ru
Feedback
🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

Открыть в Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

Больше
2 214
Подписчики
+124 часа
-67 дней
-3430 день
Архив постов
📹 ይህ እንዴት የሙስሊሞች ኢባዳ ሊሆን ይችላልን? የኢባዳ መስፈርቱ ለአላህ በኢኽላስ መፈፀሙና በነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ፈለግና አርአያነት መሰረት መተግበሩ ነው። ኢባዳ ለአላህ በፍፁም ውዴታ መተናነስን የምናሳይበት ነው። ለመሆኑ ከሳቸውና ከሰሀቦች ይህ አይነቱ ድለቃ ይታወቃልን? ዱዓ ከሆነ ደግሞ ለአላህ እራስን ዝቅ በማድረግ የሚፈፀም ብቻ ነው። አላህ እንዲህ ይላል፤ { ٱدۡعُوا۟ رَبَّكُمۡ تَضَرُّعࣰا وَخُفۡیَةًۚ إِنَّهُۥ لَا یُحِبُّ ٱلۡمُعۡتَدِینَ } ጌታችሁን ተዋርዳችሁ በድብቅም ለምኑት፡፡ እርሱ ወሰን አላፊዎችን አይወድምና፡፡ [Surah Al-Aʿrāf: 55] ሱብሀነላህ! ወዴት ወዴት ነው? አላህ በዚህ መልኩ ቅጥ ያጣ አምልኮ የሚፈፅሙ ብሎ የጠቀሰው ኢአማንያንን ነበር። { وَمَا كَانَ صَلَاتُهُمۡ عِندَ ٱلۡبَیۡتِ إِلَّا مُكَاۤءࣰ وَتَصۡدِیَةࣰۚ فَذُوقُوا۟ ٱلۡعَذَابَ بِمَا كُنتُمۡ تَكۡفُرُونَ } በቤቱ ዘንድም (በካዕባ) ስግደታቸው ማፏጨትና ማጨብጨብ እንጂ ሌላ አልነበረም፡፡ ትክዱት በነበራችሁትም ነገር ቅጣትን ቅመሱ (ይባላሉ)፡፡ [Surah Al-Anfāl: 35] በቀድሞ ዘመን ኩፋሩ ቁረይሽ ባሁንም ዘመን የሌላ እምነት ተከታዮች ዘንድ በሚታወቅ ሁኔታ የሚፈፀም ኢባዳ የአላህን ውዴታ ያስገኛል ተብሎ ነውን? አላህ ከጭፍን ተከታይነትና መታወር ይጠብቀን። ሀቅን ይግለጥልን በሱና ላይ ያፅናን። አሚን! 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/523 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

የመውሊድ በዓል በሚዛን ላይ """""""""""""""""""""""" ነሲሓ መጽሔት ቅጽ Vol2 ቁጥር 1 ምስጋና ለአለማት ጌታ ለአላህ የተገባ ነው ፡፡ ሰላት እና ሰላም ለዐለማት እዝነት በተላኩት በነቢያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በሰሃባዎቻቸው እና እነርሱን በመልካም በተከተሉት ሁሉ ላይ እስከ እለተ ቂያማ (ትንሳኤ) ድረስ ይውረድ፡፡ ቁርዓን እና ሐዲስን እንዲሁም ዝርዝር የሸሪዓ ህግጋትን በትክክል መረዳት ለሁሉም ሙስሊም በእጅጉ አስፈላጊ ቢሆንም ቀላል ግን አይደለም። አላህ ለዚህ ኡማ ታላቅ ውለታ በመዋል ኡለማዎችን ሰጥቶን ያላቸውን ታላቅ ክብር ገልፆልናል፡፡ የሙስሊሞችን እምነት፣ የአምልኮ ‘ዒባዳ’ አተገባበር እና የስነምግባር እሴቶችን ማረም የዑለሞች ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ ከሰሀቦችና እነሱን ከተከተሉ ታቢዒዮች መካከል ታላለቅ ዑለማዎች እና የፊቅህ ጠበብቶች ቁርዓንን በተገቢው መልኩ በመረዳት እና ዕድሜያቸውን ሙሉ በማስተማር ሀላፊነታቸውን ተወጥተዋል። ሰሃባዎች ከማንም በበለጠ በዕውቀት የበለፀጉ ከመሆናቸው ባሻገር የመልእክተኛውን ﷺ ንግግር እና ሱና በመተግበር ፋና ወጊዎች እንደነበሩ አያጠያይቅም። አብደላህ ኢብን መስዑድ አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና በአንድ ወቅት ስለሰሃባዎች እንዲህ ብለው ነበር፤ "ከዚህ ከነቢዩ ዑመት ከማንም በበለጠ፤ ቅን ልቦና፣ የጠለቀ እውቀት፣ የተቃና ፈለግ እና ያማረ ስብዕና ባለቤት ነበሩ። እነሱ ማለት አላህ ለነብዩ ጓደኝነት የመረጣቸው ህዝቦች ናቸው፡፡ ክብራቸውን እወቁላቸው። ፋናቸውንም ተከተሉ። እነሱ ቀጥተኛው መንገድ ላይ ነበሩ።" ኢብኑ ዐብደል በር / ጃሚዑል በያኒል ዒልም በሚባለው ኪታባቸው ቅጽ 2/946-947 ሰሃባዎች በሐቅ ላይ አንድነታቸውን ለመጠበቅ የተለያዩ ሸሪዓዊ አጀንዳዎች ላይ ይመካከሩና ይተራረሙ ነበር፡፡ ያልደረሳቸውን መረጃ ሲያገኙም ወደ ሐቅ ከመመለስ የሚያግዳቸው ነገር አልነበረም። ለሐቅ ተገዢ ስለነበሩ እርምት ለሰጣቸው አካል ምስጋና እና ክብራቸው ከመጨመሩ ባሻገር በመካከላቸው የነበረው ወዳጅነት አልጎዳም። ኢብኑ ተይሚያ እንዲህ ብለዋል "ሰሃባዎች፣ ታቢዒዮች እና ከእነርሱ በኋላ የመጡት ዑለማዎች በመካከላቸው አለመግባባት በተፈጠረ ጊዜ የአላህን ትዕዛዝ ይከተሉ ነበር፡፡ አላህ እንዲህ ብሏል «በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ብትሆኑ የተከራከራችሁበትን ነገር ወደ አላህና ወደ መልክተኛው መልሱት፡፡ ይህ የተሻለ መጨረሻውም ያማረ ነው፡፡» ሱረቱ ኒሳዕ : 59 በተለያዩ የዲን አጀንዳዎች ላይ በምክክር መልክ ይወያያሉ፡፡ አልፎ አልፎ የዒልምና እና የተግባር ጉዳዮች ላይ የአቋም ልዩነት ሲኖር መዋደድን፣ መተሳሰርን እና ኢስላማዊ ወንድማማችነትን በጠበቀ ሁኔታ ይተራረማሉ።" መጅሙዑል ፈታዋ 24/172 በየዓመቱ የረቢዐል አወል ወር በገባ ቁጥር የነቢያችንን የልደት በዓል መውሊድን የማክበር ጉዳይ ሰዎችን ሲያወዛግብና መነጋገሪያ ሲሆን ይታያል። አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ሙእሚኖችን በመሰረታዊም ይሁን በቅርንጫፋዊ የዲን ጉዳዮች ላይ አለመግባባት ቢፈጠሩ ጉዳያቸውን ወደ ቁርዓንና ሐዲስ በመመለስ መፍትሄ እንዲፈልጉ በሚከተለው የቁርዓን አንቀጽ አዟል፡፡ فَإِن تَنَازَعْتُمْ فِي شَيْءٍ فَرُدُّوهُ إِلَى اللَّهِ وَالرَّسُولِ إِن كُنتُمْ تُؤْمِنُونَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ ذَٰلِكَ خَيْرٌ وَأَحْسَنُ تَأْوِيلًا ٤:٥٩ «በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ብትኾኑ የተከራከራችሁበትን ነገር ወደ አላህና ወደ መልክተኛው መልሱት፡፡ ይህ የተሻለ መጨረሻውም ያማረ ነው» ሱረቱ ኒሳዕ : 59 ከዚህ ቁርአናዊ መመሪያ በመነሳት ለአንባቢዎቻችን ነሲሓ ይሆን ዘንድ ትክክለኛውን አቋም እናመላክታለን። አላህ ሀቁን አይተው ከሚከተሉት ሰዎች ያድርገን። ይህ በዓል በሸሪዓ መሰረት የሌለውና ሰዎች በዲን ውስጥ የጨመሩት አዲስ ነገር ከመሆኑ ባሻገር አላህና መልእክተኛው ያልደነገጉትን ተግባር በቀን የተገደበ ወደ አላህ መቃረቢያ አምልኮ ማድረግ መሆኑ ዋነኞቹ የመውሊድ ችግሮች ሲሆኑ፤ በተጨማሪም ክርስቲያኖችን በመፎካከር የመጣ መሆኑ ከእነሱ ጋር መመሳሰል ነው። በተጨማሪ በዚህ በዓል ውስጥ በሸሪዓ የተወገዙ በርካታ ተግባራት ይፈፀማሉ። መውሊድ አንድን ስራ ቢድዓ የሚያሰኙ ምክንያቶች ሁሉ እንዳሉበት አያጠራጥርም። ይህም በሚከተሉት ሶስት ነጥቦች ይብራራል፤ 1) አዲስ ነገር መፍጠር (ኢሕዳስ) ካለ ሸሪዓዊ ማስረጃ፤ ማንኛውንም ቀን ወይም ወር ልዩ ሀይማኖታዊ ክንውን የሚፈፀምበት እንደሆነ በማሰብ በዋጂብነት ወይም ሱናነት ሰዎችን የምናበረታታበት ከሆነ በዲን ውስጥ አዲስ ነገር መፍጠር ነውና ሀራም ነው። አሏህ እንዲህ ብሏል:- أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ شَرَعُوا لَهُمْ مِنَ الدِّينِ مَا لَمْ يَأْذَنْ بِهِ اللَّهُ «ከሀይማኖት አላህ በእርሱ ያልፈቀደውን ለእነሱ የደነገጉ ተጋሪዎች ለእነርሱ አሏቸውን?» ሱረቱ ሹራ ቁጥር 21 ቡኻሪ እና ሙስሊም በዘገቡት የተረጋገጠ ሰሂህ ሐዲስ ነቢያችን ﷺ ብለዋል፤ مَنْ أحْدَثَ في أمْرِنَا هَذَا مَا لَيْسَ مِنْهُ فَهُوَ رَدٌّ «በዲናችን ውስጥ ከእርሱ ያልሆነን ነገር የፈጠረ ስራው ተመላሽ ይደረግበታል» ብለዋል። ይህ ማለት በሸሪዓ ያልተደነገገን ነገር ፈጥሮ ቢፈፅም ተቀባይነት አያገኝም ማለት ነው። እንደሚታወቀው፤ መውሊድን ረሱል ﷺ የተከበሩት ኸሊፋዎች እና ሌሎችም ሰሀባዎች አላከበሩትም። እንደዚሁ በተከበረው ዘመን ውስጥ የኖሩት ሰሀባዎችን በመልካም ሲከተሉ የነበሩ ታቢዒዮች አልሰሩትም። እነሱ ደግሞ ከማንም በላይ የሱና አዋቂዎችና ለነቢያችን የነበራቸው ውዴታም ከማንም በላይ እንደነበር እሙን ነው። የነብዩን ፈለግ በሚገባ በመከተልም የማይታሙ እንደ ነበሩ ለማንም ግልፅ ነው። ለኛ አርአያ መሆናቸውም ተነግሮናል። ምንም ሳንጨምር መንገዳቸውን አጥብቀን እንድንይዝ የአላህ መልዕክተኛ አደራ ብለውናል፤ عَلَيْكُمْ بِسُنَّتِي وَسُنَّةِ الْخُلَفَاءِ الرَّاشِدِينَ الْمَهْدِيِّينَ، وَعَضُّوا عَلَيْهَا بِالنَّوَاجِذِ، وَإِيَّاكُمْ وَمُحْدَثَاتِ الْأُمُورِ، فَإِنَّ كُلَّ مُحْدَثَةٍ بِدْعَةٌ، وَكُلَّ بِدْعَةٍ ضَلَالَةٌ «የእኔን እና የቅን ምትኮቼን ሱና አደራ! በጥርሶችችሁ አጥብቃችሁ ያዙ! አዳዲስ ፈጠራዎችን ተጠንቀቁ (ተከልከሉ)፣ በዲን ውስጥ የተጨመረ ፈጠራ ሁሉ ጥመት ነው» ኢማሙ አህመድ ዘግበውታል መውሊድ በቀደምቶቹ ዘመን እንዳልነበረ እና ኃላ የተፈጠረ (ሙህደስ) ለመሆኑ መውሊድ አክባሪዎች ሁሉ የማይክዱት እውነታ ነው። መውሊድ ማክበርን ለመጀመሪያ ጊዜ የጀመሩት ከአራተኛው ክ/ዘመን በኋላ እራሳቸውን ፋጢሚዮች ብለው ይጠሩ የነበሩት ኡበይዲዩች ግብፅን በ362 ዓመተ ሂጅራ የወራሩ ጊዜ ነበር። ቀጣዩን ያንብቡ👇 https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=1336321059824881&id=1003047829818874

🍂 የሰለፎች ብሩህ ፋና! 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/521 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔖 የኑህ መርከብ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ Share link https://t.me/nesihastudio/2152 @nesihastudio

🔖 የኑህ መርከብ 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ የቢድዓን አደጋዎች የሚያብራራ እና ለቢድአ አራማጆች ማደናገሪያ ሹብሐዎች ምላሽ የሚሰጥ በጃሊያ አዳራሽ የቀረበ ጠቃሚ ትምህርት ትምህርቱ በነሲሓ ድረ http://nesiha.com/wp-content/uploads/2018/05/የኑህ-መርከብ.mp3 @abujunaidposts

ቅድሚያ ለተውሒድ Arabic/Amharic 🎙 ዶ/ሸይኽ አብደላህ አልጀርቡዕ ሀፊዘሁላህ 💾 የ1424 የፓልቶክ ሙሐደራ ከአማርኛ ትርጉም ጋር በአቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/125 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

እናስተውል፤ ፀባይ (አኽላቅ) ልክ እንደ ሪዝቅ ነው! የዱንያ ሀብታምና ደሀ እንዳለ ሁሉ የአኽላቅም ሀብታምና ደሀ አለ። አላህ ዘንድ በፆምና በለይል ሰላት የማይገኝ ክብርና ደረጃ በመልካም ፀባይ ይገ
እናስተውል፤ ፀባይ (አኽላቅ) ልክ እንደ ሪዝቅ ነው! የዱንያ ሀብታምና ደሀ እንዳለ ሁሉ የአኽላቅም ሀብታምና ደሀ አለ። አላህ ዘንድ በፆምና በለይል ሰላት የማይገኝ ክብርና ደረጃ በመልካም ፀባይ ይገኛል። እውነተኛው ሀብታም አመለ ሸጋ ሰው ነው! ስለዚህም፤ وَإِنَّكَ لَعَلَىٰ خُلُقٍ عَظِیمࣲ "አንተም በታላቅ ፀባይ ላይ ነህ" በማለት አላህ የመሰከረላቸው ታላቁ ነብይ ስለ ፀባያቸው ማማር በመጨነቅ "አላህ ሆይ አፈጣጠሬን እንዳሳመርከው ጠባዬንም አሳምርልኝ" ብለው ዱዓ ያደርጉ ነበር። ሙስሊም በዘገቡት ሐዲስ ደግሞ፤ وَاهْدِنِي لِأَحْسَنِ الْأَخْلَاقِ لَا يَهْدِي لِأَحْسَنِهَا إِلَّا أَنْتَ، وَاصْرِفْ عَنِّي سَيِّئَهَا لَا يَصْرِفُ عَنِّي سَيِّئَهَا إِلَّا أَنْتَ (ካንተ ውጭ ማንም ለመልካም ፀባይ ሊገራኝ አይችልምና ያማረ ፀባይን አግራልኝ። ካንተ ውጭ ከመጥፎ ፀባይ የሚያርቀኝ የለምና ከመጥፎው አንተው አርቀኝ) ይሉ ነበር። የአኽላቅ ደረጃ ከፍ ያለ ነው። በሐዲስ እንደተላለፈው፤ «የቂያማ ቀን ከመልካም ስነ-ምግባር የበለጠ ሚዛን የሚደፋ ምንም ነገር የለም። የመልካም ስነ-ምግባር ባለቤት የስነ-ምግባሩ ማማር፤ ከፈርድ አልፎ ሱንና ሰላትና ጾም የሚያዘወትር ሰው ደረጃ ላይ ያደርሰዋል» ቲርሚዚ ዘግበውታል አላህ መልካም ፀባይን ይለግሰን፤ ከነፍሳችንና ከሸይጣን ክፋት ሁሉ ይጠብቀን! ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔖 ሱናን መከተል 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/394 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

📹 መውሊድ ኢስላማዊ በዓል ነውን? በነሲሓ ቲቪ  የቀረበ አጭር  ውይይት  🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/514 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

መውሊድ ኢስላማዊ በዓል ነውን? ⌚️ በነሲሓ ቲቪ የቀረበ አጭር ውይይት 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/411 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

📌 بشرى لطلبة العلم دورة ميراث الأنبياء العلمية الثالثة من ١٠ صفر ١٤٤٥هے‍ الموافق ٢٦\٨\٢٠٢٣م إلى يوم الأحد ١٨ صفر ١٤٤٥هے‍ الم
📌 بشرى لطلبة العلم دورة ميراث الأنبياء العلمية الثالثة من ١٠ صفر ١٤٤٥هے‍ الموافق ٢٦\٨\٢٠٢٣م إلى يوم الأحد  ١٨ صفر ١٤٤٥هے‍ الموافق ٢\٩\٢٠١٩م ١) كتاب البيوع من عمدة الأحكام 🎙 د/ حسن أحمد الهواري حفظه الله   ےے❊❊ےے ٢) رسالة لطيفة في أصول الفقه 🎙 د/ عبد الرحمن حامد آل نابت حفظه الله ےے❊❊ےے ٣) منهج أهل السنة والأشاعرة في الصفات 🎙 د/ خالد عبد اللطيف حفظه الله ےے❊❊ےے ٤) التأسيس في بيان آيات المواريث 🎙 الدكتور خليل حامد خليل حفظه الله ےے❊❊ےے ٥) نخبة الفكر في المصطلح 🎙 د/معاذ عبدالرحيم خوجة حفظه الله ےے❊❊ےے ٦) منظومة أصول الفقه والقواعد للعثيمين 🎙الشيخ أبو حنيف إلياس أحمد محمد ےے❊❊ےے ملاحظة - * هناك محاضرات مختلفة تصاحب الدورة * الخدمات للطلاب المسجلين فقط ولكن يحق الحضور والاستفادة من الدروس للجميع * يتم نقل الدروس والمحاضرات على قناة المركز على تيليغرام * جميع الدروس باللغة العربية فقط 🕌 مكان إقامة الدورة معهد دار الحديث لتعليم اللغة العربية والعلوم الشرعية بمبنى المركز في حي ١٨ _ مركز ابن مسعود الإسلامي بأديس أبابا t.me/merkezuna الموقع على الخريطة:- https://goo.gl/maps/oC7GZtpeLwkzxrVr8

📌 بشرى لطلبة العلم دورة ميراث الأنبياء العلمية الثالثة من ١٠ صفر ١٤٤٥هے‍ الموافق ٢٦\٨\٢٠٢٣م إلى يوم الأحد ١٨ صفر ١٤٤٥هے‍ الم
📌 بشرى لطلبة العلم دورة ميراث الأنبياء العلمية الثالثة من ١٠ صفر ١٤٤٥هے‍ الموافق ٢٦\٨\٢٠٢٣م إلى يوم الأحد  ١٨ صفر ١٤٤٥هے‍ الموافق ٢\٩\٢٠١٩م ١) كتاب البيوع من عمدة الأحكام 🎙 د/ حسن أحمد الهواري حفظه الله   ےے❊❊ےے ٢) رسالة لطيفة في أصول الفقه 🎙 د/ عبد الرحمن حامد آل نابت حفظه الله ےے❊❊ےے ٣) منهج أهل السنة والأشاعرة في الصفات 🎙 د/ خالد عبد اللطيف حفظه الله ےے❊❊ےے ٤) التأسيس في بيان آيات المواريث 🎙 الدكتور خليل حامد خليل حفظه الله ےے❊❊ےے ٥) نخبة الفكر في المصطلح 🎙 د/معاذ عبدالرحيم خوجة حفظه الله ےے❊❊ےے ٦) منظومة أصول الفقه والقواعد للعثيمين 🎙الشيخ أبو حنيف إلياس أحمد محمد ےے❊❊ےے ملاحظة - * هناك محاضرات مختلفة تصاحب الدورة * الخدمات للطلاب المسجلين فقط ولكن يحق الحضور والاستفادة من الدروس للجميع * يتم نقل الدروس والمحاضرات على قناة المركز على تيليغرام * جميع الدروس باللغة العربية فقط 🕌 مكان إقامة الدورة معهد دار الحديث لتعليم اللغة العربية والعلوم الشرعية بمبنى المركز في حي ١٨ _ مركز ابن مسعود الإسلامي بأديس أبابا http://www.t.me/merkezuna الموقع على الخريطة:- https://goo.gl/maps/oC7GZtpeLwkzxrVr8

🍂 ደስተኛ ኢስላማዊ ቤተሰብ 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚️ የ 51 ደቂቃ ሙሀደራ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/103 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

የሺዓና የአህሉሱና የዓሹራ ውሎ ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ ሙሀረም 12/ 1436 ዓ.ሒ ተፃፈ የዓሹራ ቀን፤ የፊዓአውንን ትእቢትና አምባገነነንነት ያከተመበትና ለሌሎችም መቀጣጫ የሆነበት፣ ነብዩላህ
የሺዓና የአህሉሱና የዓሹራ ውሎ ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ ሙሀረም 12/ 1436 ዓ.ሒ ተፃፈ የዓሹራ ቀን፤ የፊዓአውንን ትእቢትና አምባገነነንነት ያከተመበትና ለሌሎችም መቀጣጫ የሆነበት፣ ነብዩላህ ሙሳም የተደሰቱበት ለአህሉሱና ታላቅ ትርጉም ያለው የድል ብስራት ቀን ነው። አህሉሱና ይህንን ቀን በአል አያደርጉትም። የተለየ ድግስም ሆነ አለባበስ የላቸውም። ሆኖም መልእክተኛው ﷺ በደነገጉት መሰረት ይፆሙታል፣ መልካም ተግባራትን ይፈፅሙበታል፣ ከአላህ ልዩ ምንዳን በመከጀልም በዒባዳ ያሳልፉታል። ሺዓዎች ግን ስለ ዓሹራ ቀን ሲያስቡ ሚታወሳቸው የታላቁ ሰሀቢይ የአሊይ ኢብኑ አቢ ጣሊብ ልጅ ሁሰይን የተገደሉበት ቀን መሆኑ ብቻ ነው። ሺዓዎች በዚህ ቀን ሀዘናቸውን ለመግለፅ እራሳቸውን የሚጎዱ ብዙ ነገሮችን በስፋት ይፈፅማሉ። ጭንቅላትንና ሌሎች አካሎቻቸውን በስለት መብጣትና ማድማት (ተጥቢር)፣ ፊታቸውን መደብደብ (ለጥም፣) እራስን በሰንሰለት መግረፍና ማንገላታት፣ በእንብርክክ መሄድ፣ ብዙዎችም ዘንድ ጥቁር መልበስና የለቅሶ ሙሾ ማውረድ ብሎም በራስ ላይ ኩነኔን መጥራት የተለመዱ የአሹራ ትእይንቶቻቸው ናቸው። በእጅጉ ይገርማል፤ ለኛ ለአህሉሱና ደስታን ሲያላብሰን፣ ተስፋን አሰንቆ ድልን ሲያበስረን፤ ለወንጀላችን ማርታን ለማግኘት ሩጫ ውስጥ ሲከተን፤ ለሺአዎች ግና፤ የሀዘን የዋይታ፣ የውድቀት የሽንፈት ማስታወሻ፣ የተስፋ ማጨለሚያ ነው!! ሁሰይን የነብዩ ﷺ የልጅ ልጅ በኢስላማዊ እውቀት ከመጠቁ ታላላቅ ሰሀቦች አንዱ ናቸው። በኢባዳ ብርቱ የተወዳጇ የመልእክተኛው ﷺ ልጅ የፋጢማ ረዲየላሁ አንሀ ልጅ ናቸው። ሆኖም... ቀሪውን በዚህ ሊንክ ያንብቡ http://clearfaith.blogspot.com/2015/10/blog-post.html?m=1 ------ 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🗞 ስለ ዓረፋ ቀን ዱዓእ ሁለት ነጥቦች ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ [1] በኢድ ዋዜማው የዓረፋ እለት ዱዓእ ተቀባይነት እንዳለው የሚዘክሩ ሀዲሶች ሀጅ ላይ የሌሉ ሰዎችንም ይመለከታሉን?? የአላህ መልእክተኛ «ከዱዓዎች ሁሉ በላጩ (የኢድ ዋዜማ) የአረፋ ቀን ዱዓ ነው...» ማለታቸውን ቲርሚዚይ ከአብዱላህ ኢብኑ ኡመር የዘገቡ ሲሆን፤ ሌሎች ተመሳይ ይዘት ያላቸው ሀዲሶችም ይገኛሉ። ታዲያ የዓረፋን እለት በዱአዕና በዚክር ያሳለፈ ሰው ታላቅ ክብርና ምንዳን የሚያገኘው ሀጅ ላይ ሲሆን ብቻ ነውን? በእርግጥ በዚህ እለት ክብር ባለው የዓረፋ ምድር የተገኘ ሰው የጊዜንም የቦታንም ክብር ተጎናፅፏልና በተሻለ ሁኔታ ላይ መገኘቱ እንዲሁም ዱአው ተቀባይነት ለማግኘት የቀረበ መሆኑ አያጠራጥርም። ይሁንና ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት፤ እነዚህ ከአረፋ እለት ክብር ጋር ተያይዞ የዱአ ተቀባይነትን የተመለከቱ ሀዲሶች በማንኛውም ቦታ የሚገኙ ሙስሊሞችን ይመለከታሉ። በመሆኑም በሀጅ ስራ ላይ የሌሉ ሰዎችም በዱዓ ሊበረቱ ይገባል። ታላቁ አሊም ሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን በዚህ እለት የሚባሉ በሀዲስ የተላለፉ ዱአዎችን አስመልክቶ ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎች መሆኑን ተጠይቀው ተከተዩን መልሰዋል¹ «በምላሻችን እንደገለፅነው፤ ይህ ለሁጃጆችንም ይሁን ሌሎችን የተመለከተ ጥቅል መልእክት ነው። ነገር ግን ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎች ይበልጥ የተገባ ነው። ምክኒያቱም ሁጃጆች በዚህ እለት በዓረፋ ምድር በኢህራም ውስጥ ስለሚገኙ ከሌሎች በበለጠ ዱዓቸው ተቀባይነት ለማግኘት የቀረበ ነው። ስለዚህም የዓረፋን እለት በሀጅ ተግባር ላይ የሌሉ ሰዎች እንዲፆሙት ተደንግጓል። እለቱ ብልጫ ያለወወ ስለሆነም አላህን በማስታወስ፣ ማርታን በመለመን እና ዱዓ በማድረግ ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ፤ ሁጃጆችንም በኢባዳ ይካፈሏቸዋል ማለት ነው።» ከሸይኹ ድረገፅ የተወሰደ የድምፅ ፈትዋ [2] በዓረፋ እለት ሁጃጆች በአረፋ ምድር እንደሚሰባሰቡት ለዱዓና ለዚክር መሰባሰብ "ታዕሪፍ"ን በተመለከተ፤ ይህ ተግባር አንዳንድ ሰለፎች እንደፈፀሙት የተረጋገጠ ነው። ከነሱም መካከል ኢብኑ አባስ ይገኙበታል፤ ኢማሙ አህመድም ባይተገብሩትም እንደሚቻል ተናግረዋል። ነገር ግን ያወገዙትና ከቢድአ የመደቡትም አሉ። የኡለማዎቻችንን ማብራሪያዎች ስንፈትሽ ተከታዮቹ ድምዳሜዎች ላይ ያደርሱናል፤ 1) "ታእሪፍ"ን መተግበር በራሱ ችግር የለውም። ተግባሩን እንደሱና ወይም ሙስተሀብ ነገር መውሰድ ግን አይገባም። ጉዳዩ የኢጅቲሀድ መስአላ ነውና ተግባሩ የሚወገዝ ተግባር አይሆንም። የፈፀመውም ሰው ቢድአ ሰራ አይባልም። 2) ታእሪፍ ስንል ከምድረ አረፋ ውጭ ባሉ የየሀገሩና የየከማው መስጂዶች መሰባሰብን የተመለከተ እነጂ ለዚህ ብሎ ጉዞ ማድረግ አይፈቀድም። አላህ የአረፋን ምድር ለዚህ ቀን ኢባዳ መሰባሰቢያ እንደመረጠው በየሀገሩ አንዳንድ ቦታዎችን፣ መስጅዶችንና ቀብሮችን በመምረጥ ወደነሱ ጉዞ አድርጎ መሰባሰብ በፍፁም አይፈቀድም። ይህ የነብዩ መስጂድንም ይሁን በይተልመቅዲስን ያካትታል። 3) ይህ መሰባሰብ ጩኸትና ሱና ያልሆኑ የጋራ አምልኮዎች ከታከሉበት ቢድአ እንደሚሆን አያጠራጥርም። በተመሳሳይ መልኩ ኢባዳ ያልሆኑ ግጥሞችና መንዙማዎችን ለዚህ መለያ ማድረግ ጥፋት ነው። እነዚህን ነጥቦች በዝርዝር ለመረዳት የሚያስችሉ ማብራሪያዎችን ከኡለማዎች ድርሳናት እንደሚከተለው እናያለን። ቀሪዉን የፅሁፍ ክፍል ተከታዩን ሊንክ በመከተል ያንብቡት https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=10160553120869684&id=682494683 __ 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች t.me/abujunaidposts

🔖 ተውሒድ እና የሐጅ ፍሬዎች 🎙 አቡጁነይድ እና ጣሀ አህመድ በ 2002 በጃሊያ አዳራሽ የቀረበ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/219 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🗞 ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው አስርቱ የዙልሂጃ ቀናት ✍ ዝግጅት፦ አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ህዳር 2004 🔗 የፅሁፉ ሊንክ https://d1.islamhouse.com/data/am/ih_articles/single/am_Virtues_of_the_Ten_Days_of_Dhul_Hijjah.pdf 🔗 telegram Share Link https://t.me/abujunaidposts/374 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🗞 ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው አስርቱ የዙልሂጃ ቀናት    ምስጋና ለአላህ የተገባ ነው፡፡ የአላህ ሰላምና እዝነት በታላቁ ነብይ በሙሀመድ በባልደረቦቻቸው እና በቤተሰቦቻቻው ሁሉ ላይ ይሁን፡፡    ከተከበሩት ወራት መካከል አንዱ የሀጅ ወር ዙልሂጃ ነው። ከቀናት ሁሉ አላህ ዘንድ የተወደዱት ደግሞ አስሩ የዙልሂጃ ቀናት ናቸው። እንደዉም ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው እነኝህ ቀናት ናቸው። የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፦ عن جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللهِ رَضِيَ الله عَنْهُ قَالَ: قَالَ رَسُولَ اللهِ صَلَّى الله عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:  "أَفْضَلُ أَيَّامِ الْدُّنْيَا أَيَّامُ الْعَشْرِ، يَعْنِي عَشْرُ ذِي الحْجَّةِ". صحيح الجامع ، رقم 1133 ጃቢር ኢብኑ ዓብዲላህ ባስተላለፉት ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል «ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው፤ አስርቱ ቀናት ናቸው። ማለትም አስሩ የዙልሂጃ ቀናት» አልባኒ ሰሂሁል ጃሚዕ 1133 ላይ አስፍረውታል عن ابن عباس رضي الله عنهما، عن النبي صلى الله عليه وسلم قال: "ما من أيام العمل الصالح فيهن أحب إلى الله منه في هذه الأيام العشر. قالوا ولا الجهاد في سبيل الله !! قال : ولا الجهاد في سبيل الله، إلا رجل خرج بنفسه وماله ولم يرجع من ذلك بشيء" أخرجه البخاري ከኢብኑ ዓባስ በተዘገበ ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል:‐ «በነዚህ አስር ቀናቶች ውስጥ ከሚፈጸሙ መልካም ስራዎች በበለጠ ስራዎች አላህ ዘንድ የተወደዱ የሚሆኑባቸው ቀናት የሉም፤ “በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሀድም ጭምር?” ተባሉ። እርሳቸውም፤ “ራሱንና ንብረቱን ይዞ ወጥቶ ምንም ያልተመለሰለት ሰው ሲቀር ጂሀድም ከዚህ አይበልጥም” አሉ።» ቡኻሪ ዘግበውታል በነዚህ ቀናቶች ትኩረት ልንሰጣቸው ከሚገቡ የዒባዳ አይነቶች መካከል:‐ 1. ጾም፦ ጾም ከስራዎች ሁሉ በላጭ ነውና በእነዚህ ቀናት መጾም እጅግ የተወደደ ነው። የአላህ መልዕክተኛ ዘጠኙን የዙልሂጃ ቀናት ይጾሙ እንደነበር ተዘግቧል። (አስረኛው ቀን ግን ዒድ ስለሆነ አይጾምም) 2. ዚክሮችን ማብዛት፦ አላህን ማመስገን (አልሀምዱሊላህ) ፣ ተክቢር፣ ተስቢህ(ሱብሀነላህ) እና ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢለላህ)፤ ኢባዳዉን ለማስታወስና የአላህን ስም ከፍ ለማድረግ በተለያዩ አጋጣሚዎች ድምጽን ከፍ አድርጎ እነዚህን ዚክሮች ማድረግ ይወደዳል። عن عبد الله بن عمر رضي الله عنهما عن النبي صلى الله عليه وسلم قال : "ما من أيام أعظم عند الله ولا أحب إليه العمل فيهن من هذه الأيام العشر فأكثروا فيهن من التهليل والتكبير والتحميد"  أخرجه احمد 7/224 وصحّح إسناده أحمد شاكر ዓብዱላህ ኢብኑ ዑመር ባስተላለፉት ሀዲስ ነብዩ እንዲህ ብለዋል፤ «ከነዚህ አስር ቀናት በበለጠ አላህ ዘንድ ታላቅ የሆኑና መልካም ስራ እጅግ የተወደደባቸው ቀናት የሉም፤ ተህሊል ተክቢር እና ተህሚድ አብዙ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል አህመድ ሻኪርም ሰሂህነቱን አረጋግጠዋል። ከተክቢር አደራረግ መካከል፤ الله أكبر ، الله أكبر لا إله إلا الله ، والله أكبر ولله الحمد “አላሁ አክበር፤ አላሁ አክበር፤ ላ ኢላሀ ኢለላህ ወላሁ አክበር ወሊላሂልሀምድ” የሚለው ዋነኛው ሲሆን ሌሎችም ይዘቶች አሉት። በእነዚህ ቀናት ውስጥ ሊደረግ የሚገባው ይህ ተክቢር ብዙ ሰዎች ስለማይፈጽሙት እየተረሱ ካሉ ሱናዎች መካከል ነው። ሰዎችን ለማስታወስ እና ሱናን ህያው ለማድረግ ድምጽን ከፍ አድርጎ ተክቢር ማድረግ ያስፈልጋል። ዓብዱላህ ኢብኑ ኡመር እና አቡሁረይራህ በነዚህ አስር ቀናት ገበያ ወጥተው ተክቢራ ሲያደርጉ ሰዎችም እያስታወሱ ተክቢራ ያደርጉ እንደነበር ተዘግቧል። ይህም፤ ሁሉም ሰው የራሱን ዚክር ያደርጋል ማለት ነው እንጂ ሰዎች እየተሰባሰቡ በአንድ ድምጽ ተክቢራ ያድርጉ ማለት አይደለም። ይህ መረጃ ያልተገኘለት የተሳሳተ አፈፃፀም ነው። 3. ሐጅና ዑምራ፦ በነዚህ ቀናት ውስጥ ከሚፈጸሙ መልካም ስራዎች መካከል ሐጅ ማድረግ ይገኝበታል፤ በነዚህ አስር ቀናት የሐጅ ዒባዳ ላይ ተገኝቶ በተገቢው መልኩ ከፈጸመው በአላህ ፍቃድ ከተከታዩ የአላህ መልዕክተኛ ብስራት ድርሻ ይኖረዋል፤ عن أبي هريرة رضي الله عنه قال: سمعته يقول: "الحج المبرور ليس له جزاء إلا الجنة" متفق عليه. ከአቡ ሁረይራ በተላለፈ ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ «ከወንጀል የራቀና ተቀባይነት ያለው ሐጅ (አል-ሐጅ አል-መብሩር) ምንዳው ጀነት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡» ቡኻሪና ሙስሊም ተስማምተውበታል 4. ኡድሂያ፦ በነዚህ አስር ቀናት ከተወደዱ ተግባሮች መካከል ኡድሂያን በማረድ ወደአላህ መቃረብ ነው። የሚከተሉት ነጥቦች አጠር ያለ ግንዘቤን ይሰጣሉ፤ - ኡድሂያ በጣም ከጠነከሩ የነብዩ ሱናዎች መካከል ነው። የነብዩ ኢብራሂምን ሱና ህያው ከማድረጉ በተጨማሪ ለድሆች እና ችግረኞች መድረስ ነው። - ኡድሂያን በተመለከተ አላህ ከኛ የሚፈልገው ለእርሱ ያለንን ፍራቻ (ተቅዋ) ነው። - ኡድሂያ የሚታረደው ከዒድ ሰላት በኋላ ነው። የአላህ መልዕክተኛ ከኢድ ሰላት በፊት ያረደ ሰው እንዲደግም አዘዋል። - ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት የዒድ ሰላት ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ የሶስተኛው ቀን ጸሀይ እስክትጠልቅ ድረስ ኡድሂያን ማረድ ይቻላል። - ግመል፣ የቀንድ ከብቶች፣ በግና ፍየል ለኡድሂያ ይታረዱሉ። - የአላህ መልዕክተኛ እንከን ያለባቸውን እንስሳት እንዳናርድ ከልክለዋል። አንድ አይኑ የታወረ፣  ስብራት ያለበት፣ የከሳና የደከመ፣ የታመመ እንስሳ ለኡድሂያ አይሆንም። - ኡድሂያን ለብቻ ማረድ እንደሚቻለው ሁሉ ለሰባት ሆኖ አንድን ወይፈን ወይም በሬ መጋርትም ይቻላል። - አንድ ሰው ኡድሂያ ሲያርድ ለራሱ እና በህይወት ላሉም ይሁን በህይወት ለሌሉ ለቤተሰቦቹ አስቦ ሊያርድ ይችላል። - ኡድሂያውን ለራሱ፣ ለስጦታ እና ለሰደቃ አድርጎ መከፋፈሉ ሱና ነው። ይህ ማለት ግን እንደ አስፈላጊነቱ ለሶስቱም ያውለዋል ማለት እንጂ ሶስት እኩል ቦታዎች ይከፋፍለዋል ማለት አይደለም። - በዒድ ቀን ኡድሂያን ለማረድ አስቦ የዙልሂጃ ወር ከገባ ጥፍሩንና ጸጉሩን አይቆርጥም። ቆዳውንም አይቀርፍም። ይህ በሀጅ ላይ ያሉ ሰዎችን የሚመሳሰልበት ነብያዊ ትዕዛዝ ነው። ሆኖም ይህ የሚመለከተው የሚያርደዉን ሰው ብቻ ነው። እያወቀ ጥፍሩን ወይም ጸጉሩን የቆረጠ ወንጀል ፈጽሟልና ወደ አላህ በተውበት ሊመለስ ይገባዋል፤ ኡድሂያው ግን አይበላሽም።    የመልካም ስራ በሮች ብዙ ናቸውና የቻልነዉን ሁሉ በመፈጸም ወደ አላህ መቃረብ ይገባል፤ የታሰረን ወይም የታመመን ሰው መጠየቅ፣ ዝምድናን መቀጠል፣ ሰደቃ ማብዛት፣ ሱና ሰላቶችን ማብዛት፣ ቁርዓን መቅራት፣ ዚክር ማብዛት፣ ዱዓን ማብዛት…ወዘተ ያስፈልጋል።    አላህ በነዚህ ወርቃማ ጊዜያት ከሚጠቀሙና አላህ ዘንድ መልካም ምንዳን ከሚያገኙ ጠንካራና ብልህ የአላህ ባሮች ያድርገን። ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ ህዳር 23/ 2004 ዓ.ል ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

በአላህ ፈቃድ ዛሬ እሁድ ግንቦት 27/2015 ወደ ምእራብ ኢትዮጵያ በተደረገ ቃፊላ የዳዕዋ ጉዞ 500 ሰዎች በኡስታዝ ሙሀመድ ሀሰን ማሜ እጅ ኢስላምን ተቀብለዋል። አላህ ፅናትና ጥንካሬን እንዲለግሳቸው እንለምነዋለን። አልሐምዱሊላህ ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር Ibnu Mas'oud Islamic Center @merkezuna

🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts - Статистика и аналитика Telegram-канала @abujunaidposts