ru
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

Открыть в Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

Больше
638
Подписчики
-224 часа
-57 дней
-1130 день
Архив постов
❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ሰኔ ፱ (9) ቀን። ❤ እንኳን ልበ አምላክ የተባለውን ታላቁን ንጉሥ መዝሙረኛው #ቅዱስ_ዳዊት ቀብቶ ላነገሠው ለታላቁ #ነቢይ_ለቅዱስ_ሳሙኤል_ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዐልና #ለቅዱስ_ሉክያኖስ ከሌሎች #አራት_ሰማዕታት ጋር ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ #ከቅዱሳን_ከዮሐንስና #ከጳጳስ_አርልክሳ_ከዕረፍታቸው_መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ነቢዩ_ቅዱስ_ሳሙኤል፦ የዚህ ቅዱስ አባቱ ሕልቃና ይባላል የእናቱም ስሟ ሐና ነው እርሱም ከሌዊ ነገድ ከካህኑ አሮን ወገን ናቸው ሐናም መካን ነበረች ክብር ይግባውና ወደ እግዚአብሔር እያለቀሰች አዘውትራ ስለ ማለች ይህን የተባረከ ልጅ ሰጣት በቤቷም ሦስት ዓመት አሳደገችው። ❤ ከዚህም በኋላ ገና ስትፀንሰው እንደተሳለች ወደ እግዚአብሔር መቅደስ አቀረበችው ካህኑ ኤሊንም በመላላክ የሚያገለግለው ሆነ። የካህኑ ልጆች ግን ክፉዎች ነበሩ እግዚአብሔርንም አይፈሩም ነበር በቅዱስ መሥዋዕቱም ላይ በደሉ። ይህ ሕፃን ሳሙኤል ግን በኤሊ ፊት ለእግዚአብሔር ሲያገለግል ኖረ በነዚያ ወራቶችም ቃለ እግዚአብሔር ውድ ነበር የሚታይ ራእይም አልነበረም። ❤ ከዚህም በኋላ በአንዲት ሌሊት እንዲህ ሆነ ኤሊ በመኝታው ተኝቶ ሳለ ዐይኖቹንም መፍዘዝ ጀምረው ነበር ማየትም አይችልም ነበር። የእግዚአብሔርንም መብራት አብርቶ ለማሳደር ገና አላዘጋጁም ነበር ሳሙኤል ግን በቤተ መቅደስ እግዚአብሔር ማደሪያ ታቦት አጠገብ ተኝቶ ነበር። እግዚአብሔርም "ሳሙኤል ሳሙኤል ሳሙኤል" ብሎ ጠራው እነሆ እኔ አለሁ አለ። ወደ ኤሊም ፈጥኖ ሔደ "ስለጠራኸኝ እነሆ እኔ መጣሁ" አለው። ኤሊም "አልጠራሁህም ተመልሰህ ተኛ" አለው ሒዶም ተኛ። እግዚአብሔርም ዳግመኛ "ሳሙኤል ሳሙኤል ሳሙኤል" ብሎ ጠራው ሳሙኤልም ተነሥቶ ወደ ኤሊ ሔደ ስለ ጠራኸኝ እነሆ መጣሁ" አለው ኤሊም "አልጠራሁህም ተመልሰህ ተኛ" አለው። ❤ ሳሙኤልም ከዚህ አስቀድሞ እግዚአብሔርን በራእይ ገና አላወቀውም ነበር ቃለ እግዚአብሔርም አልተገለጠለትም ነበር። ዳግመኛም እግዚአብሔር ሳሙኤልን ሦስት ጊዜ ጠራው ተነሥቶም ወደ ኤሊ ሔደ "ስለጠራኸኝ እነሆ መጣሁ" አለው ኤሊም ያንን ልጅ እግዚአብሔር እንደጠራው አሰበ። "ልጄ ተመልሰህ ተኛ የሚጠራህ ካለ እኔ ባሪያህ እሰማለሁና ጌታዬ ተናገር በለው" አለው ሳሙኤልም ሒዶ በመኝታው ተኛ። እግዚአብሔር መጥቶ እንደ መጀመሪያው በፊቱ ቁሞ ጠራው። ሳሙኤልም "እኔ ባሪያህ እሰማለሁና ጌታዬ በል ተናገር" አለው እግዚአብሔርም ሳሙኤል "የሰማው ሁሉ ሁለቱን ጆሮዎቹን ይይዝ ዘንድ እንሆ እኔ በእስራኤል ላይ የተናገርሁት ቃሌን አደርጋለሁ። በዚያችም ቀን በኤሊና በወገኑ ላይ የተናገርኹትን ሁሉ አጸናለሁ እጀምራለሁ እፈጽማለሁም። ልጆቹ እግዚአብሔርን ቃል አቃልለዋልና እርሱም አልገሠጻቸውምና በልጆቹ ኃጢአት እኔ ወገኑን በዘላለም እንደ ምበቀለው ነገርሁት። ስለዚህ ነገር በዕጣንም ቢሆን በመሥዋዕትም በመሆን የኤሊ የወገኑ ኃጢአት እስከ ዘላለሙ ድረስ እንዳይሠረይ ራሴ እንዲህ ብሎ ማልሁ"። በኤሊ ወገኖችና ልጆች ላይ እግዚአብሔር የተናገረው ሁሉ ተፈጸመ። ❤ ከዚህም በኋላ የቂስ ልጅ ሳኦልን ቀብቶ ለእስራኤል ልጆች ያነግሠው ዘንድ እግዚአብሔር ሳሙኤልን አዘዘው እንዲአነግሥላቸው ለምነዋልና። ሳኦልም የልዑል ትዕዛዝ በተላለፈ ጊዜ ዳግመኛ ለእስራኤል ንጉሥ ሊሆን የዕሴይ ልጅ ቅዱስ ዳዊትን ይቀባው ዘንድ ይህን ነቢይ ሳሙኤልን ዳግመኛ አዘዘው። ❤ ይህም ነቢይ ሳሙኤል በሕይወት በኖረበት ዘመን ሁሉ እስራኤልን አስተዳደራቸው። ከዚህም በኋላ ሰኔ 9 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በነቢዩ ቅዱስ ሳሙኤል ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ቅዱስ_ሉክያኖስና_አራቱ_ሰማዕታት፦ ይህም ቅዱስ አስቀድሞ የጣዖት ካህን ነበር የሰማዕታትንም መከራቸውን በእሳት ሲአቃጥሏቸውና ሕዋሳታቸውን ሲቆራርጧቸው ሲሰቅሏቸው ከእሳት ምድጃ ውስጥም ሲጥሏቸው ምንም ምን ጉዳት እንዳልደረሰባቸው በአየ ጊዜ ከዚህ ሥራ የተነሣ አደነቀ ክብር ይግባውና በጌታችን አመነ ያገለግላቸው የነበሩ ጣዖታት ከእሳት ቢጥሏቸው ፈጥነው ይቃጠላሉ እንጂ ይህን ሥራ ሊሠሩ እንደማይችሉ ተረድቷልና። ዳግመኛም እንዲህ አለ "ይህን ድንቅ ሥራ የሚሠራ አምላክስ በእውነት እርሱ አምላክ ነው"። ❤ ከዚህ በኋላም በንጉሥ ፊት "እኔ ክርስቲያን ነኝ ክብር ይግባውና በክርስቶስ አምናለሁ" ብሎ በግልጥ ጮኾ ተናገረ። ንጉሡም ወደርሱ አቅርቦ ጣዖት ማምለክን እንዳይተው መከረው ወደ አምልኮ ጣዖት ይመለስ እንደሆነ ብሎ ብዙ ቃል ኪዳኖችን ገባለት። እርሱም ግን አልሰማውም ሥቃዩንም አልፈራም ከዚህም በኋላ ንጉሡ ጽኑዕ ሥቃይን ሊአሠቃየው ጀመረ ዘቅዝቀው እንዲሰቅሉት መንጋጋውንም በደንጊያ አሰንዲሰብሩት ታላቅ ግርፋትንም እንዲገርፉት አዘዘ። ❤ ከዚህም በኋላም አራት ክርስቲያን እሥረኞች ቀረቡና ከእርሱ ጋራ አቆሟቸው ንጉሡም "ለአማልክት ዕጣን ዕጠኑ ይህ ካልሆነ ግን ታላቅ ሥቃይን አሠቃያችኋለሁ" አላቸው። እነርሱም ለስሕተቱ አልታዘዙለትም በላያቸውም ተቆጥቶ በእሳት ምድጃ ውስጥ ጨመራቸው ያንጊዜ ዝናብ ዘነበ እሳቱንም አጠፋው። ❤ ቅዱስ ሉክዮስን ግን "እንደ አምላክህ እሰቅልሃለሁ" ብሎ በዕንጨት መስቀል ላይ እንዲሰቅሉት አዘዘ በረጃጅም ችንካሮችም ሥጋውን ሁሉ ቸነከሩት ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ። እንዚያን አራቱን ሰዎችም ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘና ቆረጡአቸው የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሉክያኖስና በከበሩ አራት ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ቴድረሰን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 9 ስንክሳር።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ "#ሰላም_ለሉክያኖስ_ዘአድምዐ_ተወድሶ። ምስለ ፬ቱ ዕደው ሥቃያተ ስምዕ በተዓግሦ። ሶበ ለአማልክት ኢሦዐ መሥዋዕተ ልዑል አስተኀይሶ። እለ ቀነውዎ እስከ ይመጡ ነፍሶ። እስመ በአዕባን ቀጥቀጡ መንከሶ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሰኔ_9።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወሳሙኤልኒ ምስለ እለ ይጼውዑ ስሙ። ይጼውዕዎ ለእግዚአብሔር ውእቱኒ ይሰጠዎሙ። ወይትናገሮሙ በዐምደ ደመና"። መዝ 98፥6-7። የሚበቡት መልዕክታት ዕብ 11፥32-ፍ.ም፣ 2ኛ ጴጥ 3፥1-7 እና የሐዋ ሥራ 13፥16-24። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥32-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የነቢዩ ቅዱስ ሳሙኤል የዕረፍት በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ አባታችንም ካዐረፉ በኋላ በደብረ ምዕዋን ቅድስት ሥላሴ ደብረ ናዝሬት ከአባታቸው ከአቡነ ብፁዐ ኣምላክ ጋር ተቀበሩ። የአቡነ ብፁዕ አምላክ እና የአቡነ በኩረ ድንግል ገዳም ደቀ መሐሪ ጎደይቲ አካባቢ ይኛል። እነርሰም ካረፉ በኋላ እየተገለጡ በጠበላቸው አጋንንት ያደሩባቸውን ሰዎች ሁለ እየፈወሱ፣ በመቃብራቸው አፈር ሙት እያስነሡ የተለያዩ ድንቅ ድንቅ ተኣምራት ሲሠሩ ታይተዋል። የሠሯቸውም ተዓምራት ተዘርዝረው የሚያልቁ አይደለም። ከአባታችን ከአቡነ በኩረ ድንግል እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን። ምንጭ፦ በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን።

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ሰኔ ፱ (9) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_ኤርትራ_አገር የሚገኘው #ደብረ_ምዕዋን ለመሰረቱ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ብፁዕ_አምላክ_ደቀ_መዝሙር ለሆኑት #ለአቡነ_በኵረ_ድንግል_ዘደብረ_ምዕዋን_ለዕረፍታቸው_በዐል በሰላም አደረሰን።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #አቡነ_በኵረ_ድንግል፦ የአቡነ ብፁዐ አምላክ ረድእ የነበሩ ሲሆን እርሳቸውም ካረፉ በኋላ ተመርጠው በደብረ ምዕዋን ገዳም ላይ አበ ምኔት ሆነው ተሾመው ብዙ አገልግለዋል" ጻድቁ በምድረ ኤርትራ በምንኩስና እና በብሕትውና ጸንተው ለትልቅ ሰማያዊ ክብር የበቁ ታላቅ ጻድቅ ናቸው። በዓለ ዕረፍታቸው ሰኔ 9 ነው። ❤ የአቡነ በኵረ ድንግል፦ አባታቸው ማርቆስ እናታቸው እግዚእ ክብራ የሚባሉ ሲሆን ጻድቁ ገና በእናታቸው ማሕፀን ሳሉ ብዙ ተኣምራት ይሠሩ ነበር" ሲወለዱም የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ከነልጇ (ምስለ ፍቁር ወልዳ) በልባቸው ላይ ተሥላ ተገኝታለች" በማሕፃን ሳሉ ተመርጠዋልና በአኵሱም ሲወለዱ እንደሌሎቹ ቅዱሳን አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ›› ብለው ስመ ሥላሴን ጠርተው አመሰገኑ። በዚያ የነበሩና ይህንን የተመለከቱ ሰዎችም ባዩትና በሰሙት ነገር እጅግ ተደነቁ። ❤ በ40ኛው ቀናቸውም በጥምቀት የሥላሴን ልጅነት እንዲቀበሉ ወላጆቻቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲወስዷቸው በወቅቱ የነበሩት ጳጳሱ አቡነ ሰላማ ሕፃኑ ትልቅ መነኵሴና የአቡነ ብፁዐ አምላክ ደቀ መዝሙር እንደሚሆን ተገልጾላቸው ትንቢት ተናገሩ። ዳግመኛም ጳጳሱ ቅብዓ ሜሮን ሊቀቡት ሲሉ ሥዕለ ማርያም ከነልጇ በሕፃኑ ደረት ላይ ተሥላ አይተዋት ደነገጡ ወዲያውም ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ተገልጸ ሳይፈሩ ሥርዓተ ጥምቀቱን እንዲፈጽሙ አዘዛቸው ዳግመኛም ..… "ስሙን በኵረ ድንግል በለው ትርጉሙም በልቡ ላይ ያየኸው ሥዕል ነው" ብሎ ነገራቸው" ሕፃኑም ከተጠመቀ በኋላ እመቤታችን ከነልጇ ጋር ተገልጻ በትእምርተ መስቀል ባረከችው ያ ትእምርተ መስቀልም ዳግመኛ በሰውነታቸው ላይ ተሳለ። ❤ ከዚህም በኋላ አቡነ በኵረ ድንግል አድገው ቤተሰቦቻቸውን እየረዱ በእረኝነት እያገለገሉ በመልካም አስተዳደግ አደጉ" ዕድሜአቸው ለትምህርት እንደደረሰ ወላጆቻቸው ለንቡረ እድ ዮፍታሔ ሰጧቸውና አስተማሯቸው። ከቋንቋዎች ግእዝ፣ ዐረብ ዕብራይስጥ፣ ጽርዕ እና ሮማይስጥ ተማሩ፤ ብሉይንና ሐዲስን እንዲሁም ቅዱሳት መጻሕፍትን ሁሉ አጠናቀው ተማሩ። ቅኔ ድጓ ጾመ ድጓ እና የቅዱስ ያሬድን ዜማዎችም በሚገባ አጠኑ። ትምህርታቸውንም ከጨረሱ በኋላ መምህራቸው ወደ ሊቀ ጳጳስ ወሰዱአቸው በልባቸው ያለች የእመቤታችን ሥዕልም ለጳጳሱ ተገልጣ "ይህ የምወደው ልጄ ስለሆነ በልቡ ተሳልሁ ስለዚህ ዲቁና ቅስና ስጠው፣ ኤጲስ ቆጵስነትም ሹመው" አለቻቸው። ጳጳሱም ባዩትና በሰሙት ነገር ተደንቀው ተነሥተው እንደተባሉት በሦስቱ መዕረግ ሾሟቸው። ከሹመታቸውም በኋላ በአከባቢው ያሉ ሰዎች አቡነ በኩረ ድንግልን ብርሃን ለብሰው ስላዩዋቸው በጣም ተደነቁ። ❤ ከዚህም በኋላ አቡነ በኵረ ድንግል ለአቅመ አዳም ሲደርሱ ወላጆቻቸው በሕገ ቤተ ክርስቲያን መሠረት ሚስት ሲያጩላቸው አቡነ በረ ድንግል ግን "እኔስ ፍላጎቴ በድንግልና መኖር እንጂ ማግባት አይደለም" ብለው ሌሊት ተነሥተው ከቤታቸው ጠፍተው ወደ እግዚአብሔር ቤት ሔደው "አቤቱ ጌታ ሆይ! ከዘለዓለም እሳት ከዲያብሎስ እሥራት ሰውረኝ መጥፎውን ሐሳብ ከእኔ አርቀህ ፍቃድህን እፈጽም ዘንድ እርዳኝ የእመቤታችን ሥዕል ከነልጇ በልቤ አለና ወደ ጋብቻ ዓለም ለመግባት ኅሊናዬ አልፈቀደልኝም ስለዚህ ፍቃድህ ቢሆንልኝ እንደ መላእክት ንጹሕ ሁኜ እንድኖር እለምንሃለሁ፣ አንተ ድኃና ምስኪን የማትንቅ አምላክ መሆንህን ዐውቃለሁና…" እያሉ ጸለዩ። እየጸለዩ ሳለ ክብርት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ ሚካኤልንና ቅዱስ ገብርኤል አስከትላ ተገለጠችላቸውና "ልጄ ሆይ! ጸሎትህ ተሰምቷልና ወደ ደብረ ዳሞ ወደ አባትህ ሒድ፣ እንዲሁም ደግሞ ወደ ደብረ ናዝሬት ወደ ብፁዐ አምላክ ዘንድ ሒድ የብዙዎች አባትም ትሆናለህ" በማላት ከባረከቻቸው በኋላ ተሰወረች። ❤ ከዚህም በኋላ ጻድቁ መጋቢት 9 ቀን በቦታቸው ሆነው በተመስጦ እየጸለዩ ሳሉ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በደመና ተሸክሞ ወስዶ ደብረ ዳሞ የቅዱሳን ማረፍያ ቦታ አደረሳቸው። እመቤታችን እንደነገረቻቸው በገዳሙ አስቀድማ እንደነገረቻቸው ለረጅም ዓመታት በትሕትና ካገለገሉ በኋላ ወደ አባታቸው ወደ አቡነ ብፁዐ አምላክ ከረጅም ጉዞ በኋላ መጡ። አቡነ ብፁዐ አምላክም አስቀድመው መምጣታቸውን ያውቁ ነበርና አሁን ሲያገኗቸው እግዚአብሔርን አመስግነው በታላቅ ደስታና ትሕትና ተቀበሏቸው። ❤ በገዳማቸውም በትሕትና እያገለገለ ከቆዩ በኋላ አንድ ቀን አቡነ ብፁዐ አምላክ "ዛሬ በእጅህ ቍርባን እንድንቀበል አንተ ቀድስ" አሏቸው። አቡነ በኩረ ድንግልም ቅዳሴ ገብተው አሐዱ አብ ቅዱስ… ብለው ሲጀምሩ ከመሬት ወደላይ 5 ሜትር ያህል ከፍ ብለው ታዩ፤ ይኽንንም አይተው አቡነ ብፁዐ አምላክ በጣም ተደንቀው እግዚአብሔርን አመሰገኑ። አቡነ በኵረ ድንግልም በእንዲህ ያለ ሕይወት አባታቸውን አቡነ ብፁዐ አምላክን ካገለገሉ በኋላ አቡነ ብፁዐ አምላክ ታኅሣሥ 9 ቀን የገዳማት መነኰሳትን ሰብስበው "ዛሬ ለሁላችሁ መሪ የሚሆን ትሑትና ደግ መምህር እሰጣችኋለሁ ከእኔ በታች እርሳቸውን ስሟቸው ታዘዙአቸውም" ብለው ነገሯቸው። ❤ ዳግመኛም አባታችን አቡነ ብፁዐ አምላክ የዕረፍታቸው ጊዜ ሲደርስ የገዳሙን መነኰሳት ሰብስበው ከእርሳቸው በኋላ አባት እንዲሆኗቸው አቡነ በኵረ ድንግልን እጃቸውን ጭነው ባርከው ሾሟቸው። ከዚህም በኋላ አቡነ በኵረ ድንግል በጾም በጸሎት በስግደት ለገዳሙና በገዳሙ ለሚኖሩ መነኰሳት ሁሉ በትሕትና እያገለገሉ በታላቅ ተጋድሎ ኖሩ። የገዳሙ መነኰሳትም በጣም ወደዷቸው። ተጋድሏቸውንና አገልግሎታቸውንም በፈጸሙ ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአቡነ በኵረ ድንግል እንዲህ የሚል ቃልኪዳን ገባላቸው። ❤ "በስምህ ዝክር የሚዘክር ስምህን የሚጠራ በዕረፍትህ ቀን የታመሙትንና የታሰሩትን የጎበኘ በስምህ የተራበ ያበላ ያጠጣ የታረዘ ያለበሰ የልጁን ስም በስምህ የጠራ ይህን ሁሉ ያደረገውን እምረዋለሁ ክፉም አይነካውም፤ በደብረ ምዕዋን በአባትህ በብፁዐ አምላክ ቦታ በአንተም ቦታ የተቀበረ በቦታው ቅዱስ ቍርባን የተቀበለ ክፉ አያገኘውም፣ እምረዋለሁ፣ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌምም አስገበዋለሁ ብሔረ ሕያዋንና ብሔረ ብፁዓንንም አወርሰዋለሁ…" የሚሉ ታላላቅ የምሕረት ኪዳናትን ከእግዚአብሔር ከተቀበሉ በኋላ ሰኔ 9 ቀን ትንሽ የራስ ምታት ሕመም ጀመራቸው። የገዳሙ መነኰሳትና ሌሎቹም ታላላቅ ቅዱሳን አባቶች እንደእነ አቡነ ዮሐንስ ዘደብረ ቢዘን ያሉት እንደየ ደረጃቸው ከያሉበት ተሰበሰቡ። በዚህም ጊዜ ሥሉስ ቅዱስ ተገልጸውላቸው ድጋሚ ቃልኪዳን ገብተውላቸው አረጋጓቸውና ቅድስት ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች።

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ሰኔ ፰ (8) ቀን። ❤ እንኳን #አምላክን_ለወለደች_በሁለት_ወገን #ድንግል_ለሆነች_ለእመቤታችን_ለቅድስት_ድንግል ማርያም ለታወቀችው በውኃ ምንጭ ዘንድ ላለች #ለቤተ_ክርስቲያንዋ_ለቅዳሴ_ቤት ከእመቤታችን #ከሠላሳ_ሦስቱ_በዓል_አንዱ_ለሆነ_በዐል (እርሱም #ጌታችን ከእርሷ ጋር ወደ ግብጽ አገር ተሰዶ ሲመለስ ያፈለቀው የተባረከ መታጠቢያ ውሃ (ጠበል) ነው፣ ለርማኖስ እናት #ለቅድስት_ትምዳ_ለዕረፍቷ መታሰቢያ በዐል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ ከአንድ ሽህ ሁለት ሰማዕታት ከመታሰቢያቸው፣ ከቅዱሳን ከአትካሮንና ከአውሎጊስ ከበዓላቸው መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤በዚች ቀን #አምላክን_የወለደች_በሁለት_ወገን #ድንግል_የሆነች_የእመቤታችን_የቅድስት_ድንግል #ማርያም የታወቀችው በውኃ ምንጭ ዘንድ ያለች የቤተ #ክርስቲያንዋ_ለቅዳሴ_ነው። እርሱም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ ጋር ወደ ግብጽ አገር ተሰዶ ሲመለስ ያፈለቀው የተባረከ መታጠቢያ ነው። ❤ ይህም እንዲህ ነው ለጻድቁ ዮሴፍ የእግዚአብሔር መልአክ በሕልም ተገልጾለት "ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ አገር ሒድ" አለው። ዮሴፍም ነቅቶ ተነሣ ክብር ይግባውና ሕፃኑን ጌታችንን እናቱንና እኅቷ ሰሎሜን ይዞ ወደ ግብጽ አገር ሔዱ በዚያም በውስጧ ባሉ በብዙ አገሮች እየዞሩ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር ኖሩ። ❤ ኄሮድስም ከሞተ በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ ሁለተኛ ተገለጠለት "ወደ እስራኤል አገር ሕፃኑንና እናቱን ይዞ እንዲመለስ" አዘዘው። በሚመለሱም ጊዜ ወደ መዓልቃ ደረሱ ከዚያም ወደ መጣርያ አገር ደረሱ ይቺም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውኃ ያፈለቀባትና የመታጠቢያ ቦታ የሆነች ናት እርሷም እስከ ዛሬ አለች ሰዎችም ከአገሩ ሁሉ ከየነገዱ ሁሉ መጥተው አምላክን ወደ ወለደችና በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ወደ ጸናች ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም ይለምናሉ ከተባረከውም የውኃ ምንጭ ታጥበው ከደዌያቸው ሁሉ ይድናሉ በዛሬዪቱ ሰኔ 8 ቀን ከከበረች ቤተ ክርስቲያንም ይባረካሉ። ❤ እርሷን እመቤታችንን ለመረጣትና ለወደዳት በሥጋም እናቱ ላደረጋት ስለርሷም ዘመድ ለሆነንና ወደርሱ ላቀረበን ወራሾቹም ላደረገን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 8 ስንክሳር።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ "#ሰላም_ዕብል_ለቅዳሴ_ቤትኪ_ሕንፅት። ኀበ አንቅዐ ወሌድኪ ማየ በረከት። #ማርያም_ድንግል በስምከመ በቊዔት። እስመ ይትወሀብ ለዘጸለየ በኵሉ ዕለት። ሠናይ ሀብት ወፍጹም ፍት"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሰኔ_8።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እፎ እስፋሕ ለከ ሥጋየ። በምድረ በድው ኀበ አልቦ ዕፅ ወማይ። ከመዝ በመቅደስከ አስተርአይኩከ"። መዝ 62፥1-2" ወይም መዝ 77፥15-16።  የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 4፥14-17።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወአስተዮሙ ከመ ዘእምቀላይ ብዙኅ። ወአውኃዘ ማየ ከመ ዘእምአፍላግ። ወአውጽአ ማየ እምዕብን"። መዝ 77፥15-16። የሚነበቡት መልዕክታት ኤፌ 2፥13-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 1፥10-13 እና የሐዋ ሥራ 7፥44-51። የሚነበበው ወንጌልን ዮሐ 4፥1-15። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለሐዋርያት_ሰኔ_ጾም_ሁለተኛ_ሳምንት #ስለ_ዕርገቱና_ስለ_ጰራቅሊጦስ ለሚነገርበት ዕለተ ሰንበት እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ሃሌ ሉያ በ፫ "#ዐረገ_እግዚአብሔር_በቃለ ቀርን #በይባቤ_ዐርገ ወበቃለ ቀርን ወነበረ በየማነ አቡሁ (ዐርገ) አዝ፣ #ዐርገ_በስብሐት_ውስተ_ሰማያት ተኰነኑ ሎቱ መላእክት (ዐርገ) አዝ፣ ተኰነኑ ሎቱ መላእክት ኵሉ ኃይል ወኵሉ ፍጥረት (ዐርገ) አዝ፣ ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ ለንጉሥነ። ትርጉም፦ እግዚአብሔር በመለከት #ድምፅ_ዐረገ በዕልልታና #በመለከት_ድምፅ ዐረገ፤ በአባቱ ቀኝ ተቀመጠ፤ በክብር በምስጋና በጌትነት #ወደ_ሰማያት_ዐረገ፤ መላእክት ተገዙለት ኃይል ሁሉ ፍጥረት ሁሉ ተገዙለት፤ ለአምላካችንም ዘምሩ፤ አመስግኑ ለንጉሣችን ዘምሩ አመስግኑ። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዚህ_ሳምንት_የዕለቱ_ምስባክ፦ "ልበ ንጹሐ ፍጥር ሊተ እግዚኦ። መንፈሰ ርቱዓ ሐድስ ውስተ ከርሥየ። ኢትግድፈኒ እምቅድመ ገጽከ"። መዝ 50፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 12፥1-12፣ 1ኛ ዮሐ 2፥20-ፍ.ም፣ የሐዋ ሥራ 2፥14-22። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 14፥22-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ። መልካም ዕለተ ሰንበትና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤              ❤ #ሰኔ ፯ (7) ቀን። ❤ እንኳን #አምላክን_ለወለደች_ለእመቤታችን #ለድንግል_ማርያም_ቤተ ክርስቲያን_ለተከፈተበትና ለከበረችበት፣ ቀሊን ከምትባል አገር ቅዱስና ቡሩክ ድል አድራጊም ለሆነ #ለአባ_አበስኪሮን_ሰማዕትነት ለተቀበሉበት #ለዕረፍታቸው_በዐል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚህ ቀን ከሚታሰቡ፦ መኰንን አርማንዮስ ካሠቃያቸው #ከአስራ_ስድስት_ሺህ_ሰማዕታት ከዕረፍታቸው መታሰቢያና ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                           ✝️ ✝️ ✝️ #በዚች_ዕለት_አምላክን_የወለደች_የእመቤታችን_የድንግል_ማርያም_ቤተ_ክርስቲያን_የተከፈተበትና_የከበረችበት ነው። እርሷም ዌላ በሚባል አደባባይ ያለች ሦስት ዓመት ከስድስት ወር ተዘግታ የኖረች ነበረች። ይኸውም በአንድ ሽህ ሃያ ዓመተ ሰማዕታት ነው። ከእመቤታችን ድንግል ማርያም ሰው ለሆነ ሕይወትና መድኃኒት አድርጎ እርሷን ለሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።                                                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #አባ_አበስኪሮስ፦ ይህም ቅዱስ ከእንዴናው ገዥ ከአርያኖስ ጭፍራ ውስጥ ነበር የከሀዲው ንጉሥ የዲዮቅልጥያኖስ ስለ አምልኮ ጣዖት የሆነች ትእዛዝ በደረሰችው ጊዜ። ወዲያውኑ ይህ በሕዝብ መካከል ተነሥቶ ንጉሡን ረገመው ጣዖታቱንም ሰደበ ወታደር ስለ ሆነም ያሠቃየው ዘንድ ማንም አልደፈረም ነገር ግን በንጉሥ አዳራሽ ውስጥ አሠሩት። ❤ መኰነንኑም ወደ አገረ አስዩጥ በሔደ ጊዜ ወደ ንጉሥ ላከው ከእርሱም ጋራ ሌሎች ወልደፍዮስ፣ አርማንዮስ፣ አርኪያስ፣ ጴጥሮስና ቀራንዮስ የተባሉ ነበሩ እሊህም ክብር ይግባውና ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደማቸውን ሊአፈሱ ከአባ አበስኪሮስ ጋር ተስማሙ። በንጉሡም ፊት በቆሙ ጊዜ በጌታችን ታመኑ ንጉሡም ትጥቃቸውን ይቆርጡ ዘንድ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይም እንዲአሠቃዩአቸው አዘዘ ንጉሡ እንዳዘዘም አደረጉባቸው። ከእኒህ ከአምስቱ ግን ራሶቻቸውን የቆረጡአቸው አሉ የሰቀሉአቸውም አሉ እንዲህም ገድላቸውን ፈጽመው የሕይወት አክሊል ተቀበሉ። ❤ የከበረ አበስኪሮስን ግን ታላቅ ግርፋትን እንዲገርፉት አዘዘ ከዚያም በኋላ ከራሱ እስከ አንገቱ ቆዳውን እንዲገፉ በፈረስ ጅራትም አሥረው በከተማው ውስጥ እንዲጐትቱት አዘዘ። ይህንም ሁሉ አደረጉበት። ከዚህም በኋላ በብረት ምጣድ ውስጥ አድርገው በላዩ አፉን ዘግተው ተሸክመው ወስደው በውሽባ ቤት ማንደጃ ውስጥ ጨመሩት በሥቃዩም ውስጥ ሁሉ የእግዚአብሔር መልአክ ወደርሱ ይመጣና ያጽናናው ነበር ያስታግሠውም ነበር ያለ ምንም ጉዳት አድኖ በደኅና ያስነሣው ነበር። ❤ ከማሠቃየቱም በደከመ ጊዜ ከሥራየኞች ሁሉ የሚበልጥ በሥራዩም ወደ አየር ወጥቶ ከአጋንንት ጋራ የሚነጋገር ሥራየኛ አመጣለት። እርሱም የውሽባ ቤቱን ዘግተው ሽንት እንዲረጩበት አዘዘ እንዲሁም አደረጉ። እባብንም ይዞ በላዩ አሾከሾከና ለሁለት ክፍልም ሁኖ ተሠነጠቀ መርዙንና ሆድ ዕቃውን ወስዶ በብረት ወጭት አድርጎ አበሰላቸው በውሽባ ቤቱ ውስጥ ወደ አባ አበስኪሮን አቅርቦ ያንን መርዝ ይበላ ዘንድ ሰጠው ቅዱሱም በላ ግን ምንም ምን ጉዳት አልደረሰበትም። ያም መሠርይ "የመኳንንተ ጽልመት አለቃቸው ሆይ በዚህ ክርስቲያናዊ ላይ ኃይልህን አድርግ" ብሎ ጮኸ ምንም ምን ጥፋት ባልደረሰበት ጊዜ መሠርዩ አደነቀ። ቅዱስ አበስኪሮንም መሠርዩን "የሚራዳህ ሰይጣንህስ በክብር ባለበት በጌታዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል አንተን ይቀጣሃል" አለው። ወዲያውኑ ጥሎ የሚያንከባልለው ክፉ ሰይጣን ተጫነበት ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እስከ ታመነ ድረስ አሠቃየው። መኰንኑም የመሠርዩን ራስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና በሰማዕትነት ሞተ። በቅዱስ አበስኪሮን ላይ ግን ቁጣና ብስጭትን በመጨመር ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃየው አባለ ዘሩንም እንዲቆርጡ አዘዘ እርሱ ግን በመከራው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግን ነበር። ከዚህም በኋላ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘና ሰኔ 7 ቀን ቆረጡት የድል አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ❤ ከቅዱስ አበስኪሮን ተአምራትም አንዱን እንነግራችኋለን በግብጽ ደቡብ በስሙ የታነፀች ቤተ ክርስቲያን ነበረች ካህናቷም ክፉ ሥራ የሚሠሩ ክፉዎች ነበሩ ቅዱስ አበስኪሮንም ከክፋታቸው ተመልሰው ንስሓ ቢገቡ ብሎ ጠበቃቸው። ባልተመለሱ ጊዜ ግን የንዳድ በሽታ አምጥቶ ሁሉም በአንዲት ጊዜ ሞተ። ❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ አበስኪሮን በፈረስ ተቀምጦ የላዕላይ ግብጽ የሆነች ብያሁ ወደምትባል አገር ደረሰ የአገር ሰዎችም በደጃቸው ተቀምጠው ሳይተኙ በጨረቃ ብርሃን እርስ በርሳቸው ያወሩ ነበር። የከበረ አበስኪሮንም ከፊታቸው ደርሶ "ሰላም ለእናንተ ይሁን" አላቸው በአዩትም ጊዜ የሰላምታውን አጸፋ እየመለሱ ተነሥተው ተቀበሉት ሁለተኛም "ያቺን የሚሻትን ምድር እያመለከታቸው ከምድራችሁ ጥቂት እንድትሰጡኝ እሻለሁ" አላቸው። እነርሱም "ጌታችን እንደወደድክ ይሁንልህ" አሉት መቶ የወርቅ ዲናርም ሰጥቷቸው ተሠወራቸው። እነርሱም ከዚህ ራእይ የተነሣ አደነቁ። ❤ ከተኙ በኋላም ቤተ ክርስቲያኒቱን አፍልሶ ከግብጽ ደቡብ ወደ ላይ ግብጽ ብያሁ ወደምትባል አገር በመቶ የወርቅ ዲናር ወደ ገዛት ምድር ከንዋየ ቅዱሳቷ ሁሉና ከዐፀዷ ጋር አምጥቶ በዚያ አቆማት። የአገር ሰዎችም በጥዋት ነቅተው ወደ ውጭ በወጡ ጊዜ ቤተ ክርስቲያቱን በደጃቸው አገኙዋት እጅግ ፈጽሞም አደነቁ ምስጉን እግዚአብሔርንም አመሰገኑት። ከዚያች ጊዜ ጀምሮ ድንቅ ተአምር የሚደረግባት ሆነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕቱ በአባ በአበስኪሮን ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 7 ስንክሳር።                        ✝️ ✝️ ✝️ ❤ "#ሰላም_ዕብል_ለርኅወተ_ቤትኪ_ዮም። ከመ ኤልያስ አርኀወ ኆኅተ ዝናም። በስሱ አውራኅ ወበሠላስ ዓም። ማርያም ሥመሪ አርኅዎቶ ለሕሊናየ ሕቱም። ከመ ላዕሌሁ ይትከዐው ምስለ ጽድቅ ሰላም"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የሰኔ 7።

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ሰኔ ፯ (7) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ለታላቁ አባት #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት_ከሾሟቸውና_በሀገራችን ለስብከተ ወንጌል ካሰማሯቸው #ከ47ቱ ቅዱሳን አንዱ ለሆኑት #ለአቡነ_ማቴዎስ_ዘእንደርታ_ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዐልና ለታላቁ አባት #ለጻድቁ_ለሐዋርያም ለደራሲም ለመላእክት በዐል የሚቀደሰው ከ14_ቅዳሴ አንዱ የሆነ በስሙ የተሰየመው ቅዳሴ ለደረሰ ለተከራካሪ መምህርም #ለያዕቆብ_ዘሥሩግ_ለዕረፍት_በዐል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #አቡነ_ማቴዎስ_ዘእንደርታ፦ እኚህ ጻድቅ ትውልድ አገራቸው እንደርታ ሲሆን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከሾሟቸውና በሀገራችን ለስብከተ ወንጌል ካሰማሯቸው ከ 47ቱ ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ናቸው። ጻድቁ መላ ሰውነታቸው እንደ እሳት ያቃጥል ነበር። ወንጌልን በመስበክና በተአምራታቸው ድውያንን እየፈወሱ ብዙ ያገለገሉ ታላቅ አባት ናቸው። መዝገበ ቅዱሳንና ቅዱሳን በዓላት ላይ።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #አቡነ_ያዕቆብ_ዘሥሩግ፦ አገሩ ሶርያ ሲሆን አባቱ ሊቀ ካህናት ነበር። በኤጲስ ቆጶስነት የተሾመባት አገር በጤግሮስና በኤፍራጥስ መካከል በምትገኝ ሥሩግ በምትባል አገር ስለሆነ ያዕቆብ ዘሥሩግ ተባለ። በ 3 ዓመቱ እናቱ ቤተ መቅደስ ስትወስደው መልአክ እጁን ይዞ በሊቀ ጳጳሱ እጅ እንዲቆርብ አድርጎታል። በዚህም ጊዜ ምሥጢራት ሁሉ ተገልጠውለታል። ገና በ 7 ዓመቱ ስለ ሦስት ነገሮች በእጅጉ ያለቅስ ነበር። "ነፍሴ ከሥጋዬ ተለይታ ስትወጣ ከጌታችን ጋር ስትገናኝና መጨረሻውን ፍርድ ስሰማ እነዚህን ሦስት ነገሮች በእጅጉ እፈራለሁ" እያለ ያለቅስ ነበር። ❤ በ 12 ዓመቱ ብሉይንና ሐዲስን አጠናቆ ተመምሮ ጨርሷል። ጸጋውን ዐውቀው 5 ቱ ታዋቂ ሊቃነ ጳጳሳት መጥተው እጅ ነስተውት አዲስ ድርሰት ድረስልን ቢሉት እርሱም በፍጹም ትሕትና "በእናንተ ፊት እንኳን አዲስ ድርሰት ልደርስ ቀርቶ የተደረሰውንም መናገር አልችልም"። አላቸው። እርሱ በነበረበት ዘመን በሮማው መናፍቅ ልዮን አማካኝነት ቤተ ክርስቲያን ለመጀመርያ ጊዜ ለሁለት የተከፈለችበት ጊዜ ነበርና እነ ዲዮስቆሮስ "የውሾች ጉባኤ" ከተባለው ከኬልቄዶን ጉባኤ ተለይተው ሃይማኖትን ሲያጸኑ ልዮንንም ማውገዛቸውን ያዕቆብ ሲሰማ በዲዮስቆሮስ ጽናት በእጅጉ ተደስቶ ደብዳቤ ጽፎ አመስግኖታል። እነ ልዮንን ግን አውግዞ እረግሟቸዋል። ልዮንም ተከታይ ባገኘ ብሎ "እኔን ምሰል" በማለት ለያዕቆብ ደብዳቤ ጻፈለት። ያዕቆብም "ሳጥናኤል ከመላእክት ጋር ምን አንድ አደረገው? አንተ ርኩስ ነህ፤ የዲዮስቆሮስን ጥርስ አስወልቀህ፣ ጢሞን አስነጭተህ፣ ሃይማኖትህን የቀየርህ ከሁለት ዓለም ስደተኛ ጋር አልተባበርም፣ ይልቅስ ንስሓ ግባ፣ ንስሓ ባትገባ ግን አንተ ዲያብሎስ ነህ ተከታዮችህም አጋንንት ናቸው። በማለት መልሱን ጽፎለታል። እምቢ ብሎ በክህደቱ ቢጸናበትም አውግዞ እረግሞ ንጽሕናውን ቅድስናው እንደ መላእክት ነው የተባለለት ያዕቆብ ዘሥሩግ ጻድቅም ሐዋርያም ደራሲም ተከራካሪ መምህርም ነው። ሦስት ድርሰቶች ያሉት ሲሆን በስሙ የተጠራው ቅዳሴም አለው። ዕረፍቱ ሰኔ 7 ቀን ነው። ከአባታችን ከአቡነ ያዕቆብ ዘሥሩግ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎቱም ይማረን። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤              ❤ #ሰኔ ፮ (6) ቀን። ❤ እንኳን #ከእስክንድርያ_ከተማ_ለሆነ_ለመነኰስ #ሰኔ #ለአባ_ቴዎድሮስ_ሰማዕትነት_ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና #ለቅዱሳን_ለአውሳብዮስ፣ #ታማን፣ #ሐርዋግና_ለባኮስ ለተባሉ #ለአገረ_እስና_ለአራት መኳንንት ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ ከአገረ መርዩጥ #ከአርባ_ሰማዕታትና_ከሌሎች_አርባ_ሰማዕታት #ከመነኰስ_ገብረ_ክርስቶስም_ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                            ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #መነኰስ_አባ_ቴዎድሮስ፦ ይህም የታመነና ንጹሕ ቅዱስ ተጋዳይ በእስክንድርያ ከሚገኙ ገዳማት በአንዱ በመልካም ገድል ተጠምዶ ኖረ። ታናሹ አርዮሳዊ ቈስጠንጢኖስ በነገሠ ጊዜ አርዮሳዊ ጊዮርጊስ በእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት አድርጎ ሾመው። ሐዋርያዊ ቅዱስ አትናቴዎስንም ከመንበሩ አሳደደው ይህ አርዮሳዊ ጊዮርጊስም በቅዱስ ማርቆስ ወንበር ላይ ሲቀመጥ ያን ጊዜ በአርዮሳውያንና በእስክንድርያ ምዕመናን መካከል ታላቅ መተላለቅ ሆነ ሃይማኖታቸው የቀና ብዙዎች ምዕመናንም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተገደለ። ❤ ከዚህም በኋላም ይህ አርዮሳዊ ጊዮርጊስ ስለ አባ ቴዎድሮስ እርሱ አርዮሳውያንን ተከራክሮ እንደሚአሸንፋቸው ከቅዱሳት መጻሕፍትም ማስረጃ በማምጣትና በማስፈረድ ያሳፍራቸው ነበር ያን ጊዜ ይህን መነኰስ አባ ቴዎድሮስን ይዘው በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ እንዲአሠቃዩት አዘዘ እንዲሁም አደረጉበት ግን ምንም ምን ጉዳት አልደረሰበትም። ❤ ከዚህ በኋላም ኃይለኞች ሩዋጮች በሆኑ ፈረሶች ላይ እግሮቹንና እጆቹን አሥረው በሰፊ ሜዳ ውስጥ እንዲአስሮጡአቸው አዘዘ ይህንንም በአደረጉ ጊዜ ሕዋሳቱ ሁሉ ተባጣጠሱ ራሱንም ተቆረጠች እንደ ዚህም ሁኖ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ። ሦስት አክላትንም ተቀዳጀ አንዱ ድንግልናውን ጠብቆ ስለ መመንኰሰ ሁሉተኛው ሃይማኖትን ስለ ማስተማሩና ተከራክሮ መናፍቃንን ስለመመለሱ ሦስትኛውም ስለ ቀናች ሃይማኖት ደሙን በማፍሰሱ ነው። ❤ ከዚህም በኋላ ምዕመናን የተቆረጡና የተበተኑ ሕዋሳቱን ሰብስበው በሣጥን ውስጥ አድረጓቸው በዚች ዕለትም ሰኔ 6 ቀን መታሰቢያ በዓሉን አደረጉ እንደ ሌሎቹ ቅዱሳን ሁሉ የምስጋና ድርሰትን በሮማይስጥ ቋንቋ ደረሱለት በጸሎት መጽሐፋቸውም ውስጥ ጻፉት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ቴዎድሮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የአገረ_እስና_አራቱ_መኳንንት፦ እሊህም ቅዱሳን ለእስና ምሰሶዎቿ ነበሩ ጸሐፊዎቿም ነበሩ ለብዙዎች ድኆችና ምስኪኖች ይመጸውቱ ነበር። ወደዚያች አገርም መኰንኑ አርያኖስ ዳግመኛ በተመለሰ ጊዜ እኛ ክርስቲያን ነን ክብር ይግባውና ሰማይና ምድር በጸኑበት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለን" በማለት በግልጥ በፊቱ እየጮኹ ተቀበሉት። ❤ አርያኖስም ሰምቶ በየራሱ በሆነ ሥቃይ አሠቃያቸው ከዚህም በኋላ ራሶቻቸውን በሰይፍ ቆረጠ የምስክርነታቸው አክሊል ሰኔ6 ቀን ተቀበሉ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ6 ስንክሳር።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ "#ሰላም_ለከቴዎድሮስ_መነኰስ። እሡረ አእጋር ወአእዳው በእግረ ፈረስ። እምኃይለ ሩጸቱ ፍሉሕ አምሳለ ነፋስ። እምአባልከ ተመቲራ ለእንተ ሠረረት ርእስ። እግዚአብሔር አስተቀጸላ በአክሊል ሠላስ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሰኔ_6።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ዘረወ ወወሀበ ለነዳይ። ወጽድቁኒ ይነብር ለዓለም። ወይትሌዓል ቀርኑ በክብር"። መዝ 111፥9-10። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 9፥13-ፍ.ም፣ ያዕ 1፥12-19 እና የሐዋ ሥራ 5፥26-32። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 12፥32-41። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ወይም የ­ቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም በዐልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ ከዚህም በኋላ አንጾኪያ ከተማ አደረሱበት ወደ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም አቀረቡት እርሱም በእሳት በአፈሉት በወይን በሙጫ ድፍድፍ በማቃጠል አሠቃየው ከዚያም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል አዳነው። ዳግመኛም በአንገቱ ከባድ ደንጊያ በሰንሰለት አሥረው ወደ ባሕርም አንከባለው ግማሽ ሥጋውን እንዲአሠጥሙ ግማሹን ግን እንዳያሠጥሙ አዘዘ እነርሱም በባሕሩ ዳር ታላቅ ምሰሶ ተከሉ በዚያም እንዳዘዛቸው አድርገው አሥረው ተዉት በዚህ ሥቃይም ከቀኑ እስከ ሰባት ሰዓት ዋለ ያን ጊዜም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ፈትቶ አወጣው እንደ ቀድሞውም ጤነኛ አደረገው ንጉሡም አይቶ አደነቀ ሰያፊውንም ፈጥኖ አንገቱን ሰኔ 5 ቀን ቆርጦ በባሕር ዳር ከምድር ላይ ጣለው ሥጋውንም አንሥቶ ከቊርበት በተሠራ ጋን ውስጥ ጨምረው ሥጋውም ከራሱ ጋራ ተገናኘና እንዳልተቆረጠ ሆነ ጋኑም በሃያ ቀን እስክንድርያ እስከሚደርስ ድረስ ሰው ሳይሸከመው ብቻውን የሚጓዝ ሆነ። ❤ የቦሀ አገር ሰዎችም በሰሙ ጊዜ መጡ ተሸክመውም በቦሀ አገር ከአለው ቤቱ ውስጥ አስገብተው ከወንድሙ አባ ጴጥሮስ ጋራ ቀበሩት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን አባ ብሶይና በአባ ጴጥሮስ በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ቅዱስ_ቢፋሞን፦ ይህ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ የእናቱ ወንድም ልጅ ነበር ዮሐንስም ታሥሮ ሳለ ያገለግለው ነበር። ዮሐንስም ገድሉን በፈጸመ ጊዜ ሥጋውን ገነዘ በበድኑ ላይም እንዲህ ብሎ አለቀሰ "ከእግዚአብሔር የተለየሁ ሁኜ ብቻዬን እንዴት ትተወኛለህ" ከቅዱስ ዮሐንስ ሥጋም እንዲህ የሚል ቃል ወጣ ወዳጄ ቢፋሞን ከእኔ ጋራ መኖርን ከፈለግህ ፈጥነህ ወደ መኰንኑ ሔደህ ክብር ይግባውና በክርስቶስ ታመን ነገም ወደ እኔ ትመጣለህ"። ይህንንም ሰምቶ የዮሐንስን ሥጋውን ቀበረ። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ መኰንኑ ሔደ። ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እየታመነ የረከሱ ጣዖታቱን ሰደበ። መኰንኑም ጽኑዕ ሥቃይ አሠቃየው ከዚህም በኋላ ራሱን ሰኔ 5 ቀን በሰይፍ ቆረጠ የምስክርነቱንም አክሊል ተቀበለ። በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                            ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #መነኰሳዪት_ቅድስት_ማርታ፦ ይቺም ቅድስት ሃይማኖቷ የጸና ምግባርዋም የቀና ክርስቶስ ያደረባት ናት። በስደትም ዐረፈችና በተራራ ውስጥ ተቀበረች የመነኰሳዪት የቅድስት ማርታ በረከቷ ከእኛ ጋር ይሁን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 5 ስንክሳር።                                                      ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ይትነሥእ እግዚአብሔር ወይዘረዉ ፀሩ። ወይጒየዩ ጸላእቱ እምቅድመ ገጹ። ከመ የኀልቅ ጢስ ከማሁ የኀልቁ"። መዝ 67፥1-2። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 2፥12-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 3፥1-11 እ የሚነበበው የሐዋ ሥራ 16፥35-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 12፥8-13። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወይም የቅዱስ ባስልዮስ   ቅዳሴ ነው። መልካም የጰራቅሊጦስ በዓል ሰሞንና የጾም ጊዜ ይሁንልን። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ሰኔ ፭ (5) ቀን። ❤ እንኳን ለታማኛና ተጋዳይ ለሆነ ለምሥራቃዊው አባት #ለቅዱስ_ያዕቆብ ፣ ለተመረጠ ኃያል ተጋዳይ #ለአባ_ብሶይ_ለዕረፍታቸው_በዓል፣ ለቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅል ለአጎት ልጅ #ለቅዱስ_ቢፋሞን ምስክር ለሆነበትና ሃይማኖቷ ለጸና ምግባርዋም ለቀና ክርስቶስ ላደረባት #ለመነኰሳዪት_ለቅድስት_ማርታ_ለዕረፍቷ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ #ከቅዱሳን_ከመርቆሬዎስና #ከመቃርስ፣ #ከይስሐቅና_ከዕብሎን_ከዕረፍታቸው መታሰቢያ፣ #ከአብላርዮስም ከምስክርነቱ መታሰቢያና በጌታችን ስም በባሕር ውስጥ በመስጠም ከዐረፈ #ከቅዱስ_መቃርስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ምሥራቃዊው_አባት ቅዱስ_ያዕቆብ፦ ይህም ቅዱስ ከምዕመን ዋልንጦስ ዘመን በኋላ የታላቁ ቈስጠንጢኖስ ልጅ በሆነ በታናሹ ቈስጠንጢኖስ ዘመንና በከሀዲው ሉልያኖስ ዘመን በምሥራቅ ካሉ ገዳማት በአንዱ ገዳም በገድል ተጠምዶ ኖረ። ዋልንጦስ ከተገደለ በኋላም በእርሱ ፈንታ ወንድሙ ነገሠ እርሱም አርዮሳዊ ነበር የጣዖት ቤቶቻቸውን እንዲከፍቱ ሃይማኖታቸው የቀናውን የምዕመናንን አብያተ ክርስቲያናትንም እንዲዘጉ አርዮሳውያንን አዘዛቸው ምዕመናን በግዳጅ እስቲገቡ ድረስ እንዲሁ አደረጉ። ይህም የንጉሡ ትእዛዝ በሚገዛው አገር ሁሉ ደረሰ። ❤ ይህም አባ ያዕቆብም ይሁን በሰማ ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ፍቅር እሳትነት ልቡ ነደደ ያንጊዜም ተነሥቶ ወደ ቊስጥንጥንያ ሔደ በምዕራብ በኩል የተነሡበትን ጠላቶቹን ሒዶ ለመውጋት ሲወጣ ንጉሡን አገኘው። ይህ አባት ያዕቆብም በፊቱ ቆሞ "ንጉሥ ሆይ በጠላቶችህ ላይ እግዚአብሔር ይረዳህ ዘንድ ምዕመናን እንዲጸልዩልህ አብያተ ክርስቲያናቸውን ክፈትላቸው ብዬ እለምንሃለሁ ይህን ካላደረግህ ግን እግዚአብሔር ይጥልሃል ከጠላቶችህም ሸሽተህ በእሳት ቃጠሎ ትሞታለህ" አለው። ንጉሡም ይዞ ለሚጠብቀው ወታደር "በሰላምና በደኅንነት እስከምመለስ ጠብቀው" ብሎ ሰጠው። ቅዱስ ያዕቆብም "አንተ በደኅና ከተመለስክ በእኔ አንደበት እግዚአብሔር አልተናገረም ማለት ነዋ" አለው። ❤ ያንጊዜም ቅዱሱን ይዘው ደብድበው አሠሩት ንጉሡም ከሠራዊቱ ጋራ ወደ ጦርነቱ ሔደ በረከሰች ጸሎታቸው አርዮሳውያን ምንም ቢራዱት ክብር ይግባውና ጌታችን በጠላቶቹ አንጻር ጣለው እነርሱም ጠላቶቹ እየተከተሉት ሸሽቶ ከአንዲት ዐፀድ ውስጥ ገባ በዚያም በረከሰች ሃይማኖቱ ከሚያምን ወገኖቹ ጋር በእሳት አቃጠሉት። የቀሩትም ሠራዊት ሁሉ ሸሽተው ወደ ቊስጥንጥንያ ተመለሱ ይህንንም መልካም ዜና ሃይማኖታቸው ለቀና ምዕመናን ተናገሩ የዚህም ጻድቅ አባት ያዕቆብም ትንቢቱ ተፈጸመ ከእሥር ቤትም በክብር አወጡት። ምዕመናንም ከሀድያንም በላዩ መንፈስ ቅዱስ እንዳደረበት ተረዱ ከአርዮሳውያንም ብዙዎቹ የአባቶቻችን ሐዋርያት ወደሆነች ቅን ሃይማኖት ተመለሱ በዚህ አባት እግር በታች ሰግደው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ በመለኮቱ ትክክል እንደሆነ ታመነ። ❤ ከዚህም በኋላ ይህ አባት ወደ ቦታው ተመለሰ አርፎ የሕይወትና የሰማዕትነት አክሊልን እስከ ተቀበለ ድረስ እንደ ቀድሞው በገድል ተጠምዶ ኖረ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ በቅዱስ ያዕቆብ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #አባ_ብሶይ፦ የዚህ ቅዱስ አባቶቹ ክብር ይግባውና ጌታ ክርስቶስን የሚያመልኩና ትዕዛዙን የሚጠብቁ ክርስቲያን ነበሩ የአባቱም ስም ታግኅስጦስ ነው እርሱም ከአንጾኪያ የቃው ገዥ ነበር የእናቱም ስም ክሪስ ይባላል። እነርሱም ልጅ ሳይኖራቸው ዐሥራ ሰባት ዓመት ኖሩ ስለዚህም እጅግ እያዘኑ ክብር ይግባውና ወደ ጌታችን ይለምኑ ነበር። ከሌሊቶችም በአንዲቱ ለታግኅስጦስ ብርሃን የለበሰ ሰው ተገልጦለት እንዲህ አለው "የእግዚአብሔር ወዳጅ ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን እነሆ ጸሎትህ በእግዚአብሔር ዘንድ ተሰምቷል ሚስትህም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች ስሙንም ብሶይ ትለዋለህ እርሱም ለእግዚአብሔር የተመረጠ ዕቃ ይሆናል እርሱም ደግሞ ክብር ይግባውና ለክርስቶስ ምስክ ይሆናልና ሥቃይና መከራም ተቀብሎ የሰማዕትነት አክሊልን ይቀዳጃል"። ከእንቅልፉ ነቅቶ ራእይ እንዳየ ለሚስቱ ነገራት። ከጥቂት ቀኖች በኋላም ፀንሳ ይህን ቅዱስ ሚያዝያ አንድ ቀን ወለደችው ዕውቀትን ጥበብንና ፈሪሀ እግዚአብሔርን በማስተማር አሳደጉት። ❤ ሰባት ዓመትም በሆነው ጊዜ ወደ አክሚም ዮሴፍ ወደሚባል አንድ አረጋዊ መምህር ላኩት በዚያም እየተማረ ከወንድሙ ጴጥሮስ ጋር በጸሎትና በጾም ተጠምዶ ድንቆች ተአምራትን እያደረገ ኖረ። ከዚያም በኋላ ሃያ ሰባት ዓመት በሆነው ጊዜ የስዒድ መኰንን ወዳለበት ወደ ቃው ከተማ መጣ እርሱም ክርስቲያኖችን እያሳደደ ከእርሳቸው ይገድል ነበር። ያን ጊዜም ክፉዎች ሰዎች ወደ መኰንኑ መጥተው "ለቃልህ የማይታዘዙና ለአማልክት መስገድንም እምቢ የሚሉ ሁለት ዲያቆናት አሉ" ብለው እኒህ የከበሩ አባ ብሶይንና አባ ጼጥሮስን ከሰሱአቸው። በዚያም ጊዜም እንዲአቀርቧቸው አዘዘና አቅርበው በፊቱ አቆሙአቸው ስለ ሥራቸውም መረመራቸው ክርስቲያን እንደ ሆኑም ከቃላቸው ሰምቶ እንዲአሥሩአቸው አዘዘ። ❤ ከሦስት ወር በኋላም የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦላቸው "እኔ የምሥራች የምናገር ገብርኤል ረዳችሁና እነግራችሁ ዘንድ ወደእናንተ እግዚአብሔር ላከኝ ስም አጠራራችሁና መታሰቢያችሁ ለዘላለሙ ይኖር ዘንድ አለውና" አላቸው። "አንተም ወዳጄ ብሶይ ታላቅ ተጋድሎ አንተን ይጠብቅሃል ወደ እስክንድርያ ከተማ ሊሰዱህ አላቸው። ከዚያም ወደ አንጾኪያ ወስደውህ በዚያ የምስክርነትህ ገድል ይፈጸማል"። ❤ ከዚህ በኋላም መኰንኑ ከወህኒ ቤት አውጥቶ ለጣዖት እንዲሰግድ አስገደደው እምቢ ባለውም ጊዜ ከባላ ላይ አውጥተው በግንድ ውስጥ እጅግ እንዲጨምቁት ወታደሮቹን አዘዘ። በዚያን ጊዜም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ወሪዶ ግንዱን ሰብሮ ቅዱስ ብሶይን በመዳሠሥ አዳነው። ከዚያም ወደ ወህኒ ቤት ጨምሩት በዚያም ብዙ በሽቶኞችን ፈወሳቸው። ዳግመኛም እንዲህ አዘዘ ከወህኒ ቤት አውጥተው በመርከብ ሆድ ውስጥ አስገብተው አንገቱን በብረት ማሠሪያ እንዲአሥሩት እንጀራና ውኃ እንዳይሰጡት አዘዘ እንደዚህም ኖረ ዐሥር ቀን ኖረ። ❤ ከዚህም በኋላ አውጥተው በፊቱ አቁሞ "ለአማልክቶቼ ስገድ" አለው እምቢ ባለውም ጊዜ ደሙ እንደ ውኃ እስቲፈስ ከባላ ግንድ ላይ አውጥተው አጥብቀው እንዲጨምቁት ሁለተኛ አዘዘ። እንዲሁም በእርሱ ላይ አድርገው በወህኒ ቤት አሠሩት። የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ደግሞ ተገለጠለትና "አይዞህ መልካም ገድልህን እስከምትፈጽም እኔ ከአንተ ጋራ እኖራለሁና አትፍራ" አለው። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ እስክንድርያ ወደ ቁልቁልያኖስ መኰንን ሰደዱት እርሱም ስለ ሥራው ሁሉ መረመረውና ሕዋሳቱ ተቆራርጦ እስቲወድቅ ድረስ ይደበድቡት ዘንድ አዘዘ። ሁለተኛም ዘይትን አፍልተው በጆሮው፣ በአፉና በደረቱ ላይ እንዲአፈስሱ ጐኖቹንም በእሳት ሠብራት እንዲአቃጥሉ አዘዘ ደግሞም በእሳት የጋሉ የብረት ችንካሮችን አምጥተው በዐይኖቹ ውስጥ አደረጓቸው። ሁለተኛም የእጆቹንና የእግሮቹን ሥሮች ሕዋሳቱንም ሁሉ እንዲነቅሉ አዘዘ ይህንንም ሁሉ አደረጉበት በዚያን ጊዜም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ሕዋሳቱን ሁሉ ፈወሰው።

ክብር ይግባውና ክርስቶስ የምታመልክ ክርስቲያን እንደሆነች በፊቱ ታመነች። ❤ ዲዮቅልጥያኖስም የክብር ባለቤት የሆነ የክርስቶስ ስም በሰማ ጊዜ ቁጣን ተሞላ ወደ እርሱም እንዲያቀርቧት አዘዘ በቀረበችም ጊዜ "ለአጵሎን ስገጂ አላት "የሰው እጅ ለሰራው ለረከሱ አጋንትም ማደርያ ለሆነው እንዴት እሰግዳለሁ" አለችው ይህንንም ከእርሷ በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ ከብረት በተሰራ ጅራፍም እንዲገርፏት አዘዘ ሁለተኛም አንገቷን ከባድ ደንጊያ አስረው ሥጋዋ ተቆራርጦ እስኪወድቅ ድረስ በከተማው ጥጋጥግ እዲጎትቷት አዘዘ ይህን አድርገው ወደ ወሂኒ ቤት አስገቧት። በማግስቱም ያመጧት ዘንድ አዘዘ በመጣችም ጊዜ "በክፉ አሟሟት እንዳትሞቺ ለአጰሎን ሰዊ" አላት እርሷም "ክፉ ሞትስ ለአንተ ነው የእኔስ ከአንተ የሚገኘው ሞት በፈጣሪዬ ዘንድ ይሕወት ነው" አለችው። እርሱም "ከገደልኩሽ በኋላ ትነሽ ትነሻለሽን?" አላት "አንተ ሰነፍ የእኔን ተዋውና ለአንተም የደይን ትንሣኤ አለህ" አለችው። ይህንንም በሰማ ጊዜ አጥንቶቷ ሁሉም እስኪሰበሩ በብረት በትሮች እዲደበድቧት አዘዘ ይህን ሁሉ አደረጉባት። ❤ ዳግመኛም በብረት አልጋ አስተኝተው ከበታቿ እሳት እንዲያነዱ አዘዘ ቀኑ በመሸም ጊዜ ወደ ወህኒ ቤት እንዲያስገቧት አዘዘ። በዚያችም ሌሊት የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ገላዋን በመዳሰስ አጽናናት። በማግሥቱም ያመጧት ዘንድ አዘዘ እርሷም ምን ሕማም እንዳላገኛት ሁና በእግራ መጣች ከመታጠቢያ ቤት ታጥባና ተቀብታ የመጣች ትመስል ነበር ንጉሡም ደኅንነቷን አይቶ አደነቀ፣ "የዚችን ክርሰቲያን ሴት የሥራይዋን ጽናት እዩ ትናንት በእሳት አሰቃይተናት ነበር ዛሬ ድናለች" አለ "ሥራይንስ አላውቀውቅም ነገር ግን ፈጣሪዬ ሥራይ የሚሽር ነው" አለችው። ❤ ከዚያም በኋላ እሺ ያሰኛት ዘንድ ሊሸነግላት ጀመረ እንቢ ባለችውም ጊዜ እራሷን በሰይፍ ሊቆርጡ ዘንድ አዘዘ። ሊቆርጧት ይዘዋት ሲሆዱ ክብር ይግባውና ጌታችን ተገለፀላት ብዙ ቃል ኪዳኖችንም ሰጣት በማይታበል ቃሉም "መታሰቢያሽን የሚያደርገውን፣ ሁሉ በስምሽ የሚመጸውተውን፣ የገድልሽንም መጻሕፍ የሚጽፈው ሁሉ እቀበለዋለሁ መንግሥተ ሰማያትን አወርሰዋለሁ" አለ። ከዚያም በኋላ አንገቷን በሰይፍ ቆረጡ በጌታችንም ዘንድ የድል አክሊልን ተቀበለች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛን በቅድስት ሶፍያ በጸሎቷ ይማረን በረከታም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ቅዱስ_ሳኑሲ፦ ይኽም ቅዱስ በልጅነቱ የአባቱን በጎች ሲጠብቅ ምሳውን ለጦም አዳሪዎች እየሰጠ እርሱ ግን እስከ ማታ ድረስ ይጾም ነበር፡፡ በአንዲት ሌሊት የታዘዘ መልአክ ተገልጦለት "የክብርን አክሊል ትቀበል ዘንድ ወደ መኰንኑ ሄደህ ስለ ፈጣሪህ ስለ ክርስቶስ መስክር" አለው፡፡ ቅዱስ ሳኑሲም ትእዛዙን በመቀበል እናቱን ተሰናብቶ ማርያ ከምትባል ደገኛ ሴት ጋር በሰማዕትነት ይሞቱ ዘንድ ወደ ከሃዲው ገዥ ወደ አርሳኖስ ዘንድ ሄዱ፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ በከሃዲው ገዥ ፊት ቀርበው ክርስቲያን መሆናቸውን ተናገሩ፡፡ ገዥውም ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን አደረሰባቸው፡፡ ቅድስት ማርያ በስቃይ ውስጥ ሳለች ዐርፋ ሰማዕትነቷን ስትፈጽም ቅዱስ ሳኑሲ ግን በጌታችን ኃይል ታደሰ፡፡ መኰንኑም ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ ወደ እንዴናው ገዥ በግዞት ላከው፡፡ በዚያም እጅግ አድርገው አሠቃዩት፡፡ ተረከዙን ሰንጥቀው ገመድ አግብተው በከተማው ውስጥ ሲጎትቱት ዋሉ፡፡ ሥራየኛ ሰው አምጥተው ሥራየኛው ሰው በጽዋ የተመላ መርዝ እንዲጠጣ ቢሰጠው ቅዱስ ሳኑሲ በመስቀል ምልክት አማትቦ ቢጠጣው ምንም አልሆነም፡፡ እንዲያውም ምግብ ሆነው፡፡ ይህንን ታላቅ ተአምር ያየው ሥራየኛም "በቅዱስ ሳኑሲ አምላክ አምኛለሁ" ብሎ በመመስከር እርሱም ሰማዕት ሆነ፡፡ መኰንኑም ቅዱስ ሳኑሲን ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ አንገቱን እንዲቆርጡት አዘዘና ሰኔ 4 ቀን የከበረች ራሱን በሰይፍ ቆርጠውት ሰማዕትነቱን በክብር ፈጽሞ የክብር አክሊልን ተቀዳጀ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን። በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 4 ስንክሳር።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ "#አቄርብ_ለከ_አሞኒ_ሰላም። #ወሶፍያ_ምስሌከ ዘተሳተፈት ሕማመ። #በእንተ_ኢየሱስ_ክርስቶስ ሥመሩ ፍጹመ። ከዊነክሙ ትሕፅኑ ኪያየ ደክታመ። ለሊከ አበ ወይእቲ እመ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሰኔ_4።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ቀስቶኒ ወተረ ወአስተዳለወ። ወአስተዳለወ ቦቱ ሕምዘ ዘይቀትል። ወአሕፃሁኒ እለ ይነዱ ገብረ"። መዝ 7፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 3፥9-18፣ 1ኛ ዮሐ 2፥12-20 እና የሐዋ ሥራ 12፥18_ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 21፥12-29። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ወይም የ­ቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤                ❤ #ሰኔ ፬ (4) ቀን። ❤ እንኳን #ለቅዱስ_ዮሐንስ_ዘሐራቅሊ_ለዕረፍቱ በዓል፣ በኪም ከሚባል አገር ለሆነ #ለቅዱስ_ሳኑሲ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል፣ በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመን አንገቷን በመቆረጥ ሰማዕትነት ለተቀበለች ተጋድይ ለሆነች #ለቅድስት_ሶፍያ ለዕረፍቷ በዓል በሰላም አደረሰን። በጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱሳን_ከአርቃድዮስ፣ ከእህቱ #የዲሙናስና ከግብጻውያን ከንጉሥ ከዲዮቅልጥያኖስ ጭፍሮችም ከገድላቸው ፍጻሜ፣ #ከአባ_አሞንና ከሚናስ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘሐራቅሊ፦ የዚህም ቅዱስ አባት ስሙ ዘካርያስ ነው እርሱም የጳንጦስና የአብልያ አገሮች ገዢ ነበር የእናቱም ስም ኤልሳቤጥ ነው እነርሱም ይህን የተባረኩ ልጅ በተሰጡ ጊዜ ስሙን ዮሐንስ ብለው ጠሩት እርሱ ከአባቱና ከእናቱ ጀምሮ ከመጥምቀ አምላክ ዮሐንስ ጋር በስም አንድ ሁኗልና በተግሣጽና በፈሪሀ እግዚአብሔር አሳደጉት የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍትን ሂሣቦችንና ጥበቦችን ሁሉ አስተማሩት እናቱም በዘመኗ ሁሉ ከእግዚአብሔር መንገድ እንዳይወጣ ታማጽነው ነበር። አባቱም እንዲሁ ይመክረውና ያስተምረው ነበር። ❤ ከዚህም አባቱ ከሞተ በኋላ የሃያ ዓመት ልጅ ሲሆን መስፍን ሆነ የጳንጦስና የሐራቅሊ ሌሎችም አገሮች ሁሉ ተገዙለት። እንዲሁም እያለ በመልአክ አምሳል ሰይጣን ታየው እንዲህም አለው "አንተ ትነግሥ ዘንድ ወደ አንጾኪያ ሒደህ የንጉሥ ኑማርያኖስን ልጅ አግባ ብሎ ጌታ አዝዞሃል" አለው ቅዱሱም "በውኑ ይህ መልአክ ነውን ግን አፉ የእግዚአብሔርን ስም ከሰማሁ አንጾኪያ እሔዳለሁ" አለ። ❤ ከዚህ በኋላም ወደ አንጾኪያ ከተማ ሔደ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስንም ተገናኘው ንጉሡም በአየው ጊዜ አከበረው እጅግም ወደደው። በማግሥቱም በምሳ ላይ ከእርሱ ጋራ እያለ ከሃዲ ዲዮቅልጥያኖስ አጰሎንን ያመጡት ዘንድ አዘዘ ያንንም ጣዖት ባመጡት ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ አይቶ አቃለለው ስለዚህም ሥራ ንጉሡን ረገመው ሰደበውም። ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም ቅዱስ ዮሐንስ ያደረገውን በአየ ጊዜ እጅግ ተቆጥቶ በእሥር ቤት አሠረው። በእሥር ቤትም ሳለ ክብር ይግባውና ጌታችን በብርሃን ሠረገላ ላይ ሁኖ ታየው ከእርሱ ጋራም መላእክት አሉ። ይዞም ሳመው ብዙዎች ቃል ኪዳኖችንም ሰጠው። ❤ በማግሥቱም ንጉሡ ልኮ ከእር ቤት አወጣው ወደ ርሱም አቀረበውና "ለአጰሎንና ለአርዳሚስ ስገድ" አለው ቅዱሱም "የሰው እጅ ለሠራው እንዴት እሰግዳለሁ" አለ ንጉሡ ግን ከእርሱ ጋራ መታረቅ ሽቶ ብዙ የሽንገላ ነገርን ተናገረው። ከዚህም በኋላ ግብርን ያስገብር ዘንድ ከሹመት ጋራ ወደ ግብጽ አገር ላከው ወደ ግብጽ ገዢ ወደ ስርያቆስም ስለ ርሱ እንዲህ ሲል ጽፎ ላከ "እንሆ ለዮሐንስ ዘሐራቅሊ ግብር በማስገበር የአማልክትንም ቤቶች አፍርሶ አዲስ እንዲአሠራ ከግብጽና ከኢየሩሳሌም እስከ ኢትዮጵያ ድረስ ሥልጣን ሰጥቼለሁ። ቅዱሱም ይህን ምክንያት ይዞ የጣዖታትን ቤቶች አፍርሶ ተዋቸው። ❤ በዚያም ወራት መኰንኑ ስርያቆስ የሰማዕታት ራስ መቆረጥን ሊያዝዝ በፍርድ አደባባይ ተቀምጦ በዚያን ጊዜ ከስዒድ፣ ዲዮስቆሮስ፣ ቢፋሞን፣ አሕራጋኖስ፣ ኪሮስ፣ ዮልዮስ እለእስክድሮስ፣ ዮሴፍ፣ ይስሐቅና እስጢፋኖስ የሚሉአቸው ሰዎች መጥተው እሊህ ሁሉም እኛ ክርስቲያኖች ነን እያሉ በግልጥ ጮኹ ያን ጊዜ መኰንኑ ይዞ ያለርኅራኄ ያሠቃያቸው ጀመር። ቅዱስ ዮሐንስ ይህን በአየ ጊዜ የሹመቱን ሥራ ትቶ "እኔ ክርስቲያን ነኝ" ብሎ በግልጥ ጮኸ መኰንኑም ተቆጥቶ በእግር ብረት እንዲአሥሩትና ወደ እንዴና አገር ወደ መኰንኑ አርያኖስ እንዲወስዱት አዘዘ እርሱም ስለሆነው ሁሉ መረመረው ከቃሉ መልስም የተነሣ ተቆጣ በባላ እንጨት ላይ ሰቅለው በመንኰራኵር አጣበቀው እንዲጨምቁት ከዚያም ከባላው አውርደው ሥጋው እስኪቀልጥ ሆዱ ላይና ራሱ ላይ በቀጭኔ እንዲደበድቡት አዘዘ ምድሪቱም በደሙ ተመላች ከዚያም ወደ እሥር ቤት አስገቡት። ❤ ከጥቂት ቀኖች በኋላም በማረጃ ቢላዋ ቆዳውን ገፈው ቁስሉን በማቅ ያሹት ዘንድ ዳግመኛም አመድ ጐዝጊዘው በላዩ የእሳት ፍም ከጐኑ በታች አድርገው በላዩ እንዲአስተኙት አዘወ እንዲሁም አደረጉበት። ሁለተኛም በእሳት የጋሉ የብረት ችንካሮችን አምጥተው በፊቱ ላይ በጀሮዎቹም ላይ እንዲያኖሩዋቸው አዘዘ። እንዲህም አድርገው ከወህኒ ቤት ጨመሩት። በዚያችም ሌሊት የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጾለት ሰላምታ ሰጥቶ አጸናው። በማግሥቱም ከወህኒ ቤት አውጥተው በጋሉ ብረት ዘንጎች ደበደቡት። ከዚህም በኋላ በግንባሩን ወደ ምድር ደፍተው እጆቹንና እግሮቹን ከፈረስ ጭራ ላይ በገመድ አሠሩ። ❤ ከዚህም በኋላም ባለ ሰይፍ መጥቶ እግርቹንና እጆቹን ራሱንም ቆረጠ እንዲህም የምስክርነቱን ተጋድሎ ሰኔ 3 ቀን ፈጽሞ የድል አክሊል ተቀበለ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ቅድስት_ሶፍያ፦ የዚች ቅድስት ወላጆቿ ክርስቲያን ነበሩ በወለዱዋት ጊዜም በመልካም አስተዳደግ እግዚአብሔርን በመፍራት የቤተ ክርስቲያንንም መጻሕፍት የአባቶቻችን ሐዋርያትንም ሥርዓት ሁሉ እያስተማሩ አሳደጓት። ❤ ከዚህም በኋላ በአደገች ጊዜ ወላጆቿ ለአንድ መስፍን ልጅ ሊአጋቧት ፈለጉ ቅድስቲቱም ይህን በመንፈስ ቅዱስ ዐውቃ ከተቀመጠችበት ተነሥታ ፊቷን ወደ ምስራቅ መልሳ መቶ ስግደትን ሰገደች ቆማም ረጂም ጸሎትን ጸለየች በጸሎቷም ውስጥ እንዲህ አለች "የክብር ባለቤት የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ወዳንተ የምደርስባት የከበረችና የቀናች መንገድህ ለእኔ ለባርያህ ለሶፍያ ምራኝ ወደ ጥፍት በሚወስድ በጠማማ መንገድ እንድንከራተት አትተወኝ የሚጠፍውንም ዓለም ያስብ ዘንድ ልቤን አትተወው ወላጆቼ በሚመክሩብኝም በረከሰ በሥጋ ፍትወት ውስጥ የኃጢአት ባርያ እንድሆን አቤቱ አትተወኝ የከበደ የዓለማዊ ፍላጐት ሸክምን ተሸካሚ አታድርገኝ ቀላልና ልዝብ የሆነ ቀንበርህን ይሸከም ዘንድ ትከሻዬ ዘንበል አድርገው እጂ"። ጸሎቷንም ከፈጸመች በኋላ በአልጋዋ ላይ ተቀመጠች ጥቂትም ቆይታ እንዲህ የሚል ሃሳብ መጣባት "ተነስቼ በስውር ልውጣ ወደ ሩቅም ሔጄ ከበረሀ ውስጥ ገብቼ ለልዑል አምላክ ላገልግል"። ❤ ከዚህም በኋላ ወላጆቿ የሰጣትን የምታገለግላት ብላቷናዋን ጠራች ወይን አምጥታ እንድታጠጣትም አዘዘቻት በአመጣችላትም ጊዜ እርሷ ጥቂት ቀምሳ ያመጣችው ወይን እስኪያልቅ ትጠጣ ዘንድ ብላቷናዋን አዘዘቻት ከስካርም የተነሣ ልባ በተሰለበ ጊዜ "ልብስሽ አንጪ የእኔንም ልብስ ውሰጂ" አላቻትና ሰጠቻት ወይኑ ስካር አእምሮዋን ነስቷታልና ተኚ አለቻት በላይዋም እንቅልፍ በከበዳት ጊዜ ማን ሳያያት ቅድስት ሶፍያ በስውር ወጣች ከወላጆቿም ማደርያ ነበርና። እርቃ በሄደችበት ጊዜ በተራራና በዋሻዎች ውስጥ ሊሰወሩ ፈልገው በሃይማኖት ምክንያት ከከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ፊት የሚሸሹ ሰዎችን አገኘች "እናንተ ከወዴት ናችሁ?" ብላ ጠየቀቻቸው የእያንዳንዳቸውን አገራቸው ነገሯት ደግማ "ወዴት ትሔዳላችሁ?" አለቻቸው እነርሱም ስለ ሃይማኖት ከዲዮቅልጥያኖስ የሆነውን ሉሁ ነገሯት። "ይቺ መንገድ ወደ ዲዮቅልጥያኖስ ታደርሰኛለችን" አለቻቸው "አዋ ታደርስሻለች" አሏት ከዚያም ጥቂ ተጉዛ ቁማ እረጅም ጸሎትን ጸለየች ወደ ዲዮቅልጥያኖስ ደርሳ