጠባችው ሌሊት ሌሊት ንስር አሞራው አልብሶት እያደረ ሕፃኑ ሦስት ዓመት ሆነው፡፡ አባ አሞኒም ከሰባት ዓመቱ ጀምረው እስከ 12 ዓመቱ ድረስ ፊደል፣ ንባብ ከነትርጓሜው፣ ብሉይንና ሐዲስን፣ ምግባር ሃይማኖትን ሥርዓተ ቤተ ክርስያንን ሁሉ አስተማሩት፡፡ 🌹 አባ አሞኒ ልጃቸው አድጎ 12 ሲሆነው ከዚህም በኋላ ዲቁና ሊያሾሙትና አክሱም ጽዮን ወስደው ሊያስባርኩት ቤተ ካህናት ከተባለው ቦታ ይዘውት ሲሄዱ ልዩ ስሙ ሲሂታ ከሚባለው ቦታ ሲደርሱ ከወገባቸው በላይ እራቁታቸውን የሆኑ እንስራ የተሸከሙ ዓሥር ሴቶች አገኙ፡፡ አባ ዮሐኒም አባታቸውን "አባቴ እነዚህ ደረታቸው ላይ ቀንድ ያላቸው ጽጉራቸው የረዘመ ምንድናቸው? እንደእኛ የሆኑ መስህታን የሚባሉት እነዚህ ናቸውን?" አሏቸው፡፡ አባ አሞኒም "አይደሉም ልጄ ዝም ብለህ ሂድ" አሏቸው፡፡ በኋላ ግን ትዝ ሲላቸው "በዱር እንስሳት ያሳደኩት ልጄ ወንድና ሴት ለይቶ ሲያውቅ በዚያው ሊሳሳት አይደልምን?" ብለው በማሰብ ዲቁናና ክህነቱ ይቅርበት ብለው ተመልሰው ወደ በዓታቸው ይዘውት ገቡ፡፡ 🌹 ከዚህም በኋላ አባ አበይዶ ወደ አባ አሞኒ መጣና እሳቸውን ከአባ ዮሐኒ ጋር እያገለገሏቸው ተቀመጡ፡፡ ዮሐኒ እየጻፈ አበይዶ የሚጻፍበትን ቆዳ እያዘጋጁ ሦስቱም በአንድነት በተጋድሎ መቀመጥ ጀመሩ፡፡ 🌹 አባ ዮሐኒ 20 ዓመት አባ አሞኒ ደግሞ 40 በሆናቸው ጊዜ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለአባ አሞኒ ተገለጠላቸውና "አሞኒ ሆይ ከእንግዲህስ እግዚአብሔር ወደኔ ና ብሎሃል" አላቸው፡፡ እሳቸውም ልጆቻቸውን አባ ዮሐኒንና አባ አበይዶን ጠርተው "በሉ እንግዲህ እኔ ወደ እግዚአብሔር መሄዴ ነውና ጸልዩልኝ" አሏቸው፡፡ ከማረፋቸውም በፊት አባ ዮሐኒን ለብቻቸው ጠርተው "አንተ አባ ዮሐኒ ካሁን በፊት ሲሂታ ላይ ያየሃቸው ሴቶች ናቸው፣ አዳምንም ከገነት ያስወጡ ናቸው፡፡ ወደፊትም እንደ እነርሱ ያለ የደረሰብህ እንደሆነ ካለህበት ገደል ተወርውረህ ውደቅ በባሕር ውስጥ ጥለቅ" ብለው ነግረዋቸው በዛሬዋ ዕለት ኅዳር 5 ቀን በሰላም ዐረፉና ወደ ጠራቸው እግዚአብሔር ሄዱ፡፡ 🌹 አባ አሞኒ ካረፉ ከ12 ዓመት በኋላ የአባ ዮሐኒ ወላጅ እናታቸው የልጇን ነገር ስታጠና ኖራ ነበርና አሁን ባሏም ስለሞተ አባ አሞኒም ስላረፉ ልጇን ልታይ ከ 32 ዓመት በኋላ መጣች፡፡ ቀሚስ ለብሳ ፀጉሯን ተሠርታ በሴትነቷ ልጇ ካለበት ቦታ በመሄድ ማነጋገር እንደማትችል ስላወቀች ፀጉሯን ተላጭታ የወንድ ልብስ ቁምጣ ለብሳ በሁለመናዋ ወንድ መስላ ወደ ደብረ ዓሣ ተራራ አመራች፡፡ እዚያም እንደደረሰች በቅዱሳን ሥርዓት መሥረት ሦስት ጊዜ "አውሎግሶን፣ አውሎግሶን፣

🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹            🌹 #ኅዳር ፬ (4) ቀን። 🌹 እንኳን #ለሮሜ_አገር ለሆኑ #ለቅዱሳን_አቢማኮስና_አዛርያኖስ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል፣ የሐርመዝ ልጅ በሆነ በፋርስ ንጉሥ በሳቦር እጅ ሰማዕትነት ለተቀበሉ #ለቅዱስ_ያዕቆብና ለአገረ ፋርስ ኤጲስቆጶስ #ለአባ_ዮሐንስ፣ በግብጽና በሶርያ እስላሞች በነገሡ ጊዜ ሰማዕትነት ለተቀበለ #ለደማስቆ_ኤጲስቆጶስ #ለቅዱስ_ቶማስ ለዕረፍት በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከታላቁ #አባት_ከዘካርያስ፣ ከእስክድርያ ሊቀ ጳጳሳት #አባ_ጴጥሮስ ከመታሰቢያቸውና #ከሰማዕታት_ጉባዔ ከሆነ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                                              ✝ ✝ ✝ 🌹 #ቅዱሳን_አቢማኮስና_አዛርያኖስ፦ እሊህም ቅዱሳን ክርስቶስን የሚያምኑ እንደሆኑ ከሀዲ ንጉሥ መክስምኖስ በሾመው መኰንን ዘንድ ወነጀሏቸው እርሱም አስቀርቦ ስለ ሃይማኖታቸው ጠየቃቸው እነርሱም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ። 🌹 እርሱም መኰንኑንም ሰማይና ምድርን በውስጣቸው ያለውንም ሁሉ የፈጠረ እውነተኛውን አምላክ ማምለክ ትቶ የሰይጣን መንፈስ በውስጣቸው ያደረባቸውን የማያዩ የማይሰሙ በሰው እጅ የተሠሩ የረከሱ ጣዕታትን ስለማምለኩ ዘለፉት። 🌹 መኰንኑም ከድፍረታቸው የተነሣ አደነቀ ቸብቸቧቸውንም በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ በመንግሥተ ሰማያትም የምስክነት አክሊል ኅዳር 4 ቀን ተቀበሉ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሰማዕታት አቢማኮስና አዛርያኖስ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                             ✝ ✝ ✝ 🌹 #ቅዱስ_ያዕቆብና_የአገረ_ፋርስ_ኤጲስቆጶስ_አባ_ዮሐንስ፦ እሊህም ቅዱሳን የሐርመዝ ልጅ በሆነ በፋርስ ንጉሥ በሳቦር እጅ በሰማዕትነት ያዐረፉ ናቸው። እርሱም ለፀሐይ፣ ለጨረቃ፣ ለእሳትም እንዲሰግዱ አዘዛቸው ትእዛዙንም ባልሰሙ ጊዜ በጽኑዕ ሥቃይ እንዲአሠቃዩአቸው አዘዘ። በሥቃይም ውስጥ እያሉ ሕዝቡን በማስተማር ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሃይማኖት ያጸኑአቸው ነበር። 🌹 የልባቸው ጥንካሬ በሥቃይም ውስጥ መታገሣቸውን ማስተማርንም አለመተዋቸውን በአየ ጊዜ ከእሳት ውስጥ እንዲጥሏቸው አዘዘ። በዚያንም ጊዜ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እጅ ነፍሳቸውን ሰጡ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ያዕቆብና በአገረ ፋርስ ኤጲስቆጶስ አባ ዮሐንስ በጸሎታቸው ይማረን። በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                           ✝ ✝ ✝ 🌹 #የደማስቆ_ኤጲስቆጶስ_ቅዱስ_ቶማስ፦ ይህ ቅዱስ በግብጽና በሶርያ እስላሞች በነገሡ ጊዜ በሰማዕትነት ያዐረፈ ነው። ይህንንም ቅዱስ ቶማስ ከመምህራኖቻቸው ውስጥ አንድ እስላም በተከራከረው ጊዜ ቅዱስ ቶማስ በረታበት ኢየሱስ ክርስቶስ ሰማይና ምድርን በውስጣቸው ያለውንም ሁሉ የፈጠረ አምላክ እንደሆነ በማስረዳት አይሎ ረታው። 🌹 ያም እስላም በዐፈረ ጊዜ ወደ መኰንናቸው ሒዶ "ይህ ክርስቲያናዊ ቶማስ ሃይማኖታችንን ረገመ" ብሎ ወነጀለው። መኰንኑም ወደርሱ አስቀርቦ "በውኑ ሃይማኖታችንን ትረግማለህን?" አለው። ቅዱሱም "መርገምስ ከአፌ አልወጣም ክርስቶስ እውነተኛ አምላክ እንደሆነ ከእርሱም ሕግ በኋላ ሌላ ሕግ እደማይመጣ አጽንቼ አስረዳሁት እንጂ" ብሎ መለሰለት። 🌹 መኰንኑም "የእኛስ ሕግ ከእግዚአብሔር ነውን? ወይስ አይደለም?" አለው ቅዱሱም "ከእግዚአብሔር አይደለም" አለው። በዚያንም ጊዜ መኰንኑ ተቆጣ ራሱንም በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘና ቅድስት ራሱን ቆረጡት። በመንግሥተ ሰማያትም የምስክርነት አክሊልን ኅዳር 4 ቀን ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በኤጲስቆጶስ በቅዱስ ቶማስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 4 ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ 🌹 "#ሰላም_ለቶማስ_ቢጸ_ዘካርያስ_መምህር። ኢጲስቆጶስ ዘደማስቀ ሀገር። እንዘ ተስፋ ሰማይ ይሬኢ በአይነ ምስጢር። ከመ ያኅድግዎ ስእኑ አፍቅሮተ ክርስቶስ ፍቁር። በመጥባሕት ስሑል ወበኵሉ ፃዕር"።  #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የኅዳር_4።                             ✝ ✝ ✝ 🌹 #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እስመ በእንቲአሁ ይቀትሉነ ኵሎ አሚረ። ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ። ንቃሕ እግዚኦ ለምንት ትነውም"። መዝ 43፥22-23። የሚነበቡት 2ኛ ቆሮ 11፥29-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 5፥9-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 9፥22-28። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ነው። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥32-ፍ.ም። መልካም የአባ አበይዶ የዕረፍት በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።               

🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹 🌹 #ኅዳር ፬ (4) ቀን። 🌹 እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ የዚህን ዓለም ሥራ ለተዉ #ለአባ_ዮሐኒ ደቀ መዝሙር ለሆኑት ለታላ
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹            🌹 #ኅዳር ፬ (4) ቀን። 🌹 እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ የዚህን ዓለም ሥራ ለተዉ #ለአባ_ዮሐኒ ደቀ መዝሙር ለሆኑት ለታላቁ አባት #ለአባ_አበይዶ_ለዕረፍት_በዓል በሰላም አደረሰን።                           ✝ ✝ ✝ 🌹 "#ብፁዕ_ውእቱ_አባ_አበይዶ ረድአ ዘኮኖ #ለአባ_ዮሐኒ ብፁዕ ብእሲ በትዕግሥቱ ዘፈጸመ ገድሎ"። ትርጉም፦ #ለአባ_ዮሐኒ_አገልጋይ የኾነው #አባ_አበይዶ ንኡድ ክቡር ነው፤ ተጋድሎውን በትዕግሥቱ የፈጸመ የኾነ ርሱም ንኡድ ክቡር ነው። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።                           ✝ ✝ ✝ 🌹 "#ሰላም_ለአባ_አብይዶ ለጸላኢ ዘኬዶ"። ትርጉም፦ ጠላትን የረገጠው ለኾነ #ለአባ_አበይዶ_ሰላምታ_ይገባል። #ሊቁ_አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ_በተአምኆ_ቅዱሳን_ላይ።

🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹             🌹 #ኅዳር ፫ (3) ቀን። 🌹 እንኳን #ከቆሮንቶስ_አገር_ለሆነ ከኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ #አባ_ቄርሎስም በመሆን የክብር ባለቤት የሆነ መንፈስ ቅዱስን ስለ አቃለለ መቅዶንዮስ #መቶ_ሃምሳው_የኤጲስቆጶሳት_አንድነት_ጉባኤ #በቊስጥንጥንያ በተደረገ ጊዜ አብሮት ለሆደ #ለቅዱስ_አባት_ለአባ_ኪርያቆስ ለዕረፍት በዓል፣ #ለአባ_አትናቴዎስና_ለእህቱ_ለቅድስት_ኢራኢ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                            ✝ ✝ ✝ 🌹 #ከቆሮንቶስ_አገር_የሆነ_ቅዱስ_አባት #አባ_ኪርያቆስ፦ የዚህም አባት ወላጆቹ ሃይማኖታቸው የቀና የከበሩ ናቸው የቤተ ክርስቲያንን ትምህርትና የቀናች ሃይማኖትን አስተማሩት ከዚህም በኋላ የቆሮንቶስ አገር ኤጲስቆጶስ ወደ ሆነ ወደ አባ ጴጥሮስ አቀረቡት እርሱም በላዩ ጸልዮ አናጒንስጢነት ሾመው ለአባ ጴጥሮስም የወንድሙ ልጅ ነው። 🌹 ከዚህም በኋላ ዘወትር መጻሕፍትን የሚያነብ የቃላቸውንም ትርጓሜ የሚመረምር የቤተ ክርስቲያንንም ሥርዓቷንና ሕጓን የሚያጸና ሆነ በትምህርቱና በእውቀቱም ከብዙዎች ከፍ ከፍ አለ ኤጲስቆጶሱም መጻሕፍት ማንበብን እንዳያቋርጥ ያዝዘው ነበር እነርሱም በሕዝቡ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለኢጲስቆጶሱ በእርሱ ደስ ይለው ነበርና። 🌹 ዕድሜውም ዐሥራ ስምንት ዓመት በሆነ ጊዜ ሚስትን ያጩለት ዘንድ ወላጆቹ ጠየቁት እርሱ ግን ይህን አልወደደም ግን ከገዳማት ወዳንዱ ይሔድ ዘንድ እንዲአሰናብቱት ወላጆቹን ለመናቸው። ከዚያም በኋላ አዘውትሮ ወደ ገዳማት የሚሒድና ወደ ወላጆቹ የሚመለስ ሆነ። መመላለሱም ከበዛ ዘንድ የከበረች የምንኲስናን ልብስ ሊለብስ ወደ ወደ ኢየሩሳሌም ሔደ ከኢየሩሳሌሙ ኤጲስቆጶስ ከአባ ቄርሎስ ጋር ተገናኝቶ ስለ ምንኲስና ኀሳብን ሁሉ ነገረው። እርሱም "በጎ ሥራን ወደሃል" አለው ታላቅ አባትም እንደሚሆንና በእርሱም የብዙዎች ነፍሳት ብሩሃን እንደሚሆኑ ትንቢት ተናገረለት። 🌹 ከዚህም በኋላ የመነኰሳት አባት ወደ ሆነ በፍልስጥዔም ወደ ሚኖር ወደ ክቡር አባ ሮማኖስ ላከው እርሱም በደስታ ተቀብሎ የምንኲስናን ልብስ አለበሰው። የምንኲስናንም ሥርዓት ያስተምረው ዘንድ የሰይጣንንም ተንኰል ያስረዳው ዘንድ በዚያው ገዳም ለሚኖር አንድ አረጋዊ ሰጠው። ከዚህም በኋላ በጾም በጸሎት በስግደት በመትጋት በታላቅ ድካም በቀንና በሌሊት በገድል ተጸምዶ በትዕግሥት በትሕትና በቅንነት ኖረ። 🌹 እግዚአብሔርም የመፈወስን ሀብት ሰጥቶት ወደርሱ የሚመጡትን በሽተኞች ሁሉ የሚፈውሳቸው ሆነ የትሩፋቱና የቅድስናውም ዜና በሁሉ ቦታ ተሰማ። የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ አባ ቄርሎስም የክብር ባለቤት የሆነ መንፈስ ቅዱስን ስለ አቃለለ መቅዶንዮስ መቶ ሃምሳው የኤጲስቆጶሳት አንድነት ወደሚሰበሰቡበት ወደ ቊስጥንጥንያ በሚሔድ ጊዜ ይህን አባት ኪርቆስን አባ ቄርሎስ ከእርሱ ጋር ወሰደው በላያቸው በአደረ መንፈስ ቅዱስ ስም ተከራክረው ከሀዲ መቅዶንዮስን ረቱት ከምዕመናንም ለይተው አሳደዱት። 🌹 ከዚህም በኋላ በመልካም ሽምግልና እግዚአብሔርን አገልግሎ ኅዳር 3 ቀን በሰላም ዐረፈ። ከዕረፍቱም በኋላ እግዚአብሔር ድንቆች የሆኑ ብዙ ተአምራትን ከሥጋው ገለጠ ከእርሳቸውም አንዱ ከኢየሩሳሌም ገዳማት በአንዱ ሥጋው ይኖራል። ከዐረፈበት ጊዜ ጀምሮ እሰሰከ ዛሬ ሥጋው አልተለወጠም ወደ ኢየሩሳሌም የሚሔዱ ሁሉ ያዩታል እነርሱም በቅርብ ጊዜ እንዳረፈ ያስባሉ እርሱ ግን ያረፈው ለአኖሬዎስና ለአርቃዴዎስ አባታቸው በሆነ በታላቁ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ዘመን ነው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ኪርያቆስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                           ✝ ✝ ✝ 🌹 #አባ_አትናቴዎስና_እኅቱ_ቅድስት_ኢራኢ፦ እሊህንም ቅዱሳን ከሀዲ ንጉሥ መክስምያኖስ ጽኑዕ የሆነ ሥቃይን አሠቃያቸው። በማሠቃየትም በደከመ ጊዜ ዕራቁታቸውን ከጒድጓድ ጨመራቸው በላያቸውም የጒድጓዱን አፍ ዘጋ በውስጧም ነፍሳቸውን አሳለፉ የሰማዕታት አክሊልንም ተቀበሉ በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 3 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ 🌹 "#ሰላም_ወአምኃ_ለኪርያቆስ_አፌኑ። ወተአምሪሁ እዜኑ። ለእለ ይምጽኡ ሕዝብ ይርአይዎ ውስተ መካኑ። ይትረከብ ከዊኖ ሐዲሰ በድኑ። እንዘ ሰዓ ሞቱ ርኁቅ ወጒዱንይ ዘመኑ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የኅዳር_3።              

🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹              🌹 #ኅዳር ፫ (3) ቀን። 🌹 እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ከኢየሩሳሌም አፈር አምጥተው ዋልድባ ሲደርሱ መነኰሳቱ "ገዳሙ በአህያ አታስረግጥ" ቢሏቸው #አህዮቹን_ክንፍ_አውጥተው_እንዲበሩ_ላደረጉት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ፍሬ_ካህንና_ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን።                              ✝ ✝ ✝ 🌹 #አቡነ_ፍሬ_ካህን፡- ጻድቁን በመጀመሪያ ከጎጃም ተነሥተው በታዘዘ መልአክ መሪነት ትግራይ ደብረ በንኰል አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ገዳም ሄደው መንነው መነኰሱ፡፡ ጻድቁ ስድስት ክንፍ የተሰጣቸው ሲሆኑ በታላቅ መንፈሳዊ ተጋድሎ ይታወቃሉ፡፡ አቡነ ፍሬ ካህን ወንጌልን ሲሰብኩ ሙታንን እያስነሡ በሲኦል ውስጥ ስላለው መከራና ሥቃይ እንዲመሰክሩ ያደርጓቸው ነበር፡፡ ጻድቁ ሐይዳ ገዳም ታቦት ተቀርጾላቸው ገድል የተጻፈላቸው ቢሆንም ሙሉ ገድላቸው ታትሞ ለምእመኑ አልተዳረሰም፡፡ አቡነ ቶማስ ካረፉ በኋላ አቡነ ፍሬ ካህን ገዳማቸውን ተረክበው በጽድቅ መንገድ መነኰሳቱን አስተዳድረዋል፡፡ አቡነ ፍሬ ካህን አፈር ከኢየሩሳሌም አምጥተው ዋልድባ ሲደርሱ መነኰሳቱ "ገዳሙን በአህያ አታስረግጥ" ቢሏቸው አህዮቹን ክንፍ አውጥተው እንዲበሩ አድርገዋቸዋል፡፡ 🌹 አባታችን ሽሬ ደብረ ሐይዳ አቡነ ፍሬ ካህን የተባለ ትልቅ ገዳም አላቸው፡፡ ገዳሙ ከአቡነ ቶማስ ዘሐይዳ ገዳም ጋር አንድ ነው፡፡ ወደዚህ ገዳም ውስጥ ሥጋና ቅቤ ተበልቶም ሆነ ተይዞ መውጣት ፈጽሞ አይቻልም፡፡ አልታየሁም ተብሎ በድብቅ ሥጋ ተይዞ ቢገባ ሥጋው ይተላል፡፡ ሥጋና ቅቤ የበላ ሰውም ዕለቱን በድፍረት ወደ ገዳሙ ቢገባ ሆዱ በኃይል ይነፋል በዚህም ይታወቅበታል፡፡ ከብቶችም ቢሆኑ ወደ ገዳሙ አይወጡም፣ ማንም ሳይመልሳቸው ራሳቸው ይመለሳሉ፡፡ የአቡነ ፍሬ ካህን ዕረፍታቸው ኅዳር 3 ነው፡፡ ከአቡነ ፍሬ ካህን እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን፣ በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።             

                             ✝ ✝ ✝ 🌹 #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወዘሕጎ ያነብብ መዓልተ ወሌሊተ። ወከውን ከመ ዕፅ እንተ ትክልት ኀበ ሙኃዘ ማይ። እንተ ትሁብ ፍሬሃ በበጊዜሃ"። መዝ 1፥2-3። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 4፥6-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 2፥15-22፣ የሐዋ ሥራ 19፥8-11። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 12፥9-14። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የጻድቁ ንጉሥ የቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ከሞት የተሰወረበት (የስዋሬ) በዓል፣ የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ፣ የአቡነ ፍሬ ካህን፣ የአቡነ ዓምደ ሚካኤል የዕረፍታቸውና የጾም ጊዜ በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።          

🌹 አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባንም አመንኵሰው መርቀው ሲሸኟቸው እንዲያገለግሏቸው አንበሶችን ከጫካ ጠርተው ያዘዙላቸው አባታቸው አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ናቸው፡፡ የዋልድባው አቡነ ሳሙኤል አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ከመነኰሱ በኋላ በደብረ በንኰል 12 ዓመት አባታችንን ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ እሳት እስከማያቃጥላቸው ድረስ ከብቃት ደረጃ ላይ ሲደርሱ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ መርቀው በማሰናበት በዓት እንዲያጸኑ ሲያደርጓቸው አቡነ ሳሙኤል በቅዱስ ሚካኤል መሪነት ጣና ደሴት ገብተው ሱባኤ ያዙ፡፡ በዚያም ሳሉ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ማረፋቸውን በመንፈስ ዐውቀው ሲያለቅሱ ጌታችን የአቡነ መድኃኒነ እግዚእን ነፍስ በእቅፉ አድርጎ ወደ ገነት ሲያሳርጋት አሳያቸው፡፡ ወዲያውም ጌታችን በብርሃን ሰረገላ አድርጎ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባን ደብረ በንኰል አድርሷቸዋል፡፡ በዚያም እስከ 40ኛው ቀን ከቆዩ በኋላ በዚሁ ዕለት ሲቀድሱ ክንድ ከስንዝር ከመሬት ከፍ ብለው ቅዱሳን ሐዋርያት እየተራዱዋቸው ከቀደሱ በኋላ ወደነበሩበት መልሷቸዋል፡፡ የጻዲቁ የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዕረፍታቸው ኅዳር 3 ቀን 1360 ዓ.ም ሲሆን ጠቅላላ ዕድሙያቸውም 180 ዓመት ነው፡፡ 🌹 ዐፄ ፋሲል ጻድቁ የተከሏቸውን የጥድ ዛፎች በሙሉ ተቆርጠው የአክሱም ቤተ ክርስቲያን እንዲሠራበት አዋጅ አወጁና መልእክተኞች መጥተው ዛፎቹን ሲቆርጡ መነኰሳቱ ግን "ጻድቁ አባታችን የተከሏቸው የጥድ ዛፎች መቆረጥ የለባቸውም" ብለው ቢከራከሩም ሰሚ አላገኙም፡፡ መነኰሳቱም ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክቱ ጩኸታቸው ተሰምቶላቸው ወዲያው እየተቆረጡ ያሉት የጥድ ዛፎች በሙሉ በተአምራት ወደ ወይራ ዛፍነት ተለወጡ፡፡ የወይራ ዛፎቹም ለዐፀድ እንጂ ለሕንፃ የማይመቹ ጎባጣ ሆኑ፡፡ የዚህም ምልክቱ ዛሬም ድረስ አለ፡፡ ግንዱ ጥድ ዛፉ ግን ወይራ የሆነ ትልቅ ዛፍ "ወይራ ዘገብረ ተአምር" በሚባል ቦታ አሁንም ድረስ ቆሞ ይታያል፡፡ 🌹 ጻድቁ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ በ1312 ዓ.ም የመሠረቱት ገዳማቸው ደብረ በንኰል ከአክሱም በእግር ሦስት ሰዓት ያስኬዳል፡፡ ይኸውም በንግሥተ ሳባ ቤተ መንግሥት አድርጎ የቀዳማዊ ሚኒሊክን መቃነ መቃብር አልፎ በመሄድ ነው፡፡ ወይም በመኪና ለመጓዝ አክሱም ጉበዱራን አቋርጦ ውቅሮ ማራይ ከተማን አልፎ በስተ ሰሜን አቅጣጫ 10 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ በስተ ምዕራብ የአቡነ አላኒቆስ ዘማይበራዝዮን ገዳም፣ በስተ ምሥራቅ የአቡነ ሰላማን ገዳም እየተለመከቱ እንደተጓዙ ጥቅጥቅ ባለ ደን የተሸፈነውን ደብረ በንኰልን ያገኙታል፡፡ ኅዳር 20 ጻድቁ ስለሚነግሱ ገዳሙም ለአክሱም ቅርብ ስለሆነ ይህ ለአክሱም ጽዮን ተጓዦች ተጨማሪ ትልቅ በረከት ነው፡፡ 🌹 ደብረ በንኰል ማለት "ሙራደ ቃል" ማለት ነው፡፡ ትርጉሙም የምሥጢር መውረጃ ማለት ነው፡፡ በቦታው ላይ ሱባኤ ለያዘ ሰው እንደ ቅዱስ ያሬድና እንደ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ምሥጢር እንደሚገለጥለት የሚጠቁም ነው፡፡ በ14ኛው መ/ክ/ዘ የነበሩት ደጋግ መነኰሳት ሕይወታቸውን በሙሉ በምንኵስና፣ በጸሎትና በታላቅ ተጋድሎ መኖር ሲፈልጉ ከደብረ ዳሞ፣ ከሐይቅ እስጢፋኖስ፣ ከደብረ ሊባኖስና ከሌሎቹም የሀገራችን ክፍሎች እየተነሡ ወደ ደብረ በንኰል አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ገዳም ነበር የሚሄዱት፡፡ 🌹 የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ቃልኪዳን፡- ጻድቁ ባርከው ያፈለቁት ጸበላቸው ላበደ ሰው መድኃኒት ነው፡፡ ከመቃብራቸው ላይ የሚነሣውን አፈር ጻድቁ ባርከው ባፈለቁት ጸበላቸው ታሽቶ በእጃቸው መስቀል ተባርኮና ታሽቶ የሚዘጋቸውን የአቡነ መድኃኒነ እግዚእን እምነታቸውን በእምነት ሆኖ የያዘን ሰው ንብረቱን ሌባ ቀማኛ ዘራፊ አይሰርቀውም፤ የመኪና አደጋ አይደርስበትም፤ ጥይት አይመታውም፡፡ "በእምነት ሆኖ የያዘን ሰው" መባሉን ልብ ይሏል፡፡ ይኸውም ለጻድቁ የተሰጣቸው ታላቅ ቃልኪዳን ነው፡፡ ከአቡነ መድኃኒነ እግዚእ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን፣ በጸሎታቸው ይማረን!።                              ✝ ✝ ✝ 🌹 #አቡነ_ዓምደ_ሚካኤል፡- ትውልዳቸው ወሎ ቦረና ነው፡፡ ወላጆቻቸው ገላውዲዮስና ኤልሳቤጥ ሁለቱም በሃይማኖትና በዓለም ገንዘብ የበለጸጉ ናቸው፡፡ ይህንንም ጻድቅ ልጃቸውን የአርባዕቱ እንስሳ በዓል ዕለት ወለዱትና ስሙን ዓምደ ሚካኤል ብለው ጠሩት፡፡ ለዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ፣ ለዐፄ በእደ ማርያምና ለዐፄ እስክንድር የሠራዊት አለቃ የነበረ ጻድቅ ነው፡፡ በአንድ ዓመቱ ወላጆቹ ወደ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ይዘውት እንደሄዱ ከወላጆቹ ተለይቶ ጠፍቶ ሳይገኝ ቀረ፡፡ መልአክም ከቤተ መቅደስ አግብቶ እየመገበው 3 ቀን አቆይቶታል፡፡ በ3 ኛው ቀን ቄሱ ሊያጥን ሲገባ በከርሰ ሐመሩ ውስጥ ሕፃኑን አገኘውና ወስዶ ለወላጆቹ ሰጣቸው፡፡ 🌹 ባደገም ጊዜ በመመጽወትና አብያተ ክርስቲያናትን በማደስ የሚተጋ ሆነ፡፡ ለድኆችም በቅንነት በመፍረድ በታላቅ ተጋድሎ የሚኖር ሆነ፡፡ ለነገሥታም ገዥ ከሆነ በኋላ በጸሎቱና በበረከቱ በሀገራችን ላይ ሁሉ ሰላም ሆነ፡፡ ጠላቶችም ሁሉ ለነገሥታቱ ተገዝተው ይገብሩ ነበር፡፡ በበጎ ምግባሩ የቀኑ ዐመፀኞችም በክፋ ተነሡበት፡፡ ጻድቁ በመንፈስ አድጎ መንኵሶ በታላቅ ተጋድሎ ሲኖር ነገር ሠሪዎች በሐሰት ወንጅለው ከሰሱት፡፡ ንጉሡም እጅግ ስለሚወደው የራራለት ቢሆንም በነገራቸው ባስጨነቁት ጊዜ ወደ ሩቅ አገር አስሮ አጋዘው፡፡ አባታችንም በግፍ ታስረው ሳሉ በእስር ቤቱ ውስጥ ብርሃን ወረደላቸው፣ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤልም ሰማያዊ መና እያመጣ ይመግባቸው ነበር፡፡ የጌታችንንም ሥና ደም በሰንበት እያመጣለቸው ያቆርባቸው ነበር፡፡ ነገረ ሠሪዎቹ ይገድሏቸው ዘንድ ንጉሡን ለመኑት፡፡ በዓመፃቸውም ብዛት ወደ ፍርድ ሸንጎ አምጥተው ገደሏቸው፡፡ 🌹 አንድ ጻድቅ መነኩሴ የቅዱስ ዓምደ ሚካኤልን ሥጋ ሦስት ቅዱሳን መላእክት ሲያጥኑ አገኛቸውና ያየውን ለሕዝቡ ተናገረ፡፡ በሌላም ጊዜ የብርሃን ፋና ከሰማይ ሲወርድላቸው ብዙ ቀን የተመለከቱ ብዙ ቅዱሳን ምስክርነታቸውን ሰጡ፡፡ ንጉሡም ይህንን ሁሉ ሲሰማ በአሳቾቹ ልበ ደንዳናነትና ክፋት እጅግ ተጸጽቶ በሞት ቀጣቸው፡፡ ቅዱስ ዓምደ ሚካኤልንም በአባቶች መቃብር በክብር አስቀበራቸው፡፡ ስማቸውንም በበጎ እንጂ በክፋ ማንም እንዳያነሳቸው በአዋጅ አስነገረ፡፡ መታሰቢያም አቆመላቸው፡፡ 🌹 ከዚህም በኋላ ዐፄ ልብነ ድንግል በነገሠ ጊዜ የአባቱን የበእደ ማርያምን ቃል ኪዳን ሰምቶ ዐፅማቸውን አፍልሶ ወደ አትሮንስ ማርያም ወሰደውና በቅዱሳን ነገሥታት መቃብር በክብር አኖረው፡፡ ሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ አረጋም ጻድቁ ሲያርፉ በደብረ ሊባኖስ ገዳም የተቀበሩ ቢሆንም ከብዙ ዘመን በኋላ ዐፅማቸውን አፍልሰው በተድባበ ማርያም እንደቀበሯቸው ጽፈዋል፡፡ ከአቡነ ዓምደ ሚካኤል እግዚአብሔር አምላክረድኤት በረከትን ያሳትፈን፣ በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ።                            ✝ ✝ ✝  🌹"#ሰላም_ለእርስከ_ዘተከለለ_ቆብዐ። አርአያ አክሊሉ ለክርስቶስ በዲበ መስቀል ሶበ ተመርዐ። #መድኃኒነ_እግዚእ አፋየ አመ ስመከ ጸውዐ። ነዓ ነዓ ምስለ ሳሙኤል ነዓ። ምስሌየ ትግበር ሰላም ወስንዓ። ሊቀ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የኅዳር 3።

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ - Статистика и аналитика Telegram-канала @finote_media