ru
Feedback
⚖️Shields Law🇪🇹 የህግ አገልግሎት / Legal service ⚖️

⚖️Shields Law🇪🇹 የህግ አገልግሎት / Legal service ⚖️

Открыть в Telegram

⚖️ Shields Law ⚖️. ነፃ የህግ የማማከር አገልግሎት፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ የውል ፎርሞች፤ መፅሐፍቶች እዚሁ ያገኛሉ። Here on our channel, we provide Free legal Aid. You could alsk get access to laws, cassation decisions, job opportunity updates. ለማስታወቂያ 👉@alexyoba21

Больше
7 713
Подписчики
-124 часа
-47 дней
-2030 день
Архив постов
መስቀለኛ ይግባኝ ( cross _ appeal ) እና መስቀለኛ መቃወሚያ ( cross _ objections ) ◾️ በኢትዮጵያ የፍትሐብሔር ሥነ _ ሥርዓት ሕግ መሠረት cross _ appeal ( መስቀለኛ ይግባኝ ) እና cross _ objections ( መስቀለኛ መቃወሚያ ) በይግባኝ ሂደት ዉስጥ የሚነሱ የተለያዩ መቃወሚያ መንገዶች ናቸው ግን በዉጤት ደረጃ ተቀራራቢ ናቸው:: https://t.me/Shields_Law https://t.me/Shields_Law 1ኛ , መስቀለኛ ይግባኝ ✍️ ( cross _ appeal ) አንድ ተከራካሪ በበታች ፍርድ ቤት ዉሳኔ በከፊል ተሸንፎ በከፊል ሲያሸንፍ ፣ ሌላኛው ወገን ( ይግባኝ ባዩ ) ይግባኝ ሲጠይቅ ፣ እርሱም በበኩሉ ባልረካበት የዉሳኔ ክፍል ላይ የሚጠይቀው የይግባኝ ዓይነት ነው ። ✔️ መቼ ይቀርባል ፦ ይግባኝ ባዩ ይግባኝ ባመጣበት መዝገብ ላይ መልስ ሰጪዉ ( Appellee) በበኩሉ ዉሳኔዉ እንዲሻሻልለት ሲፈልግ። ✔️ ምሳሌ ( Example ) አቶ "x" አቶ " y" ን 200,000 ብር እንዲከፍለው ከሰሰው ። ፍርድ ቤቱ ግን አቶ " y " 150,000 ብር ብቻ እንዲከፍል ወሰነ። ይግባኝ ፦ አቶ " y " 150,000 ብሩንም አልከፍልም ብሎ ይግባኝ ጠየቀ ። መስቀለኛ ይግባኝ ፦ አቶ " x " ደግሞ " ቀሪዉ 50,000 ብርም ሊከፈለኝ ይገባል " ብሎ በዚያው መዝገብ ላይ መስቀለኛ ይግባኝ ያቀርባል ። 2ኛ , መስቀለኛ መቃወሚያ ✍️ ( cross _ objections ) ይህ ደግሞ መልስ ሰጪዉ የስር ፍርድ ቤት የሰጠውን ዉሳኔ ( Decree ) ዉጤት ቢስማማም ፣ ፍርድ ቤቱ ለዉሳኔ መነሻ የተጠቀመባቸው ምክንያቶች ( Finding / Reasons ) ላይ ቅሬታ ሲኖረዉ የሚያቀርበው መቃወሚያ ነው ። ✔️ መቼ ይቀርባል ፦ በዉሳኔዉ ዉጤት ( ለምሳሌ ማሸነፍ ) ደስተኛ ሆኖ ነገር ግን ፍርድ ቤቱ አንድን ነጥብ ዉድቅ በማድረጉ ወይም ባለመቀበሉ ምክንያት ያ ነጥብ እንዲታይለት ሲፈልግ። ✔️ ዓላማው ፦ የላይኛው ፍርድ ቤት የሥር ፍርድ ቤቱን ዉሳኔ በሌላ ምክንያት እንዲያፀናዉ ለማሳመን ነው ። ✔️ ምሳሌ ( Example ) ፦ አቶ " x " አቶ " y " ን " ዉል አፍርሷል " እና " የፍትሐብሔር ጥፍት ( Tort) ፈጽሟል " በሚሉ ሁለት ምክንያቶች ካሳ ጠየቀ ። ፍርድ ቤቱ " ዉል አላፈረሰም " ብሎ ወሰነ ፣ ነገር ግን " የፍትሐብሔር ጥፍት ፈፅሟል " በማለት አቶ " y " ካሳ እንዲከፍል ወሰነ ። ይግባኝ ፦ አቶ " y " የፍትሐብሔር ጥፍት አልፈፀምኩም " ብሎ ይግባኝ አለ። መስቀለኛ መቃወሚያ ፦ አቶ " x " የካሳ ዉሳኔዉ ቢስማማዉም ፣ ፍርድ ቤቱ " ዉል አላፈረሰም " ማለቱን በመቃወም " ዉልም አፍርሷል ተብሎ ዉሳኔዉ ሊፀና ይገባል " በማለት መቃወሚያ ያቀርባል ። ◾️ ህጋዊ መሠረት /source ፦ የፍትሐብሔር ሥነ _ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 340. https://t.me/Shields_Law https://t.me/Shields_Law https://t.me/Shields_Law

⚖️ በፍርድ ቤት ክስ ከመመስረትዎ በፊት ሊያውቋቸው የሚገቡ ወሳኝ የሕግ ነጥቦች! ⚖️ https://t.me/Shields_Law ​የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በተለያዩ መዝገቦች ላይ የሰጣቸውን የሕግ ትርጓሜዎች አጠናቅረን አቅርበንልዎታል፡፡ ​እነዚህ ነጥቦች፣ አንድ ክስ በፍርድ ቤት ተቀባይነት እንዲያገኝ ምን ዓይነት መሠረታዊ ነገሮችን ማሟላት እንዳለበት፣ እንዲሁም ክሱ ተቀባይነት ሊያጣ የሚችልባቸውን ሁኔታዎች ያሳያሉ፡፡ ​1. የክስ ምክንያት እጦት (Lack of Cause of Action) ​አንድ ክስ ከሕግ አንጻር ተቀባይነት ያለው መሠረት ከሌለው፣ ፍርድ ቤቱ ከመጀመሪያው ውድቅ ሊያደርገው ይችላል፡፡ ​🚫 ሕገወጥ የገጠር መሬት ውል: የገጠር መሬትን ለረጅም ዓመታት (ለምሳሌ ለ80 ዓመት) በውል መስጠት የሽያጭ ውጤት ስላለው ሕገወጥ ነው፡፡ በዚህ ሕገወጥ ውል መሠረት ይዞታ የያዘ ወገን እንዲለቅ ይገደዳል፡፡ (ሰ/መ/ቁ. 199452) ​🚫 የማይንቀሳቀስ ንብረት ውል ማስረጃ: የቤት ሽያጭ ውል መኖሩን ለማስረዳት፣ በሕግ ሥልጣን ባለው አካል ፊት በጽሑፍ የተደረገ ውል መቅረብ አለበት፡፡ (ፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1723(1)) (ሰ/መ/ቁ. 199400) ​🚫 "ውል ይፈረምልኝ" ጥያቄ: "የሽያጭ ውል ይጸናልኝ" ወይም "ተከሳሽ ቀርቦ ይፈርምልኝ" የሚል የዳኝነት ጥያቄ፣ ውል በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ፣ በሕግ ተቀባይነት የሌለውና ሊቀርብ የማይችል ጉዳይ ነው፡፡ (ሰ/መ/ቁ. 225310) ​🚫 በውል ያልተገደበ አካል: ውልን መሠረት በማድረግ፣ በውሉ ተዋዋይ ባልሆነ 3ኛ ወገን (ለምሳሌ በንብረት አስተዳዳሪ) ላይ የክስ መሠረት የለውም፡፡ (ሰ/መ/ቁ. 190775) ​🚫 የስጦታ ውል መፍረስ: በስጦታ ውል ላይ ያልተመዘገበ ቅድመ ሁኔታን (ለምሳሌ "ሊጦረኝ" በሚል) በማንሳት ውሉ እንዲፈርስ መጠየቅ የክስ ምክንያት ሊሆን አይችልም፡፡ (ሰ/መ/ቁ. 197354) ​2. ክስ የማቅረብ መብትና ጥቅም (Locus Standi - ፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁ. 33) ​ክስ ማቅረብ የሚችለው በጉዳዩ ላይ ሕጋዊ መብት ወይም ጥቅም ያለው ወገን ብቻ ነው፡፡ ​📌 የሕጋዊ ጥቅም መኖር: ማንኛውም ሰው ለክሱ መነሻ በሆነው ነገር ላይ ጥቅም ወይም መብት ያለው መሆኑን ካላረጋገጠ በቀር ክስ ማቅረብ አይችልም፡፡ (ሰ/መ/ቁ. 180756) ​📌 የሕጋዊ ሰውነት መኖር: የንግድ ማኅበራትና ድርጅቶች ክስ ሊያቀርቡ የሚችሉት ሕጋዊ ሰውነት (በአግባቡ የተመዘገቡ) ሲሆኑ ብቻ ነው፡፡ (ሰ/መ/ቁ. 199173) ​📌 የበሰለ ክስ መሆን: አንድ ባለአክሲዮን "ወደፊት ተጠያቂ ልሆን እችላለሁ" በሚል ስጋት ብቻ ግብር እንዲከፈል ክስ ማቅረቡ፣ እዳው ገና "ያልበሰለ" (not mature) በመሆኑ ሕጋዊ ጥቅም የለውም፡፡ (ሰ/መ/ቁ. 206807) ​📌 የሁከት ክስ አቅራቢ: "ሁከት ይወገድልኝ" ክስ ለማቅረብ၊ አመልካች በሕጋዊ መንገድ ይዞታውን በቁጥጥሩ ሥር አድርጎ የያዘ መሆኑን ማረጋገጥ አለበት፡፡ (ሰ/መ/ቁ. 197775) ​3. በይርጋ (Prescription) የመክሰስ መብት መገደብ ​ሕግ፣ መብትን ለመጠየቅ የተወሰነ የጊዜ ገደብ ያስቀምጣል፡፡ ይህ ጊዜ ካለፈ መብቱ በይርጋ ይታገዳል፡፡ ​⏳ የጋራ ንብረት ገቢ: በጋራ ሀብት የተገኘ ገቢ (ፍሬ) እንዲካፈል የሚቀርብ ክስ፣ ያላግባብ መበልጸግን መሠረት ያላደረገ በመሆኑ በ2 ዓመት ይርጋ አይታገድም፡፡ (ሰ/መ/ቁ. 197753) ​⏳ የውርስ ይርጋ መቋረጥ: ወራሾች የውርስ ይዞታውን በጋራ ሲጠቀሙበት ከቆዩ፣ የ3 ዓመቱ የውርስ ጥያቄ ይርጋ (ፍ/ሕ/ቁ 1000) ይቋረጣል፡፡ (ሰ/መ/ቁ. 197567) ​⏳ የሕፃናት ውርስ መብት: የወላጅ ውርስ ድርሻ የሚጠየቅበት የይርጋ ጊዜ መቆጠር የሚጀምረው፣ ወራሹ (ሕፃኑ) አካለ መጠን ከደረሰ በኋላ ነው፡፡ (ሰ/መ/ቁ. 197567) ​⏳ ሥልጣን በሌለው ፍ/ቤት መክሰስ: ክስን ሥልጣን ለሌለው ፍ/ቤት አቅርቦ መከራከር፣ ይርጋውን የሚያቋርጥ በቂ ምክንያት ሆኖ ይወሰዳል፡፡ (ሰ/መ/ቁ. 199323) ​4. ሥነ ሥርዓታዊ ገደቦች (Procedural Bars) ​📜 Res Judicata (በፍርድ ያለቀ ጉዳይ): አንድ መሠረታዊ ጭብጥ (ለምሳሌ የውል መቋረጥ ጥፋት) ቀደም ሲል በሌላ መዝገብ ተወስኖ የጸና ከሆነ፣ በድጋሚ ሊመረመር አይገባም፡፡ (ፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 5) (ሰ/መ/ቁ. 197790) ​📜 ከተጠየቀው ዳኝነት ውጪ መወሰን: ፍርድ ቤት በክሱና በመከላከያው ላይ በተነሱት ጭብጦች ላይ ብቻ መወሰን ሲገባው፣ ከተጠየቀው ዳኝነት ውጪ ሊወስን አይችልም፡፡ (ሰ/መ/ቁ. 197942) ​📜 የሁከት ክስ vs. ባለቤትነት: በባለይዞታነት (ሁከት) ክርክር ላይ፣ ፍርድ ቤቱ አድማሱን አልፎ በባለሀብትነት (የመፋለም) ጉዳይ ላይ መወሰኑ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ነው፡፡ (ሰ/መ/ቁ. 198594) ​📜 በፍርድ አፈጻጸም ላይ አዲስ ዳኝነት: የአፈጻጸም ችሎት፣ በዋናው ክርክር ያልተጠየቀን ነገር (ለምሳሌ ቤት የማፍረስ ትዕዛዝ) በአፈጻጸም መዝገብ ላይ ሊሰጥ አይገባም፡፡ (ሰ/መ/ቁ. 199518) ​እነዚህ ነጥቦች የፍትሐብሔር ክርክሮች ውስብስብነትና የሥነ ሥርዓት ሕጎችን በአግባቡ መረዳት ምን ያህል አስፈላጊ መሆኑን ያሳያሉ። https://t.me/Shields_Law https://t.me/Shields_Law https://t.me/Shields_Law

Income_Tax_(Amendment)_Proclamation.pdf9.60 KB

new-income-tax-amendment.pdf2.42 MB

ውል_መሰረዝ_ማፍረስ_እና_በስምምነት_ማቋረጥ_GMAN.pdf2.76 KB

10 መሰረታዊ የውል አተረጓጎም ደንብ.pdf3.88 KB

የስሚ_ስሚ_ማስረጃ_HEARSAY_EVIDENCE_250708_205315.pdf4.40 KB

47 Most Important Doctrines In Law.pdf3.51 KB

CIVIL CODE PROPERTY LAW (1).pdf1.92 MB

CIVIL CODE SUCCESSION ARTICLES AMHARIC-ENGLISH (1).pdf5.40 KB

CIVIL CODE LAW OF CONTRACTS.pdf5.73 KB

about_new_criminal_procedure_lawStudentDiscussions_telegram_channel.pdf0.78 KB

Final_1_28_full_published_cassation_Daniel_Fikadu_Law_Office_Reduced.pdf107.12 MB

employment one .pdf2.22 MB

BDU - Employment Law PPT (2023) (1).pdf2.55 MB

PIL_Note_By_MIK.pdf4.71 MB

+1
የወንጀል_ቅጣት_አወሳሰን_ማብራሪያመ2_.pdf23.86 MB

የፌደራል የመንግስት ሰራተኛ የስራ ውል ስለሚቋረጥበት ሁኔታ የሥራ ውል በሕግ እንደተቋቋመ ሁሉ የሚቋረጠውም በሕግ መሠረት ነው። የሥራ ውል በሁለቱም ወገኖች ስምምነት ሊቋረጥ የሚችልበት ሁኔታ ቢኖርም በአንድ ወገን ፍላጎትም ሊቋረጥ ይችላል። ውሳኔው ለባለቤቱ የተሰጠ ቢሆንም ሌላውን ወገን እንዳይጎዳ የተወሰነ የማስጠንቀቂያ ጊዜ እንዲኖር በሕግ ተደንግጓል፡፡ በዚህ ጽሁፍ በፌዴራል የመንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2017 የሥራ ውል የሚቋረጥባቸውን ሁኔታዎችን በአጭሩ እንመለከታለን፡፡ 👉በራስ ፈቃድ የሥራ ውልን ስለ ማቋረጥ በአዋጁ በአንቀጽ 135 መሠረት ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በማንኛውም ጊዜ የሁለት ወር ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ሥራውን በፈቃዱ ሊለቅ ይችላል፡፡ መስሪያ ቤቱ ሠራተኛውን በቀላሉ ሊተካው የሚችል ከሆነ የሁለት ወሩን ጊዜ ሳይጠብቅ ስንብቱን ሊፈቅድለት ይችላል። ነገር ግን የመንግሥት ሠራተኛው ለሥራው እጅግ አስፈለጊና በቀላሉ ለመተካት የማይቻል ሆኖ ሲገኝ ወደ ፊት ከሚቀጠርበት መስሪያ ቤት ጋር በመስማማት የመልቀቂያ ጥያቄው ሠራተኛው ካመለከተበት ቀን ጀምሮ ከአራት ወር ለማይበልጥ ጊዜ ሊራዘም እንደሚችል ተደንግጓል። የሁለት ወር የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ አገልግሎቱን ያቋረጠ የመንግሥት ሠራተኛ ግዴታውን ባለመወጣቱ ለሚደርሰው ጉዳት እንደተገቢነቱ በፍትሐብሔር እና በወንጀል ሕግ መሠረት ተጠያቂ ይሆናል። 👉በሕመም ምክንያት የሥራ ውልን ስለ ማቋረጥ በአዋጁ እንቀጽ 136 መሠረት ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በአዋጁ አንቀጽ 66(2) ወይም (4) በተመለከተው ጊዜ ውስጥ ማለትም የሙከራ ጊዜውን ያጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ በተከታታይ ወይም በተለያየ ጊዜ ቢወስድም ሕመሙ ከደረሰበት የመጀመሪያ ቀን አንስቶ ባለው አሥራ ሁለት ወር ጊዜ ውስጥ ከስድስት ወር ወይም በአራት ዓመት ውስጥ ከአሥራ ሁለት ወር ወይም የሙከራ ጊዜወን ያላጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ በአንድ ወር ውስጥ ወደ ሥራ ለመመለስ ካልቻለ በሕመም ምክንያት አገልግሎቱ ይቋረጣል። ሆኖም በሥራ ምክንያት ጉደት የደረሰበት ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በአዋጁ አንቀጽ 84(3) መሠረት የጉዳቱ መጠን ታይቶ በህክምና ማስረጃ በሚገልፃው መሠረት ድኖ ወደ ሥራው እስከሚመለስ ወይም በጉዳቱ ምክንያት ለዘለቄታ መሥራት የማይችል መሆኑ በሕከምና ማስረጃ እስከሚረጋገጥ ድረስ የሕመም ፈቃድ ከሙሉ ደመወዝ ጋር ይሰጠዋል። የመንግሥት ሠራተኛው ለዘለቄታው መሥራት ያለመቻሉ በሕክምና ማሰረጃ ከተረጋገጠ ግን በዚህ አዋጅ አንቀጽ 85 መሠረት የጉዳት ጡረታ አበል እና የጉዳት ዳረጎት የሚከፈለው ሆኖ አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡ እንዲሁም አንድ የመንግሥት ሠራተኛ በጤና መታወክ ምክንያት በያዘው የሥራ መደብ ወይም ባለበት የሥራ ቦታ ላይ ሊስራ አለመቻሉ በሕክምና ማስረጃ በረጋገጥ በተመሳሳይ ደረጃ ሊመደብ የሚችልበት ክፍት የሥራ መደብ ከሌለና ደረጃው ተቀንሶ ወደ ሚስማማው የሥራ መደብ ዝቅ ባለ ደረጃ ለመሥራት ፈቃደኛ ካልሆነ በአዋጁ አንቀጽ 51 ንዑስ አንቀጽ (3) (ለ) መሠረት የሥራ ውል ይቋረጣል። 👉በችሎታ እና ብቃት ማነስ ምክንያት ከሥራ ማሰናበት የሙከራ ጊዜውን ያጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወር በሥራ አፈፃፀም ውጤቱ የችሎታ ማነስ ከታየበት ምክርና ተገቢው የአቅም ማጎልበት ስልጠና የሚሰጠው ሆኖ የመንግሥት ሠራተኛ በተመደበበት ሥራ ላይ የሥራ አፈፃፀም ውጤቱ በበጀት ዓመት ለሁለት ጊዜ ያህል ከመካከለኛ ውጤት በታች ካገኘ በአዋጁ አንቀጽ 137 መሠረት በዕቅድ አፈፃፀም የችሎታ ማነስ ምክንያት ከሥራ ይሰናበታል፡፡ በተጨማሪም ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ ከተመደበበት ሥራ ጋር በተያያዘ በብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ሂደት በስድስት ወር ለሁለት ጊዜ  ተመዝኖ ከዝቅተኛ ማለፍያ ውጤት በታች ካገኘ በብቃት ማነስ ምክንያት ከሥራ ይሰናበታል። ነገር ግን የመንግሥት ሠራተኛውን ከሥራ ማሰናበት የሚቻለው እንደ አስፈላጊነቱ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 47 የሥራ አፈፃፀም ምዘና ዓላማ እና እንቀጽ 136 ላይ የጡረታ መብት ተጠብቆ አገልግሎትን ስለማቋረጥ የተደነገገውን በመከተል ይሆናል። 👉ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት የሥራ ውልን ስለ ማቋረጥ በፌደራል የመንግሥት ሰራተኞች አዋጅ አንቀጽ 138 መሠረት የሙከራ ጊዜውን ያጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት በሥራ ገበታው ላይ ካልተገኘ ምክንያቱን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለመስሪያ ቤቱ ማሳወቅ አለበት። በዚህ መሠረት ሪፖርት የተደረገለት የመንግሥት መሥሪያ ቤት የበላይ ኃላፊ ወይም ተወካዩ ሠራተኛው ከሥራ ገበታው ላይ የተለየበት ምክንያት ከአቅም በላይ መሆኑን ካረጋገጠ የመንግሥት ሠራተኛው ይዞት የነበረውን የሥራ መደብ ለሦስት ወር ክፍት አድርጎ መጠበቅ አለበት፡፡ ሆኖም የመንግሥት ሠራተኛው በሦስት ወር ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራው ካልተመለሰ ከሥራ ማሰናበት ይቻላል። ነገር ግን የመንግሥት ሠራተኛው ከሦስት ወር በላይ በሥራ ላይ ያልተገኘው በእስር ምክንያት ከሆነና ከተጠረጠረበት የወንጀል ድርጊት በነፃ ስለመለቀቂ ማስረጃ ካቀረበ የመንግሥት መስሪያ ቤቱ ባለው ክፍት የሥራ መደብ ቀደም ሲል ይከፈለው የነበረውን ደመወዝ እያገኘ ወደ ሥራ እንዲመለስ ማድረግ አለበት። በተጨማሪም የሙከራ ጊዜውን ያጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ ባልታወቀ ምክንያት ለተከታታይ ሰባት የሥራ ቀናት ከመደበኛ የሥራ ቦታው ላይ ከተለየ በየሰባት ቀናት ልዩነት በተከታታይ ለሁለት ጊዜ በማስታወቂያ ተጠርቶ ለመንግሥት መሥሪያ ቤቱ ሪፖርት ካላደረገ ከሥራ ይሰናበታል፡፡ በማስታወቂያ ጥሪ የተደረገለት የመንግሥት ሠራተኛ ከሥራ ከተለየበት ቀን ጀምሮ አንድ ወር ከመሙላቱ በፊት ወደ ሥራው ለመመለስ ለመንግሥት መሥሪያ ቤቱ ሪፖርት ካደረገ የመሥሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ ሠራተኛው ከሥራ የቀረበትን ምክንያት በመመርመር የሚወስደው አስተዳደራዊ እርምጃ እንደተጠበቀ ሆኖ ወደ ሥራው እንዲመለስ ይደረጋል። ነገር ግን ከሥራ የተሰናበተ ሠራተኛ ከሥራ ከቀረበት ቀን ጀምሮ በሦስት ወር ጊዜ ውስጥ ከሥራ የቀረበት ምክንያት ከአቅም በላይ ለመሆኑ ለመሥሪያ ቤቱ ሪፖርት ካደረገና በቂ ማስረጃ ካቀረበ በመሥሪያ ቤቱ ውስጥ ተመሳሳይ የሆነ ክፍት የሥራ መደብ ከተገኘ የመሥሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ ወይም ተወካዩ ሲፈቅድ ወደ ሥራ ሊመለስ ይችላል። የሙከራ ጊዜወን ያላጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ ባልታወቀ ምክንያት ለአሥራ አምስት ቀናት በሥራ ገበታው ላይ ካልተገኘ ያለተጨማሪ ሥነ-ሥርዓት የሥራ ውሉ ይቋረጣል፡፡ 👉በሠራተኛ ቅነሳ ምክንያት ከሥራ ማሰናበት ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ የሥራ መደቡ ሲሰረዝ፣ መሥሪያ ቤቱ ሲዘጋ እና ትርፍ የሰው ኃይል ሲኖር፤ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 55 ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት ለመደልደል ካልተቻለ ወይም የመንግሥት ሠራተኛው ዝቅ ባለ የሥራ  ደረጃ ላይ ለመሥራት ፈቃደኛ ካልሆነ እንዲሁም የመንግሥት ሠራተኛው በመሥሪያ ቤት ውስጥ በተመሳሳይ የሥራ መደብ ላይ ካሉ ሌሎች የመንግሥት ሠራተኞች ጋር ሲወዳደር በሥራ ውጤቱና ባለው ችሎታ ዝቅተኛ መሆኑ ሲረጋገጥ በአዋጁ አንቀጽ 139 መሠረት ከሥራ ይሰናበታል፡፡                                          #Join the channel via :- https://t.me/Shields_Law https://t.me/Shields_Law https://t.me/Shields_Law

ዛሬ የሕግ መውጫ ፈተናቹ እንዴት ነበረ?
Anonymous voting