fa
Feedback
🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

رفتن به کانال در Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

نمایش بیشتر
2 213
مشترکین
-224 ساؚت
-67 عوز
-3430 عوز
آرشیو پست ها
ሱናን መከተል

አላህ ተውሂድ ሩቡቢያን ወደ ተውሂድ ኡሉሂያ መጣሪያ ጥበብ ማድረጉ ------------- የአላህን ብቸኛ ፈጣሪነት፣ ለጋስነት፣ ንጉስነትና አስተናባሪነት የሚያስተምረው የተውሂድ ክፍል ተውሂድ ሩቡቢያ ነው። የአላህን በባሮቹ በብቸኝነት ሊመለክ እንደሚገባ የሚያስተምረው የተውሂድ ክፍል ተውሂድ ኡሉሂያ ነው። የተውሂድ ሩቡብያ እውቀት መጨረሻው ሰዎች ተውሂድ ኡሉሂያን እንዲገነዘቡና ለአላህ በመተናነስ በብቸኝነት እንዲያመልኩት ማድረጉ ነው። ይህንን አስመልክቶም ቁርአናዊ አስረጆች በርካታ ናቸው። ኡስታዝ ሳላህ አህመድ ይህን ያብራራልናል። በኡስታዝ ሳላህ አህመድ 𒊹︎︎︎አጫጭርና ጠቃሚ መልዕክቶች ለማግኘት ይቀላቀሉን☟︎︎︎ ☟︎︎︎ 𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍 ❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀ ☀️ሁዳ መልቲሚዲያ ቴሌግራም 👇 t.me/huda4eth ፌስቡክ👇 fb.com/huda4eth ዩትዩብ👇 http://www.youtube.com/c/HudaMultimedia

የኢስላም አስተምህሮ መስጂዶችን ለአምልኮ መቃብሮችን ለመቅበሪያ ሲሆን የ#10አመታት_የአህባሽ_ጫና የዋሆችን ባዕድ አምልኮ ውስጥ ዘፍቋል! #ዳዕዋ_ድኅረ_አህባሽ @abujunaidposts

🏷 ኢስላማዊ ማንነት 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/391 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

አልሐምዱሊላህ የዛሬው የሸራተን ውሎ የተለየ ነበር። መንዛዛት በሌለበት አካሄድ ጠቅላላ ጉባኤና አመራሮች ተመርጠዋል። የተቋሙን መስተካከል የምትናፍቁ ሁሉ እንኳን ደስ ያላችሁ! ዛሬ የተሾሙት አባላት አማናን እንዲወጡና ሙስሊሙን እንዲያገለግሉ ብርታቱን ይሰጣቸው ዘንድ አላህን እለምነዋለው። الحمد لله الذي بنعمته تتم الصالحات አቡጁነይድ ሐምሌ 11/2014

ያ ጀማዓ! ስጋቶች እንዳሉ ሆነው የነገው የመጅሊስ ስብሰባ መልካም ፍሬ እንደሚያስገኝ ተስፋ አለኝ። ስኬት ከአላህ ነውና ዱዓ እናድርግ። ተቋሙ አስፈላጊውን ለውጥ በማድረግ በተስተካከለ አመራር መላውን
ያ ጀማዓ! ስጋቶች እንዳሉ ሆነው የነገው የመጅሊስ ስብሰባ መልካም ፍሬ እንደሚያስገኝ ተስፋ አለኝ። ስኬት ከአላህ ነውና ዱዓ እናድርግ። ተቋሙ አስፈላጊውን ለውጥ በማድረግ በተስተካከለ አመራር መላውን ሙስሊም ከፍ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን ሊተገብር ይገባል። የለውጡ እውን መሆን የብዙ አጥፊዎችን ጥቅም ስለሚነካ ባለ በሌለ ኃይላቸው እየተፍጨረጨሩ ነው። በመጅሊስ በጀትና መዋቅር የሺርክና የቀብር አምልኮ ጥሪ ሊስተጋባበት፣ በጫትና በሬ ሊያልቅ አይገባም። ሲኻደሙ የኖሩ እርማቸውን ያውጡ። የእስካሁኑ ይበቃልና መጅሊሳችን የመዝባሪዎችና የፖለቲከኞች መፈንጫ ከመሆን መውጣቱ ግድ ነው። በአላህ ፈቃድ ይህ እስኪሆን መላቀቅ የለም። ኢን ሻ አላህ! @abujunaidposts

📌 በተከበሩት ወራቶች ነብሳችንን ከመበደል እንጠንቀቅ!!  ምስጋና ለአለማት ጌታ ለአላህ የተገባ ነው። የአላህ ሰላምና እዝነት በተከበሩት መልእክተኛ በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸው ላይ ሁሉ ይሁን። በመቀጠል፤ ያለንበትን የረጀብ ወር በማስመልከት የሚፈፀሙ የቢድዓ ተግባራት ተበራክተዋል። የረጀብን የመጀመሪያ እለት፣ የመጀመሪያ ጁምዓ፣ አስራ አምስተኛውን እለት እንዲሁም ሀያ ሰባተኛውን ቀን ማክበር ቢድዓ መሆኑን፤ በሌሎች ወሮች  እንደሚፈፀሙት የሰኞና ሀሙስ ወይም አያመልቢድ ፃሞች ካልሆነ ወሩን አስመልክቶ የተደነገገ ልዩ ፆምም ይሁን ሰላት እንደሌለ ገልጫለሁ።   ይህ ማለት ግን ረጀብን ከሌሎች ወራቶች የሚለየው ምንም ነገር የለም ማለት አይደለም።  የረጀብ ወር፤ በሱረቱል ተዉባህ ቁጥር 36  ከተጠቆሙት የተከበሩ አራት ወራት (አሽሁሩል ሁሩም) አንዱ  ነው። አላህ እንዲህ ይላል፤  [إِنَّ عِدَّةَ الشُّهُورِ عِنْدَ اللَّهِ اثْنَا عَشَرَ شَهْراً فِي كِتَابِ اللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالأَرْضَ مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ ذَلِكَ الدِّينُ الْقَيِّمُ فَلا تَظْلِمُوا فِيهِنَّ أَنْفُسَكُمْ] التوبة/36  ÂŤ አላህ ዘንድ የወሮች ቁጥር፤  በአላህ መጽሐፍ ዉስጥ (በጥብቁ ሰሌዳ ለውሀልማህፉዝ) ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን (የሰየመው) ዐሥራ ሁለት ወር ነው፤ ከነሱ አራቱ የተከበሩ ናቸው፤ ይህ ቀጥተኛው ሃይማኖት ነው፤ በነርሱ ውስጥም ነፍሶቻችሁን አትበድሉ፤» አልተውባህ 36 عَنْ أَبِي بَكْرَةَ رضي الله عنه عَنْ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ : ( السَّنَةُ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ , ثَلاثٌ مُتَوَالِيَاتٌ : ذُو الْقَعْدَةِ وَذُو الْحِجَّةِ وَالْمُحَرَّمُ , وَرَجَبُ مُضَرَ الَّذِي بَيْنَ جُمَادَى وَشَعْبَانَ) رواه البخاري ومسلم. ከአቢ በክራህ በተዘገበ ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ  እንዲህ ብለዋል፤ «አመት አስራ ሁለት ወራት ነው፤ ከነሱ ዉስጥ አራቱ የተከበሩ ናቸው። ሶስቱ ተከታታይ ሲሆኑ፤ ዙልቂእዳ ዙልሂጃና ሙሀረም ናቸው። ሌላው ደግሞ በጁማዳና በሻዕባን መካከል ያለው የሙደር (ጎሳዎች የታወቁበት)  የ”ረጀብ” ወር ነው።» ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል። ዙልሂጃ የታወቀው የሀጅ ወር ነው፤  ዙልቂዕዳ ደግሞ ሁጃጆች ወደ መካ የሚያቀኑበት ወር ሲሆን፤  ሙሀረምም ከሀጅ ስነስርአት በኋላ ሰዎች ወደቀያቸው የሚመለሱበት ወር ነው።  አላህ ረጀብንም ከእነዚህ  የረከበሩ ወራት  አድርጎታል።  እነዚህ ወራት (የተከበሩ) ናቸው ስንል፤ 1- እነዚህ ወረሰቶች ጦርነት የተከለከለባቸው ወራት ናቸው።   ሙስሊሞች ላይ ጥቃት ከፈፀመባቸው እራሳቸውን ለመከላከል ብቻ ካልሆነ በስተቀር ውጊያ አይፈቀድም። 2- በነዚህ ወራት አላህ ክልክል ያደረጋቸውን ነገሮች መፈፀም በሌላ ወራት ወንጀልን እንደመፈፀም አይደለም። ስለዚህም አላህ እነዚህን ወራቶች ለይቶ ነብሳችንን እንዳንበድል አሳስቦናል፤ «በነርሱ ውስጥም ነፍሶቻችሁን አትበድሉ» ።  እራስን መበደል አስከፊ መሀይምነት ነው። በአንድ ሰውና በጌታው መካከል የሚፈፀም እራስን መበደል ለአላህ መፈፀም የሚገባን ሀላፊነት አለመወጣት ነው። በራስ ላይ ከሚፈፀሙ በደሎች ሁሉ ትልቁ  በአምልኮ ፍጥረታትን ከአላህ ጋር ማጋራት “ሽርክ" ነው። ሰዎች ላይ የሚፈፀም በደልም ቢሆን የሚጎዳው ሰሪዉን ነውና እራስን መበደል ነው። ለልሹ ያወቀ በማንኛውም ጊዜ ከበደል ይርቃል።  ኢባደላህ! አላህ እነዚህን ወራቶች አክብሯቸዋልና እኛም ከፍተኛ ክብር መስጠት ይገባናል።  እነዚህ ወራቶች ሲገቡ፤ አላህ ክብርን እንደለገሳቸው ልናስታውስና ከወንጀል ለመራቅ ያለንን ቁርጠኝነት ልናድስ ይገባል። ይህ ልባዊ ኢባዳ ነው።  ወንጀልን በማንኛውም መፈፀም የተከለከለ ቢሆንም በነዚህ ወራት ግን ክልክልነቱ የበረታ ነው። ስለዚህም ከምንም አይነት ወንጀሎች መጠንቀቅ እና ወደ አላህ መመለሾ ያስፈልገናል።   ከትናንሽም ይሁን ከትላልቅ ወንጀሎች በአላህ እንጠበቅ።  ሸይጣንን እናሸንፍ! አላህ ከጥፋት ይጠብቀን.. አሚን!! አኹኩም ፊላህ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ http://t.me/abujunaidposts

በሚዳሰሱ ሞዴሎች ሐጅና ኡምራን ማስተማር እንዴት ይታያል? ከቅርብ አመታት ወዲህ የሐጅ አፈፃፀም ስርአትን ለህፃናት በማስተማር አላማ የሚዘጋጁ ፕሮግራሞች ተበራክተዋል። የአዘጋጆቹ ሀሳብ መልካም ቢሆንም በሸሪዓ እንዴት ይታያል የሚለውን ማጥናት ተገቢ ይሆናል። ከዚህ አንፃር የፕሮግራሞቹ አዘጋጆች ጉዳዩን ትኩረት ሰጥተው እንዲያጤኑት ጥሪዬን አቀርባለው። ይህ የማስተማሪያ ዘዴ በተለያዩ ሀገራት የተተገበረ በመሆኑ ብይኑን በተመለከተ ኡለማዎች ትኩረት ሰጥተው ውይይትና ምክክር አድርገውበታል። ምንም እንኳ አላማውን በመመልከት ይቻላል ያሉ አንዳንድ ኡለማዎች ቢኖሩም አብዛኞቹ ኡለማዎች እና የፈትዋና የምርምር ተቋማት ግን እንደማይፈቀድና ተገቢም እንዳልሆነ ገልፀዋል። የዓለም የፊቅህ ሊቃውንት ምክር ቤት (መጅመዕ አልፊቅህ አልኢስላሚ) በሒጅራ አቆጣጠር ከሻዕባን 5/1412 እ.ኤ.አ በ 8/2/1992 ጀምሮ ባደረገው አስራ ሶስተኛ መደበኛ ጉባኤው የካዕባ ሞዴል በመስራት ልጆችን ማስተማርን በተመለከተ ተወያይቶ ባሳለፈው ውሳኔ (ይህ ተግባር ክልክል ወደሆኑ ክፉ ነገሮች ሊያዳርስ ስለሚችል መከልከልና በር መዝጋት ዋጂብ መሆኑን) አፅንቷል። [ቀራራት አልመጅመዕ ገፅ 285] እንደዚሁ የሳውዲ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴም (ካዕባ፣ መቃሙ ኢብራሂም፣ ጀመራት እና መሰል ቦታዎችን በሚዳሰስ ሞዴል በመስራት የሐጅና ዑምራ ክንዋኔዎችን ማስተማር አየፈቀድም) ካሉ በኋላ ምክንያቶችን ሲጠቅሱ፤ ሞዴሎቹን ማላቅ ወይም ማዋረድን የመሳሰሉ መጥፎ ውጤቶችን ሊያስከትል ይችላል ብለዋል። ገላጭ የሆኑ ፅሁፎችን በማብራራት ለሰፊው ህዝብ በቂ በሆነ መልኩ ማስተማር ስለሚቻል ሞዴል መስራት አስፈላጊ እንዳልሆነ ተናግረዋል። [ፈታዋለጅናህ 14/11] ታላቁ አሊም ሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚንም በዚህ መልኩ ማስተማር የማይገባና የማይፈቀድ እንደሆነ በመግለፅ በምትኩ ቦርድ ላይ የካዕባን ስእል በመሳል ጠዋፍ እንደሚደረግ ማስተማር እንደሚቻል ተናግረዋል። በሞዴል ማሳየት በቀልብ ውስጥ ለኢባዳው ያለንን ቦታ በማሳጣት እንቅስቃሴ ብቻ ያደርገዋል ብለዋል። [መጅሙዕ ፈታዋ ቅፅ 24 ገፅ 91] በሞዴል ማስተማር ይቻላል ያሉ አንዳንድ ኡለማዎችም ቢሆን የዚህ አይነቱ ትምህርት በኢስላማዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር (ዊዛራ) ክትትል ሊፈፀም እንደሚገባ ከመጠቆማቸው ጋር ሞዴሎቹ እውነተኛውን የካዕባና የሐጅ ክንውን ቦታዎችን በጣም የማስመሰል ስራ እንዳይሰራ ከልክለዋል። እንደውም ሞዴሎቹ ትንንሽ ሆነው በአካባቢውና በያንዳንዱ ሞዴል ላይ መማሪያ መሆኑ እንዲገለፅበት፣ እንደ ኢባዳ ሳይሆን እንደ ትምህርት መማሪያ ብቻ መሆኑ ተደጋግሞ እንዲነገርና የሞዴሎቹን ክብር ከመንካት መጠንቀቅና ሌሎች መስፈርቶችን አስቀምጠዋል። የእነዚህ ፕሮግራሞች አላማ የኢባዳው ፍቅር በልጆች ልቦና እንዲያድር ማድረግ እንጂ በዚህ እድሜ የሐጅ አፈፃፀም ህግጋትን የማወቃቸው አስፈላጊነት ጎልቶ አይመስለኝም። የሚዳሰሱ ሞዴሎችን በመገንባት ማስተማር የኡለማዎችን ትችት ያስተናገደና ቢያንስ በሸሪዓ ስለመፈቀዱ አጠራጣሪ የሆነ የማስተማሪያ መንገድ ነው። የሚያጠራጥርን ነገር በመተው ታዘናልና አዘጋጆች ሌሎች የማስተማሪያ መንገዶችን ቢጠቀሙ የተሻለ ይሆናል። ለምሳሌ ዘመናዊው ቴክኖሎጂ ባመጣቸው እንደ 3D፣ ፓወር ፖይንትና እና ሞሽን ግራፊክስ በመጠቀም ማስተማር ይቻላል። ከዚህም በተሻለ በተቀረፀ እውነተኛ የሐጅ አፈፃፀም ቪድዮ ማስተማር ቀላል ነው። ወላሁ አዕለም {إِنۡ أُرِیدُ إِلَّا ٱلۡإِصۡلَـٰحَ مَا ٱسۡتَطَعۡتُۚ وَمَا تَوۡفِیقِیۤ إِلَّا بِٱللَّهِۚ عَلَیۡهِ تَوَكَّلۡتُ وَإِلَیۡهِ أُنِیب} በተቻለኝ ያክል ማበጀትን እንጂ አልሻም። (ለደግ ሥራ) መገጠሜም በአላህ እንጂ በሌላ አይደለም፡፡ በእርሱ ላይ ተመካሁ፡፡ ወደ እርሱም እመለሳለሁ» አላቸው፡፡ [Surah Hûd: 88] ሐምሌ 3/2014 አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ http://T.me/abujunaidposts

ውድ የኢስላም ወንድም እህቶቼ፤ እንኳን ለኢድ አልአድሓ በአል በሰላም አደረሳችሁ መጪው ዘመን ለሁላችንም የኢማን የእድገትና የስኬት እንዲሆንልን አላህን እንለምነዋለሁ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال وأعاده الله علينا ونحن في عز وكرامة وسعادة أخوكم في الله أبو جنيد صالح أحمد T.me/abujunaidposts

‎⁨من_جوامع_دعاء_النبي_بطاقة⁩_pdf_pdf.pdf6.93 MB

የቲጃኒዮች ሸይኽ ይናገራል [የውመል ቂያማ ከሸኽ (አህመድ) አቲጃኒ በኋላ ያለ የትኛውም ወሊይ ጀነት ቀድሞኝ እንዲገባ አልፈቅድለትም! እንደዚሁ የትኛውም ወሊይ ተማሪዎቹን ከኔ ተማሪዎች በፊት ጀነት እንዲያስገባ አልፈቅድለትም!!] #ከራማት #ሱፍያ #ዱስቱር #ቲጃኒያ https://youtu.be/XWuL4HrZzXo @abujunaidposts

ስለ ሪፋዒይ የሚነገር ታላቅ ቅጥፈት! የአህባሹ ሸኽ ጀሚል ሀሊም ከአብዱላሂ አልሀረሪ እንደተማረው ስለ ሪፋዒያ ኹራፋት ሲዘክር እንዲህ በማለት ይቀጥፋል። አህመድ አሪፋዒ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰልም) ቀብር ዘንድ ሄዶ (አሰላሙአለይኩም) ብሎ ሰላምታ በማቅረብ በግጥም እጃቸውን እንዲዘረጉለት ሲጠይቃቸው። ከቀብሩ (ውአለይኩሙሰላም ልጄ ሆይ! በማለት ከመለሱለት በኃላ ቀብራቸው ተሰንጥቆ እጃቸውን አወጡና ሪፋኢይ በተሰበሰቡት ሰዎች ፊት እጃቸውን ሳመ) ይለናል። ይህ አይን ያወጣ ውሸት መሆኑ አያጠያይቅም። በቅድሚያ ታሪኩ ለመከሰቱ የሸይኹ አድናቂዎች ከሚቀባበሉት ወሬ ባለፈ የሚቀርብ ምንም አይነት መረጃ የላቸውም። ይህ ደግሞ ታላቅ ክስተት እንደመሆኑ እውነት ቢሆን ኡለማዎችና የታሪክ ሰዎች ባላለፉት ነበር። ሌላው አላህ ሰዎች ከሞቱ በኀላ እስከ ትንሳኤ ድረስ በነሱና በዱንያ ሰዎች መካከል ግርዶሽ አድርጓል። አላህ እንዲህ ይላል፦ { حَتَّىٰۤ إِذَا جَاۤءَ أَحَدَهُمُ ٱلۡمَوۡتُ قَالَ رَبِّ ٱرۡجِعُونِ * لَعَلِّیۤ أَعۡمَلُ صَـٰلِحࣰا فِیمَا تَرَكۡتُۚ كَلَّاۤۚ إِنَّهَا كَلِمَةٌ هُوَ قَاۤىِٕلُهَاۖ وَمِن وَرَاۤىِٕهِم بَرۡزَخٌ إِلَىٰ یَوۡمِ یُبۡعَثُونَ } አንዳቸውንም ሞት በመጣበት ጊዜ እንዲህ ይላል «ጌታዬ ሆይ! (ወደ ምድረ ዓለም) መልሱኝ፡፡ «በተውኩት ነገር በጎን ሥራ ልሠራ እከጅላለሁና፡፡» (ይህን ከማለት) ይከልከል፡፡ እርስዋ እርሱ ተናጋሪዋ የኾነች ከንቱ ቃል ናት፡፡ ከስተፊታቸውም እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ ግርዶሽ አልለ፡፡ [አልሙእሚኑን: 99-100] ይህ ባይሆን ኖሮ በሰሐቦች ዘመን መልእክተኛው ተነስተው ቢያናግሯቸው የሚያስመኝ ብዙ ፈተናዎች ሲከሰቱ ባስነሳቸው ነበር። አህመድ አሪፋዒ የኖረው በሂጅራ አቆጣጠር (512–578) ነበር። ይህ ቢከሰት ኖሮ ከሱ በፊት በድንቁ የሰለፎች ዘመን የኖሩት ሰሀቦች፣ ታቢኢዮችና ሷሊሆች ለዚህ የተገቡ ነበሩ። ከዚህም አልፎ በሞቱ ግዜ ሰሀቦች ዱንያ ስትጨልምባቸው ያፅናኗቸው ነበር። ግን ይህ አልሆነም! ታላቁ አሊም ሸይኽ ኢብኑ ባዝ ስለዚህ ቅጥፈት ተጠይቀው የመለሱትን ብንመለከት፦ ይህ ምንም እውነትነት የሌለው ባጢል። አላህ እንደነገረን መልእክተኛው (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አላህ በፃፈባቸውን ሞት አልፈዋል። { إِنَّكَ مَیِّتࣱ وَإِنَّهُم مَّیِّتُونَ } (አንተ ሟች ነህ፤ እነርሱም ሟቾች ናቸው) አዝ’ዙመር: 30 በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱ መላእክት የኡመቶቻቸውን ሰላምታ እንደሚያደርሷቸው፣ ሰዎች ሰለዋት በሳቸው ላይ ሲያደርጉም እንደሚያደርሷቸውና እንደሚመልሱም ተናግረዋል። በዚህ ዙርያ ብዙ ሀዲሶች ተዘግበዋል ሆኖም እጅ ዘርግተው ሰዎችን ይጨብጣሉ የሚል መረጃ ግን የለም። ይህ ክስተት ሀሰት ለመሆኑ ይህ በቂ መረጃ ነው። ሆኖም ተከስቷል ቢባል እንኳ ሸይጧን ተመሳስሎበት እሱንና ተከታዮቹን እያጭበረበራቸው ነውና አላህን እንድንፈራና ዲናችንን ምንጩ በመረጃ እንድንከተል አደራ ብለዋል። ምንጭ፦ አል መጅሙዕ 9/310 አህባሾች የሚሰብኩትን የጥመት ጦሪቃ #ሪፋዒያ ሰባኪዎች እንደ አንዳንድ የሂንዱ እና የኢቫንጀሊዝም ሰባኪዎች በድግምትና ከጅኖች ጋር በመመሳጠር ተአምር ፈፀምን ይላሉ። እራስን በስለት የመውጋትና እሳት የመንካት ከራማ አለን በማለት ይመፃደቀሉ። ይህ ፍፁም የሷሊሆች መንገድ አይደለም!! አላህ ከጥመት ይጠብቀን አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ @abujunaidposts ___ * ሸይኽ ኡሰይሚን ስለ ሪፋዒያ ጦሪቃ https://youtu.be/68EhI_vDE-I * The Rifaa’is who stab themselves with knives but are not affected by it https://islamqa.info/en/answers/9338/the-rifaais-who-stab-themselves-with-knives-but-are-not-affected-by-it * بطلان تقبيل الرفاعي يدى النبي صلى الله عليه وسلم https://youtu.be/hSEoUm_FgG0 #ከራማት #ዱስቱር #ሱፊያ #ሪፋዒያ #አህባሽ #አሻዒራ

ስለ ዓረፋ ቀን ዱዓእ ሁለት ነጥቦች [1] በኢድ ዋዜማው የዓረፋ እለት ዱዓእ ተቀባይነት እንዳለው የሚዘክሩ ሀዲሶች ሀጅ ላይ የሌሉ ሰዎችንም ይመለከታሉን?? የአላህ መልእክተኛ «ከዱዓዎች ሁሉ በላጩ (የኢድ ዋዜማ) የአረፋ ቀን ዱዓ ነው...» ማለታቸውን ቲርሚዚይ ከአብዱላህ ኢብኑ ኡመር የዘገቡ ሲሆን፤ ሌሎች ተመሳይ ይዘት ያላቸው ሀዲሶችም ይገኛሉ። ታዲያ የዓረፋን እለት በዱአዕና በዚክር ያሳለፈ ሰው ታላቅ ክብርና ምንዳን የሚያገኘው ሀጅ ላይ ሲሆን ብቻ ነውን? በእርግጥ በዚህ እለት ክብር ባለው የዓረፋ ምድር የተገኘ ሰው የጊዜንም የቦታንም ክብር ተጎናፅፏልና በተሻለ ሁኔታ ላይ መገኘቱ እንዲሁም ዱአው ተቀባይነት ለማግኘት የቀረበ መሆኑ አያጠራጥርም። ይሁንና ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት፤ እነዚህ ከአረፋ እለት ክብር ጋር ተያይዞ የዱአ ተቀባይነትን የተመለከቱ ሀዲሶች በማንኛውም ቦታ የሚገኙ ሙስሊሞችን ይመለከታሉ። በመሆኑም በሀጅ ስራ ላይ የሌሉ ሰዎችም በዱዓ ሊበረቱ ይገባል። ታላቁ አሊም ሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን በዚህ እለት የሚባሉ በሀዲስ የተላለፉ ዱአዎችን አስመልክቶ ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎች መሆኑን ተጠይቀው ተከተዩን መልሰዋል¹ «በምላሻችን እንደገለፅነው፤ ይህ ለሁጃጆችንም ይሁን ሌሎችን የተመለከተ ጥቅል መልእክት ነው። ነገር ግን ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎች ይበልጥ የተገባ ነው። ምክኒያቱም ሁጃጆች በዚህ እለት በዓረፋ ምድር በኢህራም ውስጥ ስለሚገኙ ከሌሎች በበለጠ ዱዓቸው ተቀባይነት ለማግኘት የቀረበ ነው። ስለዚህም የዓረፋን እለት በሀጅ ተግባር ላይ የሌሉ ሰዎች እንዲፆሙት ተደንግጓል። እለቱ ብልጫ ያለወወ ስለሆነም አላህን በማስታወስ፣ ማርታን በመለመን እና ዱዓ በማድረግ ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ፤ ሁጃጆችንም በኢባዳ ይካፈሏቸዋል ማለት ነው።» ከሸይኹ ድረገፅ የተወሰደ የድምፅ ፈትዋ [2] በዓረፋ እለት ሁጃጆች በአረፋ ምድር እንደሚሰባሰቡት ለዱዓና ለዚክር መሰባሰብ "ታዕሪፍ"ን በተመለከተ፤ ይህ ተግባር አንዳንድ ሰለፎች እንደፈፀሙት የተረጋገጠ ነው። ከነሱም መካከል ኢብኑ አባስ ይገኙበታል፤ ኢማሙ አህመድም ባይተገብሩትም እንደሚቻል ተናግረዋል። ነገር ግን ያወገዙትና ከቢድአ የመደቡትም አሉ። የኡለማዎቻችንን ማብራሪያዎች ስንፈትሽ ተከታዮቹ ድምዳሜዎች ላይ ያደርሱናል፤ 1) "ታእሪፍ"ን መተግበር በራሱ ችግር የለውም። ተግባሩን እንደሱና ወይም ሙስተሀብ ነገር መውሰድ ግን አይገባም። ጉዳዩ የኢጅቲሀድ መስአላ ነውና ተግባሩ የሚወገዝ ተግባር አይሆንም። የፈፀመውም ሰው ቢድአ ሰራ አይባልም። 2) ታእሪፍ ስንል ከምድረ አረፋ ውጭ ባሉ የየሀገሩና የየከማው መስጂዶች መሰባሰብን የተመለከተ እነጂ ለዚህ ብሎ ጉዞ ማድረግ አይፈቀድም። አላህ የአረፋን ምድር ለዚህ ቀን ኢባዳ መሰባሰቢያ እንደመረጠው በየሀገሩ አንዳንድ ቦታዎችን፣ መስጅዶችንና ቀብሮችን በመምረጥ ወደነሱ ጉዞ አድርጎ መሰባሰብ በፍፁም አይፈቀድም። ይህ የነብዩ መስጂድንም ይሁን በይተልመቅዲስን ያካትታል። 3) ይህ መሰባሰብ ጩኸትና ሱና ያልሆኑ የጋራ አምልኮዎች ከታከሉበት ቢድአ እንደሚሆን አያጠራጥርም። በተመሳሳይ መልኩ ኢባዳ ያልሆኑ ግጥሞችና መንዙማዎችን ለዚህ መለያ ማድረግ ጥፋት ነው። እነዚህን ነጥቦች በዝርዝር ለመረዳት የሚያስችሉ ማብራሪያዎችን ከኡለማዎች ድርሳናት እንደሚከተለው እናያለን። ቀሪዉን የፅሁፍ ክፍል ተከታዩን ሊንክ በመከተል ያንብቡት https://www.facebook.com/682494683/posts/10158937378539684/ t.me/abujunaidposts @abujunaidposts

🍂 አህባሾች ያስተውሉ..! ታላቁ የሀዲስ ዘጋቢ ቲርሚዚይ በሀዲስ ጥንቅራቸው ኪታቡዘካት ሀዲስ ቁ .662 ስለ አላህ ሲፋት አህሉሱና እና ጃህሚያዎች ያላቸውን አቋም በግልፅ አስፍረዋል! ፍልስፍና ሳይ
🍂 አህባሾች ያስተውሉ..! ታላቁ የሀዲስ ዘጋቢ ቲርሚዚይ በሀዲስ ጥንቅራቸው ኪታቡዘካት ሀዲስ ቁ .662 ስለ አላህ ሲፋት አህሉሱና እና ጃህሚያዎች ያላቸውን አቋም በግልፅ አስፍረዋል! ፍልስፍና ሳይሆን ሸሪአዊ መረጃዎችን መከተል መታደል ነው። አላህ ማስተዋልን ይለግሳችሁ!! @abujunaidposts

በዙልሒጃ ቀናት አላህን ማውሳትና ማላቅ በነዚህ ቀናት አላህን ማመስገን፤ (አልሀምዱሊላህ)፣ ተክቢር፣ ተስቢህ (ሱብሀነላህ) እና ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢለላህ) በማለት በማለት የአላህን ስም ከፍ ማድረግ
በዙልሒጃ ቀናት አላህን ማውሳትና ማላቅ በነዚህ ቀናት አላህን ማመስገን፤ (አልሀምዱሊላህ)፣ ተክቢር፣ ተስቢህ (ሱብሀነላህ) እና ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢለላህ) በማለት በማለት የአላህን ስም ከፍ ማድረግ ይወደዳል። عن عبد االله بن عمر رضي االله عنهما عن النبي صلى االله عليه وسلم قال : "ما من أيام أعظم عند االله ولا أحب إليه العمل فيهن من هذه الأيام العشر فأكثروا فيهن من التهليل والتكبير والتحميد" أخرجه احمد ዓብዱላህ ኢብኑ ዑመር ባስተላለፉት ሀዲስ ነብዩ እንዲህ ብለዋል፤ «ከእነዚህ አስር ቀናት በበለጠ አላህ ዘንድ ታላቅ የሆኑና መልካም ስራ ምን እጅግ የተወደደባቸው ቀናት የሉም፤ ስለዚህ ተህሊል ተክቢር እና ተህሚድ አብዙ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል ከተክቢር አደራረግ መካከል الله أكبر ، االله أكبر لا إله إلا االله ، واالله أكبر والله الحمد “አላሁ አክበር፤ አላሁ አክበር፤ ላ ኢላሀ ኢለላህ ወላሁ አክበር ወሊላሂልሀምድ" የሚለው ዋነኛው ሲሆን ሌሎች አባባሎችም አሉ በእነዚህ ቀናት ውስጥ ሊደረግ የሚገባው ይህ ተክቢር ብዙ ሰዎች ስለማይፈጽሙት እየተረሱ ካሉ ሱናዎች መካከል ነው። ሰዎችን ለማስታወስ እና ሱናን ህያው ለማድረግ ድምጽን ከፍ አድርጎ ተክቢር ማድረግ ይቻላል። አብዱላህ ኢብኑ ኡመር እና አቡሁረይራህ በነዚህ አስር ቀናት ገበያ ወጥተው ተክቢራ ሲያደርጉ ሰዎችም እያስታወሱ ተክቢራ ያደርጉ እንደነበር ተዘግቧል። ሆኖም ሁሉም ሰው የራሱን ዚክር ያደርጋል ማለት እንጂ ሰዎች እየተሰባሰቡ በአንድ ድምጽ ተክቢራ ያድርጉ ማለት አይደለም አላህ መልካም ስራን ያግራልን፣ ከሚቀበላቸው ባሮቹ ያድርገን። አሚን! @abujunaidposts

🔖 ተውሒድ እና የሐጅ ፍሬዎች 🎙 አቡጁነይድ እና ጣሀ አህመድ በ 2002 በጃሊያ አዳራሽ የቀረበ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/219 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

የዙልሒጃ ወር ነገ ሐሙስ ሰኔ 23/2014 / June 30/2022 አንድ ብሎ ይጀምራል ጃቢር ኢብኑ ዓብዲላህ ባስተላለፉት ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል «ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው፤ አስርቱ ቀናት ናቸው። ማለትም አስሩ የዙልሂጃ ቀናት» አልባኒ ሰሂሁል ጃሚዕ 1133 ላይ አስፍረውታል ከነገ ጀምሮ ያሉትን ተከታታይ ቀናት በኢባዳ እናሳልፋቸው! @abujunaidposts