ar
Feedback
⚖️Shields Law🇪🇹 የህግ አገልግሎት / Legal service ⚖️

⚖️Shields Law🇪🇹 የህግ አገልግሎት / Legal service ⚖️

الذهاب إلى القناة على Telegram

⚖️ Shields Law ⚖️. ነፃ የህግ የማማከር አገልግሎት፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ የውል ፎርሞች፤ መፅሐፍቶች እዚሁ ያገኛሉ። Here on our channel, we provide Free legal Aid. You could alsk get access to laws, cassation decisions, job opportunity updates. For additional 👉 @eyob_PP

إظهار المزيد
7 925
المشتركون
-224 ساعات
+57 أيام
+19030 أيام
أرشيف المشاركات
#ቀልድ_መስለው_ነገር_ግን_ወንጀል_የሆኑ_ድርጊቶች ‼️ **** 1. የሰውን ፎቶ/ቪዲዮ መለጠፍ ድርጊቱ፦ መንገድ ላይ ያዩትን ጠብ ወይም አስቂኝ ነገር ያለ ባለቤቱ ፈቃድ ቀርጾ ፌስቡክ ላይ መለጠፍ። ውጤቱ፦ የግል ነፃነትን መጣስ ተብሎ ያስከስሳል። 2. የሀሰት ወሬ ማሰራጨት ድርጊቱ፦ "እውነት ይመስላል" ብለው መረጃን ሳያረጋግጡ "Share" ማድረግ። ውጤቱ፦ ሀ, በሀሰተኛና ጥላቻ ንግግርን የማሰራጨት ተጠያቂነት ለ,የኮምፒውተር ወንጀል አዋጅን መጣስ እና የሰላም መታወክ ተጠያቂነት። 3. በኮሜንት መሳደብ ድርጊቱ፦ በፖስት ስር ሰዎችን በብሄር፣ በሃይማኖት ወይም በግል ማንነታቸው መስደብ። ውጤቱ፦ የጥላቻ ንግግር እና ስም ማጥፋት ወንጀል። 4. ያለፈቃድ ገንዘብ ማሰባሰብ ድርጊቱ፦ "ለታመመ ሰው እርዳታ" በሚል የባንክ አካውንት እየለጠፉ በሶሻል ሚዲያ ገንዘብ መለመን። ውጤቱ፦ ያለፈቃድ የገንዘብ ማሰባሰብ እና የማጭበርበር ጥርጣሬ። 5. የሰው ዲዛይን መስረቅ ድርጊቱ፦ የሌላ ሰውን ሎጎ ወይም የፈጠራ ስራ "የእኔ ነው" ብሎ መጠቀም። ውጤቱ፦ የቅጂ መብት (Copyright) ጥሰት ክስ። 6. የግል መልዕክትን ማጋራት (Screenshot) ድርጊቱ፦ በ "Inbox" የተላከልዎትን ሚስጥራዊ መልዕክት ያለ ሰውየው ፈቃድ ለሰው እንዲታይ ፖስት ማድረግ። ውጤቱ፦ የግል ሚስጥርን ማባከን (Privacy violation)። ማሳሰቢያ፦ በኢንተርኔት የምንለጥፈው ነገር ሁሉ "ዲጂታል አሻራ" ስላለው በሕግ ፊት ማስረጃ ሆኖ ሊቀርብ ይችላል። https://t.me/Shields_Law

#ክፍት_የስራ_ቦታ_ማስታወቂያ 📍ኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት 📍የስራው ዓይነት: ረዳት የወረዳ ፍርድ ቤት ጠበቃ 📍ብዛት: 100 (አንድ መቶ) 🎗 ዝርዝሩን ከተያያዘው ምስል ይመልከቱ። ⭐#Sha
+2
#ክፍት_የስራ_ቦታ_ማስታወቂያ 📍ኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት 📍የስራው ዓይነት: ረዳት የወረዳ ፍርድ ቤት ጠበቃ 📍ብዛት: 100 (አንድ መቶ) 🎗 ዝርዝሩን ከተያያዘው ምስል ይመልከቱ። ⭐#Share To Your Friends 🈴 Join Us Your Trusted Legal Info Centre @Law_School_Media @Law_School_Media @Law_School_Media

በወንጀል ክርክር ሂደት “ከአምስት ማቅለያ በላይ ማቅረብ እና መያዝ !!? 💠በመሠረቱ፥ በወንጀል ሕጋችን የወንጀል ቅጣት ማቅለያዎች ጠቅላላ የቅጣት ማቅለያዎች (general mitigating circumstances) እና ልዩ የቅጣት ማቅለያዎች (special mitigating circumstances) ተብለው በ2 ተከፍለዋል:: ጠቅላላ የቅጣት ማቅለያዎች ቅጣትን በአንድ እርከን የሚያቀሉ ሲሆኑ አደነጋገጋቸውም ሁለት ዓይነት ነው:: 💠እነሱም በወንጀል ሕግ በግልጽ በአንቀጽ 82 ሥር የተዘረዘሩትን እና በአንቀጽ 86 መሠረት በዳኞች ፈቃድ (judicial discretion) የሚያዙ በግልጽ ያልተዘረዘሩ የማቅለያ ምክንያቶችን ያካትታል:: እርግጥ ነው፤ በአንቀጽ 82 (1/ሀ-ሠ) የተዘረዘሩት ጠቅላላ የቅጣት ማቅለያ ሆነው ሊቀርቡ የሚችሉ ምክንያቶች ብዙ ማለትም ከ5 በላይ ቢሆኑም ፍ/ቤቱ ለተከሳሽ ይህን አንቀጽ መሠረት በማድረግ ከ5 ጠቅላላ የቅጣት ማቅለያዎች በላይ ሊይዝ አይችልም:: ▷ይሁንና በአንቀጽ 86 መሠረት በዳኞች ፈቃድ የሚያዙ በሕግ በግልጽ ያልተጻፉ ምክንያቶች ብዙ ሊሆኑ ይችላሉ:: ስለሆነም በአንቀጽ 82 መሠረት 5 ጠቅላላ የቅጣት ማቅለያዎች የተያዙለት ሰው በተጨማሪነት በአንቀጽ 86 መሠረት በዳኞች ፈቃድ ሌሎች ብዙ ጠቅላላ የቅጣት ማቅለያዎች ሊያዙለት ይችላሉ::  💠እንዲሁም ተከሳሽ ከጠቅላላ የቅጣት ማቅለያዎች በተጨማሪ (ጎን ለጎን) ልዩ የቅጣት ማቅለያዎች ካሉትም ሊያዙለት ይችላሉ:: ልዩ የቅጣት ማቅለያዎች ቅጣትን በሕግ በተወሰነ ምትክ ቅጣት መሠረት የሚያቀሉ ወይም ዳኛው በመሰለው (በነጻነት) ቅጣትን እንዲያቀል የሚፈቅዱ ወይም ዳኛው ተከሳሽን ከማናቸውም ቅጣት ነጻ እንዲያደርግ ወይም ሙሉ ወይም በከፊል ቅጣትን እንዲተውለት የሚያስችሉ ናቸው:: 💠▷እነዚህ ልዩ የቅጣት ማቅለያ ምክንያቶች በወንጀል ሕጉ ውስጥ የሚገኙት በተለያዩ አንቀጾች ውስጥ ተበታትነው ነው:: ለምሳሌ:- በወንጀል ሕግ አንቀጽ 83:-ዝምድናና የጠበቀ ወዳጅነት)፣ አንቀጽ 27(3)+31:-ሙከራ)፣ አንቀጽ 28(2:-መተውና መጸጸት)፣ አንቀጽ 29(ሊፈጸም የማይቻል ወንጀል)፣ አንቀጽ 36(3:-ለወንጀል ማነሣሣት)፣ 37(4: አባሪነት)፣ አንቀጽ 49(2: ከፊል የወንጀል ኃላፊነት)፣ አንቀጽ 56(2:-ወጣት ጥፋተኞች)፣ 72:-ለማሸነፍ የሚቻል መገደድ)፣ አንቀጽ 74(2:-የበላይ ትእዛዝ)፣ አንቀጽ 75(የሰውን ሕይወትና ደኅንነት ለመጠበቅ ሲል ልዩ የሙያ ግዴታ ያለበት ሰው የሚፈጸማቸው አስገዳጅ ድርጊቶች)፣ አንቀጽ 76:-የአስገዳጅ ሁኔታን ወሰን መተላለፍ)፣ አንቀጽ 77(2:-ወታደራዊ አስገዳጅ ሁኔታን ማለፍ)፣ አንቀጽ 79(1: ሕጋዊ መከላከልን ማለፍ)፣ አንቀጽ 81(2-3:- በሕግ ላይ መሳሳት እና ሕን አለማወቅ) መጥቀስ ይቻላል:: 💠▮▷ልዩ የቅጣት ማቅለያዎች ቅጣትን በአንድ ርከን ሳይሆን እንደ ሁኔታው በወንጀል ሕግ አንቀጽ 179 በተደነገገው መደበኛ የቅጣት ማቅለያ ደንብ(ordinary mitigation) መሠረት፣ በአንቀጽ 180 በተደነገገው በመሰለው ቅጣትን ማቅለያ ደንብ (free mitigation) እና በአንቀጽ 181 (ከቅጣት ነጻ የማድረግና ቅጣትን የመተው ደንብ (exemption & Waiving) መሠረት የቅጣት የቅጣት ውሳኔን እንዲወስን የሚደነግጉ ናቸው:: ▷ስለሆነም "ከአምስት ማቅለያ በላይ ማቅረብ  ሆነ  መያዝ  የሚቻልበት ሁኔታ እዳለ መረዳት ያስፈልጋል!! https://t.me/Shields_Law

🌼🌼🌼መልካም አዲስ አመት🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ክቡራን የShields Law 🇪🇹 ገፅ ቤተሰቦች አዲሱ አመት የሰላም እና የስኬት አመት እንዲሆን እና ሀገራችን ሰላም
🌼🌼🌼መልካም አዲስ አመት🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ክቡራን የShields Law 🇪🇹 ገፅ ቤተሰቦች አዲሱ አመት የሰላም እና የስኬት አመት እንዲሆን እና ሀገራችን ሰላም ሆና ፍላጎታቹ ሚሳካበት ዘመን እንዲሆን እንመኛለን፡፡ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼 A HAPPY NEW YEAR 🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼Baga Bara Haaraa Geessan🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 Kabajamtoota miseensota fuula Shields Law 🇪🇹, barii haaraan kun bara nagaa fi milkaa'inaa akka isiniif ta'u, akkasumas biyyi keenya nagaa tatee fedhiin keessan hunduu kan keessatti furaamu akka isiniif ta'u hawwii keenya. 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼 BAGA BARA HAARAAN GEESSAN 🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 Eyob.A

🌼🌼🌼መልካም አዲስ አመት🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ክቡራን የShields Law 🇪🇹 ገፅ ቤተሰቦች አዲሱ አመት የሰላም እና የስኬት አመት እንዲሆን እና ሀገራችን ሰላም
🌼🌼🌼መልካም አዲስ አመት🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ክቡራን የShields Law 🇪🇹 ገፅ ቤተሰቦች አዲሱ አመት የሰላም እና የስኬት አመት እንዲሆን እና ሀገራችን ሰላም ሆና ፍላጎታቹ ሚሳካበት ዘመን እንዲሆን እንመኛለን፡፡ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼 A HAPPY NEW YEAR 🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

በኢትዮጵያ ህግ መሠረት ውል ፈራሽ የሚሆንባቸው ምክንያቶች ========================== በኢትዮጵያ የፍትሐ ብሔር ሕግ (የ1952 ዓ.ም) መሠረት፣ አንድ ውል ሕጋዊ መሠረት ኖሮት የሚጸናውና በሕግ ፊት ተፈጻሚነት የሚኖረው የተወሰኑ መሠረታዊ መሥፈርቶችን አሟልቶ ሲገኝ ብቻ ነው። እነዚህ መሥፈርቶች ሲጓደሉ ወይም ጉድለት ሲገኝባቸው ውሉ ፈራሽ (Void) ወይም ሊፈርስ የሚችል (Voidable) ይሆናል። ​የሕግ ባለሙያዎች እንደሚረዱት፣ በሕጋችን ላይ «ውል ፈራሽ የሚሆንባቸው ምክንያቶች» ሰፊ ቢሆኑም፣ በዋናነት በሁለት ትልልቅ ክፍሎች ተለይተው ይታያሉ፦ የውል content ፈራሽ የሚሆኑ ውሎች (Void Ab Initio) እና ሊፈርሱ የሚችሉ ውሎች (Voidable Contracts)። ​ዝርዝር ምክንያቶቹ የሚከተሉት ናቸው፦ ​1. ፍጹም ፈራሽ የሚሆኑ ውሎች (Void Contracts) ​እነዚህ ውሎች ገና ከጅምሩ በሕግ ፊት እንደሌሉ (የማይጸኑ) ተደርገው የሚቆጠሩ በመሆናቸው፣ ማናቸውም ወገን ፍርድ ቤት ሄዶ ውሉ እንዲፈርስ የመጠየቅ መብት አለው። ​የውሉ ዓላማ ወይም ይዘት ሕገ-ወጥ ወይም ከሕዝብ መልካም ጠባይ ውጪ መሆን (Illegal or Immoral Object): የውሉ መሠረታዊ ዓላማ በሕግ የተከለከለ (ለምሳሌ ኮንትሮባንድ ዕቃ ለማሻሻጥ) ወይም የኅብረተሰቡን መልካም ጠባይ የሚቃረን ከሆነ ውሉ ፍጹም ፈራሽ ነው። (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1716) ​የውሉ ነገር የማይቻል መሆን (Impossible Object): ውሉ የተደረገበት ጉዳይ በተፈጥሮም ሆነ በሕግ ሊከናወን የማይችል (Absolute Impossibility) ከሆነ ውሉ አይጸናም። (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1715) ​የውሉ ፎርም አለመጠበቅ (Lack of Required Form): ሕጉ ለአንዳንድ ውሎች የግድ በጽሑፍ መሆን አለባቸው ወይም በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ (በዋናው መዝገብ ቤት) ፊት መፈረም አለባቸው ብሎ ሲደነግግ (ለምሳሌ የሪል ስቴት/የቤት ሽያጭ፣ የዋስትና ውል)፣ ይህ ፎርም ካልተጠበቀ ውሉ ፈራሽ ነው። (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1719 - 1725) ​የውሉ ይዘት በግልጽ አለመታወቁ (Indeterminate Object): በውሉ ውስጥ ግዴታዎቹ ምን እንደሆኑ በግልጽ ካልተለዩ ወይም በግልጽ ሊታወቁ የሚችሉ ካልሆኑ ውሉ አይጸናም። (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1714) ​2. ሊፈርሱ የሚችሉ ውሎች (Voidable Contracts) ​እነዚህ ውሎች መሠረታዊ ጉድለት ያለባቸው ቢሆንም፣ ውሉ እንዲፈርስ የመጠየቅ መብት ያለው ተጎጂው ወገን (ወይም ሕጋዊ ወኪሉ) ብቻ ነው። ተጎጂው ወገን ውሉን ካላጸደቀው በስተቀር ሊፈርስ ይችላል። ​ሀ. የፈቃድ ጉድለቶች (Defects in Consent) ​አንድ ሰው ውል ሲያደርግ ሙሉ በሙሉ በነጻነትና በእውነተኛ ፍላጎት ላይ ተመስርቶ መሆን አለበት። ይህ ፍላጎት በሚከተሉት ምክንያቶች ከተበላሸ ውሉ ሊፈርስ ይችላል፦ ​ስሕተት (Mistake): በውሉ መሠረታዊ ጉዳይ ወይም በባሕርዩ ላይ የተሳሳተ ግንዛቤ ይዞ ውል መፈጸም። ስሕተቱ ወሳኝ መሆን አለበት። (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1697 - 1703) ​ማታለል/ተንኰል (Fraud): አንደኛው ወገን ሆን ብሎ ውሸት በመናገር ወይም እውነታውን በመደበቅ ሌላኛውን ወገን አታልሎ ውል እንዲገባ ሲያደርገው። (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1704 - 1705) ​ማስገደድ/ማስፈራራት (Duress): በአካል፣ በንብረት ወይም በክብር ላይ ከባድና ሊደርስ የሚችል አደጋ እንደሚደርስ በማስፈራራት የተገኘ ፈቃድ ውልን ሊያፈርስ ይችላል። (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1706 - 1709) ​ያለአግባብ ተጽዕኖ ማሳደር (Undue Influence): አንደኛው ወገን በሌላኛው ላይ ያለውን የሥልጣን፣ የሃይማኖት፣ የሕክምና ወይም የዝምድና የበላይነት በመጠቀም (Reverential Fear) ፈቃዱን ሰርቆ ውል እንዲገባ ሲያደርገው። (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1710) ​ለ. የሕግ ችሎታ ማጣት (Incapacity of Parties) ​ውል ለመዋዋል ሕጋዊ ችሎታ (Capacity) ሊኖር ይገባል። ችሎታ በሌላቸው ወገኖች የተደረገ ውል ሊፈርስ ይችላል፦ ​ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናት (Minors): ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጆች የሚያደርጓቸው ውሎች (የዕለት ተዕለት አነስተኛ ግብይቶችን ሳይጨምር) በሕጋዊ ሞግዚታቸው አማካኝነት እንዲፈርሱ ሊደረግ ይችላል። (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 313) ​በሕግ ችሎታቸው የተከለከሉ ሰዎች (Judicially/Legally Interdicted Persons): በአእምሮ ሕመም ወይም በሌላ ምክንያት ፍርድ ቤት ውል የመዋዋል ችሎታቸውን የከለከላቸው ሰዎች የሚያደርጉት ውል ሊፈርስ ይችላል። (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 378) ​3. ልዩ ሁኔታ፡ ያለአግባብ መበለጥ (Lesion) ​በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት የውል ግዴታዎች አለመመጣጠን (ለምሳሌ አንድን ውድ ዕቃ በጣም በትርኪምሪ ዋጋ መሸጥ) ብቻውን ውልን አያፈርስም። ነገር ግን፣ ይህ መበለጥ የተከሰተው የአንደኛውን ወገን መቸገር፣ አለማወቅ፣ ወይም በእድሜ መግፋት (Weakness) መሠረት በማድረግ ያለአግባብ ለመበልጸግ ታስቦ ከሆነ ውሉ እንዲፈርስ ወይም እንዲስተካከል ፍርድ ቤት ሊወስን ይችላል። (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1711) ​📌 ማስታወሻ (Limitation Period): ሊፈርሱ የሚችሉ ውሎችን (Voidable Contracts) ለማፍረስ ሕጉ የጊዜ ገደብ ያስቀምጣል። ውሉ እንዲፈርስ የሚፈልገው ወገን፣ ምክንያቱ (ማስገደዱ፣ ማታለሉ ወይም ስሕተቱ) ከታወቀበት ወይም ከቀረበት ጊዜ ጀምሮ ባለው በ2 ዓመት ጊዜ ውስጥ ክስ ማቅረብ አለበት። (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1810) Join us👇👇👇👇 https://t.me/Shields_Law https://t.me/Shields_Law https://t.me/Shields_Law

ሰላም እንዴት ናችሁ የተወደዳችሁ የ Shields Law 🇪🇹 ቤተሰቦች? እንሁ ለእናንተ ትኩስ እና ታማኝ ህግ ነክ መረጃዎችን በቅንነት፤ በታማኝነት፤ በብቃት ሳይታክተን እያደረስን 2018 ዓ.ም እ
ሰላም እንዴት ናችሁ የተወደዳችሁ የ Shields Law 🇪🇹 ቤተሰቦች? እንሁ ለእናንተ ትኩስ እና ታማኝ ህግ ነክ መረጃዎችን በቅንነት፤ በታማኝነት፤ በብቃት ሳይታክተን እያደረስን 2018 ዓ.ም እየተጠናቀቀ ነው። በዚህ ቆይታችን ይህንን ብታስተካክሉ፤ ይህ ቢቀጥል ፤ ሌላም ያላችሁን አስተያየት ሁሉ በመወያያ ግሩፑ በኩል ብታደርሱን። ስለ ሁሉም ነገር እናመሰግናለን!!! https://t.me/Shields_Law 🇪🇹🇪🇹🇪🇹 https://t.me/Shields_Law

Vacancy /የስራ ማስታወቂያ መደ ወላቡ ዩንቨርስቲ የህግ መምህራንን ይፈልጋል። ለፈጣን ትኩስ መረጃ ከስር ያለዉን ሊንክ በመጫን ቤተሰብ ዩሁኑን።👇👇👇 https://t.me/Shields_Law
+2
Vacancy /የስራ ማስታወቂያ መደ ወላቡ ዩንቨርስቲ የህግ መምህራንን ይፈልጋል። ለፈጣን ትኩስ መረጃ ከስር ያለዉን ሊንክ በመጫን ቤተሰብ ዩሁኑን።👇👇👇 https://t.me/Shields_Law

የስራ ማስታወቂያ
+1
የስራ ማስታወቂያ

የላቀ የሕግ ባለሙያ መሆን ከዕውቀት ባሻገር ጥበብ:ሥነ-ምግባርን እና የመፍጠር ብቃትን አዋህዶ መያዝን ይጠይቃል!! Join our chanal 👇👇 https://t.me/Shields_Law

criminal-procedure-code-amharic (1).pdf4.01 MB

employement-and-labour-law (1).pdf1.18 MB

Formation and Effects of Contracts (1).pdf2.24 MB