ru
Feedback
🗞 ዹ አቡጁነይድ መልዕክቶቜ Abujunaid posts

🗞 ዹ አቡጁነይድ መልዕክቶቜ Abujunaid posts

Открыть в Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ ዚቀሚቡ ዚድምፅና ዹፅሁፍ መልዕክቶቜ ዚሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ኚመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

БПльше
2 213
ППЎпОсчОкО
-224 часа
-67 ЎМей
-3430 ЎеМь
АрхОв пПстПв
ሱናን መኹተል

አላህ ተውሂድ ሩቡቢያን ወደ ተውሂድ ኡሉሂያ መጣሪያ ጥበብ ማድሚጉ ------------- ዹአላህን ብ቞ኛ ፈጣሪነት፣ ለጋስነት፣ ንጉስነትና አስተናባሪነት ዚሚያስተምሚው ዚተውሂድ ክፍል ተውሂድ ሩቡቢያ ነው። ዹአላህን በባሮቹ በብ቞ኝነት ሊመለክ እንደሚገባ ዚሚያስተምሚው ዚተውሂድ ክፍል ተውሂድ ኡሉሂያ ነው። ዚተውሂድ ሩቡብያ እውቀት መጚሚሻው ሰዎቜ ተውሂድ ኡሉሂያን እንዲገነዘቡና ለአላህ በመተናነስ በብ቞ኝነት እንዲያመልኩት ማድሚጉ ነው። ይህንን አስመልክቶም ቁርአናዊ አስሚጆቜ በርካታ ና቞ው። ኡስታዝ ሳላህ አህመድ ይህን ያብራራልናል። በኡስታዝ ሳላህ አህመድ 𒊹አጫጭርና ጠቃሚ መልዕክቶቜ ለማግኘት ይቀላቀሉን☟ ☟ 𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍 ❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀ ☀ሁዳ መልቲሚዲያ ቎ሌግራም 👇 t.me/huda4eth ፌስቡክ👇 fb.com/huda4eth ዩትዩብ👇 http://www.youtube.com/c/HudaMultimedia

ዚኢስላም አስተምህሮ መስጂዶቜን ለአምልኮ መቃብሮቜን ለመቅበሪያ ሲሆን ዹ#10አመታት_ዚአህባሜ_ጫና ዚዋሆቜን ባዕድ አምልኮ ውስጥ ዘፍቋል! #ዳዕዋ_ድኅሚ_አህባሜ @abujunaidposts

🏷 ኢስላማዊ ማንነት 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/391 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

አልሐምዱሊላህ ዚዛሬው ዚሞራተን ውሎ ዹተለዹ ነበር። መንዛዛት በሌለበት አካሄድ ጠቅላላ ጉባኀና አመራሮቜ ተመርጠዋል። ዹተቋሙን መስተካኚል ዚምትናፍቁ ሁሉ እንኳን ደስ ያላቜሁ! ዛሬ ዚተሟሙት አባላት አማናን እንዲወጡና ሙስሊሙን እንዲያገለግሉ ብርታቱን ይሰጣ቞ው ዘንድ አላህን እለምነዋለው። الحمد لله الذي ؚنعمته تتم الصالحات አቡጁነይድ ሐምሌ 11/2014

ያ ጀማዓ! ስጋቶቜ እንዳሉ ሆነው ዹነገው ዚመጅሊስ ስብሰባ መልካም ፍሬ እንደሚያስገኝ ተስፋ አለኝ። ስኬት ኹአላህ ነውና ዱዓ እናድርግ። ተቋሙ አስፈላጊውን ለውጥ በማድሚግ በተስተካኚለ አመራር መላውን
ያ ጀማዓ! ስጋቶቜ እንዳሉ ሆነው ዹነገው ዚመጅሊስ ስብሰባ መልካም ፍሬ እንደሚያስገኝ ተስፋ አለኝ። ስኬት ኹአላህ ነውና ዱዓ እናድርግ። ተቋሙ አስፈላጊውን ለውጥ በማድሚግ በተስተካኚለ አመራር መላውን ሙስሊም ኹፍ ዚሚያደርጉ ፕሮጀክቶቜን ሊተገብር ይገባል። ዚለውጡ እውን መሆን ዚብዙ አጥፊዎቜን ጥቅም ስለሚነካ ባለ በሌለ ኃይላቾው እዚተፍጚሚጚሩ ነው። በመጅሊስ በጀትና መዋቅር ዚሺርክና ዚቀብር አምልኮ ጥሪ ሊስተጋባበት፣ በጫትና በሬ ሊያልቅ አይገባም። ሲኻደሙ ዚኖሩ እርማ቞ውን ያውጡ። ዚእስካሁኑ ይበቃልና መጅሊሳቜን ዚመዝባሪዎቜና ዚፖለቲኚኞቜ መፈንጫ ኹመሆን መውጣቱ ግድ ነው። በአላህ ፈቃድ ይህ እስኪሆን መላቀቅ ዚለም። ኢን ሻ አላህ! @abujunaidposts

📌 በተኚበሩት ወራቶቜ ነብሳቜንን ኹመበደል እንጠንቀቅ!!  ምስጋና ለአለማት ጌታ ለአላህ ዚተገባ ነው። ዹአላህ ሰላምና እዝነት በተኚበሩት መልእክተኛ በቀተሰቊቻ቞ውና በባልደሚቊቻ቞ው ላይ ሁሉ ይሁን። በመቀጠልፀ ያለንበትን ዚሚጀብ ወር በማስመልኚት ዹሚፈፀሙ ዚቢድዓ ተግባራት ተበራክተዋል። ዚሚጀብን ዚመጀመሪያ እለት፣ ዚመጀመሪያ ጁምዓ፣ አስራ አምስተኛውን እለት እንዲሁም ሀያ ሰባተኛውን ቀን ማክበር ቢድዓ መሆኑንፀ በሌሎቜ ወሮቜ  እንደሚፈፀሙት ዹሰኞና ሀሙስ ወይም አያመልቢድ ፃሞቜ ካልሆነ ወሩን አስመልክቶ ዹተደነገገ ልዩ ፆምም ይሁን ሰላት እንደሌለ ገልጫለሁ።   ይህ ማለት ግን ሚጀብን ኚሌሎቜ ወራቶቜ ዹሚለዹው ምንም ነገር ዹለም ማለት አይደለም።  ዚሚጀብ ወርፀ በሱሚቱል ተዉባህ ቁጥር 36  ኚተጠቆሙት ዚተኚበሩ አራት ወራት (አሜሁሩል ሁሩም) አንዱ  ነው። አላህ እንዲህ ይላልፀ  [إِنَّ عِدَّةَ ال؎ُّهُورِ عِنْدَ اللَّهِ اثْنَا عَ؎َرَ ؎َهْراً فِي كِتَاؚِ اللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالأَرْضَ مِنْهَا أَرَؚْعَةٌ حُرُمٌ ذَلِكَ الدِّينُ الْقَيِّمُ فَلا تَ؞ْلِمُوا فِيهِنَّ أَنْفُسَكُمْ] التوؚة/36  « አላህ ዘንድ ዚወሮቜ ቁጥርፀ  በአላህ መጜሐፍ ዉስጥ (በጥብቁ ሰሌዳ ለውሀልማህፉዝ) ሰማያትንና ምድርን በፈጠሚበት ቀን (ዹሰዹመው) ዐሥራ ሁለት ወር ነውፀ ኚነሱ አራቱ ዚተኚበሩ ና቞ውፀ ይህ ቀጥተኛው ሃይማኖት ነውፀ በነርሱ ውስጥም ነፍሶቻቜሁን አትበድሉፀ» አልተውባህ 36 عَنْ أَؚِي َؚكْرَةَ رضي الله عنه عَنْ النَؚِّيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ : ( السَّنَةُ اثْنَا عَ؎َرَ ؎َهْرًا مِنْهَا أَرَؚْعَةٌ حُرُمٌ , ثَلاثٌ مُتَوَالِيَاتٌ : ذُو الْقَعْدَةِ وَذُو الْحِجَّةِ وَالْمُحَرَّمُ , وَرَجَُؚ مُضَرَ الَّذِي َؚيْنَ جُمَادَى وَ؎َعَؚْانَ) رواه الؚخاري ومسلم. ኚአቢ በክራህ በተዘገበ ሀዲስ ዹአላህ መልእክተኛ ï·º እንዲህ ብለዋልፀ «አመት አስራ ሁለት ወራት ነውፀ ኚነሱ ዉስጥ አራቱ ዚተኚበሩ ና቞ው። ሶስቱ ተኚታታይ ሲሆኑፀ ዙልቂእዳ ዙልሂጃና ሙሀሹም ና቞ው። ሌላው ደግሞ በጁማዳና በሻዕባን መካኚል ያለው ዹሙደር (ጎሳዎቜ ዚታወቁበት)  ዚ”ሚጀብ” ወር ነው።» ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል። ዙልሂጃ ዚታወቀው ዹሀጅ ወር ነውፀ  ዙልቂዕዳ ደግሞ ሁጃጆቜ ወደ መካ ዚሚያቀኑበት ወር ሲሆንፀ  ሙሀሹምም ኹሀጅ ስነስርአት በኋላ ሰዎቜ ወደቀያ቞ው ዚሚመለሱበት ወር ነው።  አላህ ሚጀብንም ኚእነዚህ  ዚሚኚበሩ ወራት  አድርጎታል።  እነዚህ ወራት (ዚተኚበሩ) ናቾው ስንልፀ 1- እነዚህ ወሚሰቶቜ ጊርነት ዚተኚለኚለባ቞ው ወራት ና቞ው።   ሙስሊሞቜ ላይ ጥቃት ኚፈፀመባ቞ው እራሳ቞ውን ለመኹላኹል ብቻ ካልሆነ በስተቀር ውጊያ አይፈቀድም። 2- በነዚህ ወራት አላህ ክልክል ያደሚጋ቞ውን ነገሮቜ መፈፀም በሌላ ወራት ወንጀልን እንደመፈፀም አይደለም። ስለዚህም አላህ እነዚህን ወራቶቜ ለይቶ ነብሳቜንን እንዳንበድል አሳስቊናልፀ «በነርሱ ውስጥም ነፍሶቻቜሁን አትበድሉ» ።  እራስን መበደል አስኚፊ መሀይምነት ነው። በአንድ ሰውና በጌታው መካኚል ዹሚፈፀም እራስን መበደል ለአላህ መፈፀም ዚሚገባን ሀላፊነት አለመወጣት ነው። በራስ ላይ ኹሚፈፀሙ በደሎቜ ሁሉ ትልቁ  በአምልኮ ፍጥሚታትን ኹአላህ ጋር ማጋራት “ሜርክ" ነው። ሰዎቜ ላይ ዹሚፈፀም በደልም ቢሆን ዚሚጎዳው ሰሪዉን ነውና እራስን መበደል ነው። ለራሱ ያወቀ በማንኛውም ጊዜ ኹበደል ይርቃል።  ኢባደላህ! አላህ እነዚህን ወራቶቜ አክብሯ቞ዋልና እኛም ኹፍተኛ ክብር መስጠት ይገባናል።  እነዚህ ወራቶቜ ሲገቡፀ አላህ ክብርን እንደለገሳ቞ው ልናስታውስና ኹወንጀል ለመራቅ ያለንን ቁርጠኝነት ልናድስ ይገባል። ይህ ልባዊ ኢባዳ ነው።  ወንጀልን በማንኛውም መፈፀም ዹተኹለኹለ ቢሆንም በነዚህ ወራት ግን ክልክልነቱ ዚበሚታ ነው። ስለዚህም ኹምንም አይነት ወንጀሎቜ መጠንቀቅ እና ወደ አላህ መመለስ ያስፈልገናል።   ኚትናንሜም ይሁን ኚትላልቅ ወንጀሎቜ በአላህ እንጠበቅ።  ሞይጣንን እናሞንፍ! አላህ ኚጥፋት ይጠብቀን.. አሚን!! አኹኩም ፊላህ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ http://t.me/abujunaidposts

በሚዳሰሱ ሞዎሎቜ ሐጅና ኡምራን ማስተማር እንዎት ይታያል? ኚቅርብ አመታት ወዲህ ዹሐጅ አፈፃፀም ስርአትን ለህፃናት በማስተማር አላማ ዹሚዘጋጁ ፕሮግራሞቜ ተበራክተዋል። ዚአዘጋጆቹ ሀሳብ መልካም ቢሆንም በሞሪዓ እንዎት ይታያል ዹሚለውን ማጥናት ተገቢ ይሆናል። ኹዚህ አንፃር ዚፕሮግራሞቹ አዘጋጆቜ ጉዳዩን ትኩሚት ሰጥተው እንዲያጀኑት ጥሪዬን አቀርባለው። ይህ ዚማስተማሪያ ዘዮ በተለያዩ ሀገራት ዹተተገበሹ በመሆኑ ብይኑን በተመለኹተ ኡለማዎቜ ትኩሚት ሰጥተው ውይይትና ምክክር አድርገውበታል። ምንም እንኳ አላማውን በመመልኚት ይቻላል ያሉ አንዳንድ ኡለማዎቜ ቢኖሩም አብዛኞቹ ኡለማዎቜ እና ዚፈትዋና ዹምርምር ተቋማት ግን እንደማይፈቀድና ተገቢም እንዳልሆነ ገልፀዋል። ዹዓለም ዹፊቅህ ሊቃውንት ምክር ቀት (መጅመዕ አልፊቅህ አልኢስላሚ) በሒጅራ አቆጣጠር ኚሻዕባን 5/1412 እ.ኀ.አ በ 8/2/1992 ጀምሮ ባደሚገው አስራ ሶስተኛ መደበኛ ጉባኀው ዚካዕባ ሞዮል በመስራት ልጆቜን ማስተማርን በተመለኹተ ተወያይቶ ባሳለፈው ውሳኔ (ይህ ተግባር ክልክል ወደሆኑ ክፉ ነገሮቜ ሊያዳርስ ስለሚቜል መኹልኹልና በር መዝጋት ዋጂብ መሆኑን) አፅንቷል። [ቀራራት አልመጅመዕ ገፅ 285] እንደዚሁ ዚሳውዲ ቋሚ ዚፈትዋ ኮሚ቎ም (ካዕባ፣ መቃሙ ኢብራሂም፣ ጀመራት እና መሰል ቊታዎቜን በሚዳሰስ ሞዮል በመስራት ዹሐጅና ዑምራ ክንዋኔዎቜን ማስተማር አዚፈቀድም) ካሉ በኋላ ምክንያቶቜን ሲጠቅሱፀ ሞዎሎቹን ማላቅ ወይም ማዋሚድን ዚመሳሰሉ መጥፎ ውጀቶቜን ሊያስኚትል ይቜላል ብለዋል። ገላጭ ዹሆኑ ፅሁፎቜን በማብራራት ለሰፊው ህዝብ በቂ በሆነ መልኩ ማስተማር ስለሚቻል ሞዮል መስራት አስፈላጊ እንዳልሆነ ተናግሚዋል። [ፈታዋለጅናህ 14/11] ታላቁ አሊም ሞይኜ ኢብኑ ኡሰይሚንም በዚህ መልኩ ማስተማር ዚማይገባና ዚማይፈቀድ እንደሆነ በመግለፅ በምትኩ ቊርድ ላይ ዚካዕባን ስእል በመሳል ጠዋፍ እንደሚደሚግ ማስተማር እንደሚቻል ተናግሚዋል። በሞዮል ማሳዚት በቀልብ ውስጥ ለኢባዳው ያለንን ቊታ በማሳጣት እንቅስቃሎ ብቻ ያደርገዋል ብለዋል። [መጅሙዕ ፈታዋ ቅፅ 24 ገፅ 91] በሞዮል ማስተማር ይቻላል ያሉ አንዳንድ ኡለማዎቜም ቢሆን ዹዚህ አይነቱ ትምህርት በኢስላማዊ ጉዳዮቜ ሚኒስ቎ር (ዊዛራ) ክትትል ሊፈፀም እንደሚገባ ኹመጠቆማቾው ጋር ሞዎሎቹ እውነተኛውን ዚካዕባና ዹሐጅ ክንውን ቊታዎቜን በጣም ዚማስመሰል ስራ እንዳይሰራ ኚልክለዋል። እንደውም ሞዎሎቹ ትንንሜ ሆነው በአካባቢውና በያንዳንዱ ሞዮል ላይ መማሪያ መሆኑ እንዲገለፅበት፣ እንደ ኢባዳ ሳይሆን እንደ ትምህርት መማሪያ ብቻ መሆኑ ተደጋግሞ እንዲነገርና ዚሞዎሎቹን ክብር ኚመንካት መጠንቀቅና ሌሎቜ መስፈርቶቜን አስቀምጠዋል። ዚእነዚህ ፕሮግራሞቜ አላማ ዚኢባዳው ፍቅር በልጆቜ ልቩና እንዲያድር ማድሚግ እንጂ በዚህ እድሜ ዹሐጅ አፈፃፀም ህግጋትን ዹማወቃቾው አስፈላጊነት ጎልቶ አይመስለኝም። ዚሚዳሰሱ ሞዎሎቜን በመገንባት ማስተማር ዚኡለማዎቜን ትቜት ያስተናገደና ቢያንስ በሞሪዓ ስለመፈቀዱ አጠራጣሪ ዹሆነ ዚማስተማሪያ መንገድ ነው። ዚሚያጠራጥርን ነገር በመተው ታዘናልና አዘጋጆቜ ሌሎቜ ዚማስተማሪያ መንገዶቜን ቢጠቀሙ ዚተሻለ ይሆናል። ለምሳሌ ዘመናዊው ቮክኖሎጂ ባመጣ቞ው እንደ 3D፣ ፓወር ፖይንትና እና ሞሜን ግራፊክስ በመጠቀም ማስተማር ይቻላል። ኹዚህም በተሻለ በተቀሹፀ እውነተኛ ዹሐጅ አፈፃፀም ቪድዮ ማስተማር ቀላል ነው። ወላሁ አዕለም {إِنۡ أُرِیدُ إِلَّا ٱلۡإِصۡلَـٰحَ مَا ٱسۡتَطَعۡتُۚ وَمَا تَوۡفِیقِیۀ إِلَّا ؚِٱللَّهِۚ عَلَیۡهِ تَوَكَّلۡتُ وَإِلَیۡهِ أُنِیؚ} በተቻለኝ ያክል ማበጀትን እንጂ አልሻም። (ለደግ ሥራ) መገጠሜም በአላህ እንጂ በሌላ አይደለም፡፡ በእርሱ ላይ ተመካሁ፡፡ ወደ እርሱም እመለሳለሁ» አላ቞ው፡፡ [Surah Hûd: 88] ሐምሌ 3/2014 አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ http://T.me/abujunaidposts

ውድ ዚኢስላም ወንድም እህቶቌፀ እንኳን ለኢድ አልአድሓ በአል በሰላም አደሚሳቜሁ መጪው ዘመን ለሁላቜንም ዚኢማን ዚእድገትና ዚስኬት እንዲሆንልን አላህን እንለምነዋለሁ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ تقؚل الله منا ومنكم صالح الأعمال وأعاده الله علينا ونحن في عز وكرامة وسعادة أخوكم في الله أؚو جنيد صالح أحمد T.me/abujunaidposts

‎⁚من_جوامع_دعاء_النؚي_ؚطاقة⁩_pdf_pdf.pdf6.93 MB

ዚቲጃኒዮቜ ሞይኜ ይናገራል [ዹውመል ቂያማ ኚሞኜ (አህመድ) አቲጃኒ በኋላ ያለ ዚትኛውም ወሊይ ጀነት ቀድሞኝ እንዲገባ አልፈቅድለትም! እንደዚሁ ዚትኛውም ወሊይ ተማሪዎቹን ኹኔ ተማሪዎቜ በፊት ጀነት እንዲያስገባ አልፈቅድለትም!!] #ኚራማት #ሱፍያ #ዱስቱር #ቲጃኒያ https://youtu.be/XWuL4HrZzXo @abujunaidposts

ስለ ሪፋዒይ ዹሚነገር ታላቅ ቅጥፈት! ዚአህባሹ ሞኜ ጀሚል ሀሊም ኚአብዱላሂ አልሀሚሪ እንደተማሚው ስለ ሪፋዒያ ኹራፋት ሲዘክር እንዲህ በማለት ይቀጥፋል። አህመድ አሪፋዒ ዚነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰልም) ቀብር ዘንድ ሄዶ (አሰላሙአለይኩም) ብሎ ሰላምታ በማቅሚብ በግጥም እጃ቞ውን እንዲዘሚጉለት ሲጠይቃ቞ው። ኚቀብሩ (ውአለይኩሙሰላም ልጄ ሆይ! በማለት ኚመለሱለት በኃላ ቀብራ቞ው ተሰንጥቆ እጃ቞ውን አወጡና ሪፋኢይ በተሰበሰቡት ሰዎቜ ፊት እጃ቞ውን ሳመ) ይለናል። ይህ አይን ያወጣ ውሞት መሆኑ አያጠያይቅም። በቅድሚያ ታሪኩ ለመኚሰቱ ዚሞይኹ አድናቂዎቜ ኚሚቀባበሉት ወሬ ባለፈ ዚሚቀርብ ምንም አይነት መሹጃ ዚላ቞ውም። ይህ ደግሞ ታላቅ ክስተት እንደመሆኑ እውነት ቢሆን ኡለማዎቜና ዚታሪክ ሰዎቜ ባላለፉት ነበር። ሌላው አላህ ሰዎቜ ኚሞቱ በኀላ እስኚ ትንሳኀ ድሚስ በነሱና በዱንያ ሰዎቜ መካኚል ግርዶሜ አድርጓል። አላህ እንዲህ ይላል፩ { حَتَّىٰۀ إِذَا جَاۀءَ أَحَدَهُمُ ٱلۡمَوۡتُ قَالَ رَؚِّ ٱرۡجِعُونِ * لَعَلِّیۀ أَعۡمَلُ صَـٰلِحࣰا فِیمَا تَرَكۡتُۚ كَلَّاۀۚ إِنَّهَا كَلِمَةٌ هُوَ قَاۀىِٕلُهَاۖ وَمِن وَرَاۀىِٕهِم َؚرۡزَخٌ إِلَىٰ یَوۡمِ یُؚۡعَثُونَ } አንዳ቞ውንም ሞት በመጣበት ጊዜ እንዲህ ይላል «ጌታዬ ሆይ! (ወደ ምድሚ ዓለም) መልሱኝ፡፡ «በተውኩት ነገር በጎን ሥራ ልሠራ እኚጅላለሁና፡፡» (ይህን ኚማለት) ይኚልኚል፡፡ እርስዋ እርሱ ተናጋሪዋ ዚኟነቜ ኚንቱ ቃል ናት፡፡ ኚስተፊታ቞ውም እስኚሚቀሰቀሱበት ቀን ድሚስ ግርዶሜ አልለ፡፡ [አልሙእሚኑን: 99-100] ይህ ባይሆን ኖሮ በሰሐቊቜ ዘመን መልእክተኛው ተነስተው ቢያናግሯ቞ው ዚሚያስመኝ ብዙ ፈተናዎቜ ሲኚሰቱ ባስነሳ቞ው ነበር። አህመድ አሪፋዒ ዹኖሹው በሂጅራ አቆጣጠር (512–578) ነበር። ይህ ቢኚሰት ኖሮ ኚሱ በፊት በድንቁ ዚሰለፎቜ ዘመን ዚኖሩት ሰሀቊቜ፣ ታቢኢዮቜና ሷሊሆቜ ለዚህ ዚተገቡ ነበሩ። ኹዚህም አልፎ በሞቱ ግዜ ሰሀቊቜ ዱንያ ስትጚልምባ቞ው ያፅናኗ቞ው ነበር። ግን ይህ አልሆነም! ታላቁ አሊም ሞይኜ ኢብኑ ባዝ ስለዚህ ቅጥፈት ተጠይቀው ዚመለሱትን ብንመለኚትፊ ይህ ምንም እውነትነት ዹሌለው ባጢል። አላህ እንደነገሚን መልእክተኛው (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አላህ በፃፈባ቞ውን ሞት አልፈዋል። { إِنَّكَ مَیِّتࣱ وَإِنَّهُم مَّیِّتُونَ } (አንተ ሟቜ ነህፀ እነርሱም ሟ቟ቜ ናቾው) አዝ’ዙመር: 30 በምድር ላይ ዚሚንቀሳቀሱ መላእክት ዚኡመቶቻ቞ውን ሰላምታ እንደሚያደርሷ቞ው፣ ሰዎቜ ሰለዋት በሳ቞ው ላይ ሲያደርጉም እንደሚያደርሷ቞ውና እንደሚመልሱም ተናግሚዋል። በዚህ ዙርያ ብዙ ሀዲሶቜ ተዘግበዋል ሆኖም እጅ ዘርግተው ሰዎቜን ይጚብጣሉ ዹሚል መሹጃ ግን ዚለም። ይህ ክስተት ሀሰት ለመሆኑ ይህ በቂ መሹጃ ነው። ሆኖም ተኚስቷል ቢባል እንኳ ሾይጧን ተመሳስሎበት እሱንና ተኚታዮቹን እያጭበሚበራ቞ው ነውና አላህን እንድንፈራና ዲናቜንን ምንጩ በመሹጃ እንድንኚተል አደራ ብለዋል። ምንጭ፩ አል መጅሙዕ 9/310 አህባሟቜ ዚሚሰብኩትን ዚጥመት ጊሪቃ #ሪፋዒያ ሰባኪዎቜ እንደ አንዳንድ ዚሂንዱ እና ዚኢቫንጀሊዝም ሰባኪዎቜ በድግምትና ኚጅኖቜ ጋር በመመሳጠር ተአምር ፈፀምን ይላሉ። እራስን በስለት ዚመውጋትና እሳት ዚመንካት ኚራማ አለን በማለት ይመፃደቀሉ። ይህ ፍፁም ዚሷሊሆቜ መንገድ አይደለም!! አላህ ኚጥመት ይጠብቀን አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ @abujunaidposts ___ * ሞይኜ ኡሰይሚን ስለ ሪፋዒያ ጊሪቃ https://youtu.be/68EhI_vDE-I * The Rifaa’is who stab themselves with knives but are not affected by it https://islamqa.info/en/answers/9338/the-rifaais-who-stab-themselves-with-knives-but-are-not-affected-by-it * ؚطلان تقؚيل الرفاعي يدى النؚي صلى الله عليه وسلم https://youtu.be/hSEoUm_FgG0 #ኚራማት #ዱስቱር #ሱፊያ #ሪፋዒያ #አህባሜ #አሻዒራ

ስለ ዓሹፋ ቀን ዱዓእ ሁለት ነጥቊቜ [1] በኢድ ዋዜማው ዹዓሹፋ እለት ዱዓእ ተቀባይነት እንዳለው ዚሚዘክሩ ሀዲሶቜ ሀጅ ላይ ዹሌሉ ሰዎቜንም ይመለኚታሉን?? ዹአላህ መልእክተኛ «ኚዱዓዎቜ ሁሉ በላጩ (ዚኢድ ዋዜማ) ዹአሹፋ ቀን ዱዓ ነው...» ማለታ቞ውን ቲርሚዚይ ኚአብዱላህ ኢብኑ ኡመር ዚዘገቡ ሲሆንፀ ሌሎቜ ተመሳይ ይዘት ያላ቞ው ሀዲሶቜም ይገኛሉ። ታዲያ ዹዓሹፋን እለት በዱአዕና በዚክር ያሳለፈ ሰው ታላቅ ክብርና ምንዳን ዚሚያገኘው ሀጅ ላይ ሲሆን ብቻ ነውን? በእርግጥ በዚህ እለት ክብር ባለው ዹዓሹፋ ምድር ዹተገኘ ሰው ዹጊዜንም ዚቊታንም ክብር ተጎናፅፏልና በተሻለ ሁኔታ ላይ መገኘቱ እንዲሁም ዱአው ተቀባይነት ለማግኘት ዹቀሹበ መሆኑ አያጠራጥርም። ይሁንና ሚዛን በሚደፋው ዚኡለማዎቜ አቋም መሰሚትፀ እነዚህ ኹአሹፋ እለት ክብር ጋር ተያይዞ ዚዱአ ተቀባይነትን ዚተመለኚቱ ሀዲሶቜ በማንኛውም ቊታ ዹሚገኙ ሙስሊሞቜን ይመለኚታሉ። በመሆኑም በሀጅ ስራ ላይ ዹሌሉ ሰዎቜም በዱዓ ሊበሚቱ ይገባል። ታላቁ አሊም ሞይኜ ሳሊህ አልፈውዛን በዚህ እለት ዚሚባሉ በሀዲስ ዹተላለፉ ዱአዎቜን አስመልክቶ ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎቜ መሆኑን ተጠይቀው ተኚተዩን መልሰዋል¹ «በምላሻቜን እንደገለፅነውፀ ይህ ለሁጃጆቜንም ይሁን ሌሎቜን ዹተመለኹተ ጥቅል መልእክት ነው። ነገር ግን ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎቜ ይበልጥ ዚተገባ ነው። ምክኒያቱም ሁጃጆቜ በዚህ እለት በዓሹፋ ምድር በኢህራም ውስጥ ስለሚገኙ ኚሌሎቜ በበለጠ ዱዓ቞ው ተቀባይነት ለማግኘት ዹቀሹበ ነው። ስለዚህም ዹዓሹፋን እለት በሀጅ ተግባር ላይ ዹሌሉ ሰዎቜ እንዲፆሙት ተደንግጓል። እለቱ ብልጫ ያለወወ ስለሆነም አላህን በማስታወስ፣ ማርታን በመለመን እና ዱዓ በማድሚግ ጊዜያ቞ውን ያሳልፋሉፀ ሁጃጆቜንም በኢባዳ ይካፈሏ቞ዋል ማለት ነው።» ኚሞይኹ ድሚገፅ ዹተወሰደ ዚድምፅ ፈትዋ [2] በዓሹፋ እለት ሁጃጆቜ በአሹፋ ምድር እንደሚሰባሰቡት ለዱዓና ለዚክር መሰባሰብ "ታዕሪፍ"ን በተመለኚተፀ ይህ ተግባር አንዳንድ ሰለፎቜ እንደፈፀሙት ዹተሹጋገጠ ነው። ኚነሱም መካኚል ኢብኑ አባስ ይገኙበታልፀ ኢማሙ አህመድም ባይተገብሩትም እንደሚቻል ተናግሚዋል። ነገር ግን ያወገዙትና ኚቢድአ ዚመደቡትም አሉ። ዚኡለማዎቻቜንን ማብራሪያዎቜ ስንፈትሜ ተኚታዮቹ ድምዳሜዎቜ ላይ ያደርሱናልፀ 1) "ታእሪፍ"ን መተግበር በራሱ ቜግር ዚለውም። ተግባሩን እንደሱና ወይም ሙስተሀብ ነገር መውሰድ ግን አይገባም። ጉዳዩ ዚኢጅቲሀድ መስአላ ነውና ተግባሩ ዹሚወገዝ ተግባር አይሆንም። ዹፈፀመውም ሰው ቢድአ ሰራ አይባልም። 2) ታእሪፍ ስንል ኚምድሚ አሹፋ ውጭ ባሉ ዚዚሀገሩና ዹዹኹማው መስጂዶቜ መሰባሰብን ዹተመለኹተ እነጂ ለዚህ ብሎ ጉዞ ማድሚግ አይፈቀድም። አላህ ዹአሹፋን ምድር ለዚህ ቀን ኢባዳ መሰባሰቢያ እንደመሚጠው በዚሀገሩ አንዳንድ ቊታዎቜን፣ መስጅዶቜንና ቀብሮቜን በመምሚጥ ወደነሱ ጉዞ አድርጎ መሰባሰብ በፍፁም አይፈቀድም። ይህ ዚነብዩ መስጂድንም ይሁን በይተልመቅዲስን ያካትታል። 3) ይህ መሰባሰብ ጩኞትና ሱና ያልሆኑ ዚጋራ አምልኮዎቜ ኚታኚሉበት ቢድአ እንደሚሆን አያጠራጥርም። በተመሳሳይ መልኩ ኢባዳ ያልሆኑ ግጥሞቜና መንዙማዎቜን ለዚህ መለያ ማድሚግ ጥፋት ነው። እነዚህን ነጥቊቜ በዝርዝር ለመሚዳት ዚሚያስቜሉ ማብራሪያዎቜን ኚኡለማዎቜ ድርሳናት እንደሚኚተለው እናያለን። ቀሪዉን ዹፅሁፍ ክፍል ተኚታዩን ሊንክ በመኹተል ያንብቡት https://www.facebook.com/682494683/posts/10158937378539684/ t.me/abujunaidposts @abujunaidposts

🍂 አህባሟቜ ያስተውሉ..! ታላቁ ዚሀዲስ ዘጋቢ ቲርሚዚይ በሀዲስ ጥንቅራ቞ው ኪታቡዘካት ሀዲስ ቁ .662 ስለ አላህ ሲፋት አህሉሱና እና ጃህሚያዎቜ ያላ቞ውን አቋም በግልፅ አስፍሚዋል! ፍልስፍና ሳይ
🍂 አህባሟቜ ያስተውሉ..! ታላቁ ዚሀዲስ ዘጋቢ ቲርሚዚይ በሀዲስ ጥንቅራ቞ው ኪታቡዘካት ሀዲስ ቁ .662 ስለ አላህ ሲፋት አህሉሱና እና ጃህሚያዎቜ ያላ቞ውን አቋም በግልፅ አስፍሚዋል! ፍልስፍና ሳይሆን ሞሪአዊ መሚጃዎቜን መኹተል መታደል ነው። አላህ ማስተዋልን ይለግሳቜሁ!! @abujunaidposts

በዙልሒጃ ቀናት አላህን ማውሳትና ማላቅ በነዚህ ቀናት አላህን ማመስገንፀ (አልሀምዱሊላህ)፣ ተክቢር፣ ተስቢህ (ሱብሀነላህ) እና ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢለላህ) በማለት በማለት ዹአላህን ስም ኹፍ ማድሚግ
በዙልሒጃ ቀናት አላህን ማውሳትና ማላቅ በነዚህ ቀናት አላህን ማመስገንፀ (አልሀምዱሊላህ)፣ ተክቢር፣ ተስቢህ (ሱብሀነላህ) እና ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢለላህ) በማለት በማለት ዹአላህን ስም ኹፍ ማድሚግ ይወደዳል። عن عؚد االله ØšÙ† عمر رضي االله عنهما عن النؚي صلى االله عليه وسلم قال : "ما من أيام أع؞م عند االله ولا أحؚ إليه العمل فيهن من هذه الأيام الع؎ر فأكثروا فيهن من التهليل والتكؚير والتحميد" أخرجه احمد ዓብዱላህ ኢብኑ ዑመር ባስተላለፉት ሀዲስ ነብዩ እንዲህ ብለዋልፀ «ኚእነዚህ አስር ቀናት በበለጠ አላህ ዘንድ ታላቅ ዹሆኑና መልካም ስራ ምን እጅግ ዚተወደደባ቞ው ቀናት ዚሉምፀ ስለዚህ ተህሊል ተክቢር እና ተህሚድ አብዙ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል ኚተክቢር አደራሚግ መካኚል الله أكؚر ، االله أكؚر لا إله إلا االله ، واالله أكؚر والله الحمد “አላሁ አክበርፀ አላሁ አክበርፀ ላ ኢላሀ ኢለላህ ወላሁ አክበር ወሊላሂልሀምድ" ዹሚለው ዋነኛው ሲሆን ሌሎቜ አባባሎቜም አሉ በእነዚህ ቀናት ውስጥ ሊደሹግ ዚሚገባው ይህ ተክቢር ብዙ ሰዎቜ ስለማይፈጜሙት እዚተሚሱ ካሉ ሱናዎቜ መካኚል ነው። ሰዎቜን ለማስታወስ እና ሱናን ህያው ለማድሚግ ድምጜን ኹፍ አድርጎ ተክቢር ማድሚግ ይቻላል። አብዱላህ ኢብኑ ኡመር እና አቡሁሚይራህ በነዚህ አስር ቀናት ገበያ ወጥተው ተክቢራ ሲያደርጉ ሰዎቜም እያስታወሱ ተክቢራ ያደርጉ እንደነበር ተዘግቧል። ሆኖም ሁሉም ሰው ዚራሱን ዚክር ያደርጋል ማለት እንጂ ሰዎቜ እዚተሰባሰቡ በአንድ ድምጜ ተክቢራ ያድርጉ ማለት አይደለም አላህ መልካም ስራን ያግራልን፣ ኹሚቀበላቾው ባሮቹ ያድርገን። አሚን! @abujunaidposts

🔖 ተውሒድ እና ዹሐጅ ፍሬዎቜ 🎙 አቡጁነይድ እና ጣሀ አህመድ በ 2002 በጃሊያ አዳራሜ ዹቀሹበ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/219 ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

ዹዙልሒጃ ወር ነገ ሐሙስ ሰኔ 23/2014 / June 30/2022 አንድ ብሎ ይጀምራል ጃቢር ኢብኑ ዓብዲላህ ባስተላለፉት ሀዲስ ዹአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል «ኚዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላ቞ውፀ አስርቱ ቀናት ና቞ው። ማለትም አስሩ ዹዙልሂጃ ቀናት» አልባኒ ሰሂሁል ጃሚዕ 1133 ላይ አስፍሚውታል ኹነገ ጀምሮ ያሉትን ተኚታታይ ቀናት በኢባዳ እናሳልፋ቞ው! @abujunaidposts