fa
Feedback
🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

رفتن به کانال در Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

نمایش بیشتر
2 174
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-27 عوز
-1930 عوز
آرشیو پست ها
🔖 የኑህ መርከብ 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ Share link https://t.me/nesihastudio/2152 @nesihastudio

🔖 የኑህ መርከብ 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ የቢድዓን አደጋዎች የሚያብራራ እና ለቢድአ አራማጆች ማደናገሪያ ሹብሐዎች ምላሽ የሚሰጥ በጃሊያ አዳራሽ የቀረበ ጠቃሚ ትምህርት ትምህርቱ በነሲሓ ድረ http://nesiha.com/wp-content/uploads/2018/05/የኑህ-መርከብ.mp3 @abujunaidposts

ቅድሚያ ለተውሒድ Arabic/Amharic 🎙 ዶ/ሸይኽ አብደላህ አልጀርቡዕ ሀፊዘሁላህ 💾 የ1424 የፓልቶክ ሙሐደራ ከአማርኛ ትርጉም ጋር በአቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/125 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

እናስተውል፤ ፀባይ (አኽላቅ) ልክ እንደ ሪዝቅ ነው! የዱንያ ሀብታምና ደሀ እንዳለ ሁሉ የአኽላቅም ሀብታምና ደሀ አለ። አላህ ዘንድ በፆምና በለይል ሰላት የማይገኝ ክብርና ደረጃ በመልካም ፀባይ ይገ
እናስተውል፤ ፀባይ (አኽላቅ) ልክ እንደ ሪዝቅ ነው! የዱንያ ሀብታምና ደሀ እንዳለ ሁሉ የአኽላቅም ሀብታምና ደሀ አለ። አላህ ዘንድ በፆምና በለይል ሰላት የማይገኝ ክብርና ደረጃ በመልካም ፀባይ ይገኛል። እውነተኛው ሀብታም አመለ ሸጋ ሰው ነው! ስለዚህም፤ وَإِنَّكَ لَعَلَىٰ خُلُقٍ عَظِیمࣲ "አንተም በታላቅ ፀባይ ላይ ነህ" በማለት አላህ የመሰከረላቸው ታላቁ ነብይ ሾለ ፀባያቸው ማማር በመጨነቅ "አላህ ሆይ አፈጣጠሬን እንዳሳመርከው ጠባዬንም አሳምርልኝ" ብለው ዱዓ ያደርጉ ነበር። ሙስሊም በዘገቡት ሐዲስ ደግሞ፤ وَاهْدِنِي لِأَحْسَنِ الْأَخْلَاقِ لَا يَهْدِي لِأَحْسَنِهَا إِلَّا أَنْتَ، وَاصْرِفْ عَنِّي سَيِّئَهَا Ů„َا يَصْرِفُ ŘšŮŽŮ†Ů‘ِي سَيِّئَهَا إِلَّا أَنْتَ (ካንተ ውጭ ማንም ለመልካም ፀባይ ሊገራኝ አይችልምና ያማረ ፀባይን አግራልኝ። ካንተ ውጭ ከመጥፎ ፀባይ የሚያርቀኝ የለምና ከመጥፎው አንተው አርቀኝ) ይሉ ነበር። የአኽላቅ ደረጃ ከፍ ያለ ነው። በሐዲስ እንደተላለፈው፤ «የቂያማ ቀን ከመልካም ስነ-ምግባር የበለጠ ሚዛን የሚደፋ ምንም ነገር የለም። የመልካም ስነ-ምግባር ባለቤት የስነ-ምግባሩ ማማር፤ ከፈርድ አልፎ ሱንና ሰላትና ጾም የሚያዘወትር ሰው ደረጃ ላይ ያደርሰዋል» ቲርሚዚ ዘግበውታል አላህ መልካም ፀባይን ይለግሰን፤ ከነፍሳችንና ከሸይጣን ክፋት ሁሉ ይጠብቀን! ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🔖 ሱናን መከተል 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/394 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

📹 መውሊድ ኢስላማዊ በዓል ነውን? በነሲሓ ቲቪ  የቀረበ አጭር  ውይይት  🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/514 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

መውሊድ ኢስላማዊ በዓል ነውን? ⌚️ በነሲሓ ቲቪ የቀረበ አጭር ውይይት 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/411 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

📌 بشرى لطلبة العلم دورة ميراث الأنبياء العلمية الثالثة من ١٠ صفر ١٤٤٥هے‍ الموافق ٢٦\٨\٢٠٢٣م إلى يوم الأحد ١٨ صفر ١٤٤٥هے‍ الم
📌 بشرى لطلبة العلم دوع؊ ميراث الأنبياء العلمية الثالثة من ŮĄŮ  ؾفع ١٤٤٥هے‍ الموافق ٢ٌ\٨\٢٠٢٣م إلى يوم الأحد  ٥٨ ؾفع ١٤٤٥هے‍ الموافق ٢\ŮŠ\٢٠١٩م ŮĄ) كتاب البيوع من عمدة الأحكام 🎙 ŘŻ/ حسن أحمد الهواري حفظه الله   ےے❊❊ےے ٢) رسالة لطيفة في أصول الفقه 🎙 ŘŻ/ ؚبد الرحمن حامد آل نابت حفظه الله ےے❊❊ےے ŮŁ) منهج أهل السنة والأشاعرة في الصفات 🎙 ŘŻ/ خالد ؚبد اللطيف حفظه الله ےے❊❊ےے ٤) التأسيس في بيان آيات المواريث 🎙 الدكتور خليل حامد خليل حفظه الله ےے❊❊ےے ŮĽ) نخبة الفكر في المصطلح 🎙 ŘŻ/معاذ عبدالرحيم ؎و؏؊ حفظه الله ےے❊❊ےے ŮŚ) منظومة أصول الفقه والقواعد للعثيمين 🎙الشيخ أبو حنيف إلياس أحمد محمد ےے❊❊ےے ملاحظة - * هناك محاضرات مختلفة تؾاحب الدورة * الخدمات للطلاب المسجلين فقط ولكن يحق الحضور والاستفادة من الدروس للجميع * يتم نقل الدروس والمحاضرات على قناة المركز على تيليغرام * جميع الدروس باللغة العربية فقط 🕌 مكان إقامة الدورة معهد داع الحديث لتعليم اللغة العربية والعلوم الشرعية بمبنى المركز في حي ٥٨ _ مركز ابن مسعود الإسلامي بأديس أبابا t.me/merkezuna الموقع على الخريطة:- https://goo.gl/maps/oC7GZtpeLwkzxrVr8

📌 بشرى لطلبة العلم دورة ميراث الأنبياء العلمية الثالثة من ١٠ صفر ١٤٤٥هے‍ الموافق ٢٦\٨\٢٠٢٣م إلى يوم الأحد ١٨ صفر ١٤٤٥هے‍ الم
📌 بشرى لطلبة العلم دوع؊ ميراث الأنبياء العلمية الثالثة من ŮĄŮ  ؾفع ١٤٤٥هے‍ الموافق ٢ٌ\٨\٢٠٢٣م إلى يوم الأحد  ٥٨ ؾفع ١٤٤٥هے‍ الموافق ٢\ŮŠ\٢٠١٩م ŮĄ) كتاب البيوع من عمدة الأحكام 🎙 ŘŻ/ حسن أحمد الهواري حفظه الله   ےے❊❊ےے ٢) رسالة لطيفة في أصول الفقه 🎙 ŘŻ/ ؚبد الرحمن حامد آل نابت حفظه الله ےے❊❊ےے ŮŁ) منهج أهل السنة والأشاعرة في الصفات 🎙 ŘŻ/ خالد ؚبد اللطيف حفظه الله ےے❊❊ےے ٤) التأسيس في بيان آيات المواريث 🎙 الدكتور خليل حامد خليل حفظه الله ےے❊❊ےے ŮĽ) نخبة الفكر في المصطلح 🎙 ŘŻ/معاذ عبدالرحيم ؎و؏؊ حفظه الله ےے❊❊ےے ŮŚ) منظومة أصول الفقه والقواعد للعثيمين 🎙الشيخ أبو حنيف إلياس أحمد محمد ےے❊❊ےے ملاحظة - * هناك محاضرات مختلفة تؾاحب الدورة * الخدمات للطلاب المسجلين فقط ولكن يحق الحضور والاستفادة من الدروس للجميع * يتم نقل الدروس والمحاضرات على قناة المركز على تيليغرام * جميع الدروس باللغة العربية فقط 🕌 مكان إقامة الدورة معهد داع الحديث لتعليم اللغة العربية والعلوم الشرعية بمبنى المركز في حي ٥٨ _ مركز ابن مسعود الإسلامي بأديس أبابا http://www.t.me/merkezuna الموقع على الخريطة:- https://goo.gl/maps/oC7GZtpeLwkzxrVr8

🍂 ደስተኛ ኢስላማዊ ቤተሰብ 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚️ የ 51 ደቂቃ ሙሀደራ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/103 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

የሺዓና የአህሉሱና የዓሹራ ውሎ ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ ሙሀረም 12/ 1436 ዓ.ሒ ተፃፈ የዓሹራ ቀን፤ የፊዓአውንን ትእቢትና አምባገነነንነት ያከተመበትና ለሌሎችም መቀጣጫ የሆነበት፣ ነብዩላህ
የሺዓና የአህሉሱና የዓሹራ ውሎ ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ ሙሀረም 12/ 1436 ዓ.ሒ ተፃፈ የዓሹራ ቀን፤ የፊዓአውንን ትእቢትና አምባገነነንነት ያከተመበትና ለሌሎችም መቀጣጫ የሆነበት፣ ነብዩላህ ሙሳም የተደሰቱበት ለአህሉሱና ታላቅ ትርጉም ያለው የድል ብስራት ቀን ነው። አህሉሱና ይህንን ቀን በአል አያደርጉትም። የተለየ ድግስም ሆነ አለባበስ የላቸውም። ሆኖም መልእክተኛው ﷺ በደነገጉት መሰረት ይፆሙታል፣ መልካም ተግባራትን ይፈፅሙበታል፣ ከአላህ ልዩ ምንዳን በመከጀልም በዒባዳ ያሳልፉታል። ሺዓዎች ግን ስለ ዓሹራ ቀን ሲያስቡ ሚታወሳቸው የታላቁ ሰሀቢይ የአሊይ ኢብኑ አቢ ጣሊብ ልጅ ሁሰይን የተገደሉበት ቀን መሆኑ ብቻ ነው። ሺዓዎች በዚህ ቀን ሀዘናቸውን ለመግለፅ እራሳቸውን የሚጎዱ ብዙ ነገሮችን በስፋት ይፈፅማሉ። ጭንቅላትንና ሌሎች አካሎቻቸውን በስለት መብጣትና ማድማት (ተጥቢር)፣ ፊታቸውን መደብደብ (ለጥም፣) እራስን በሰንሰለት መግረፍና ማንገላታት፣ በእንብርክክ መሄድ፣ ብዙዎችም ዘንድ ጥቁር መልበስና የለቅሶ ሙሾ ማውረድ ብሎም በራስ ላይ ኩነኔን መጥራት የተለመዱ የአሹራ ትእይንቶቻቸው ናቸው። በእጅጉ ይገርማል፤ ለኛ ለአህሉሱና ደስታን ሲያላብሰን፣ ተስፋን አሰንቆ ድልን ሲያበስረን፤ ለወንጀላችን ማርታን ለማግኘት ሩጫ ውስጥ ሲከተን፤ ለሺአዎች ግና፤ የሀዘን የዋይታ፣ የውድቀት የሽንፈት ማስታወሻ፣ የተስፋ ማጨለሚያ ነው!! ሁሰይን የነብዩ ﷺ የልጅ ልጅ በኢስላማዊ እውቀት ከመጠቁ ታላላቅ ሰሀቦች አንዱ ናቸው። በኢባዳ ብርቱ የተወዳጇ የመልእክተኛው ﷺ ልጅ የፋጢማ ረዲየላሁ አንሀ ልጅ ናቸው። ሆኖም... ቀሪውን በዚህ ሊንክ ያንብቡ http://clearfaith.blogspot.com/2015/10/blog-post.html?m=1 ------ 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🗞 ስለ ዓረፋ ቀን ዱዓእ ሁለት ነጥቦች ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ [1] በኢድ ዋዜማው የዓረፋ እለት ዱዓእ ተቀባይነት እንዳለው የሚዘክሩ ሀዲሶች ሀጅ ላይ የሌሉ ሰዎችንም ይመለከታሉን?? የአላህ መልእክተኛ «ከዱዓዎች ሁሉ በላጩ (የኢድ ዋዜማ) የአረፋ ቀን ዱዓ ነው...» ማለታቸውን ቲርሚዚይ ከአብዱላህ ኢብኑ ኡመር የዘገቡ ሲሆን፤ ሌሎች ተመሳይ ይዘት ያላቸው ሀዲሶችም ይገኛሉ። ታዲያ የዓረፋን እለት በዱአዕና በዚክር ያሳለፈ ሰው ታላቅ ክብርና ምንዳን የሚያገኘው ሀጅ ላይ ሲሆን ብቻ ነውን? በእርግጥ በዚህ እለት ክብር ባለው የዓረፋ ምድር የተገኘ ሰው የጊዜንም የቦታንም ክብር ተጎናፅፏልና በተሻለ ሁኔታ ላይ መገኘቱ እንዲሁም ዱአው ተቀባይነት ለማግኘት የቀረበ መሆኑ አያጠራጥርም። ይሁንና ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት፤ እነዚህ ከአረፋ እለት ክብር ጋር ተያይዞ የዱአ ተቀባይነትን የተመለከቱ ሀዲሶች በማንኛውም ቦታ የሚገኙ ሙስሊሞችን ይመለከታሉ። በመሆኑም በሀጅ ስራ ላይ የሌሉ ሰዎችም በዱዓ ሊበረቱ ይገባል። ታላቁ አሊም ሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን በዚህ እለት የሚባሉ በሀዲስ የተላለፉ ዱአዎችን አስመልክቶ ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎች መሆኑን ተጠይቀው ተከተዩን መልሰዋል¹ «በምላሻችን እንደገለፅነው፤ ይህ ለሁጃጆችንም ይሁን ሌሎችን የተመለከተ ጥቅል መልእክት ነው። ነገር ግን ሀጅ ላይ ላሉ ሰዎች ይበልጥ የተገባ ነው። ምክኒያቱም ሁጃጆች በዚህ እለት በዓረፋ ምድር በኢህራም ውስጥ ስለሚገኙ ከሌሎች በበለጠ ዱዓቸው ተቀባይነት ለማግኘት የቀረበ ነው። ስለዚህም የዓረፋን እለት በሀጅ ተግባር ላይ የሌሉ ሰዎች እንዲፆሙት ተደንግጓል። እለቱ ብልጫ ያለወወ ስለሆነም አላህን በማስታወስ፣ ማርታን በመለመን እና ዱዓ በማድረግ ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ፤ ሁጃጆችንም በኢባዳ ይካፈሏቸዋል ማለት ነው።» ከሸይኹ ድረገፅ የተወሰደ የድምፅ ፈትዋ [2] በዓረፋ እለት ሁጃጆች በአረፋ ምድር እንደሚሰባሰቡት ለዱዓና ለዚክር መሰባሰብ "ታዕሪፍ"ን በተመለከተ፤ ይህ ተግባር አንዳንድ ሰለፎች እንደፈፀሙት የተረጋገጠ ነው። ከነሱም መካከል ኢብኑ አባስ ይገኙበታል፤ ኢማሙ አህመድም ባይተገብሩትም እንደሚቻል ተናግረዋል። ነገር ግን ያወገዙትና ከቢድአ የመደቡትም አሉ። የኡለማዎቻችንን ማብራሪያዎች ስንፈትሽ ተከታዮቹ ድምዳሜዎች ላይ ያደርሱናል፤ 1) "ታእሪፍ"ን መተግበር በራሱ ችግር የለውም። ተግባሩን እንደሱና ወይም ሙስተሀብ ነገር መውሰድ ግን አይገባም። ጉዳዩ የኢጅቲሀድ መስአላ ነውና ተግባሩ የሚወገዝ ተግባር አይሆንም። የፈፀመውም ሰው ቢድአ ሰራ አይባልም። 2) ታእሪፍ ስንል ከምድረ አረፋ ውጭ ባሉ የየሀገሩና የየከማው መስጂዶች መሰባሰብን የተመለከተ እነጂ ለዚህ ብሎ ጉዞ ማድረግ አይፈቀድም። አላህ የአረፋን ምድር ለዚህ ቀን ኢባዳ መሰባሰቢያ እንደመረጠው በየሀገሩ አንዳንድ ቦታዎችን፣ መስጅዶችንና ቀብሮችን በመምረጥ ወደነሱ ጉዞ አድርጎ መሰባሰብ በፍፁም አይፈቀድም። ይህ የነብዩ መስጂድንም ይሁን በይተልመቅዲስን ያካትታል። 3) ይህ መሰባሰብ ጩኸትና ሱና ያልሆኑ የጋራ አምልኮዎች ከታከሉበት ቢድአ እንደሚሆን አያጠራጥርም። በተመሳሳይ መልኩ ኢባዳ ያልሆኑ ግጥሞችና መንዙማዎችን ለዚህ መለያ ማድረግ ጥፋት ነው። እነዚህን ነጥቦች በዝርዝር ለመረዳት የሚያስችሉ ማብራሪያዎችን ከኡለማዎች ድርሳናት እንደሚከተለው እናያለን። ቀሪዉን የፅሁፍ ክፍል ተከታዩን ሊንክ በመከተል ያንብቡት https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=10160553120869684&id=682494683 __ 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች t.me/abujunaidposts

🔖 ተውሒድ እና የሐጅ ፍሬዎች 🎙 አቡጁነይድ እና ጣሀ አህመድ በ 2002 በጃሊያ አዳራሽ የቀረበ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/219 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🗞 ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው አስርቱ የዙልሂጃ ቀናት ✍ ዝግጅት፦ አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ህዳር 2004 🔗 የፅሁፉ ሊንክ https://d1.islamhouse.com/data/am/ih_articles/single/am_Virtues_of_the_Ten_Days_of_Dhul_Hijjah.pdf 🔗 telegram Share Link https://t.me/abujunaidposts/374 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🗞 ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው አስርቱ የዙልሂጃ ቀናት    ምስጋና ለአላህ የተገባ ነው፡፡ የአላህ ሰላምና እዝነት በታላቁ ነብይ በሙሀመድ በባልደረቦቻቸው እና በቤተሰቦቻቻው ሁሉ ላይ ይሁን፡፡    ከተከበሩት ወራት መካከል አንዱ የሀጅ ወር ዙልሂጃ ነው። ከቀናት ሁሉ አላህ ዘንድ የተወደዱት ደግሞ አስሩ የዙልሂጃ ቀናት ናቸው። እንደዉም ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው እነኝህ ቀናት ናቸው። የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፦ عن جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللهِ رَضِيَ الله عَنْهُ قَالَ: قَالَ رَسُولَ اللهِ صَلَّى الله عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:  "أَفْضَلُ أَيَّامِ الْدُّنْيَا أَيَّامُ الْعَشْرِ، يَعْنِي عَشْرُ ذِي الحْجَّةِ". صحيح الجامع ، رقم 1133 ጃቢር ኢብኑ ዓብዲላህ ባስተላለፉት ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል «ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው፤ አስርቱ ቀናት ናቸው። ማለትም አስሩ የዙልሂጃ ቀናት» አልባኒ ሰሂሁል ጃሚዕ 1133 ላይ አስፍረውታል عن ابن ؚباس رضي الله عنهما، عن النبي صلى الله عليه وسلم قال: "ما من أيام العمل الصالح فيهن أحب إلى الله منه في هذه الأيام العشر. قالوا ولا الجهاد في سبيل الله !! قال : ولا الجهاد في سبيل الله، إلا رجل ؎ع؏ بنفسه وماله ولم يرجع من ذلك بشيء" أخرجه البخاري ከኢብኑ ዓባስ በተዘገበ ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል:‐ «በነዚህ አስር ቀናቶች ውስጥ ከሚፈጸሙ መልካም ስራዎች በበለጠ ስራዎች አላህ ዘንድ የተወደዱ የሚሆኑባቸው ቀናት የሉም፤ “በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሀድም ጭምር?” ተባሉ። እርሳቸውም፤ “ራሱንና ንብረቱን ይዞ ወጥቶ ምንም ያልተመለሰለት ሰው ሲቀር ጂሀድም ከዚህ አይበልጥም” አሉ።» ቡኻሪ ዘግበውታል በነዚህ ቀናቶች ትኩረት ልንሰጣቸው ከሚገቡ የዒባዳ አይነቶች መካከል:‐ 1. ጾም፦ ጾም ከስራዎች ሁሉ በላጭ ነውና በእነዚህ ቀናት መጾም እጅግ የተወደደ ነው። የአላህ መልዕክተኛ ዘጠኙን የዙልሂጃ ቀናት ይጾሙ እንደነበር ተዘግቧል። (አስረኛው ቀን ግን ዒድ ስለሆነ አይጾምም) 2. ዚክሮችን ማብዛት፦ አላህን ማመስገን (አልሀምዱሊላህ) ፣ ተክቢር፣ ተስቢህ(ሱብሀነላህ) እና ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢለላህ)፤ ኢባዳዉን ለማስታወስና የአላህን ስም ከፍ ለማድረግ በተለያዩ አጋጣሚዎች ድምጽን ከፍ አድርጎ እነዚህን ዚክሮች ማድረግ ይወደዳል። عن ؚبد الله بن عمر رضي الله عنهما عن النبي صلى الله عليه وسلم قال : "ما من أيام أعظم عند الله ولا أحب إليه العمل فيهن من هذه الأيام العشر فأك؍عوا فيهن من التهليل والتكبير والتحميد"  أخرجه احمد 7/224 وصحّح إسناده أحمد شاكع ዓብዱላህ ኢብኑ ዑመር ባስተላለፉት ሀዲስ ነብዩ እንዲህ ብለዋል፤ «ከነዚህ አስር ቀናት በበለጠ አላህ ዘንድ ታላቅ የሆኑና መልካም ሾል እጅግ የተወደደባቸው ቀናት የሉም፤ ተህሊል ተክቢር እና ተህሚድ አብዙ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል አህመድ ሻኪርም ሰሂህነቱን አረጋግጠዋል። ከተክቢር አደራረግ መካከል፤ الله أكبع ، الله أكبع لا إله إلا الله ، والله أكبع ولله الحمد “አላሁ አክበር፤ አላሁ አክበር፤ ላ ኢላሀ ኢለላህ ወላሁ አክበር ወሊላሂልሀምድ” የሚለው ዋነኛው ሲሆን ሌሎችም ይዘቶች አሉት። በእነዚህ ቀናት ውስጥ ሊደረግ የሚገባው ይህ ተክቢር ብዙ ሰዎች ስለማይፈጽሙት እየተረሱ ካሉ ሱናዎች መካከል ነው። ሰዎችን ለማስታወስ እና ሱናን ህያው ለማድረግ ድምጽን ከፍ አድርጎ ተክቢር ማድረግ ያስፈልጋል። ዓብዱላህ ኢብኑ ኡመር እና አቡሁረይራህ በነዚህ አስር ቀናት ገበያ ወጥተው ተክቢራ ሲያደርጉ ሰዎችም እያስታወሱ ተክቢራ ያደርጉ እንደነበር ተዘግቧል። ይህም፤ ሁሉም ሰው የራሱን ዚክር ያደርጋል ማለት ነው እንጂ ሰዎች እየተሰባሰቡ በአንድ ድምጽ ተክቢራ ያድርጉ ማለት አይደለም። ይህ መረጃ ያልተገኘለት የተሳሳተ አፈፃፀም ነው። 3. ሐጅና ዑምራ፦ በነዚህ ቀናት ውስጥ ከሚፈጸሙ መልካም ስራዎች መካከል ሐጅ ማድረግ ይገኝበታል፤ በነዚህ አስር ቀናት የሐጅ ዒባዳ ላይ ተገኝቶ በተገቢው መልኩ ከፈጸመው በአላህ ፍቃድ ከተከታዩ የአላህ መልዕክተኛ ብስራት ድርሻ ይኖረዋል፤ عن أبي هريرة رضي الله عنه قال: سمعته يقول: "الحج المبرور ليس له ؏زاإ إلا الجنة" متفق عليه. ከአቡ ሁረይራ በተላለፈ ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ «ከወንጀል የራቀና ተቀባይነት ያለው ሐጅ (አል-ሐጅ አል-መብሩር) ምንዳው ጀነት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡» ቡኻሪና ሙስሊም ተስማምተውበታል 4. ኡድሂያ፦ በነዚህ አስር ቀናት ከተወደዱ ተግባሮች መካከል ኡድሂያን በማረድ ወደአላህ መቃረብ ነው። የሚከተሉት ነጥቦች አጠር ያለ ግንዘቤን ይሰጣሉ፤ - ኡድሂያ በጣም ከጠነከሩ የነብዩ ሱናዎች መካከል ነው። የነብዩ ኢብራሂምን ሱና ህያው ከማድረጉ በተጨማሪ ለድሆች እና ችግረኞች መድረስ ነው። - ኡድሂያን በተመለከተ አላህ ከኛ የሚፈልገው ለእርሱ ያለንን ፍራቻ (ተቅዋ) ነው። - ኡድሂያ የሚታረደው ከዒድ ሰላት በኋላ ነው። የአላህ መልዕክተኛ ከኢድ ሰላት በፊት ያረደ ሰው እንዲደግም አዘዋል። - ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት የዒድ ሰላት ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ የሶስተኛው ቀን ጸሀይ እስክትጠልቅ ድረስ ኡድሂያን ማረድ ይቻላል። - ግመል፣ የቀንድ ከብቶች፣ በግና ፍየል ለኡድሂያ ይታረዱሉ። - የአላህ መልዕክተኛ እንከን ያለባቸውን እንስሳት እንዳናርድ ከልክለዋል። አንድ አይኑ የታወረ፣  ስብራት ያለበት፣ የከሳና የደከመ፣ የታመመ እንስሳ ለኡድሂያ አይሆንም። - ኡድሂያን ለብቻ ማረድ እንደሚቻለው ሁሉ ለሰባት ሆኖ አንድን ወይፈን ወይም በሬ መጋርትም ይቻላል። - አንድ ሰው ኡድሂያ ሲያርድ ለልሹ እና በህይወት ላሉም ይሁን በህይወት ለሌሉ ለቤተሰቦቹ አስቦ ሊያርድ ይችላል። - ኡድሂያውን ለራሱ፣ ለስጦታ እና ለሰደቃ አድርጎ መከፋፈሉ ሱና ነው። ይህ ማለት ግን እንደ አስፈላጊነቱ ለሶስቱም ያውለዋል ማለት እንጂ ሶስት እኩል ቦታዎች ይከፋፍለዋል ማለት አይደለም። - በዒድ ቀን ኡድሂያን ለማረድ አስቦ የዙልሂጃ ወር ከገባ ጥፍሩንና ጸጉሩን አይቆርጥም። ቆዳውንም አይቀርፍም። ይህ በሀጅ ላይ ያሉ ሰዎችን የሚመሳሰልበት ነብያዊ ትዕዛዝ ነው። ሆኖም ይህ የሚመለከተው የሚያርደዉን ሰው ብቻ ነው። እያወቀ ጥፍሩን ወይም ጸጉሩን የቆረጠ ወንጀል ፈጽሟልና ወደ አላህ በተውበት ሊመለስ ይገባዋል፤ ኡድሂያው ግን አይበላሽም።    የመልካም ሾል በሮች ብዙ ናቸውና የቻልነዉን ሁሉ በመፈጸም ወደ አላህ መቃረብ ይገባል፤ የታሰረን ወይም የታመመን ሰው መጠየቅ፣ ዝምድናን መቀጠል፣ ሰደቃ ማብዛት፣ ሱና ሰላቶችን ማብዛት፣ ቁርዓን መቅራት፣ ዚክር ማብዛት፣ ዱዓን ማብዛት…ወዘተ ያስፈልጋል።    አላህ በነዚህ ወርቃማ ጊዜያት ከሚጠቀሙና አላህ ዘንድ መልካም ምንዳን ከሚያገኙ ጠንካራና ብልህ የአላህ ባሮች ያድርገን። ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ ህዳር 23/ 2004 ዓ.ል ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

በአላህ ፈቃድ ዛሬ እሁድ ግንቦት 27/2015 ወደ ምእራብ ኢትዮጵያ በተደረገ ቃፊላ የዳዕዋ ጉዞ 500 ሰዎች በኡስታዝ ሙሀመድ ሀሰን ማሜ እጅ ኢስላምን ተቀብለዋል። አላህ ፅናትና ጥንካሬን እንዲለግሳቸው እንለምነዋለን። አልሐምዱሊላህ ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር Ibnu Mas'oud Islamic Center @merkezuna

⛱ የመስጂዶች ሚና 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/399 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

⛱ የመስጂዶች ሚና 🎙አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Telegram Link https://t.me/abujunaidposts/397 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

የእናቶች ቀን... ሙስሊሞች እንዴት ያዩታል? እኛ ሙስሊሞች፤ እናትን በመታዘዝ፣ ለእናት መልካም በመዋልና አሷን በማስደሰት ታዘናል። እናትን ከመበደልና በሷ ላይ ከማመፅ በእጅጉ ተከልክለናል። ለእናት ክብር እንሰጥ ዘንድ በእርግዝና ወቅት ምን ያክል ድካምና እንግልት እንደሚገጥማት ቁርአን ያሳስበናል። (ﻭَﻭَﺻَّﻴْﻨَﺎ اﻹِْﻧﺴَﺎﻥَ ﺑِﻮَاﻟِﺪَﻳْﻪِ ﺣَﻤَﻠَﺘْﻪُ ﺃُﻣُّﻪُ ﻭَﻫْﻨًﺎ ﻋَﻠَﻰٰ ﻭَﻫْﻦٍ ﻭَﻓِﺼَﺎﻟُﻪُ ﻓِﻲ ﻋَﺎﻣَﻴْﻦِ ﺃَﻥِ اﺷْﻜُﺮْ ﻟِﻲ ﻭَﻟِﻮَاﻟِﺪَﻳْﻚَ ﺇِﻟَﻲَّ اﻟْﻤَﺼِﻴﺮُ) لقمان 14 «ሰውንም በወላጆቹ (በጎ እንዲያደርግ) በጥብቅ አዘዝነው፡፡ እናቱ ከድካም በላይ በሆነ ድካም አረገዘችው፡፡ ጡት መጣያውም በሁለት ዓመት ውስጥ ነው፡፡ ለእኔም ለወላጆችህም አመስግን በማለት አዘዝነው፡፡ መመለሻውም ወደኔ ነው፡፡» ሉቅማን 31:14 እኛ ዘንድ እናትን ማገልገል በህይወት ዘመኗ ብቻ ሳይሆን ከሞተችም በኃላ ይቀጥላል። አንድ ሙስሊም ለእናቱ ያለውን ክብር ከሚገልፅባቸው ተግባራት መካከል፤  የእናትን ኑዛዜ ተግባራዊ ማድረግ፣ ዱዓ ማድግ፣ ከአላህ ማርታን መጠየቅ፣ ቤተሰቧንና ጓደኞቿን ማክበር ይገኝበታል።  በጥቅሉ እናትን ማስደሰት ለጀነት ከሚያበቁ ታላላቅ መልካም ስራዎች ይመደባል። በኢስላማዊ ሸሪዓ ለእናት የተሰጠውን ክብር በየትኛውም ምድራዊ ህግ ወይም ሀይማኖት አናገኘውም። እናትን አስመለክቶ የተጣለብን ሀላፊነት ከአባት የበለጠ መሆኑም ተገልፆልናል።   عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ : [جَاءَ رَجُلٌ إِلَى رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ فَقَالَ : يَا رَسُولَ اللَّهِ ، مَنْ أَحَقُّ النَّاسِ بِحُسْنِ صَحَابَتِي ؟ قَالَ : أُمُّكَ . قَالَ : ثُمَّ مَنْ ؟ قَالَ : ثُمَّ أُمُّكَ . قَالَ : ثُمَّ مَنْ ؟ قَالَ : ثُمَّ أُمُّكَ . قَالَ : ثُمَّ مَنْ ؟ قَالَ : ثُمَّ أَبُوكَ] رواه البخاري ومسلم አቡ ሁረይራ እንዲህ ብለዋል፤ «አንድ ሰው የአላህ መልእክተኛ  ዘንድ መጣና እንዲህ አላቸው፤ የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ከማንም በላይ መልካም ልውልለት የሚገባ ሰው ማነው? በማለት ጠየቀ። "እናትህ" አሉት። ቀጥሎስ? አላቸው። "እናትህ" አሉት። ቀጥሎስ? አላቸው። "እናትህ" አሉት። ቀጥሎስ? አላቸው። "አባትህ" አሉት» ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል የእናቶች ቀንን ማክበር እንዴት ይታያል? ኢስላም ለእናት ታላቅ ክብርን አጎናፅፏል። ይሁንና "የእናቶች ቀን" በማለት በአመት አንድ ቀን ብቻ እንድትከበር አላዘዘም። ይህንንም ለማብራራት፤ 1)  የእናቶችን ቀን በዓል አድርጎ ማክበር በዲናችን ያልነበረ እንግዳ ተግባር ነውና በዲን ውስጥ እንደተጨመረ ቢድዓ እንጂ እንደመልካም ሾል አይታይም። መልእክተኛው፤  እንዲሁም ሰሀቦችም ይሁኑ የዚህ ኡማ ታላላቅ መሪዎች ሁሉ አልፈፀሙትም። መልእክተኛው  ከቢድዓ ሲያስጠነቅቁ እንዲህ ብለዋል፤ وشَرُّ الْأُمُورِ مُحْدَثَاتُهَا ، وَكُلُّ بِدْعَةٍ ضَلَالَةٌ رواه مسلم  والنسائي وزاد:وَكُلُّ ضَلَالَةٍ فِي النَّارِ. «የነገሮች ሁሉ ክፉ፤ (በዲን ውስጥ) አዳዲስ ፈጠራዎች ናቸው፤ ቢድዓ ሁሉ ጥመት ነው!Âť ሙስሊም ዘግበውታል። በነሳኢ ዘገባ ደግሞ «ጥመት ሁሉ ደግሞ የእሳት ነው» የሚለውን ጭማሪ እናገኛለን። ሆኖም፤ ቢድዓ በዲን ውስጥ መጨመር ነው። ይህ ተግባር ኢባዳ አይደለም በአሉም እንዲሁ ነውና ታዲያ ለምን ቢድአ ይሆናል የሚል ጥያቄ የሚያነሱ አሉ። በቅድሚያ፤ ለጉዳዩ ያለንን እይታ ሙስሊም ያልሆኑ ሰዎች ዘንድ ባለው መልካም ሾል የመስራት ግንዛቤ ሳይሆን እንደ ኢስላም የመልካም ተግባራት ትርጓሜ ልናጤነው ይገባል። እንደ ኢስላም የሚታዩም ይሁን ልባዊ መልካም ስራዎች ሁሉ ኢባዳ ናቸው። እናትን ማስደሰት በአኼራ ታላቅ ደረጃን የሚያስገኝ የፅድቅ ዲናዊ ተግባር ኢባዳ መሆኑ ግልፅ ነው። አመታዊ በአሉም ቢሆን እንደሙስሊም ካሰብነው ለእናት መልካም በመዋል አጅር ለማግኘት ዲናዊ ሾል የሚሰራበት ቀን ነው። በዓል ማለት፤  በየአመቱ በሆነ ቀን በቋሚነት የሚደጋገምና ሰዎች በአልነቱን አስበውት የሚውሉት ቀን ነው። ቀናት ሁሉ የአላህ ናቸውና ለሆነ መልካም ሾል የሆነን ቀን በመምረጥ ቋሚ እና አመታዊ በአል አድርገን ስንደነግገው ከዲን ጋር የሚጋጭ ተግባር ይሆናል። በአል ማድረግ የምንችለው በዲናችን የታወቁትን አላህ የደነገጋቸውን የዒድ አልፊጥር እና የኢድ አል አድሐ በአላት ብቻ ነው። ከዚህ ውጭ ያሉ በአላት ወይ ከሌላ እምነቶች የተወሰዱ ወይም ደግሞ በዲን ውስጥ መሰረት የሌላቸው ፈጠራዎች ናቸውና አይፈቀዱም።  ስለዚህም ታላላቅ ኡለማዎችን ያቀፈው ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ የእናቶች ቀንን ማክበር እንደማይፈቀድ ብይን ሰጥቷል (ፈታዋለጅናህ ቅፅ 3 ገፅ 86) 2) የእናቶች ቀን የተቀዳው ቤተሰባዊና ማህበራዊ ትስስራቸው በእጅጉ ከተጎዳ ካፊር ማህበረሰቦች ተግባር ስለሆነ ቢድዓ ከመሆኑ በተጨማሪ ከካፊሮች ጋር መመሳሰል ነው። ሙስሊም በማንነቱ ሊኮራና ምርጥ የሙስሊም ትውልዶችን አርአያ ሊያደርግ እንጂ የሌሎች ጭራ ሊሆን አይገባም። የሚገርመው ይህ በአል የመጣብን የወላጆች ክብር ከጠፋባቸውና በደል ከተንሰራፋባቸው ማህበረሰቦች መሆኑ ነው። ወላጆቻቸውን የአዛውንቶች መጦርያ ጥለው በአመት እንኳ ለመጠየቅ ፍቃደኛ የማይሆኑ ሰዎች ከበዙባቸው ሀገራት ነው። እነሱ ዘንድ ወላጆችን ማስከፋትና መበደል እጅጉን ተንሰራፍቷል። ይህም ስለሆነ እናታቸውን የሚያስታውሱበትን ቀን መመደባቸው አይገርምም። አለዚያማ ከብዙ አመታት መማፀን በኃላ ልጆቻቸው ሳያዩዋቸው የሚሞቱ ወላጆች በርካታ መሆናቸውን በነዚህ ሀገራት የሚኖሩ ወዳጆቻችን ያጫውቱናል። ለነሱ በእናቶች ቀን የሚፈፅሙት ዚያራና መልካም ሾል አመቱን ሙሉ ያሳዩትን ጉድለት የሚያካክስ ይመስላቸዋል። እኛ ሙስሊሞች ዘንድ ግን ሁኔታው ይለያል። አመቱን ሙሉ የእናትን ፍቅር ስናገኝና ስናገለግል ብንኖር ውለታዋን እንደማንመልስ ዲናችን ያስተምረናል።  ታዲያ በአመት አንድ ቀን መርጦ እናት እናት ማለት እና ማሟሟቅ ምንም ትርጉም አይኖረውም። ሸይኽ ኡሰይሚን እንዲህ ብለዋል፤ «እናት፤  በአመት አንድ ቀን ብቻ ትኩረትን ከመቸሯ የበለጠ ሀቅ አላት።  እንደውም ልጆች እናታቸውን የመንከባከብ ግዴታ አለባቸው። እንደዚሁ፤ ከአላህ ትእዛዝ ጋር እስካልተጋጨ ድረስ እናትን በማንኛውም ጊዜና ቦታ መታዘዝ ግዴታ ነው» መጅሙዑል ፈታዋ 2/301 እዝነትና መልካምነትን ያቀፈ ነውና ይህንን ታላቅ ዲን ጠንክረን እንያዝ! ከአዳዲስ ድንጋጌዎችም በርሱ እንብቃቃ፤ ስርአትና ድንጋጌዎቹንም እንተግብር። ምስጋና ለአላህ የተገባ ነው! ወንድማቸሁ አቡጁነይድ ግንቦት 3/2007 --------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts