ru
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

Открыть в Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

Больше
636
Подписчики
Нет данных24 часа
-47 дней
-1230 день
Архив постов
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #ግንቦት ፲፯ (17) ቀን። ❤ እንኳን #ለታላቁና_ለተመሰገነው_ለቆጵሮስ ኤጲስቆጶስ #ለቅዱስ_አባ_ኤጲፋንዮ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ #ቅዱስ_ኤፋንዮስን ወደ ክርስትና ከመራው #ከአባ_ሉክያኖስ ከመታሰቢያው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱስ_አባ_ኤጲፋንዮስ፦ ይህም ቅዱስ ከቤተ ገብርኤል ዐፀድ አቅራቢያ ነው ወላጆቹም በኦሪት ሕግ የጸኑ አይሁድ ናቸው። እነርሱም ድኆች ናቸው አባቱም ገባር ስለ ነበር ይህን ቅዱስና አንዲት እኅቱን ሳያሳድጋቸው ሞተ እርሱም ክፉ አህያ ነበረውና የተወላቸው እርሱን ነው እናታቸውም የኦሪትን ትምህርት በማስተማር አሳደገቻቸው። ❤ እናቱም አህያውን እንዲሸጠውና ከእርሱም እንዲያርፍ በሺያጩም እንዲረዳ ቅዱስ ኤጲፋንዮስን መከረችው። ሊሸጠውም ከአህያው ጋራ ሲጓዝ አንድ ክርስቲያን ጻድቅ ሰው ስሙ ፊላታዎስ የሚባል ተገናኘው ያንን አህያ ሊገዛ ወዶ ከቅዱስ ኤጲፋንዮስ ጋራ ቁሞ ሲነጋገር ያን ጊዜ አህያው ቅዱስ ኤጲፋንዮስን ኵላሊቱን ረገጠው በምድር ላይ ወድቆ ለመሞት ደረሰ። አባ ፊላታዎስም በመስቀል ምልክት ኵላሊቱ ላይ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ብሎ አማተበ ቅዱስ ኤጲፋንዮስም ያን ጊዜ ከሕማሙ ድኖ ተነሣ ከቶ ምንም ሕማም እንዳልነካው ሆነ። ከዚህ በኋላም አባ ፊላታዎስ በዚያ ክፉ አህያ ላይ እንዲህ ብሎ ጮኸ "ስለ እኛ በተሰቀለው በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ትሞት ዘንድ ይገባል" ወዲያውኑ ያ አህያ ወድቆ ሞተ። ቅዱስ ኤጲፋንዮስም እሊህን ሁለት ተአምራት አይቶ "በስሙ ተአምራት የምታደርግበት የተሰቀለ ኢየሱስ ክርስቶስ ማነው?" አባ ፊላታዎስን ጠየቀው። እርሱም እንዲህ ብሎ መለሰለት "የክብር ባለቤት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ በኢየሩሳሌም አይሁድ የሰቀሉት ነው" አለው ይህም ነገር በቅዱስ ኤጲፋንዮስ ልብ ተቀረጸ። ❤ በዚያም ወራት አንድ ባለጠጋ አይሁዳዊ ነበር ኤጲፋንዮስንም ወሰደው የኦሪትንም ሕግ በማስተማር አሳደገው። የሚሞትበትም በቀረበ ጊዜ ልጅ ስሌለው ጥሪቱን ሁሉ አወረሰው የኦሪትንም ሕግ ትምህርት ሁሉ ተማረ። ❤ በአንዲት ዕለትም ስሙ ሉክያኖስ ከሚባል መነኰስ ጋራ ተገናኘ እርሱም የተማረና የእግዚአብሔር ጸጋ ያደረበት ነው ከእርሱ ጋራ ተጓዘ። ሁሉቱም በአንድነት ሲጓዙ ድኃ ሰው አገኛቸውና ምጽዋትን እንዲሰጠው ያንን መነኰስ ለመነው። ገንዘብም ስለሌለው የሚለብሰውን  የጸጉር ዐጽፍ አውልቆ ለድኃው ሰጠው በዚያን ጊዜ ለዚያ መነኰስ የብርሃን ልብስ ከሰማይ ሲወርድለት ኤጲፋንዮስ አየ። ስለዚህም ድንቅ ተአምር አደነቀ ከመነኰስ እግር በታች ሰግዶ "አንተ ማህን ሃይማኖትህስ ምንድ ነው?" ብሎ ጠየቀው እርሱም "ክርስቲያን እንደሆነ" ነገረው። ደግሞ ክርስቲያን እንዲያደርገው ለመነው መነኵሴውም ኤጲፋንዮስን  ወስዶ ወደ አንድ ኤጲስቆጶስ አደረሰው። እርሱም የክርስትና ጥምቀትን አጥምቆ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሥርዓቷንም ሁሉ አስተማረው። ❤ ኤጲፋንዮስም ኤጲስቆጶሱን "እኔ መነኰስ መሆን እፈልጋለሁ" አለው ኤጲስቆጶሱም "ብዙ ገንዘብ  እያለህ መነኰስ መሆን አይገባም" አለው። ኤጲፋንዮስም ሒዶ እኅቱን አምጥቶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃት ገንዘቡን ሁሉ ለድኆችና ለምስኪኖች ለባልቴቶችና ለሙት ልጆች አብያተ ክርስቲያናትም ሰጠ መጻሕፍትንም ከእርሱ ገዛ። ❤ ከዚህ በኋላ መነኰሰ ለእርሱም ለእኅቱም ለጥምቀት ምክንያት ወደሆነው ስሙ ሉክያኖስ ወደተባለው መነኰስ ገዳም ገባ ዕድሜውም ዐሥራ ሰድስት ዓመት ነበር። ከዚህም በኋላ ታላቁን አባ ኢላርዮስን አገኘው እርሱም በዕድሜው ጐልማሳ በገድልም ሽማግሌ ነው። ቅዱስ ኤጲፋንዮስንም ተቀብሎ የምንኵስናን ሕግና የክርስትናን ሥርዓት አስተማረው የእግዚአብሔር ጸጋ አድሮበት የቤተ ክርስቲያንን ሕግና ሥርዓት የምንኵስናንም ሕግ በጥቂት ቀኖች አጠና። ❤ ከዚህ በኋላ ታላላቅ ተአምራቶችን በመሥራት ሙታንን እስሚአስነሣቸው ሰይጣናትን ከሰዎች ላይ እስከሚያስወጣቸው ውኃ ከሌለበት ከደረቅ ቦታ ውኃን እስከሚአፈልቅ ያለ ጊዜውም ብዙ ዝናምን እስከ ማውረድ ደርሶ በገድልና በትሩፋት ፍጹም ሆነ። የትሩፋቱም ወሬ አዋቂነቱም ተሰማ ከእርሱ ጋራም ሊከራከሩ ብዙ አይሁድ ወደ እርሱ መጡ። ስሕተተታቸውንም ገለጠላቸው በእርሱ ትምህርት አምነው የክርስትናን ጥምቀት አጠመቃቸው። እንዲሁም ጥበበኞች ዮናናውያን በትምህርቱ ተመለሱ ወደ ክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሃይማኖትም ውስጥ ገቡ። ❤ መምህሩ ቅዱስ ኢላርዮስም በቆጵሮስ አገር  ኤጲስቆጶስነት እንደሚሾም ትንቢት ተናገረለት። ወደዚያም ሒዶ በታዘዘለት ቦታ በዚያ እንዲኖር አዘዘው። እንዲህም አለው "ኤጲስቆጶስነት ሊሾሙህ በፈለጉህ ጊዜ እምቢ አትበል ይህ በእግዚአብሔር ፈቃድ ሁኖአልና"። ቅዱስ ኤጲፋንዮስም ወደ ቆጵሮስ ሒዶ መምህሩ ቅዱስ ኢላርዮስ በአዘዘው ቦታ ተቀመጠ። ❤ የቆጵሮስ ደሴት ኤጲስቆጶስም በዐረፈ ጊዜ በዚያን ሰሞን ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ምግቡን ሊገዛ ወደ ገበያ ገባ። ከእርሱም ጋራ ሁለት መነኰሳት አሉ። ደግሞም በዚያች ገዳም ጻድቅ የሆነ ሽማግሌ ኤጲስቆጶስ ነበረ ለእርሱም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ ብሎ ነገረው "ወደ ገበያም ሒድ በእጁም ሁለት የወይን ዘለላ የያዘ መነኰስ ታገኛለህ ከእርሱ ጋራም ሁለት መነኰሳት አሉ ስሙንም ጠይቀው። ስሜ ኤጲፋንዮስ ነው ይልሃል እርሱን ያዝ በእጁ ያለውንም አስጥለህ ከአንተ ጋራ አምጣው" አለው። ያ ኤጲስቆጶስ የክብር ባለቤት ጌታችን እንደ አዘወው አደረገ በአለመለከተውም ቦታ አግኝቶ ይዞ ወደ ቤተ ክርስቲያን ወስዶ ዲቁና ሾመው። በሦስተኛውም ቀን ኤጲስቆጶስነት ሾመው። ❤ ከዚህም በኋላ ሽማግሌው ኤጲስቆጶስ የኤጲፋንዮስን ልብ ደስ ለማሰኘት ሽቶ ስለ ኤጲፋንዮስ ያየውን ራእይ ለሕዝቡ ገለጠላቸው። ስለ ርሱም ታላቅ ደስታ ሆነላቸው። ይህም ቅዱስ እግዚአብሔር በሚወድለት በሹመቱ ሁኖ በበጎ ሥራ ላይ ጸና። ጥቅም ያላቸውን ብዙ ድርሳኖችንም ደረሰ። ርኅራኄ ስለ ሌለው ሰው በሚሰማ ጊዜ ተመልሶ ቸር እስከሚሆን ድረስ ሁል ጊዜ ይገሥጸዋል ይመክረዋል። ❤ በኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ በአባ ዮሐንስ ላይ ምክንያት ፈጠረ ስለ ርሱ ርኅራኄ እንደሌለው በሰማ ጊዜ ከወርቅ የተሠሩ የማዕዱን ዕቃዎች የሚመገብባቸውን በውሰት ወሰደ። እነርሱም በወርቅና ብር ናቸው ቅዱስ ኤጲፋንዮስም ሸጣቸውና ለድኆችና ለምስኪኖችም መጸወታቸው። አባ ዮሐንስም እንዲመልስለት በሻ ጊዜ ምንም ምን አልሰጠውም በክብር ባለቤት ጌታ መቃብር ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቅዱስ ኤጲፋንዮስን የልብሱን ጫፍ ስጠኝ ብሎ ያዘው። ቅዱስ ኤጲፋንዮስም ወደ እግዚአብሔር ጸለየ የአባ ዮሐንስም ዐይኖቹ ያንጊዜ ታወሩ። ከዚህ በኋላም ይምረው ዘንድ በብዙ ልቅሶ ወደርሱ ፈጽሞ ማለደ ዐይኖቹንም ይገልጥለት ዘንድ ለመነው። ሁለተኛም ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ጸለየ አንድ ዐይኑንም ገለጠለት የማዕዱንም ዕቃዎች ሽጦ ለድኆችና ለምስኪኖች እንደሰጣቸው ነገረው።

                         ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ዕብል_ለሲራክ_ፍጹም። #ወልደ_አልዓዛር ዘኢየሩሳሌም። ቈሪር ማይ ከመ ያጠፍኦ ለፍሕም። ያጠፍእ ይቤ መጽዊቶ ብእሲ ድኩም። ኃጣውኢሆሙ ለሥጋ ወደም"፡፡ #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የግንቦት_16።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "አመ ትሠምር መሥዋዕተ ጽድቅ። መባዓኒ ወቊርባነኒ። አሜሃ ያዐርጉ ውስተ ምሥዋዒከ አልሕምተ"። መዝ 50፥19። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 14፥29-ፍ.ም።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወአርመመ ማዕበል። ወተፈስሥሑ እስመ አዕረፋ። ወመርሆሙ ውስተ ምርሶ ኀበ ፈቀዱ"። መዝ 106፥29-30። የሚነበቡት መልዕክታት ቈላ 2፥1-6፣ ራእ.ዮሐ 1፥1-12 ወይም 1ኛ ዮሐ 1፥1-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 8፥14-26። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 21፥20-25። የሚቀደሰው ቅዳሴ የወልደ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቅዳሴ ነው። መልካም የሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ የመታሰቢያ በዓልና የቅዱስ ሢራክ የዕረፍት በዓልና የበዓለ ሃምሳ ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን ፡፡

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ግንቦት ፲፮ (16) ቀን። ❤ እንኳን #ለሐዋርያው_ለወልደ_ነጐድጓድ #ለቅዱስ_ዮሐንስ በእስክድርያ ቅዳሴ ቤቱ፣ በኤፊሶን መከራና ስብከቱ፣ በደሴተ ፍጥሞ ግዞቱ ለሚታሰብበት ዓመታዊ በዓልና ዕውቀትን ከልቡ ላፈለቀ ለኢየሩሳሌሙ ሰው #ለአልዓዛር_ልጅ_ለቅዱስ_ኢያሱ_ሢራክ ለዕረፍት በዓል መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚህ ከሚታሰበው፦ በሰማዕትነት ከዐረፉ ኤጲስ ቆጶሳት #ከዮሴፍ_ልጅ_ይምንዋስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                     ✝ ✝ ✝ ❤ #በዚች_ቀን_ወንጌላዊ_ቅዱስ_ዮሐንስ መታሰቢያው ነው። በእስያና በኤፌሶን በዙሪያቸው በአሉ አገሮች ሁሉ ስለ መስበኩና ከባሕር በመስጠምም ወደ ፈጣሪያቸው እግዚአብሔር እስከ መለሳቸውና የክብር ባለቤት ጌታችን በእጆቹ ላይ በሚያደርገው ተአምራት በትምህርቶቹም ከሰይጣን ወጥመድ እስከ አዳናቸው ድረስ ጣዖታትን ከሚያመልኩ ከክፉዎች ሰዎች ስለደረሰበት መከራ ነው። ❤ በሸመገለም ጊዜ ወንጌልን ጻፈላቸው ሦስቱ ወንጌላውያን ያስቀሩትን እስከሚጽፍ መንፈስ ቅዱስ አነሣሥቶታልና የወልድንም አኗኗሩንና ሰው መሆኑን ዓለም የማይወስነውንም ተአምራትን። ❤ ከዚህ በኋላም ወደ ሰማይ እንደ ወጣና በሰማይ የሚኖሩ መላእክት ሠራዊት ሥርዓታቸውን አይቶ አቡቀለምሲስ የሚባለውን ጻፈ። ለስብከቱም የበዓሉ መታሰቢያ ሊሆን ግብጻውያን ይህን ሠሩ ዳግመኛም በእስክንድርያ አገር ውስጥ ቤተ ክርስቲያን የከበረችበት ቀን ነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በከበረ ሐዋርያ በቅዱስ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የአልዓዛር_ልጅ_ቅዱስ_ኢያሱ_ሢራክ፦ እርሱም ጥንተ ትንቢት "የባሕር አሸዋን የዝናም ጠብታን የዘመንን ቁጥር ማን ቈጠረ" አለ። ከአብ ጋራ ስለ አለው አንድነት "የጥበብ ምክሯንስ ማን አወቀ በእግዚአብሔር ዙፋን ላይ የምትቀመጥ እጅግ የምታስፈራ ናት" አለ። ሁለተኛም "እኔ ከልዑል አፍ ወጥቼ ምድርን እንደ ጉም ሸፈንኋት በሰማያትም እኖራለሁ ዙፋኔንም በደመና ምሰሶ ላይ ዘረጋሁ ብቻዬን በሰማይ ዳርቻ ዞርኩ በውቅያኖስም ጥልቅ ውስጥ ማረፊያ እየፈለግሁ በባሕሩ ውኃ ላይ ሁሉ ተመላለስኩ" አለች አለ። ስለ ወልደ እግዚአብሔር ሰው መሆን እንዲህ አለ "እግዚአብሔር በያዕቆብ ዘንድ እደሪ በእስራኤልም ዘንድ ተዋረሺ አለኝ አለች"። ❤ ደግሞ ስለ መድኃኒታችን ሞትና ስለ አይሁድ መጥፋት "በወጥመዱ ይጠመዳሉ የመሞቻቸው ጊዜም ሳይደርስ ይሠጥማሉ" አለ። ስለ ንስሓና ከንስሓ በኋላ ወደ ኃጢአት ስለ መመለስ እንዲህ አለ "ከታጠቡ በኋላ ቆሻሻን መዳሰስ ምን ይጠቅማል"። ❤ ደግሞ ስለ ቤተ ክርስቲያን መታነፅና ስለ ሕዝቡ እንዲህ አለ "አቤቱ በስምህ የተጠሩና በበረከት ያባዛኃቸውን ወገኖችህን ይቅር በል መመስገኛህና ማደሪያህ የሆነች አገርህ ኢየሩሳሌምንም ይቅር በል። የቃልህንም በረከት በጽዮንና በልጆቿ ላይ ምላ"። ❤ ስለ ሹማምንትና ስለ ሰባቱ መዐርጋት ሲናገር እንዲህ አለ "ሰባቱን ኃይሎች የተቀበለች የሰው ሰውነቱ ጉበኛ ናት። ከዚህም ሁሉ ጋር መንገድህን ያቀናልህ ዘንድ ወደ ልዑል እግዚአብሔር ጸልይ"። ❤ ስለ ጻድቃንም እንዲህ አለ "የጻድቃን ልጆች በዱር ጠል የዱር አበባ እንዲአብብ እንዲሁ ብቀሉ አብቡም እንደ ሊባኖስም መዓዛ መዓዛቹ እንዲሁ የጣፈጠ ይሁን" ዳግመኛም የእግዚአብሔር ሥራ ሲያስቡ እንዲህ "የሰማይ ንጽሕናውንና ጽናቱን ብርሃኑንም ያሳይ ዘንድ በሰማይ ገጽ ላይ ፀሓይን ማውጣቱን በቀትርም ጊዜ አገሩን ማቃጠሉን አስቦ እንደ ምድጃ እሳት የሚነድ ላቦቱን ማን ይቀወመዋል የፀሐይ ዋዕይ" ሦስተኛውም "ተራራችን ያቃጥላቸዋል ከእርሱም የእሳት ወላፈን ይወጣል" አለ። "ጨረቃም ለዓለም ምልክቱ ነው በእርሱም ዘመናት የበዓላት ምልክት ይታወቃል"። ስለ ከዋክብትም "የሰማይ ጌጦቿ የከዋክብት ብርሃናቸው ነው በእግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃድ እንዲሁ ያበራሉና በሥርዓታቸውም ጸንተው ከልካቸውም ሳይፋለሱ ሳይሳሳቱ ጸንተው ይኖራሉና" አለ። ስለ ቀስተ ደመናም ተናገረ "ቀስቱን አየሁ ፈጣሪውንም አከበረ ብርሃኑ መልካም ነውና የልዑል ሥልጣንም ያዘጋጀዋል"። ❤ ስለ በረድና መብረቅም ተናገረ ስለ እርሱ "ትዕዛዝም በረድ ይዘንማል በቃሉም መብረቅ ይፈጥናል ደመናትም እንደ አዕዋፍ ይበራሉ ነፋስም በእርሱ ፈቃድ ይነፍሳል የነጐድጓዱ ድምፅና ብልጭልጭታም ምድርን ያስፈራታል ዐውሎውና ውርጩ ነፍስን ያስጨንቃታል። ሰማይን እንደ ብረት ልብስ የሚሸፍነው እንደ ስለታም የብርጭቆ ስባሪ ይብለጨለጫል" አለ። ❤ ስለ ዝናምም ተናገረ "ዝናም የወረደ እንደሆነ ምድርን ደስ ያሰኛታል በትዕዛዙም ባሕር ይደርቃል" አለ። አባቶችንም በተሰጣቸው ሀብት ሲያመሰግናቸው "ኄኖክ እግዚአብሔርን ደስ እንዳሰኘው። ኖኅም ጻድቅ ሁኖ እንደተገኘ። አብርሃም ታማኝ እንደሆነ ይስሐቅም ለሰው ሁሉ የሚጠቅም በረከት እንደተሰጠው ለያዕቆብም በቸርነቱ እንደ ተገለጠለት ዐሥራ ሁለቱንም ነገድ እንደወለዳቸው በሰውና በእግዚአብሔርም ዘንድ እንደ ተወደዱ። ❤ ሙሴንም ስም አጠራሩ የከበረ የመላእክትም ብርሃን መልኩና ስም አጠራሩ የሆነ" አለ። ወንድሙ አሮንንም "የዘላለም ሕግን እንደ ሠራለት በልብሰ ተክህኖና በወርቅ አክሊል እንዳስደነቀው" አለ። ሹመቱ ሦስተኛ የሚሆን የአልዓዛር ልጅ ፊንሐንስም ወደሰ። ❤ የነዌ ልጅ ኢያሱን ለእስራኤል ልጆች የርስታቸውን ምድር እንዳወረሳቸው እጁንም በአነሣ ጊዜ እንደተመሰገነ። ሳሙኤልንም በእግዚአብሔር ዘንድ የተወደደ እንደሆነ ናታንንም በዳዊት ዘመን ትንቢት እንደተናገረ። ዳዊትንም ታናሽ ሁኖ ሳለ አርበኛውን ጎልያድን እንደገደለው አመስግኖታል ሰሎሞንንም በሰላም ወራት እንደነገሠ። ❤ ኤልያስንም ሙት እንዳስነሣ እሳትንም ከሰማይ እንዳወረደ ራሱም በእሳት ሠረገላና በእሳት ፈረሶች እንደዐረገ ኤልሳዕንም በዘመኑ ጠላቶች እንዳስደነገጡት ሁለት ሙታኖችንም እንዳስነሣ አንዱን በሕይወት ሳለ አንዱን ከሞተ በኋላ ። ❤ ሕዝቅያስንም አገሩን አጽንቶ እንደጠበቀ የፋርስንም ሠራዊት በጸሎቱ አጥፍቶ ስለ አገራቸው ጽዮን የሚያለቅሱትን ደስ እንዳሰኛቸው ርኵሰትንና ኃጢአትንም እንደ አስወገደ። ኢዮስያስንም የኢዮስያስ ስም አጠራሩ መልካም ነው እንዳለው። ❤ ኤርምያስንም ከእናቱ ማሕፀን ጀምሮ እንዳከበረው። ሕዝቅኤልም የእግዚአብሔርን ጌትነቱን እንዳየ። ዘሩባቤልንም በቀኝ እጅ እንዳ ኀቲም ቀለበት ነው እንዳለው። ዐሥራ ሁለቱ ነቢያትንም በየቦታቸው ዐፅማቸው እንደሚለመልም። ሆሴዕና ነህምያንም የወደቀች ቅጽርን አንሥተው ጠቃሚ ሥራ እንደሠሩ። ❤ ዮሴፍንም እርሱን የመሰለ ደግ ሰው እንዳልተወለደ። ኖኅና ሴምንም ክብራቸው ከሰው ሁሉ እንደሚበልጥ። አዳምንም በፍጥረት ሁሉ ላይ ንጉሥ እንደ ሆነ። ሰምዖንን በዘመኑ ቤተ መቅደስ እንደ ታነፀ በሕዝቡ ከምርኮ መመለስም እንደ ተመሰገነ በመጽሐፋ መጨረሻም "በሁሉ ቦታ ታላላቅ ሥራ የሚሠራና ዕድሜያችንን የሚያስረዝም እግዚአብሔር አምላክን አመስግኑት" አለ። ይህንንም ተናግሮ በፍቅር አንድነት ግንቦት16 ቀን ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የቅዱስ ሢራክ በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን::

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ባደረገው ስብሰባ የሚከተለውን ውሳኔ አስተላልፏል፦ 1. ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆርስን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፤ 2. ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስን የመንበረ ፓትርያር
+2
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ባደረገው ስብሰባ የሚከተለውን ውሳኔ አስተላልፏል፦ 1. ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆርስን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፤ 2. ብፁዕ አቡነ  ሳዊሮስን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤  3. ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስን የሐዲያ ሀ/ስብከትን እንደያዙ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ 4. ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ዘኮሎራዶን የቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ገዳማት ሊቀ ጳጳስ፤ 5. ብፁዕ አቡነ ናትናኤልን ሚኒሶታን እንደያዙ የኮሎራዶ ሀ/ስብከትን እንዲመሩ፤ 6. ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የደቡብ አፍሪካ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳ ጳስ፤ 7. ብፁዕ አቡነ ዕንባቆምን የገዳማት መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲመሩ፤ 8. ብፁዕ አቡነ ሙሴ አውስትራልያን እንደያዙ የግቢ ቅዱስ ገብርኤልና የበዐታ ለማርያም ገዳም ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲመሩ ወስኗል።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ግንቦት ፲፭ (15) ቀን። ❤ እንኳን #ለሐዋርያው_ስምዖን ለተባለው #ለቅዱስ_ናትናኤል ለዕረፍት በዓል፣ በላይኛው ግብጽ ውስጥ በደንደራ ከተማ በሰማዕትነት ለዐረፉ #ለአራት_መቶ_ሰዎች ለዕረፍታቸው በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚህ ቀን ከሚታሰቡት፦ #ከባሕታዊ_ሚናስ፣ #ከዲያቆንና_ከአባ_ሐርበጥላክያ ሰማዕታት ከሆኑ #ከኤስድሮስም_ማኅበር ከሆኑ #ቀርጢኖስና_ሚስቱ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #ሐዋርያው_ስምዖን_የተባለው_ቅዱስ_ናትናኤል፦ እርሱም ናትናኤል ተብሎ ይጠራል በገሊላ አውራጃ የቃና ሰው ነው የኦሪትና የነቢያትንም መጻሕፍት ተምሮ ያወቀ ነው። መንፈሳዊ ቅንዓትም በውስጡ አለበት ስለዚህም ቀናዒ ተባለ እርሱም ንጹሕ ፊት አይቶ የማያደላ በሃይማኖቱ ዕውነተኛ ነው። ስለዚህ ፊልጶስ "ስለርሱ ሙሴ የጻፈለትን የዮሴፍ ልጅ የሚሉት የናዝሬቱን ኢየሱስ ክርስቶስን አገኘነው" ባለው ጊዜ "ከናዝሬት ደግ ሰው ሊወጣ ይችላልን?" አለው እንጂ አላደላለትም ፊልጶስም "ታይ ዘንድ ና" አለው። በመጣም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን "ይህ በልቡ ሽንገላ የሌለበት እውነተኛ እስራኤላዊ ነው" አለው። አሁንም ምስጋና ወደመቀበል አልተመለሰም "በየት ታውቀኛለህ" አለው እንጂ ልብንና ኵላሊትን የሚመረምር ጌታችንም "ፊልጶስ ሳይጠራህ በፊት በበለስ ዕንጨት ሥር አየሁህ" አለው። ያን ጊዜም የተሠወረውን የሚያውቅ አምላክ መሆኑን ተረድቶ "ጌታዬና ፈጣሪዬ በእውነት አንተ የእግዚአብሔር ልጅ የእስራኤልም ንጉሥ ነህ" አለው እንደ አይሁድ መምህራንም አልተቃወመም እርነሱ ከዚህ የሚበልጥ ድንቅ ተአምራትንና ኃይሎችን አይተው በእውነት አልተገዙምና። ❤ ስርሱ እንዲህ ተብሏል ጐልማሳ ሁኖ ሳለ ከአሕዛብ ወገን ከሆነ ጐልማሳ ጋራ ተጣልቶ አንዲት አመታትን መትቶ ገደለው በቤቱ ዐፀድም በአለ ዕፅ በለስ በሥሩ ቀበረው ይህንንም ማንም አላወቀበትም። ሁለተኛም በሕፃናት ዕልቂት ጊዜ እናቱ በአገልግል ውስጥ አድርጋ በበለስ ዕንጨት ላይ ሰቅላ ትሸሽገው እንደ ነበር በጭልታም አውርዳ አጥብታ መልሳ ትሰቅለዋለች የመከራውም ጊዜ ጸጥ እስከ አለ ድረስ እንዲህ ታደርግ ነበር። መድኃኒታችንም በምልክት ከእርሱ የሆነውን በገለጠለት ጊዜ የተሠወረውን የሚያውቅ ሁሉንም የሚመረምር በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ተረዳ። ያንጊዜም ራሱን ዝቅ አድርጎ ለመድኃኒታችን ተገዛለት። ከዚያችም ሰዓት ጀምሮ ተከተለው ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያትም ጋራ ተቈጠረ። ❤ አጽናኝ የሆነ የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ በተቀበለ ጊዜ የአገሩ ሁሉ ቋንቋ ተገለጠለት መለኮታዊ ምሥጢርንም አወቀ ወደ ኵርጅ አገርና ወደ እልብጅህ ከተማ በሀድያን በድንቁርና ወደሚኖሩበት ሁሉ ገብቶ የሃይማኖትን ብርሃን አበራላቸው። ከተራቃቂዎችና ከሰነፎችም ብዙዎችን መልሶ በክብር ባለቤት ክርስቶስ ሃይማኖት ልባቸውን አበራላቸው። የክርስትና ጥምቀትንም አጥምቆ ነጣቂዎች ተኵላ የነበሩትን የዋሃን በጎች አደረጋቸው። ❤ ሁለተኛም ወደሌሎች የከሀድያን አገሮች ወደ በራንጥያ ደሴትም ሒዶ በውስጣቸው ሰበከ። ይዘውም ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃዩት እርሱ ግን ኃይልና ብርታትን ተጨመረ በእግዚአብሔርም ኃይል ሙታንን አስነሣ እንዲአጠምቃቸውም ለመኑት የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው ብዙ ዘመንም ኖረ። ከዚያም በኋላ ከሀድያን ይዘው በዕንጨት ላይ ሰቀሉት በዚህም ምስክርነቱን ፈጽሞ ከወንድሞቹ ሐዋርያት ጋራ የማይጠፋ መንግሥት ወረሰ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ናትናኤል ጸሎት ይማረን ለሁላችን የክርስቲያን ወገኖችም በረከቱ ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #አራት_መቶ_ሰማዕታት፦ ብዙ ሥቃንም ሲያሠቃዩአቸው ከኖሩ በኋላ የምስክርነታቸው ፍጻሜ በዲዮቅልጥያኖስ ዘመነ መንግሥት መጨረሻ ራስን በመቆረጥ ሆነ። በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የግንቦት 15 ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ዕብል_ብእሴ_ምሁር። ዘመጽሐፈ ኦሪት ሕገ ወዘነቢያት መዝሙረ። አመ ውእቱ ወሬዛ ታሕተ ዕፀ በለስ ዘገብረ። #ወልደ_ማርያም_አምላክ ሶበ ኅቡአቶ አእመረ። ለትእዛዘ #ጽድቁ_ናትናኤል_ገረረ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የግንቦት_15።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ብፁዕ ብእሲ ዘኢኈለቈ ሎቱ እግዚአብሔር ኃጢአቶ። ወዘአልቦ ጽልሑት ውስተ ልቡ። እስመ አርመምኩ በልያ አዕፅምትየ"። መዝ 31፥2-3። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 1፥44-ፍ.ም።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ቅዳሴ_ምስባክ፦ "አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ። ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ። ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ"። መዝ 18፥3-4። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 8፥24-35፣ ይሁ 1፥17-23 የሐዋ ሥራ 1፥12-15። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥1-16። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱሳን ሐዋርያት ነው። መልካም የሐዋርያው ስምዖን የተባለው የቅዱስ ናትናኤል የዕረፍት በዓልና የበዓለ ሃምሳ ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ ንዑድ ክብር ቅዱስ ያሬድም ስውር ዋሻ ውስጥ ገብቶ ፈጣሪውን እግዚአብሔር እንዲህ በማለት ለመነው "መታሰቢያዬን የመምህሬን የጌድዮንን መታሰቢያ የሁላችንንም አባት የአዳምን መታሰቢያ ያደረገው እንግዲህ ዋጋው ምንድን ነው?" አለው። እግዚአብሔርም እንዲህ አለው "የክብር መቀውጫ አስቀምጠው ዘንድ በመንግሥቴ ማልኩልኽ በፍርድ ቀን ማለትም በዕለተ ምጽዋት ያለ ሐፍረት በግልጥ ከአንተ ጋራ ይለፍ" አለው። መታሰቢያህን ያደረገ የገድልኽንም መጽሐፍ የጻፈ ወይም ያጻፈ ንዑድ ምስጉን ክብር ነው፤ እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጠዋለኹ፤ የክብር ዙፋንም አወርሰዋለኹ" አለው። ይህንንም ቃል ኪዳን ጌታችን ከሰጠው በኋላ በስሜን ከሚገኝ አንድ ገዳም በኅቡእ (በስውር) እስከ ዕለተ ምጽአት ይኖል ዕረፍቱ ይህ ነው። ከቅዱስ ያሬድ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎቱም ይማረን!። ምንጭ፦ የቤተ ክርስቲያን ብርሃን ቅዱስ ያሬድና የቅዱስ ያሬድ ታሪክ ከሚሉት መጻሕፍት።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ለይትፈሣሕ ልብ ዘየኀሦ ለእግዚአብሔር። ኅሥዎ ለእግዚአብሔር ወትፀንዑ። ወኅሡ ገጾ በኲሉ ጊዜ"። መዝ 104፥3-4። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 26፥7-17።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "መድኃኔ ገጽየ እግዚአብሔር ተወክፈኒ። እሴብሕ ለስመ አምላኪየ በማኅሌት። ወአዐብዮ በስብሐት"።  መዝ 68፥29-30። የሚነበቡት መልዕክታት ኤፌ 5፥15-21፣ ያዕ 5፥12-14 እና የሐዋ ሥራ 26፥24-30። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 21፥1-7። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው ወይም የቅዱስ ቄርሎስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ያሬድ ከሞት የተሰወረበት በዓልና የበዓለ ሃምሳ ለሁላችንም ይሁንልን።         

ተቀምጦ ዝማሬ መዋሥዕት የተባለውን መጽሐፍ ለሦስት ዓመት ከሦስት ወር ስላስተማረበት ይህም ቦታ ገዳም እስከ ዛሬ ድረስ የዝማሬና የመዋሥዕት ምስክር ቦታ ሆኖ ይኖራል። ❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ያሬድ ከአኵሱም ወደ ማይኪራህ አምርቶ እመቤታችን ቅዱስ ኤፍሬምን በአካለ ነፍስ ከሶርያ አባ ሕርያቆስ ከብሕንሳ አምጥታ ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን ንባቡን እየነገሩት በዜማ እንዲደርስላት አድርጋለች። ከዚህም አያይዞ ለሥጋ ወደሙ ጸሎት የሚያገለግሉትን ንባቡ የሌሎች ሊቃውንት ድርሰት የሆኑትን ዐሥራ አራቱን ቅዳሴዎች በዜማ አዘጋጀ። ❤ ከዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ ሰሜን ተራሮች ጸለምት ሔዶ ምዕራፍ የተባለውን ድርሰቱን ደረሰ። ከዚህ በኋላ አገው፣ ፎገራ እና ወደ ሌሎችም ቦታዎች እየዞረ አስተማረ። ❤ ቅዱስ ያሬድ በአኵሱም ወንበር ዘርግቶ፣ ጉባኤ አስፍቶ ደቀ መዛሙርቱን እያስተማረ ሲኖር በጾመ ፵ ሱባኤ ላይ ሳለ አንድ ቀን በምኵራብ ሰሞን ስለምናኔው እያስታወሰ በተመስጦ ሲዘምር የዜማው ጣዕም እንኳን ሌላውን ራሱን እጅግ ይመሥጠው ነበር። በጣዕመ ዝማሬው ተመሥጦ ሲያዳምጥ የነበረው ኢትዮጵያዊው ንጉሥ የዐፄ ገብረ መስቀል ዐይን ዐይኑን እየተመለከተ ሳይታወቀው በመስቀል ስላጢኑ (በበትረ መንግሥቱ ዘንግ) ጫፍ የቅዱስ ያሬድን እግር ወጋው። ቅዱስ ያሬድ ግን ከሰማያት የተገኘች ቃለ ማሕሌቱን እስኪፈጽም ድረስ ከቆመበት ሳይንቀሳቀስ ሕመሙ ሳይታወቀው ቀጠለ፤ ደሙም ያለማቋረጥ ፈሰሰ። ❤ ቅዱስ ያሬድ የጀመረውን በፈጸመ ጊዜ ንጉሡ ደንግጦ በትሩን ከቅዱስ ያሬድ እግር ላይ ቢነቅለው ደሙ በኃይል ይፈስ ጀመር። ያን ጊዜ ንጉሡ ዐፄ ገብረ መስቀል የቅዱስ ያሬድን ትዕግሥት ባለ ጊዜ በመደነቅ፣ በመገረምና በመደንገጥ ዝም በማለት አፉን ይዞ ቆመና ምድራዊ ዋጋ የሚፈልግ መስሎት "ካህን ያሬድ ሆይ የምትፈልገውን ዋጋ ጠይቀኝ" አለው። ቅዱስ ያሬድ መልሶ "የፈለግኹትን እንዳትከለክለኝ ቃል ኪዳን ግባልኝ" አለው። ንጉሡም የጸና ቃል ኪዳን ለቅዱስ ያሬድ ገባለት። ቅዱስ ያሬድም "ከዚህ ሐላፊ ዓለም ክብር ተለይቼ መናኝ ሆኜ እንድኖር ተወኝ አሰናብተኝ" ብሎ አሳብን ገለጸለት። ከዚህም በኋላ ንጉሥ ዐፄ ገብረ መስቀል ያሬድ ካህን የጠየቀውን እንዳይከለክለው ከአፉ የወጣውን መሐላ አስቦ በምናኔ አሰናበተው እንጂ ሊከለክለው አልቻለም። ❤ ቅዱስ ያሬድ ካህንም የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ታቦት ወዳለችበት ጽዮን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ሁለት እጆቹን በታቦተ ጽዮን ላይ አኑሮ "ቅድስት ወብፅዕት፣ ስብሕት ወቡርክት፣ክብር ወልዕልት አንቀጸ ብርሃን መዓርገ ሕይወት" ብሎ በደረሰው አንቀጸ ብርሃን ጸሎት እመቤታችንን አመሰገ። በዚህ ጊዜ እጁ በታቦተ ጽዮን ላይ ረቦ በመንፈስ ቅዱስ እየተቃኘ ስለነበር ከመሬት አንድ ክንድ ከፍ ከፍ ብሎ ይታይ ነበር። እስከመጨረሻው በከፍተኛ ቃል በዕዝል ዜማ እየዘመረ እግዚአብሔር እና እመቤታችንን ከአመሰገነ በኋላ እመቤታችን የቀና መንገድ እንድትመራውና እስከ ፍጻሜ ገድሉ ትረዳው ዘንድ በጸሎት ለመናት። እመቤታችንም መልሳ "ሰማያዊት ጽዮን ያደረግኻት መቅደሴን፣ በመዝሙር በማሕሌት ምስጋና የኪሩቤልና የሱራፌል ወገን ሰማያውያን ያደረግኻቸው ልጆቼ ካህናትን እንዴት ትተህ ትሔዳለህ" ብላ ቃል በቃል አነጋገረችው። የመንገዱን ስንብት እስክትፈቅድለት ድረስ በለቅሶና በእንባ ዳግመኛ ለመናት እርሷም እንዲሔድ ፈቀደችለት። ❤ የቅዱስ ያሬድ ምናኔ፦ ወደ ገዳም ሊሆድ ተዘጋጀ በዚህ ጊዜ የሚወዱት ካህናት፣ ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ተከትለውት እስከ ተከዜ ወንዝ ድረስ ሸኙት። ከእርሱ በሚለዩበትም ጊዜ "ሰላመ ነሳእነ ወሰላም ኃደግነ ለክሙ ወሰላመ እግዚአብሔር የሀሉ ምስለ ኩልክሙ፤ ሰላምን ከእናንተ ተቀበልን ለእናንተም ሰላምን ተውንላችሁ የእግዚአብሔር ሰላምም ከሁላችሁ ጋራ ይኹን" ብሎ በዜማ ተሰናበታቸው። ዳግመኛ "ወሰላም እግዚአብሔር እንተ ኵሉ ባቲ ተሀሉ ወትረ ምስለ ኵልክሙ፤ ፍቅርና ስምምነት ሁሉ ያለበት የእግዚአብሔር ሰላምታ ሁል ጊዜ ከሁላችሁ ጋራ ትኑር" ብሎ በጣዕ ዜማው መረቃቸው። ካህናቱም ይህን ሰምተው አለቀሱ። እርሱም ከእርሱ ጋራ አለቀሰ። በዚሁ ጣዕመ ዜማው የመጨረሻ ቡራኬውን ሰጣቸውና እርስ በእርሳቸው ተሳስመው ተነሰነባብተው ከእርሱ በመለየታቸው እያዘኑና እየተከዙ ወደ አገራቸው አኵሱም ተመለሱ። እርሱ ግን የተከዜን ወንዝ ተሻገረ። የወንዙ ፏፏቴና ጎርፍ እንሚጮህ አንበሳ ሲጮህ በሰማ ጊዜ "አኅለፍኮሙ በእግር እንተ የብስ ማእከለ ባሕር ተከዜ...፤ በተከዜ ባሕር መካከል በእግር እንደሚሻገር በደረቅ አሻገርካቸው..." እያለ በረቀቀ ምስጢር እግዚአብሔርን በማመስገን እየዘመረ ሲሒድ አንዲት ሴት ውሃ ቀድታ ወደ ቤቶ ስትመለስ ድምፁን ሰምታ ወይ ቃል! ወይ ቃል! እንዴት አንጀት ይበላል! ምንኛስ ያሳዝናል! ብላ ደጋግማ ስለተናገረች ቅዱስ ያሬድ ቆሞ የዘመረባት ቦታ "ወይ ቃል" ተብላ ተጠራች። ዛሬ ይህች ቦታ ጎንደር ክፍለ አገር ደባርቅ አካባቢ "ወይ ቃል" ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ተብላ ትጠራለች። ❤ ቅዱስ ያሬድ ወደ ሰሜን ተራሮች ሔዶ ጸለምት ወጥቶ ብርድ በጸናበት በረዶ በተከማቸበት ሳኔር ተብሎ በሚጠራ በሐዊ ዐምባ ጽሞና ይዞ ተቀመጠ። በዚያም በብዙ ትጋት በጾምና በጸሎት ይልቁንም በስብሐት እግዚአብሔር ብቻ ተወስኖ ጉባኤ ዘርግቶ፣ ትምህርት አስፍቶ ከሱራፌል መላእክት እንደተማረው አድርጎ ከጸለምት፣ ከስሜን፣ ከአገውና ከሌላ አገር ወደ እርሱ የሚመጡትን ሰዎች ሁሉ ማሕሌተ እግዚአብሔር እያስተማረ ኖረ። ❤ ቅዱስ ያሬድ ከትውልድ አገሩ አኵሱም መንኖ ከወጣ በኋላ ትዕግሥቱን እያዘወተረ ወደ እርሱ የመጡትን ሁሉ በማስተማር በገዳመ ስሜን ኖረ። ቅዱስ ቍርባን ለመቀበልና ቅዱሳት ገዳማትን ለመሳለም በፈለገ ጊዜ በሠረገላ ብርሃን ተጭኖ አኵሱም ደርሶ ቅዱስ ቍርባን ተቀብሎ ሌሎች ገዳማትንም ይሳለም ነበር። ❤ በመጨረሻ ቅዱስ ያሬድ ካህን ዘመኑን ሁሉ በመላእክት ማኅሌት እግዚአብሔርን በማገልገልና ይህን ማኅሌት ለሚከተሉት ደቀ መዛሙርት በማስተማር ዘመኑን ፈጽሞ ለሃያ ሁለት ዓመታት በላይ በምናኔ ታግሦ በገድሉና በጣዕመ ዜማው ፀላኤ ሠናያትን ድል አድርጎ ከዚህ ዓለም ድካምና መከራ የሚያርፍበት፣ የሚሰወርበት ቀንና ሰዓት መድረሱን በጸጋ በዐወቀ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን ሰብስቦ "ይቤ ጳውሎስ ኃላፊ ንብረቱ ለዝንቱ ዓለም አኃውየ አስተፋጥኑ ገቢረ ሠናየ አነሰ በድረየኒ ፈጸምኩ ወሃይማኖትየኒ ሠለጥኩ እንከሰ ጽኑሕ ሊተ አክሊል ዘየዓሥየኒ መኰንነ ጽድቅ" 2ጢሞ4፥7-8 እያለ በሚያራራ ቃል ምክሩን ሰጥቶ ተሰናበታቸው። እነርሱም ምክሩን ተቀብለው "አባ አቡነ፣ አባ መምህርነ አይቴ ተሐውር ወለመኑ ተኀድገነ፤ አባታችን መምህራችን ወደ የት ትሔዳለኽ? ለማንስ ትተወናለኽ? እያሉ ሲያዝኑ ሲያለቅሱ በአንድ ዋሻ ውስጥ ገብቶ ግንቦት11 ቀን በ571ዓ.ም ተሰወረ። ❤ ቅዱስ ያሬድ ከመሰወሩ በፊት በእግዚአብሔር አምነው በእርሱ ቃል ኪዳን ለተማፀኑ፣ በስሙ ቤተ ክርስቲያን ላሳነጹና ላነጹ፣ መጽሐፈ ገድሉን ለጻፈና ላጻፈ፣ ዕጣን ቋጥረው ጧፋና ጥላ ገዝተው መገብሪያ ሰፍረው፣ መጋረጃና ሌሎችንም ንዋያተ ቅዱሳት ገዝተው አምጥተው በስሙ ለታነጹ አብያተ ክርስቲያናት ላበረከቱት ሁሉ የማየሠልፈውን ርስት መንግሥተ ሰማያት እንደሚያወርስለት እግዚአብሔር ቃል ኪዳን ገብቶለታል።

❤ በዚያም ቅዱሳን መላእክት የሚታየውንና የማይታየውን የፈጠረ እግዚአብሔር በቅኔና በከፍተኛ ደምፅ ያለማቋረጥ በመንበሩ ዙሪያ ኾነው ሲያመሰግኑ እንዲሁም የእንዚራ፣ የበገና የመሰንቆ ድምፅ በሰማ ጊዜ ካለበት ሥፍራ እነርሱ ወዳሉበት ሊገባ ወደደ ነገር ግን አልተቻለውም። በመጨረሻም እነዚያ አዕዋፍ ወደ እርሱ ተመልሰው መጡ። "ያሬድ ሆይ፤ የሰማኸውን አስተውለኸዋል?" ብለው ጠየቁት እርሱም "አላስተዋልኸም" ብሎ መለሰላቸው። እንግዲያውስ አዲሱን የእግዚአብሔር ምስጋና ጥራ፤ እርሱም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስም ነው። ከእግዚአብሔር መዘምራን ከቅዱሳን መላእክት በየዐይነቱ ዜማ ያለውን ማሕሌት ትማራለኽ፤ ታጠናለኽ" አሉት። ከዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ማሕሌቱን በየዓይነቱ አውጥቶ "መልካምን ነገር ልቤ ተናገረ" እያለ ከቅዱሳን መላእክት ተማረ። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም "ሌሎችን አገልጋዮች ሰዎች ይሾሟቸዋል፤ አንተን ግን እኔ ሢመተ ክህነት (ቅስና) ሾሜኻለሁ" አለው። ❤ ቅዱስ ያሬድም የመላእክት ሥርዓታቸው ዐይቶ፤ ማሕሌታቸውን አጥንቶ ኅዳር 6 ቀን 527 ዓ.ም በጠዋት ሦስት ሰዓት ወደ ቀድሞ ቦታው ተመልሷል። ከዚያም ኾኖ ፊቱን ታቦተ ጽዮን ወዳለችበት ወደ ምሥራቅ አዙሮ እጆቹን ዘርግቶ እንዲህ ብሎ ሰማያዊ ዜማን ለመጀመርያ ጊዜ በአኵሱም አደባባይ (ዐውደ ምሕረት) ዘመረ። ❤ "ሃሌ ሉያ ለአብ፣ ሃሌ ሉያ ለወልድ፣ ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ ዘከመ ይገብር ግብር ግብራ ለደብተራ"። ብሎ በዓራራይ ዜማ አዜመ። ይህም ማለት ዓለም ሳይፈጠር ለነበረ ዓለምን አሳልፎ ለዘለዓለም ለሚኖር አሁንም ላለ ለአብ ምስጋና ይገባል፤ ለወልድም ምስጋና ይገባል፤ ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል፤ ከጽዮን አስቀድሞ ሰማይን ፈጠረ፤ ዳግመኛም ደብተራ ኦሪትን እንዴት አድርጎ መሥራት እንዳለበት ለሙሴ አሳየው ማለት ነው። ስለምን በዓራራይ ዜማ ጀመረ ቢሉ ቋንቋን የሚያናግር ምስጢር የሚያስተረጉም መንፈስ ቅዱስ የገለጠልኝ ዜማ ነው ሲል ነው። ምክንያቱም ዓራራይ ዜማ የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ነውና። ❤ ከሰማይ እንደተመለሰ ለመጀመሪያ ጊዜ ጣዕመ ዜማውን ያሰማበት ቦታ "ሙራደ ቃል" (የቃል መውረጃ) እየተባለ ይጠራል። ይኸውም ዜማው ከሰማይ የወረደ ለመኾኑ እውነተኛ ማስረጃ ነው። ይህችንም ዜማ "አርያም" አላት። ይህም ማለት ከመላእክት ወይም ከሰማይ የተገኘች ማለት ነው። ❤ ከዚህም በኋላ ከብሉይና ከሐዲስ፣ ከሊቃውንት መጻሕፍትም ከነ አትናቴዎስ፣ ቄርሎስ፣ ዮሐንስ አፈወርቅ መጻሕፍት ለምስጋናና ለጸሎት የተስማሙትን ቃላት እየመረጠና እያቀና በአራቱ ክፍለ ዘመን፣ በመፀውና በሐጋይ በጸደይና በክረምት እንዲነገር አድርጎ ወስኖ አዘጋጀ። የመጽሐፉ የድርሰቱ ስም ድጓ ተባለ። ድጓ ማለትም በትግርኛ ደጉዓ ማለት መዝሙረ ኃዘን፥ የኃዘን ዜማ፥ ማለት ነው፤ ሙሾ የዜማውን ዓይነት በሦስት ክፍል ወስኖ ተናግሮታል። እነርሱም ግእዝ፣ ዕዝል፣ ዓራራይ ይባላሉ። ግእዝ ማለትም አንደኛ በመጀመሪያ የተገኘ ማለት ነው ፤ ዕዝል ማለትም ሁለተኛ ሆኖ ከግእዙ ጋር ተደርቦ፣ ተጨምሮ ፣ታዝሎ የሚነገር ማለት ነው። ዓራራይ ማለትም ሦስተኛ ተጨማሪ ሆኖ አራኅራኂ፣ ርኅራኄ፣ አሳዛኝ ልብን የሚመስጥና ደስ የሚያሰኝ ማለት ነው። ይህን ድርሰቱን ያዘጋጀበት ዘመን ከ540 ዓ.ም ሲሆን በአፄ ገብረ መስቀል መንግሥት ነው። ❤ አፄ ገብረ መስቀልና አባ አረጋዊ ቅዱስ ያሬድ እነዚህ ሦስቱ በአንድነት እንደነበሩ ታሪከ ነገሥቱና ገድለ አረጋዊ ይገልጽልናል። አቡነ አረጋዊ የደብረ ዳሞን ተራራ አቀማመጥ አይተው ደስ ስላላቸው፣ ንጉሡ አፄ ገብረ መስቀል በዚሁ ተራራ ላይ እንዲኖሩበትና እንዲጸልዩበት ፈቀደላቸው። እርሳቸውም ይህንን ተራራ ከተረከቡ በኋላ በተራራው ላይ የጸሎት ቤት ስለሌለ ንጉሡ አፄ ገብረ መስቀልን አንድ ቤተ ክርስቲያን እንዲሠራላቸው ለመኑት። ንጉሡም ቤተክርስቲያን ልሠራ የምችልበትን ሥፍራ መርጠው ያመልክቱኝ ብሎ ነገራቸው አቡነ አረጋዊም ተነሥተው ዞረው ቦታውን መርጠው አሳዩት። ❤ ከዚህ በኋላ ንጉሡ በአዋጅና በትዕዛዝ ድንጋዩና እንጨቱ እየተሰበሰበ በከብትና በሠረገላ እየተጋዘ ተሰበሰበና ከታች ወደ ተራራው ላይ ወጥቶ ተሠራና የቤተ ክርስቲያኑ ሥራ በሁለት ዓመት አለቀ። ባለቀም ጊዜ የቤተክርስቲያኑ ሥራ ተመልካቾች አስደነቀ። ለዚህም ቤተክርስቲያን ልዩ ልዩ የሆኑ አልባሳት፣ የብርና የወርቅ የተደጎሱና የተከፈፉ መጻሕፍትን አበረከቱ። ከማኅበረ በኩር የመጣውን የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ጽላት አግብተው አቡነ አረጋዊ ባርከውና ቀድሰው ንጉሡና ጳጳሱ ቆረቡ። ከዚያም አፄ ገብረ መስቀል በተራራው ላይና በግርጌ ላሉት ሠራዊት ግብር አብልተው ነዳያን ሁሉ ጠገቡ። ❤ ከዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ በአክሱም ሲያስተምር ሳለ በንጉሡ አፄ ገብረ መስቀልና አቡነ አረጋዊ፥ ወደዚህ ተራራ መጥቶ ቤተክርስቲያኑን እንዲጎበኝና እንዲዘምር ተጠርቶ ሲመጣ ከተራራው ሥር ሲደርስ የአቡነ አረጋዊን ደቀመዛሙርት ማትያስና ዮሴፍ የሚባሉትን ከወንዝ ዳር ዓሣ ሲያጠምዱ አግኝቶ "ዳኅንኑ ዝስኩ አረጋዊ አቡክሙ ፤ ይህ አረጋዊ አባታችሁ ደህና ነው" ብሎ ጠየቃቸው። እነርሱም ደኅንነታቸውን ነገሩት። ከዚያም ቅዱስ ያሬድ ወደ ተራራው ላይ ወጥቶ ከአቡነ አረጋዊ ጋር በመንፈሳዊ አምኃ በፍቅር ተገናኙ ወደ ቤተ ክርስቲያኑም ሄዶ 3 ጊዜ ሰግዶ ከተሳለመ በኋላ የሕንጻውን ማማር በአድናቆት ተመልክቶ ከፍ ባለ የዜማ ድምፅ እያጉረመረመ እንዲህ ሲል ዘመረ። "ይሔውጽዋ መላእክት እንተ በሰማያት ይሔውጽዋ መላእክት እስመ ማኅደረ መለኮት ይእቲ ዖድክዋ ዖድክዋ ዖድክዋ ወርኢኩ ሥነ ሕንፄሃ ለቅድስት ቤተክርስቲያን ምስአል ወምስጋድ ወምስተስርዬ ኃጢአት ይእቲ ቅድስት ደብተራ፤ በሰማያት ያሉ መላእክት ይጎበኟታል፤ የመለኮት ማደሪያ ናትና መላእክት ይጎበኟታል፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ዞርኋት፣ ዞርኋት፣ ዞርኋት የሕንፃዋን ማማር ዐየኹ፤ እርሷ መጸለያ፣ መስገጃና የኃጢያት ማስተሰረያ ቅድስት ማደርያ ናትና"። እያለ ስለዘመረ ደብረ ሃሌ ሉያ ተብሎ ተጠራ። ደብረ ዳሞ የሚለው ስያሜ በኋላ የወጣ ስም እንደሆነ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ይናገራሉ። ቅዱስ ያሬድ በዚሁ ገዳም ስምንት ቀን ያህል ከአቡነ አረጋዊ ጋር ሰንብቶ ወደ አክሱም ተመለሰ። ❤ ከዚህ በኋላ ንጉሡ አፄ ገብረ መስቀልና አቡነ አረጋዊ ከቅዱስ ያሬድ ጋር አብረው ወደ ሌላ ጠቅላይ ግዛት ጉብኝት ሄዱ። ከዚያም በጣና በአንዱ ደሴት ላይ የቅዱስ ቂርቆስን ቤተ ክርስቲያን ሠርተው ተቀመጡ። በዚያም ቦታ ቅዱስ ያሬድ ሁለት ዓመት አስተማረ። እርሱ እራሱ ጻፈው የሚባል ድጓ ምልክት የሌለው ዛሬ በዚሁ ደሴት በጣና ቂርቆስ ይገኛል። ❤ ከዚህም ደሴት ከጣና ቂርቆስ ተነሥተው ንጉሡና አቡነ አረጋዊ ቅዱስ ያሬድም ወደ ደጋው ወደ ጋይንት ወጡ። በዚያም አንድ ትልቅ ተራራ አግኝተው መውጫው ጠፍቶባቸው ሲጨነቁ አንድ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ መጥቶ አቡነ አረጋዊን "ዑድ አባ መንገለ ምሥራቅ ወዑዳ ለዛቲ ደብር፤ ዙር አባ ወደ እርስዋም ትወጣ ዘንድ በምሥራቅ በኩል ዙር" አላቸው ወደ ምስራቅ ሲዞሩ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነጭ ሐረግ ዘረጋላቸው እርሱን ይዘው ወደ ተራራው ላይ ወጡ። በዚሁ ተራራ ላይ የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያን ሠሩ። የተራራውም ስም እስከ ዛሬ ድረስ ዙር አምባ ተብሎ ይጠራል። በዚህ ገዳም ምሥራቃዊ አቅጣጫ ቅዱስ ያሬድን የምትዘክር "ከርሞ አይደርቅ" የምትባል ዛፍ አለች። ቅዱስ ያሬድ በዚች ዛፍ ሥር

ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ) Teamho Kidusan Wegtsawe (Yekidusa Selamta): ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ግንቦት፲፩ (11) ቀን። ❤ እንኳን #ለማኅቶተ_ቤተ_ክርስቲያን ለሱራፌል አምሳላቸው ለሆነ #ለኢትዮጵያዊው_ለታላቁ_ማኅሌታይ_ለካህኑ_ቅዱስ_ያሬድ ከዚህ ዓለም ከሞት ለተሰወረበት ቀን ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን።                                                                                     ✝ ✝ ✝ ❤ #ማኅቶተ_ቤተ_ክርስቲያን_ታላቁ_ማኅሌታይ_ካህኑ_ቅዱስ_ያሬድ፦ የስሙ ትርጓሜ ያሬድ ማለት ርደት፣ ወሪድ፣ ማለትም መውረድ ማለት ነው። ከአዳም ስድስተኛ በሆነው በመላልኤል ልጅ በያሬድ ጊዜ ደቂቅ ሴት ከደብር ቅዱስ ወደ ደቂቀ ቃየን ወደ ምድረ ፍዳ ስለወረዱ ያንን ለማስታወስ አባቱ መላልኤል ያሬድ ብሎታል። ኩፍ5፥21-22 ❤ በኢትዮጽያም ዳግማዊ ያሬድ በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ተነስቶ ሰማያዊውን ልዩ ጣዕመ ዜማ ወደ ኢትዮጵያ የሚያወርድ ነውና ይህንን ለመግለጽ እግዚአብሔር አምላክ በእናቱ እና በአባቱ ላይ አድሮ ያሬድ እንዲባል አድርጓል። ምስጢሩ ልዩ ጣዕመ ዜማን ከሰማይ የሚወርድ መሆኑን ያሳያል። ❤ አንድም ያሬድ፦ ማለት ንብ ማለት ነው። ንብ የማይቀስመው አበባ እንደሌለ ሁሉ ቅዱስ ያሬድም ከቅዱሳት መጻሕፍት የማይጠቅሰው የለምና። ❤ አንድም ያሬድ፦ ማለት ረአዬ ምስጢር ነጻሬ ኅቡአት "ምስጢር ተመልካች ምስጢር ገላጭ ማለት ነው። ምስጢር ገላጭ መባሉ የመላእክት ምስጢራት የነበሩትን ጸዋትወ ዜማ አምልቶ አስፍቶ ተናግሯልና፤ " ዋይ ዜማ ዘሰማዕኩ በሰማይ እመላእክት ቅዱሳን፤ ከቅዱሳን መላእክት በሰማይ የሰማኹት ዜማ ምን ይረቅ! ምን ይጠልቅ!" እንዲል። ምስጢር ተመልካች መባሉ ደግሞ ኅቡእ (ስውር) የኾነ የነቢያት፣ የሐዋርያትን፣የሰማዕታትና የጻድቃን ገድል አምልቶ አስፍቶ ስለሚናገር ነው። ❤ አንድም ያሬድ፦ ማለት እንዚራ፣ በገና፣ መሰንቆ ማለት ነው። እነዚህ በስልት በስልት ሲመቱ ለሚሰማቸው ደስ እንዲያሰኙ፤ የቅዱስ ያሬድም ዜማ በንጉሠ ነገሥት ክርስቶስ አደባባይ በቤተ ክርስቲያን ሲሰማ መላእክት ፣ሰውንና እንስሳትን ደስ ያሰኛልና። ❤ ታላቁ ማኅሌታይ ካህኑ ቅዱስ ያሬድ፦ ከእናቱም ቅድስት ክርስቲና (ታውክልያ) ከአባቱ ከቅዱስ አብዩድ (ይስሐቅ) በአኵስም (አክሱም) በ505ዓ.ም ሚያዝያ5 ቀን ተወለደ። አባቱ የአክሱም ጽዮን ቄሰ ገበዝ ነበር። በዚያን ጊዜ የብሉያትና የሐዲሳት መምህራንና ተማሪዎች የሚገኙት አክሱም ጽዮን ነውና የአኵሱም ቤተ ቀጢን (ቤተ ጉባኤ) መምህር የነበረው የእናቱ ወንድም አጎቱ መምህር ጌዴዎን ይባል ነበር። ❤ ቅዱስ ያሬድ የሰባት ዓመት ሕጻን በኾነ ጊዜ አባቱ ስለ ሞተ ትምህርት ቤት ከመግባቱ በፊት በዚያ ዘመን አጠራር ለጌታው ዐደረ። ጌታውም የዐፄ ገብረ መስቀል ቢትወድድ አዛዥ ዜና ገብርኤል ይባላል። ያሬድን ዐቅሙ ለጉልበት ሥራ እንዳነሰ አይቶት "አንተ ልጅ ጋሻ ቢያስይዙህ አትችል፤ ሾተል ቢያሸክሙህ አይሆንልህ ለምን ከዚህ መጣህ?" ብሎ መለሰለት። ከዚያ በኋላ ከአጎቱ ዘንድ ሔደ። መምህሩም "ከዚህ የመጣህበት ምክንያት ምንድ ነው?" አለው። እርሱም "መጽሐፍት እማራለኹ ብዬ ነው የመጣኹት" አለው። መምህር ጌድዎንም ዐቅሙንና ዕውቀቱን በመገመት ለተማሪዎች "በሉ ፊደል አስቆጥሩት" አላቸውና ትምህርቱን ጀመረ። ኾኖም ቃለ እግዚአብሔርን የመቀበል ችሎታው ደካማ ስለነበር አብረው የሚማሩትም ሕፃናት "ሰነፍ ያሬድ ዕንጨት ስበር ውሃ ቅዳ" እያሉ አፌዙበት፤ ቀለዱበት። አጎቱ ጌዴዎንም ከትምህርቱ ድክመት የተነሣ በጨንገር (በአለንጋ) ቢገርፈው ሕፃኑ ያሬድም በዚህ ተበሳጭቶና ተስፋ ቆርጦ ከአክሱም ከተማ ወጥቶ ወደ እናቱ መንደር ወደ መደባይ ወለል ደረሰ። ለጥሙ ከምንጭ ውሃ ጠጥቶ ለድካሙ ከዛፋ ጥላ አረፈ። በምን ምክንያት ከጓደኞቹ በታች እንደኾነ ሲያስብና ሲያሰላስ ሳያዝንና ሲተክዝከቆየ በኋላ እግዚአብሔር አንድ የሚያጽናና ምልክት አሳየው። ይኸውም አንድ ትል የዛፏን ፍሬ ለመመገብ ፈልጎ ወደ ላይ እየወጣና እየወደቀ ተደጋጋሚ ሙከራ ሲያደርግ ከቆየ በኋላ በሰባተኛው ጊዜ ወደ ዛፋ ወጥቶ ፍሬዋን ሲመገብ ተመለከተ ተማሪ ያሬድም ከዚህ ትል ትዕግሥትን፣ ጽናትን፣ ጥረትን፣ ስኬትን ትምህርት ወስዶ እኔም እኮ ተስፋ ሳይቆርጥ ብዙ ጥረት ካደረግኹ እግዚአብሔር ያሳካልኛል ብሎ በተስፋ ተጽናንቶ እንደገና ወደ መምህሩ በመመለስ ትምህርቱን ለመቀጠል ወሰነ። ወደ መደባይ ያደረገው የነበረውን ጉዞ ሠርዞ ወደ አክሱም ከተማ ወደ መምህሩ ጌድዬን ጉባኤ ቤት ተመለሰ። በመጸጸት አጎቱን "አባቴ ስለተቆጣኸኝና ስለገረፍከኝ ተበሳጭቼ ሔጄ ነበር ፤ ነገር ግን በመንገድ ላይ እግዚአብሔር ስላስተማረኝ ተጸጽቼ መጥቻለኹ። ከእንግዲህስ ወዲህ እየተቆጣኽና እየገሠጽህ አስተምረኝ" ሲል አሳቡን ሳይደብቅ ገለጸለት። ❤ አጎቱም ያሬድ ተጸጽቶ በመመለሱ በጣም ተደስቶ ዐይነ ልቡናውን ያበራለት ዘንድ ፈጣሪውን እያለቀሰ በለመነለት ጊዜ እግዚአብሔርም ጸሎቱን ሰምቶ ለያሬድ ዕውቀትን ገለጸለት። የያሬድ ኅሊናው ተከፍቶለት መዝሙረ ዳዊትን፣ ውዳሴ ማርያምን፣ መሓልየ ነቢያት፣ መሐልየ ሰሎሞንን፣ መጻሕፍተ ብሉያትንና ሐዲሳትን ንባባቸውን እስከ አገባባቸው አወቀ። ❤ ቅዱስ ያሬድ ቅዱሳት መጻሕፍትን በቃሉ ይዞ ሲያስተምር ሳለ የትምህርቱን ጥራት፣ የሃይማኖት ጽናት፣ ደግነቱንና ትዕግስቱን፣ ትሕትናውና ተልኮውን በመምህሩና በካህናቱ ተመስክሮለት የአክሱም ጳጳሱ አባ ዮሐንስ ሢመተ ዲቁና ሾመው። ቅዱስ ያሬድ የታላቋ የአክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን አጋልጋይ ዲያቆን ኾነ። ❤ ትምህርቱን በስፋት ስለቀጠለበት የመጻሕፍት ብሉያትና ሐዲሳት፣ የመጻሕፍት ሊቃውንት ትርጓሜ ሊቅ ኾነ። ቅዱስ ሬድም ለመንፈሳዊ አገልግሎት ወደ ኢትዮጵያ ከመጡት ከዘጠኙ ቅዱሳን ጋራ በቤተ ቀንጢን ጉባኤ ቤት ይውል ስለነበር ገዳማዊ ሕይወት ከእነርሱ በመማር እንደ እነ አቡነ አረጋዊ፣ አባ ገሪማ፣ አባ ጰንጠሌዎን በድንግልና ተወስኖ በንጽሕና ሲያገለግል ቆይቷል። ❤ ለቅዱስ ያሬድ ሰማያዊ ዜማ መገለጽ፦ ኅዳር 5 ቀን 527 ዓ.ም ከጠዋቱ በሦስት ሰዓት እግዚአብሔር ከኤዶም ገነት ሦስት አዕዋፍን (መላእክት በአዕዋፍ ተመስለው) እርሱ ወዳለበት ላከለት። እነርሱም ያሬድ ባለበት ቦታ አንጻር በአየር ላይ ረብበው በግእዝ ቋንቋ "ብፁዕ ያሬድ ብፅዕት ከርሥ እንተ ጾረተከ ወብፁዕት አጥባት እለ ሐፀናከ (የተመሰገንክና የተባረክ ያሬድ ሆይ፤ አንተን የተሸከመች ማሕፀን የተመሰገነች ናት፤ አንተን ያሳደጉ ጡቶችም የተመሰገኑ ናቸው") ብለው አወደሱት። ቅዱስ ያሬድም ይህን ቃል በሰማ ጊዜ ወደ ሰማይ አንጋጦ ሦስቱን አዕዋፍ አየና "እናንተ በሰው አንደበት የምትናገሩ ከወዴት መጣችኹ" አላቸው። ከሦስቱ አዕዋፍ አንዷም "ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ማሕሌትን ሰምተኽ እንድታዜም የተመረጥኽ መኾኑን እነግርህና እናበሥርህ ዘንድ ወደ አንተ ተልከን መጥተናል" አለችው። ከዚያም ቅዱሳን መላእክት በዜማወደሚያመሰግኑባት ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም በአካል ተነጠቀ።

🔴🔴🔴 የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ፅ/ቤት በቤተል 1600 ካሬ ከመንግስት በቅርብ ቀን እንደተሰጠው ይታወቃል። ሆኖም በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ በአዲስ አበባ
+1
🔴🔴🔴 የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ፅ/ቤት በቤተል 1600 ካሬ ከመንግስት በቅርብ ቀን እንደተሰጠው ይታወቃል። ሆኖም በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ በአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ፅ/ቤት ግንባታ፤ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማትያስ እንዲሁም ብፁፅ አቡነ ሄኖክና ሌሎች ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ። በመርሐ ግብሩም የኮልፌ ቀራንዮ የአድባራትና የገዳማት አባቶች የተገኙ ሲሆን። የደብራችን የቅድስት አርሴማ ቤ/ክ አስተዳዳሪና ካህናት እንዲሁም ውስን የሰ/ት ቤታችን አባላት በመገኘት የመርሐ ግብሩ ተሳታፊ ሆነዋል።

❤ በዚያም ወቅት ቅዱስ ዮሐንስ ተነሣ እናቱንና አባቱንም ተሰናብቶ ወደ አትሪብ ከተማ ሔደ መኰንኑንም በውሽባ ቤት አገኘውና በወጣ ጊዜ በፊቱ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ። መኰንኑም ለአንድ ወታደር ሰጥቶት ምናልባት ከምክሩ ተመልሶ ቢታዘዝለት አስቦ እንዲአባብለው ወታደሩን አዘዘው። ከዚህ በኋላ መኰንኑ ወደ ሥራው ሔደ ወታደሩም ቅዱስ ዮሐንስን ወደ ቤቱ ወሰደው። ቅዱሱም ተአምራትን አደረገ ያ ወታደርም በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ አመነ። መኰንኑም በተመለሰ ጊዜ ያ ወታደር በክብር ባለቤት በጌታችን በመኰንኑ ፊት ታመነ የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበለ። ❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ዮሐንስን እንዲአሠቃዩት መኰንኑ አዘዘ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይም አሠቃዩት። እግዚአብሔርም ያጽናውና ያስታግሠው መልአኩንም ልኮ ቊስሎቹን አድኖ ያለ ጉዳት በደኅና ያነሣው ነበር። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ እንዴናው ከተማ ላከው በዚያም ታላቅ ሥቃይን አሠቃዩት። መኰንኑም ማሠቃየቱን በሰለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማዕትነትንም አክሊል ግንቦት 8 ቀን ተቀበለ። የአቅፍሐሲ ዮልዮስም ሥጋውን ወስዶ ገነዘው ወደ አገሩ ስንሑትም ላከው። የአገሩ ሰዎች ሁሉም ወጥተው በፍጹም ደስታ ተቀበሉት ከማዕጠንት ጋራ እየዘመሩና እያመሰገኑ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አኖሩት ከሥጋውም ብዙዎች ድንቆች ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ዮሐንስ በአማላጅነቱ ያድነን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የግንቦት8 ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለዮሐንስ_ጸጋዊተ_ምጽዋት_እዱ። ባዝግና ብርሃን ጽሩየ እስከ አጥርየ በዐውዱ። አመ አነዳሁ ዘሐቁ ወሌለዩ እምነ ድዱ። አፍሐመ እሳት ላዕሌሁ አንደዱ ወዕብን ቀይሕ ሥጋሁ በርደዱ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የግንቦት_8።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ። ወእግዚእነ በቃለ ቀርን። ዘምሩ ለአምላክ ዘምሩ"። መዝ 46፥5-6። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 21፥12-15።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ደለወኒ ዘአሕመምከኒ። ከመ አእምር ኵነኔከ። ይኄይሰኒ ሕገ አፉከ እምአእላፍ ወርቅ ወብሩር"። መዝ 118፥71-72። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 6፥7-ፍ.ም፣ ያዕ 1፥7-17 እና የሐዋ ሥራ 13፥1-13። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 6፥19-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወይም የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የጥንት የዕርገት በዓልና የበዓለ ሃምሳ ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ግንቦት ፰ (8) ቀን። ❤ እንኳን #ለክብር_ባለቤት_ለጌታችን_ለአምላካችን_ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ_ለጥንት_ለዕርገቱ_በዓል፣ ለአስቄጥስ ገዳም አበ ምኔት የወፍጮ ድንጊያ ለሚሰራው ለአውሎጊስ ተውሶ ከእግዚአብሔር ወርቅ እንዲያገኝ ላደረገው ለምኖ ለታላቁ ለገድለኛው አባት #ለአባ_ዳንኤል ለዕረፍት በዓልና ስንሑት ከሚባል አገር ለሆነ #ለቅዱስ_ዮሐንስ ለምስክርነቱ ፍጻሜ ለዕረፍቱ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱስ_ዮሐንስ ማኅበር #ከሁለት_መቶ_ሃያ_ሁለት_ሰማዕታት፣ #ከሱሲስና+ከንቡረ_እድ_ማትያስ በምስክርነት ራሳቸውን ከተቆረጡ፣ #ከከበረ_ታጋዳ_ማክሲምስ ምስክር ሁኖ ከዐረፈ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                           ✝ ✝ ✝     ❤ "#ሰላም_ለዕርገቱ_መድምም እንዘ ያንበለብል ጸዳሉ ግሩም"። ትርጉም፦ አስፈሪ ብርሃኑ እያንበለበለ (ቦግ ቦግ እያለ) ለተደረገ #ድንቅ_ዕርገቱ_ሰላምታ_ይገባል። #ሊቁ_አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ_በተአምኆ_ቅዱሳን_ላይ።                              ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ዕለት የክብር ባለቤት ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእኛ በነሣው ሥጋ ከአባቱና ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ ወደአለው የአንድነት አኗኗሩ ከሰማያት በላይ ያገረበት ሆነ። ❤ እርሱም በረቀቀ ጥበቡ በመከራው በሞቱና በመነሣቱ ሥራውን ከፈጸመ በኋላ አርባው ቀን ሲፈጸም በነፋሳት ክንፍ ላይ ሁኖ ዐረገ። ያን ጊዜ በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ ወጣ በነፋሳትም ክንፎች ላይ ሁኖ ወጣ ያለው የዳዊት ትንቢት ተፈጸመ። ❤ በዚህም ዕርገቱ የሚያምኑበት በልዕልና ወደሚኖሩበት የሚዐርጉ መሆናቸው ተረዳ ተረጋገጠ ራስ በአለበት ሕዋሳት ሊኖሩ ይገባልና። አዳም አስቀድሞ በምድራዊ ርስቶች በሲኦልም እንደኖረ መኖርንም እንደቀደመ እንዲሁ ዳግማዊ አዳም ጌታ በመንግሥተ ሰማያት ርስት መኖርን ቀደመ። ❤ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ዕርገቱን ከትንሣኤው አከታታትሎ ወዲያውኑ አላደረገም መናፍቃን ዕርገቱ ምትሐት ናት ብለው እንዳያስቡ። ጌታችንም በረቀቀ ጥበቡ የደቀ መዛሙርቱን ተሽብሮ የነበረ ልቡናቸውን እያጽናና መነሣቱንም እያስረዳቸው ከትንሣኤው በኋላ አርባ ቀን ኖረ። ❤ በጌታችንም ዕርገት የቅዱስ ዳንኤል ትንቢት ተፈጸመ እንዲህ የሚል "ሌሊት በራእይ አየሁ እንሆ ታላቅ እንደ ሰው ልጅ የሆነ መጣ ዘመናትን ወደሚያስረጃቸው ደረሰ ከፊቱም አቀረቡት። የዘላለም አገዛዝ፣ ጌትነት፣ መንግሥት፣ የዘላለም ሥልጣን ተሰጠው ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው መንግሥቱም የሚያልፍ የማይጠፋ ነዋሪ ነው"። ለእርሱም ምስጋና ይሁን ከቸር አባቱ ሕይወት ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ለዘላለሙ አሜን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ዳንኤል፦ ይህም ቅዱስ ዕውነተኛ ንጹሕ ፍጹም ነው ዜናው በሁሉ ቦታ በተሰማ ጊዜ ሹመት ያላት ቅድስት አንስጣስያ የመኳንንቶችን ልብስ ለብሳ ወደርሱ መጥታ ከእርሱ መነኰሰች። በእርሱ አቅራቢያም ሃያ ስምንት ዓመት በበዓት ውስጥ ኖረች እርሷ ሴት እንደሆነች ማንም አላወቀም። ❤ ይህም ቅዱስ ስሙ አውሎጊስ የሚባለውን ሰው አየው ይህም አውሎጊስ የወፍጮ ድንጋይ እየወቀረ ለግርሽ እየሸጠ ሁል ጊዜ በመጠኑ እየተመገበ ለድኆችንና ጦም አዳሪዎችን ይመግባቸዋል የተረፈውንም ፍርፋሪ ለውሾች ይጥላል ለነገ ብሎ ምንም አያሳድርም። አባ ዳንኤልም ይህን መልካም ሥራውን አይቶ በርሱ ደስ አለው እጅግም አማለው ለአውሎጊስም የዚህን ዓለም ብልጽግና እንዲሰጠውና ለድኆች የሚመጸውተው እንዲጨመርለት ወደ እግዚአብሔር ለመነ። ❤ ለአውሎጊስም ዋስ ሆነው የሚወቅረውንም ደንጊያ ሲፈነቅል በሸክላ ዕቃ የተደፈነ ወርቅን አገኘ ወደ ከቊስጥንጥንያ ከተማ ሒዶ የንጉሥ የሠራዊት አለቃ ሁኖ ተሾመበት የሚሠራውንም የቀደመ በጎ ሥራውን ተወ። አባ ዳንኤልም ስለርሱ ሰምቶ ወደርሱ በሔደ ጊዜ የንጉሥ ሠራዊት አለቃ ሆኖ በፈረስ ላይም ተቀምጦ ብዙ ሠራዊት አጅቦት እርሱም በትዕቢት ተመልቶ የቀድሞ በጎ ሥራውንና ለድኃ መመጽወቱንም ትቶ አገኘው። አባ ዳንኤልም አይቶ አዘነ ስለርሱ በመለመኑ ተጸጸተ። ❤ ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለፍርድ እንደ መጣ አባ ዳንኤልንም እንዲሰቅሉት ሲያዝ የአውሎጊስንም ነፍስ ከእርሱ እንዲሹ በእርሱ ምክንያት ጠፍቷልና የከበረች ድንግል እመቤታችን ማርያምም የክብር ባለቤት ጌታችንን ልጅዋ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ አባ ዳንኤል እንደ ለመነችው በሌሊት ራእይ አባ ዳንኤል ራሱ አየ። በነቃም ጊዜ ደነገጠ አውሎጊስንም ወደ ቀድሞ ሥራው ይመልሰው ዘንድ በጸሎትና በምሕላ በመትጋት ወደ እግዚአብሔር እየለመነ ግብር ገባ ሱባኤ ያዘ። ከዚህ በኋላ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለት "በፍጥረቱ ላይ በሚያደርገው በእግዚአብሔር ፍርድ ውስጥ ለመግባት በመድፈሩ ገሠጸው"። ❤ በዚያንም ወቅት አውሎጊስን የሾመው ንጉሥ ሞተ ሌላ ንጉሥም ነገሠ በአውሎጊስም ላይ ተነሥቶ ገንዘቡን ሁሉ ወረሰ። ደግሞም ሊገድለው ፈለገው አውሎጊስም ነፍሱን ለማዳን ከንጉሡ ሸሽቶ ወደ አገሩ ደረሰ እንደ ቀድሞውም ደንጊያ ይወቅር ጀመረ አባ ዳንኤልም ወደርሱ ተመልሶ ስለርሱ ያየውን ሁሉ ስለ ርሱም እንደሰቀሉትና ነፍሱንም ከእርሱ እንደፈለጉ ነገረው። ❤ በዚህ በአባ ዳንኤል የትንቢት መንፈስ አድሮበት ነበር ከእርሱም ብዙዎች ታላላቅ ታምራት ተገለጡ። መናፍቃን አርዮሳውያንም ከቀናች ሃይማኖት ሊያወጡት በፈለጉ ጊዜ እንቢ አለ። ያቺንም የክህደት ደብዳቤ ተቀብሎ ቆራረጣት የአርዮሳዊ ንጉሥ ወታደርም ይዞ ብዙ ሥቃይን አሠቃየው። ❤ በአንዲት ዕለትም ቅዱሳት ደናግል ወደ ሚኖሩበት ወደ ሲሐት ገዳም አባ ዳንኤልን ተመስሎ ሽፍታ ገባ። ደናግሉም በደስታ ተቀብለው እግሩቹን አጠቡ። እነርሱም አባ ዳንኤል እንደሆነ አምነው የወንበዴውን የእግር እጣቢ ውኃ በረከቱን ለማግኘት በላያቸው ረጩት። በዚያም አንድ ዐይኗ የታወረ ነበረች ውኃው በነካት ጊዜ ዐይኗ በርቶላት አየች። ወንበደውም አይቶ ደነገጠ ሥራውንም ገለጠ ንስሐ ገብቶም መነኰሰ በበጎ ገድል ሁሉ ተጠምዶ እግዚአብሔርን አገለገለው። ❤ ጌታችንም ከዚህ ዓለም ድካም ሊአሳርፈው በወደደ ጊዜ መልአኩን ልኮለት ከዓለም የሚወጣበትን ጊዜ አስረዳው። መነኰሳቱንም ሰብስቦ በበጎ ሥራ እንዲጸኑ አዘዛቸው አጽናናቸው አረጋጋቸውም። ከዚህም በኋላ ግንቦት 8 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ በአባ ዳንኤል ጸሎት ይማረን በረከቱም ትድረሰን ለዘለዓለሙ አሜን።                            ❤ #ቅዱስ_ዮሐንስ፦ የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም መቃርስ የእናቱም ስም ሐና ነው። እርሱም የአባቱን በጎች ሲጠብቅ የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦ የብርሃን አክሊልን አሳየው። "እነሆ ተጋድሎ ተዘርግቶ በክርስቶስ ስም ለሚጋደል አክሊላት ተዘጋጅተው ሳሉ አንተ ለምን ከዚህ ተቀመጥክ። አሁንም ወደ አገረ አትሪብ ሒድ የክብር ባለቤት ስለሆነ ስለ ክርስቶስ ስም ተጋደል" አለው። ከዚያም ሰላምታ ሰጥቶት ከእርሱ ዘንድ ሔደ።