ru
Feedback
🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

Открыть в Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

Больше
2 213
Подписчики
-224 часа
-67 дноК
-3430 день
Архив постов
🍂||• ጣፋጭ ቲላዋ •||🍂 ቃሪእ ኢብራሂም ዓሲሪ 📖 [የአደም ልጆች ሆይ! ሰይጣንን አትገዙ፤ እርሱ ለእናንተ ግልጽ ጠላት ነውና በማለት ወደእናንተ አላዘዝኩምን? ] ያሲን 60 #تلاوات_لا_أنساها @abujunaidposts

ብዙዎች ከመሬት ግዢ እስከ ግንባታ አሻራቸውን አኑረው እዚህ ያደረሱትን መርከዝ በጋራ እንጨርሰው! በንግድ ባንክ ለመርዳት 444 አጭር ቁጥር አካውንታችን ነው። በኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር 18
+1
ብዙዎች ከመሬት ግዢ እስከ ግንባታ አሻራቸውን አኑረው እዚህ ያደረሱትን መርከዝ በጋራ እንጨርሰው! በንግድ ባንክ ለመርዳት 444 አጭር ቁጥር አካውንታችን ነው። በኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር 18 አደባባይ አካባቢ ተገንብቶ ለረጅም ግዜ አገልግሎት የሰጠውን መርከዝ የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጥ የግንባታ ማስፋፊያና ማሻሻያ በማድረግ ላይ እንገኛለን። በአላህ ፈቃድ ሲጠናቀቅ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን ይሰጣል። መስጂድ፣ ላይብረሪ፣ የወንዶች ኮሌጅ ከነማደሪያው፣ የሴቶች ኮሌጅ፣ የሒፍዝ ማእከል፣ የነሲሓ ቲቪ ስቱድዮና ቢሮዎችን ያካትታል። ተባብረን እናሳካው! መርከዙ የለበትን ሁኔታ ለመጎብኘትና ለበለጠ መረጃ +251972757575 Ibnu Masoud islamic center በንግድ ባንክ ለመርዳት 444 አጭር ቁጥር አካውንታችን ነው። —————— @merkezuna

የመልካም ስራ ጥሪ ቀርቧል በኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር 18 አደባባይ አካባቢ ተገንብቶ ለረጅም ግዜ አገልግሎት የሰጠውን መርከዝ የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጥ የግንባታ ማስፋፊያና ማሻሻያ በማድረግ ላይ እንገኛለን። በአላህ ፈቃድ ሲጠናቀቅ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን ይሰጣል። መስጂድ፣ ላይብረሪ፣ የወንዶች ኮሌጅ ከነማደሪያው፣ የሴቶች ኮሌጅ፣ የሒፍዝ ማእከል፣ የነሲሓ ቲቪ ስቱድዮና ቢሮዎችን ያካትታል። ተባብረን እናሳካው! በንግድ ባንክ ለመርዳት 444 አጭር ቁጥር አካውንታችን ነው። መርከዙ የለበትን ሁኔታ ለመጎብኘትና ለበለጠ መረጃ +251972757575 Ibnu Masoud islamic center @merkezuna

🗞 ጥቂት የጥቢ ዝምድና (ረዷዕ) ህግጋት ✍ ዝግጅት፦ አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 የፅሁፉ ሊንክ https://t.me/abujunaidposts/433 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

ረዷዕ_የጥቢ_ዝምድና_ህግጋት.pdf4.90 KB

📃 ስለ ኢስላም አጭር ማብራሪያ 🎤 የድምፅ ንበብ፦ መህዲ ሙሰማ ✍ ዝግጅት፦ አል ጃሚዓ አል ኢስላሚያ ✍ ትርጉም፦ አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ (1427 ዓ.ሒ) 🔗 የፅሁፉ ሊንክ https://d1.islamhouse.com/data/am/ih_articles/single/am_Brief_Presentation_of_Islam.pdf 🔗 Audio Share Link https://t.me/abujunaidposts/121 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

ዛሬ በተፈረመው የሰላም ስምምነት የተሰማኝን ከፍተኛ ደስታ እገልፃለው። አልሐምዱሊላህ! ስምምነቱ በፍጥነት ተግባራዊ ሆኖ በሰሜን ኢትዮጵያ የሰላም አየር መተንፈስ እንደሚጀመር፣ ባለፉት ሁለት አመታት የተጠፋፉ ቤተሰቦችና ወዳጆችም እንደሚገናኙ ተስፋ አደርጋለው። አላህ በጦርነቱ የሞቱ ዘመድ ወዳጆቻችንን በእዝነቱ ይማራቸው። ሌሎች ክልሎችንም ሰላም ያድርግልን። አሚን @abujunaidposts

ከሶስቱ መስጂዶች ውጭ መንፈሳዊ ጉዞዎችን ማድረግ በሸሪዓ ይፈቀዳልን? ክፍል 2/2 (ማደናገሪያዎች እና ምላሾቻቸው) ባለፈው ክፍል ከሶስቱ መስጂዶች ውጭ የሚደረጉ (መንፈሳዊ) ጉዞዎችን ክልክልነት የሚገልፀውን ሀዲስ እና ተያያዠ መረጃዎችን ቃኝተናል። በዚህ ክፍል ደግሞ በተቃራኒ ወገኖች ለሚቀርቡ ማደናገሪያዎች ምላሽ አቀርባለው። 1) áŠĽáŠá‹šáˆ…áŠ• ጉዞዎች በቀብር ዚያራ በማስታከክ ህጋዊነትን ለማላበስ፤ ‹‹ቀብርን መጐብኘት ከልክያችሁ ነበር አሁን ግን ጐብኙ›› የሚለውን የነብያችን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሐዲስ ይጠቅሳሉ።  áˆáˆ‹áˆ˝:–  ነብያችን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ቀብር ዘይረዋል፣ ዘይሩ ብለውም አዘዋል። የዚያራው ዋነኛ አላማ አኼራን ማስታወስ እንደሆነም ተናግረዋል። እሳቸውም ሆኑ ሶሐቦቻቸው ቀብር ለመዘየር ብለው ጉዞ አልወጡም ሌሎች እንዲጓዙም አልፈቀዱም። በመመርመር ላይ ያለነው ግን በአካባቢያችን የሚገኙ ቀብሮችን ስለመዘየር ሳይሆን በቀብር ዚያራ አላማ ከሚኖሩበት ከተማ ወይም ሀገር ወደ ሌላ ቦታ ጉዞ ማድረግን ነው። ቀብር ዚያራ ለማድረግ የሚፈልግ በአካባቢው ወደሚገኝ መቃብር መሄድ እንጂ ጉዞ በሚያስወጣ ርቀት የሚገኝ ቀብርን ለመዘየር ጓዝ አስሮ መነሳት ክልክል መሆኑ ያሳለፍነው ሐዲስ ግልፅ መረጃ ነው። 2) ነቢዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) የኡሁድ ሸሂዶችን ቀብር ለመዘየር መውጣታቸውን እንደማስረጃ በመጥቀስ ጉዞ ወጥቶ ቀብር ዚያራ እንደሚቻል የሚሞግቱም አሉ።   ምላሽ፦ ኡሁድ ባሁኑ የከተማው ሁኔታ በመዲና ከተማ ለነብዩ መስጂድ ቅርብ ከሚባሉ ቦታዎች አንዱ ሲሆን ቀድሞ በነበረው የከተማዋ ሁኔታም ቢሆን እንደ ሌላ ከተማ የሚታይና ጉዞ የሚባል ርቀት ላይ የሚገኝ አለመሆኑ ግልፅ ነው። 3)  áŠá‰˘á‹Š (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) የእናታቸውን ቀብር መዘየራቸውን በመጥቀስ ለቀብር ዚያራ ሲባል ርቀት ጉዞ መሄድ እንደሚቻል ይሞግታሉ።  ምላሽ፦ ነቢዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) የእናታቸውን ቀብር የዘየሩት መካን ለመክፈት በተጓዙት ዘመቻ ላይ እግረ መንገዳቸውን እንጂ በዚያራ አላማ ስንቅ ሰንቀውና ጓዝ ሸክፈው ተጉዘው አልነበረም። 4)  áŠ áŠ•á‹łáŠ•á‹śá‰˝ አቡ ሑረይራ ከልካይ ሀዲሶችን ከማወቃቸው ጋር ጡር ወደተባለው ተራራ መሄዳቸው እንደሚፈቀድ ያሳይል ይላሉ። ምላሽ፦ ሀቅን ለመደበቅ ሆን ብለው ካልሞከሩ በቀር፤ አል ኢማም ማሊክ እና አስሀቡሱነን በዘገቡት እና ይህ ክስተት በተወሳበት ሀዲስ ላይ አቡሁረይራ ከጉዞ ሲመለሹ ያገኛቸው አቡ በስራ አልጊፋሪይ ከሶስቱ መስጂዶች ውጭ ወደ ሌላ ስፍራ ለኢባዳ ጉዞ ማድረግ እንደማይፈቀድ መረጃ በመጥቀስ፤ "ከመሄድህ በፊት ባገኝህ ኖሮ (ጉዞ) አትወጣም ነበር] á‰Ľáˆˆá‹ ስራቸው ተገቢ እንዳልነበረ አስታውሰዋቸዋል። አቡሁረይራም ተቀበሉ እንጂ አልሞገቱም!! 5)  á‹¨áˆ€á‹˛áˆą ክልከላ የሚመለከተው ወደ መስጂዶች የሚደረግን ጉዞ እንጂ ቀብሮች እና የዚያራ ቦታዎችን አይመለከትም ይላሉ። ምላሽ፦ የሀዲሱ ክልከላ መስጂዶች ቢልም ከላይ የተጠቀሰው ሀዲስ፤ የነብያት እና ሷሊሆች ቀብር እንዲሁም ታዋቂ እና ታሪካዊ ቦታዎችንም ክልከላው እንደሚመለከት የአቡ በስራ ግንዛቤ እና የአቡሁረይራ መስማማት ግልፅ መረጃ ነው።  ኢብኑ ተይሚያህ ረሂመሁላህ እንዲህ ብለዋል፤ “ይህ ክልከላ ወደ መስጂዶችም ሆነ ወደ አላህ ለመቃረብ በሚፈፀም ማንኛውም ጉዞ ግብ የሚደረጉ ቦታዎችን ይመለከታል።” ካሉ በኃላ  በአቡ በስራ እና በአቡ ሁረይራ መካከል የተከሰተውን ክስተት ጠቅሰው እንዲህ አሉ። “ጡር እና መሰል አንቢያዎችን ያስተናገዱ ቦታዎች በዚህ ሀዲስ ክልከላ ውስጥ እንደሚገቡ ሀዲሱን ያስተላለፈው ይህ ሰሐቢይ ተገንዝቧል… ይህ ታሪካዊ ቦታዎችን ከተመለከተ የአምልኮ ቤቶችም በዋናነት ክልከላው ይመለከታቸዋል።” ኢቅቲዷኡ ሲራጥ ቅፅ 2 ገፅ 645 6)  á‰ áˆ€á‹˛áˆą ላይ በተፈቀደው መሰረት የነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) መስጂድ ስንሄድ ከጎን የሚገኘው ቀብራቸው ጋር ሄደን እንዘይራለን። ይህ ቀብሮችን ለመዘየር በማሰብ መጓዝ እንደሚቻል መረጃ ነው በማለትም ይሞግታሉ።  ምላሽ፦ የነብዩን መስጂድ ለመዘየር የሄደ ሰው በዛው ወደ ነቢዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ቀብር ሄዶ መዘየር ይችላል። ሆኖም የሳቸው ንግግር እንደሚያመለክተው ጉዞ ማድረግ ያለብን ወደ ሶስቱ መስጆዶች ብቻ ነው። በጉዞዬ ቀብራቸውን መዘየር እንጂ መስጂዳቸውን  መዘየርን አላማ አላደረኩም በማለት መጓዝ  የሳቸውን ክልከላ መጣስ ነው። በዚሁ አጋጣሚ ልብ ልንል የሚገባው፤ ቀብርን መዘየር ሙስተሐብ ሲሆን የሳቸውን ቀብር መዘየር ደግሞ ታላቅ መልካም ነገር ነው።  የርሳቸውም ቀብር ከዚህ እንደሚካተት ግልጽ ነው፡፡ ሆኖም ከእርሳቸው ቀብር ጋር ተያይዘው የሚነገሩት ሐዲሶች ዶኢፍ ወይም ጭራሹኑ የተቀጠፉ መውዱእ ናቸው። በመጨረሻም፤ ይህ ድንጋጌ አላማው ተውሒድን ከሰርጎ ገብ አመለካከት መጠበቅ ነው። ጉዞ የሚደረግባቸውን ብዙ ቀብሮች ብንመለከት ከጉብኝት እና ጉዞ ጋር በተያያዘ ብዙ የአቂዳ ግድፈቶችን እናስተውላለን። ለዚህም ውቅሮ ከሚገኘው የነጃሺ ቀብር በምሳሌነት መመልከት ይቻላል። በቀብሮች ላይ መስጊድን መገንባት ፍፁም የተከለከለ መሆኑ ግልፅ ነው። ምንም እንኳ ታላቁን ነጃሺ ቢን አስሀማ (ረሂመሁላህ) የምናከብርና የምንወድ ብንሆንም ከሱ ፍቃድና ፍላጎት ውጪ እነዚህ ነቢያዊ ትእዛዛትን በመጣስ በቀብሩ ላይ የሚደረጉት ክልክል ተግባራት ሁሉ እናወግዛለን። ነጃሺን በምሳሌነት ጠቀስን እንጂ በየአካባቢው ይህ አይነቱ ፈተና ይገኛል። በብዙ መሰል ቦታዎች አላዋቂዎች ወደ ቀብር ሄደው ስለት በማስገባት ከጭንቅ እንዲያወጣቸው እና ሀጃቸውን እንዲያወጣላቸው ይለምናሉ። ወደ አላህ ብቻ ሊዘረጉት የሚገባውን እጃቸውን በማንሳት የሚፈልጉት ሁሉ እንዲሰጧቸው ሙታንን ይማፀናሉ። ይህ ግልፅ የጃሂሊያ ተግባር ወደሚፈፀምበት ቦታ የጉዞ ጥሪ ማስተጋባት ፍፁም ስህተት ነው። ቅርስን ለመንከባከብም ይሁን ለሌላ ምክንያት ወደ ቀብሮች የሚደረግ ጉዞ መጤ ተግባር ላይ መሳተፍ ከመሆኑም በላይ፤ የነብዩን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ግልፅ ክልከላ መጣስ ነው። ከከባድ ወንጀል አንስቶ እስከ ቢድዓ እና ሺርክ የሚያደርሱ ጥፋቶችን ሊያስከትል እንደሚችል አውቀናልና መልእክቱን ሁሉም ሊያስተጋባውና ሙስሊሙን ሊያነቃ ይገባል። አላህ ከጅህልና ይጠብቀን! አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ t.me/abujunaidposts

ከሶስቱ መስጂዶች ውጭ መንፈሳዊ ጉዞዎችን ማድረግ በሸሪዓ ይፈቀዳልን? ክፍል 1/2 በሀገራችን እና በብዙ ሀገራት በሚኖሩ የሌላ እምነት ተከታዮች ዘንድ ከተለመዱ ተግባራት አንዱ መንፈሳዊ ጉዞ áŠá‹á˘  ይህ አይነቱ ጉዞ ሰዎች  ቅዱስነቱን ወደሚያምኑበት ስፍራ ወይም ቅዱሳን መሆናቸው የሚታመንባቸው ሰዎች ወደተቀበሩበት ቦታ የሚደረግ ሲሆን፤  ከየሄዱበት ስፍራ በረከትንና ፈውስን የመሳሰሉ ጥቅሞችን ይከጅላሉ። መነሻው በጥቂት አስተባባሪዎች እና ተሳታፊዎች ቅንጅት ይከወን የነበረ ቢሆንም ቀስ በቀስ ነጋዴዎች ስርአት እያስያዙትና የጉዞ ማህበራት በማቋቋም እያደራጁት ሄደዋል። ይህንን ተሞክሮ ወደ ሙስሊሙ በማምጣት የታላላቅ ሰዎችን ቅዱስነት እና ወልይነት አጉልቶ መስበክ፣ ወደቀብራቸውም ጉዞ ማድረግ፣ የተለያዪ ፕሮግራሞችን በቀብራቸው ዙርያ ማዘጋጀት በተደራጀ መልኩ ቀጥሏል።  ከዚህ ቀደም ባልተደራጀ መልኩ ጉዞዎችን የሚያስተናግዱ እንደ ነጃሺ፣ አናጂና፣ አብሬት፣ ቃጥባሬ እና መሰል ቦታዎች አሁን አሁን ሌሎች ጋር የተለመደውን የጉዞ አደረጃጀት በመከተል መጠናከረቸውን የሚያሳዩ ማስታወቂያዎችና እና እንቅስቃሴዎች በመስጂዶቻችን ላይ በስፋት እየታዩ ነው። ባእድ አምልኮ የሚፈፀምባቸውን የቀብር ስፍራዎች፤ ቅርስን በመንከባከብ እና ባህላዊ እሴቶች በመጠበቅ ስም ለማነፅ በከፍተኛ በጀት የሚበጅቱት የአንዳንድ ሀገራት ኤምባሲዎች አላማ ከህዝበ ሙስሊሙ የተደበቀ አይደለም። በሌሎች እምነቶች ተፅእኖ ሾር የወደቁትን የሱፊያ አስተሳሰብ መስመሮች ለሙስሊሙ ህብረተሰቡ በማስተዋወቅ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች መገለጫ አድርገው በማቅረብ ሙስሊሙን እኛ እናውቅልሀለን የሚሉት ወገኖች አላማም አጠያያቂ ነው። ይህ አይነቱ ጉዞ በሸሪአ እንዴት ይታያል የሚለውን ለመቃኘት እንሞክራለን፤ 1)  áŠá‰˘á‹Ťá‰˝áŠ• (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) {ወደ ሶስት ቦታዎች ካልሆነ ጓዝን ጠቅልሎ ጉዞ አይወጣም፤ መስጅድ አልሐረም (መካ) መስጂድ አነበዊ (መዲና) እና መስጂድ አልዓቅሷ} áˆ›áˆˆá‰łá‰¸á‹ በሰሒሕ ቡኻሪ እና ሌሎችም ድርሳናት ተዘግቧል ይህ ሐዲስ እንደሚጠቁመው አምልኮትን ፍለጋ አንድን ቦታ በማላቅ የሚደረግ ጉዞ ወደ ሶስቱ መስጅዶች ካልሆነ ወደ ሌላ ቦታ መሄድን ይከለክላል። ይኸውም ሰዎች አንድን ቦታ በተለየ ቀድሰው በቦታው የሚገኝን ቀብር ወይም ሌላ ነገር በማላቅ ወደ ማምለክ(ሽርክ) እንዳይገቡና ከዲናቸው እንዳይወጡ ለመጠበቅ ሲባል ነው። ከዚህም በመነሳት፤  አንድን ቦታ በማላቅ ወይም ከሌሎች ቦታዎች ይልቅ አምልኮት ተቀባይነት ያገኙበታል በሚል ግምት፤ ከሶስቱ መስጅዶች ውጭ መንፈሳዊ ጉዞ ማድረግ ሀራም ነው። ይህ አላህን በሰላት ዱአ እና መሰል ኢባዳዎች ለማምለክ ከሆነ ነው። ስለት በማስገባት፣ ድረሱልን ወይም አማልዱኝ በማለት  ቅዱሳንን መማፀን ከሆነ ግን ባእድ አምልኮ ነውና  በእጅጉ ከዚህ የከበደ የሽርክ ተግባር ነው።  2) በአምልኮት ተግባራቸው እና ሌሎች  በሚለዩባቸው ባህልና ልማዶች አርአያ አድርጎ መመሳሰል ብሎም መከተል የማይፈቀድ ክልክል ተግባር ነው። ነብያችን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) በአንድ ሐዲስ ... [ከናንተ በፊት የነበሩትን ፈለግ ስንዝር በስንዝር፣ ክንድ በክንድ ትከተላላችሁ፤ የአርጃኖ ጉድጓድ ቢገቡ እንኳ ትከተሏቸዋላችሁ] áŠ áˆ‰á¤ ይህን የሚሰሙት ሶሐቦችም "የአላህ መልእክተኛ ሆይ የየሁዳና ነሳራዎችን (ፈለግ ማለት ነው) ?] á‰Ľáˆˆá‹ ሲጠይቋቸው እሳቸውም ]ታዲያስ?] á‰Ľáˆˆá‹ መለሱላቸው። ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል፡፡  á‹¨áŠ áˆ‹áˆ… መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ [ከህዝቦች የተመሳሰለ እርሱ ከነርሱ ነው] áŠ á‰Ą ዳውድ ዘግበውታል   ቅዱሳንን በማላቅ አላማ የሚካሄዱ ጉዞዎች የሌሎችን  የአምልኮ ተግባራት በመኮረጅ ኢስላማዊ ቅብ መቀባት በመሆኑ መመሳሰል (ተሸቡህ) ነውና አይፈቀድም። በዲናችን አንድን ቦታ በማላቅ ወይም ከፍ በማድረግ ወደዛ ስፍራ ሄዶ አምልኮትን መፈፀም የሚፈቀደው ወደ ሶስቱ መስጅዶች ብቻ ነው። 3) áˆ¸áˆŞá‹“ችን ከተደነገጉት ሶስቱ መስጂዶች ውጭ አንድን ቦታ በማላቅ ወይም አንዳች ጥቅም በመፈለግ የሚደረግ የጀመዓ ጉዞ ነብያችንም ሆኑ ሶሐቦቻቸው በኖሩበት ጊዜ የማይታወቅ የቢድአ ተግባር ነው።  ወደ ተለያዩ ዶሪሆች እና መሳጂዶች የሚደረገው ጉዞ በእስልምናችን የማይታወቅ ነብያችን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ያላዘዙት መጤ የቢድአ ተግባር ነው። ነብያችንም (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሸሪዓችንን በሚገባ አስተምረው እሳቸው ያላዘዙትን ከመፈፀም በብርቱ አስጠንቅቀው አልፈዋል። እናታችን አዒሻ ባስተላለፉት ሐዲስ ነብያችን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል [የኛ ትእዛዝ የሌለበትን (የአምልኮ) ሾል የሰራ፤ (ስራው) ተመላሽ ነው] áˆ™áˆľáˆŠáˆ ዘግበውታል፡፡ ስለሆነም ይህ በሸሪዓ እንዲጎበኝ ወዳልታዘዘ ቦታ በመጓዝ አጅር አገኛለሁ ብሎ መሳተፍ አላህም ሆነ መልእክተኛው ያላዘዙትን መስራት በመሆኑ አደገኛ የቢድዓ ወንጀል ነው! 4)  áŠ áˆ‹áˆ… ዲናችንን የተሟላ እና ምንም አይነት ጭማሪም ሆነ ማሻሻያ የማይሻ የማይፈልግ ለሁሉም ዘመንና ቦታ የሚሆን ሐይማኖት አድርጎታል። መንፈሳዊ ጉዞ ታላላቅ የዲን መሪዎች በኖሩባቸው የኢስላም ቀዳሚ ዘመናት ሙስሊሞች የማያውቁት ከሌሎች የተኮረጀ እንግዳ ሾል ነው። اليَومَ أَكمَلتُ لَكُم دينَكُم وَأَتمَمتُ عَلَيكُم نِعمَتي وَرَضيتُ لَكُمُ الإِسلامَ دينًا «ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ፡፡ ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ፡፡ ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ» ሱረቱ'ል-ማኢዳህ 3 በመሆኑም፤ መንፈሳዊ ጉዞ በሚል በተለያዩ መስጅዶች እየተዋወቀ ያለው ጥሪ ትኩረት አድርገን ካልተከላከልነው ለብዙ ጥፋቶች የሚያጋልጥ ነው። በሸሪአችን በግልፅ የተከለከለ በመሆኑ  ሙስሊሙ እንዲጠነቀቅ፣ ራሱንና ቤተሰቡን በዲን ስም ከሚፈፀም ጥፋት እንዲጠብቅ እናሳስባለን።  5) በብዙ አካባቢዎች፤ መቃብሮች ከአንድ ስንዝር በላይ ከፍ እንዳይሉ፣ እንዳይገነቡና እንዳይቀቡ እንዲሁም መቃብሮች መስጂድ ተደርገው እንዳይያዙ የሚከለክሉ ነብያዊ ትእዛዛትን የተቃረነ ተግባር በስፋት ይፈፀማል። ጁንዱብ ኢብኑ አብደላህ ባስተላለፉት ሐዲስ  የአላህ መልዕክተኛ (ሰለላሁ ዓለይሁ ወሰለም) ከመሞታቸው ከአምስት ቀናት በፊት እንዲህ ሲሉ ሰምቻለው ብለዋል ‹‹ከእናንተ በፊት የነበሩ ህዝቦች የነቢያቸውንና የደጋግ ባሮችን ቀብር መስገጃ ስፍራ አደረጉ፡፡ አደራ! ቀብሮችን መስገጃ እንዳታደርጉ ከልክያችኃለው››  ሙስሊም ዘግበውታል በሌላ ዘገባም ጃቢር እንዲህ ብለዋል፤ ‹‹የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ቀብርን በጄሶ መመረግ፣ ላዩ ላይ መቀመጥ፣ ከላዩ መገንባት፣ ከአፈሩ ውጭ መጨመርና ቀብር ላይ መፃፍ ከልክለዋል››  ከላይ የተዘረዘሩት መረጃዎች በግልፅ እንደሚያሳዩት ከሶስቱ መስጂዶች ውጭ ወደ ወልዮች ሷሊሆችና ነብያት መቃብሮችም ይሁን መናገሻ ከተማዎች የሚደረጉ ጉዞዎች በሸሪዓ የተወገዙ ለሽርክ እና ባእድ አምልኮ የሚያጋልጡ መሆናቸው ግልፅ ነው። በአላህ ፈቃድ በቀጣይ ክፍል ሙስሊሙን ማህበረሰብ ለማደናገርና ወደ ቀብር አምልኮ ለመምራት በዚህ ሀዲስ ዙርያ ለሚቀርቡ ማደናገሪያዎች ምላሽ እንሰጣለን። አምልኮ ሁሉ የሚገባው ለአላህ ብቻ ነው። ስላሳወቀን የተውሂድ ብርሀን እናመሰግነዋለን። መንገድ ከመሳት በርሱ እንጠበቃለን። ወልሐምዱ ሊላሂ ረቢል ዓለሚን! T.me/abujunaidposts

🔗 ንፁሕ ልብ 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/137 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🍂 منزلة السكينة من روائع كلام ابن القيم في مدارج السالكين ____ @abujunaidposts

٤٣) منزلة السكينة ص(٢١٥-٢١٦)

🔖 5 ምክሮች ለቁርአን ሐፊዞች 🎁 ለመርከዝ ኢብኑ መስኡድ ተመራቂ ተማሪዎች የቀረበ ሙሀደራ 🎙 አቡ ጁነይድ ሳላህ አሕመድ ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

ዲን እየተማሩ ነውን? ኢስላም ከማንኛውም ነገር በፊት ዕውቀትን በመገብየት ላይ አደራ ይላል፡፡ ምክንቱም የምናደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ዕውቀትን መሰረት ያላደረጉ ከሆነ አላዋቂ ሳሚ ... እንደሚባለው ብሂል ከልማቱ የምንዘፈቅበት አዘቅቱ ያመዝናል፡፡ አንዳንዴም በኛ ሳይገደብ የኛው የጥፋት ረመጥ ይቀጥልና ሌሎችን እኛ የሰመጥንበት አዘቅጥ ውስጥ እንዲዋኙ የጥፋት ጀልባ እና መቅዘፊያ እንድንሆን ያደርገናል፡፡ ቁርአን ስለ እውቀት ፋይዳዎችና ስለ አዋቂዎች ደረጃ ብዙ ይላል። ዓዋቂው አምላካችን ስለ እውቀት ባለቤቶች ከፍ ያለ ደረጃ ዓዋቂዎች በሚገነዘቡት መልኩ እንዲህ ይላል፡- يَرْفَعِ اللَّهُ الَّذِينَ آمَنُوا مِنكُمْ وَالَّذِينَ أُوتُوا الْعِلْمَ دَرَجَاتٍ [٥٨:١١] «አላህ ከናንተ እነዚያ ያመኑትንና እነዚያ ዕውቀት የተሰጡትን በደረጃ ከፍ ያደርጋል» ሙጃደላህ፡11 ታላቁ ሶሃብይና የቁርአን ተፍሲር ዓዋቂ ዓብደላህ ኢብኑ ዓባስ እንዲህ ሲል የአንቀፁን መልዕክት የሚያጠናክር ንግግር አላቸው «የተማሩ ሰዎች ደረጃ ከተራው ሙዕሚን ሰባት መቶ እጥፍ ይበልጣል፡፡ ከአንዱ ደረጃ ወደ ሌላ ደረጃ ያለው ርቀት የአምስት መቶ ዓመት ርቀት ይሆናል» በሌላ የቁርአን አንቀፅ አላህ እንዲህ ይላል፡- إِنَّمَا يَخْشَى اللَّهَ مِنْ عِبَادِهِ الْعُلَمَاءُ [٣٥:٢٨] «አላህን ከባሮቹ ውስጥ የሚፈሩት ዐዋቂዎቹ ብቻ ናቸው» ፋጢር፡28 መልዕክተኛው (ﷺ) እንዲህ አሉ፤ «ዕውቀትን ቅሰሙ አላህን የምትፈሩት ባወቃችሁት ልክ ነውና» አዎን! የማያውቁትን አካል እንዴት ተገቢውን ፍራቻ ይፈሩታል?! አላህ መልዕክተኛው (ﷺ) እንዲጨምርላቸው እንዲጠይቁት ያዘዘው ብቸኛ ነገር ዕውቀት ነው! ከየት አመጣኸው ትይኝ ይሆናልና ማስረጃውን :- وَقُل رَّبِّ زِدْنِي عِلْمًا «ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ጨምርልኝ በል» 20፡114 የትኛውም የዕውቀት ደረጃ ላይ ብንገኝ በአላህ ከታገዝንና ጥረት ካደረግን ብዙ መሻሻል ይቻላልና አሁኑኑ ጥረት ማድረጉን እንጀምር። አላህ በኢስላማዊ ዕውቀት ወደተሻለ ደረጃ ከፍ እንል አንድ ያግዘን፤ እውቀትን ያግራልን። ልባችንን በቁርአን ያብራልን። አሚን ! _ @abujunaidposts

*ዲን እየተማሩ ነውን?* ኢስላም ከማንኛውም ነገር በፊት ዕውቀትን በመገብየት ላይ አደራ ይላል፡፡ ምክንቱም የምናደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ዕውቀትን መሰረት ያላደረጉ ከሆነ አላዋቂ ሳሚ ... እንደሚባለው ብሂል ከልማቱ የምንዘፈቅበት አዘቅቱ ያመዝናል፡፡ አንዳንዴም በኛ ሳይገደብ የኛው የጥፋት ረመጥ ይቀጥልና ሌሎችን እኛ የሰመጥንበት አዘቅጥ ውስጥ እንዲዋኙ የጥፋት ጀልባ እና መቅዘፊያ እንድንሆን ያደርገናል፡፡ ቁርአን ስለ እውቀት ፋይዳዎችና ስለ አዋቂዎች ደረጃ ብዙ ይላል። ዓዋቂው አምላካችን ስለ እውቀት ባለቤቶች ከፍ ያለ ደረጃ ዓዋቂዎች በሚገነዘቡት መልኩ እንዲህ ይላል፡- يَرْفَعِ اللَّهُ الَّذِينَ آمَنُوا مِنكُمْ وَالَّذِينَ أُوتُوا الْعِلْمَ دَرَجَاتٍ [٥٨:١١] *«አላህ ከናንተ እነዚያ ያመኑትንና እነዚያ ዕውቀት የተሰጡትን በደረጃ ከፍ ያደርጋል»* ሙጃደላህ፡11 ታላቁ ሶሃብይና የቁርአን ተፍሲር ዓዋቂ ዓብደላህ ኢብኑ ዓባስ እንዲህ ሲል የአንቀፁን መልዕክት የሚያጠናክር ንግግር አላቸው *«የተማሩ ሰዎች ደረጃ ከተራው ሙዕሚን ሰባት መቶ እጥፍ ይበልጣል፡፡ ከአንዱ ደረጃ ወደ ሌላ ደረጃ ያለው ርቀት የአምስት መቶ ዓመት ርቀት ይሆናል»* በሌላ የቁርአን አንቀፅ አላህ እንዲህ ይላል፡- إِنَّمَا يَخْشَى اللَّهَ مِنْ عِبَادِهِ الْعُلَمَاءُ [٣٥:٢٨] *«አላህን ከባሮቹ ውስጥ የሚፈሩት ዐዋቂዎቹ ብቻ ናቸው»* ፋጢር፡28 መልዕክተኛው (ﷺ) እንዲህ አሉ፤ *«ዕውቀትን ቅሰሙ አላህን የምትፈሩት ባወቃችሁት ልክ ነውና»* አዎን! የማያውቁትን አካል እንዴት ተገቢውን ፍራቻ ይፈሩታል?! አላህ መልዕክተኛው (ﷺ) እንዲጨምርላቸው እንዲጠይቁት ያዘዘው ብቸኛ ነገር ዕውቀት ነው! ከየት አመጣኸው ትይኝ ይሆናልና ማስረጃውን :- وَقُل رَّبِّ زِدْنِي عِلْمًا *«ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ጨምርልኝ በል»* 20፡114 የትኛውም የዕውቀት ደረጃ ላይ ብንገኝ በአላህ ከታገዝንና ጥረት ካደረግን ብዙ መሻሻል ይቻላልና አሁኑኑ ጥረት ማድረጉን እንጀምር። አላህ በኢስላማዊ ዕውቀት ወደተሻለ ደረጃ ከፍ እንል አንድ ያግዘን፤ እውቀትን ያግራልን። ልባችንን በቁርአን ያብራልን። አሚን ! _ @abujunaidposts

አሰላሙአለይኩም በአላህ ፈቃድ በቀጣይ ቀናት ወሳኝ መልዕክት ሼር አደርጋችኃለው። ኢን ሻ አላህ አቡጁነይድ @abujunaidposts

የወቅፍን ህግጋት በሰፊው የሚተነትን ባለ አምስት ክፍል የሸይኽ ኢልያስ አህመድ የጥያቄና መልስ ፕሮግራም ነው። እጅግ ጠቃሚ ስለሆነ እንድታደምጡት እጋብዛለው። https://youtube.com/playlist?list=PLEfTeB2txaf3_674TRqlIyCNt2MZVvHll

ልዩ የሙሃደራ ፕሮግራም ባህርዳር ከተማ 🎤 በሸይኽ ኢልያስ አህመድ 🎤 በሸይኽ ሙሀመድ ኢድሪስ 🎤 በኡስታዝ መሃመድ ሃሠን ማሜ አድራሻ፦ ቀበሌ 16 ከኖክ ማደያ ፊት ለፊት ተውፊቀል ኸይራት መስጂድ እሁድ ጥቅምት 06 ከዓሱር ሶላት በኋላ ነሲሓ ቲቪ... ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም!! @nesihatv

ሰዎች አራት አይነት ናቸው ከየትኛው ነን? ራሳችንን እንገምግም! ከኢብኑ ተይሚያህ አልሀራኒ ምርጥ ገለፃዎች (በአጭሩ የቀረበ) 1) በሰዎች ላይ አምባገነንነትን ማሳየት የሚፈልጉ፣ የአመፀኝነትን መስፋፋትና የአላህ ትእዛዝ መጣሱን የሚወዱ ናቸው። እነዚህም እንደ ፊርአውን እና መሰሎቹ ያሉት መሪዎች ሲሆኑ ከፍጥረታት ሁሉ መጥፎዎች ናቸው። ከነዚህ በምድር ላይ ጥፋትን የሚያስፋፉ ሰዎች መገለጫዎች መካከል *ኩራት ዋነኛው ሲሆን እርሱም ራስን ከሀቅ በላይ ማድረግና አለመቀበል እንዲሁም ሰዎችን መናቅና ማጣጣል* ነው። 2) ሌላኛዎቹ እራሳቸውን ከሰዎች በላይ ማድረግን ባይፈልጉም የአላህን ትእዛዛት ማመፅን የተያያዙና ወንጀልን የሚተገብሩ ናቸው፤ የሰዎችን ንብረት እንደሚሰርቁ ሰዎች ማለት ነው። እነዚህም የማህበረሰቡ ዝቃጭ ናቸው። 3) እንደ አንዳንድ ዲን ያላቸው ሰዎች፤ በአላህ ትእዛዛት ላይ ማመፅን የማይወዱ ነገር ግን *ዲኑን በመጠቀም እራሳቸውን ከሰዎች በላይ የሚያደርጉ* ሰዎች። 4) የመጨረሻዎቹ ክፍሎች የጀነት ሰዎች ሲሆኑ፤ እነርሱም፦ አላህ እንዳለው፤ قَالَ اللَّهُ تَعَالَى : { وَلَا تَهِنُوا وَلَا تَحْزَنُوا وَأَنْتُمُ الْأَعْلَوْنَ إنْ كُنْتُمْ مُؤْمِنِينَ } آل عمران 139 *አትሥነፉ፣ አትዘኑም፤ ምእምናን እስከሆናችሁ እናንተ የበላዮች ናችሁ* አል ኢምራን 139 በኑሯቸው ከሰዎች በላይ ሊሆኑ ይችላሉ፤ ነገር ግን፤ እራሳቸውን ከሰዎች በላይ ማድረግን እና በአላህ ትእዛዛት ላይ ማመፅን የማይፈልጉ ናቸው። አላህ በአኼራ ከፍታን የሚለግሰው ለትሁቶች ነው። قال تعالى: {تِلْكَ الدَّارُ الْآخِرَةُ نَجْعَلُهَا لِلَّذِينَ لَا يُرِيدُونَ عُلُوًّا فِي الْأَرْضِ وَلَا فَسَادًا وَالْعَاقِبَةُ لِلْمُتَّقِينَ} [القصص: 83]. *የመጨረሻይቱም ሀገር (አኺራ) ለነዚያ በምድር ላይ ኩራትንና በአላህ ትእዛዛት ላይ ማመፅን ለማይፈልጉት እናደርጋታለን፤ መልካም መጨረሻም አላህን ለሚፈሩት ጥንቁቆች ነው* አል ቀሰስ 83 ከሰዎች ሁሉ የበላይ መሆንን እየፈለገ ወደ ታች የሚወርድ ስንቱ ነው!! የበላይነትን ሳይመኝ አምባገነን ሳይሆን አላህ ከፍ የሚያደርገውስ ስንቱ ነው!! አልፈታዋ አል ኢራቂያህ 2/972 አላህ ከነሱ ያድርገን ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts