ru
Feedback
Kolfe P.P - ብልፅግና

Kolfe P.P - ብልፅግና

Открыть в Telegram
1 671
Подписчики
Нет данных24 часа
-177 дней
-8030 дней
Архив постов
ጅግጅጋ Jijigaa

ኑ! ታሪካችሁን ጎብኙ! Koottaa Seenaa keessan Daawwadhaa!! የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ከነገ ጀምሮ በሚወጣው መርሃ ግብር መሰረት ለጎብኚዎች ክፍት ይሆናል። የአድዋ ድል፤ መታሰቢያውም የሁላችንም ነው ! ኑ ቤታችሁን እና ታሪካችሁን ጎብኙ። Godaambaan yaadannoo injifannoo Adawaa akkaataa sagantaa bori irraa eegalee baahuun dawwattootaaf banaa ni ta'a. Injifannoon Adawaas, yaadannoon isaas kan hunda keenyati ! Koottaa mana keessanii fi seenaa keessan daawwadhaa. #Adanech_Abiebie #Abiy_Ahimed_Ali

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሶማሌ ክልል ጎዴ ከተማ ያስገነባውን ኡጋዝ ሚራድ አየር ማረፊያ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል እና የአውሮፕላን ማረፊያ መርቀው ከፍተዋል።
+8
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሶማሌ ክልል ጎዴ ከተማ ያስገነባውን ኡጋዝ ሚራድ አየር ማረፊያ  የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል እና የአውሮፕላን ማረፊያ መርቀው ከፍተዋል። አየር ማረፊያው በአንድ ጊዜ አራት ቦይንግ 737 አውሮፕላኖችን ማስናገድ የሚችል ነው። የተርሚል ግንባታው ሶስት አመት የፈጀ ሲሆን የተሳፋሪዎችን ምቾት ለመጠበቅ በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች የተደራጀ ነው።

ዓድዋ የኢትዮጵያዊነት ከፍታ፤ የአንድነት አርማ! ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ የወል የሆነ ታሪኮች ያሏት ታላቅ ሀገር ነች፡፡ ከእነዚህም ታሪኮች መሀከል አብሮነት ፣ መከባበር ፣መደማመጥ ፣ የጋራ አላማ
ዓድዋ የኢትዮጵያዊነት ከፍታ፤ የአንድነት አርማ! ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ የወል የሆነ ታሪኮች ያሏት ታላቅ ሀገር ነች፡፡ ከእነዚህም ታሪኮች መሀከል አብሮነት ፣ መከባበር ፣መደማመጥ ፣ የጋራ አላማ ከተያዘ የትኛውንም ምድራዊ ፈተናን ማለፍ እንደሚቻል ለዓለም ያሳየችበት የዓድዋ ድል በዓል አንዱ ነው ። ሀገራት ዜጎቻቸውን ለተሻለ ድልና ስኬት ከሚያነሳሱባቸው ትርክቶች መሀከል የሆነው የእኛ የዓድዋ ድል ለጥቁር ህዝቦችም ጭምር ድል ነው። ታላቅ የሆነች ለሁላችንም የምትሆን ሀገር በፅኑ መሰረት ላይ መገንባት የሚቻለውና በየወቅቱ ከሚገጥሙን ፈተናዎቻችን በዘላቂነት መላቀቅ የምንችለው በዚህ ልክ ተጨማሪ የወል የሆኑ አሰባሳቢ ታሪኮችን መስራት እና ያሉንን ደማቅ የሆኑ ታሪኮች መጠበቅ ሲቻል ነው። የሀገር ዋልታና ማገር የሆነ ትውልድ ለመገንባትም የአንድነት አርማ የሆነው የዓድዋን ድል ከትውልድ ወደ ትውልድ ክብርና ሞገሱን ጠብቀን በጋራ ማስቀጠል ሲቻል ነው ። "ዓድዋ መሪና ተመሪ - አስተዳዳሪና ተዳዳሪ ሲደማመጡ፣ ሲግባቡና ለአንዲት ሀገር ሲሰሩ የሚበግራቸው ነገር እንደማይኖር አስተምሮን ያለፈ ታሪክ ነው፡፡ የክብርህ መመኪያ ደስታና ህይወትህ የሆነችውን ውብ ሀገር ከወራሪ ትታደግ ዘንድ የምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜኑ እና የደቡቡ ሰው ፊትህን ወደ አድዋ አዙረህ ወረኢሉ ላይ ቆየኝ ያለውን የመሪውን ቀጠሮ አክብሮ ለነፍስ ቀጠሮ በነብስ የደረሰ ሳተና ህዝብ፣ የድል አክሊል የተቀናጀበት ታሪካዊ ቀን ነው"

‘የታከመ ስብራት’ ቅዳሜ ምሽት ይጠብቁን!

የኢትዮጵያን መንግሥት አመራር ለማጠናከር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ለጤና ሚኒስትርነት ያቀረቧቸው ዕጩዎች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተቀ
+4
የኢትዮጵያን መንግሥት አመራር ለማጠናከር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ለጤና ሚኒስትርነት ያቀረቧቸው ዕጩዎች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተቀባይነት አግኝተው ጸድቀዋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀድሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንንንም በክብር አሰናብቷል። ከጠዋቱ  ምስሎች በጥቂቱ።

ዶክተር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ ስብሰባው ዶክተር መቅደስ ዳባ ሹመት አጽድቋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አ
ዶክተር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ ስብሰባው ዶክተር መቅደስ ዳባ ሹመት አጽድቋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዶክተር መቅደስ ዳባ  የሥራ ልምድ ዘርዝረው ለምክር ቤቱ ባቀረቡት መሰረት ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ሹመቱን አጽድቋል፡፡

አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ ስብሰባው አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ ሹመት አጽድቋል፡፡ ጠቅላይ
አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር  ሆነው ተሾሙ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ ስብሰባው አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ ሹመት አጽድቋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ  የሥራ ልምድ ዘርዝረው ለምክር ቤቱ ባቀረቡት መሰረት ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ሹመቱን ማጽደቁን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡

አቶ ተመስገን ጥሩነህ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ ስብሰባው የአቶ ተመስገን ጥሩነህን ሹመት አጽድቋል፡፡ ጠቅላይ ሚ
አቶ ተመስገን ጥሩነህ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ ስብሰባው የአቶ ተመስገን ጥሩነህን ሹመት አጽድቋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአቶ ተመስገንን የሥራ ልምድ ዘርዝረው ለምክር ቤቱ ባቀረቡት መሰረት ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ሹመቱን ማጽደቁን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡

አድዋ ነጠላ ትርክትን የናደ፣ የኢትዮጵያዊያንን ህብረት ያነፀና የብሔራዊ አርበኝነትን በማይነቀነቅ ዓለት ላይ ያስቀመጠ የወል እውነታችን ማጽኛ ነው! ኢትዮጵያውያን ብዝሃነታቸው የጥንካሬያቸው መሰረት
አድዋ ነጠላ ትርክትን የናደ፣ የኢትዮጵያዊያንን ህብረት ያነፀና የብሔራዊ አርበኝነትን በማይነቀነቅ ዓለት ላይ ያስቀመጠ የወል እውነታችን ማጽኛ ነው! ኢትዮጵያውያን ብዝሃነታቸው የጥንካሬያቸው መሰረት መሆኑን በተግባር የተገለፀበት  ኢትዮጵያዊነት ብሎም አፍሪካዊነት ከፍ እንዲል ፈር የቀደደ የታሪካችን አሻራ ነው ዓድዋ! ዓድዋ ኢትዮጵያዊያን በህብረት ከጫፍ ጫፍ ተምመው በአብሮነት ደምና አጥንታቸውን የገበሩበት የሕብረ ብሔራዊ አንድነት ዓርማ ነው። ዓድዋ ኢትዮጵያዊያን በብሔራዊ ገዥ ሀሳብ ሲሰባሰቡ ጠንካራ የማስተባበር፤ የመምራት፤ የመደማመጥና ፈተናዎችን በአብሮነት የመሻገር  ችሎታ እንዳላቸዉ ያስመሰከሩበት ታላቅ ታሪክ ነው። የዓድዋ ድል ለኢትዮጵያዉያን ሁሉ የአርበኝነት አምድ የሆነ በእሳት ተፈትኖ የነጠረ በወጀብ የማይናወጥ ህብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት የታነፀበት የብሔራዊ አርበኝነት ምሰሶ ነው። ዓድዋ የኢትዮጵያዊያን አይበገሬነት፤ ጀግንነት፣ ሕብረትና አንድነት በተግባር የተመሰከረበት የብሔራዊነት ምልክት፣ የወል ታሪካችን አርማ ነዉ። ዓድዋ የብሔራዊነት ምሰሶ ነው ስንል ኢትዮጵያዊያን ከጫፍ ጫፍ በወል ተምመዉ ያስመዘገቡት ድል የጋራ ትናንትን ከነገ ጋር ማስተሳሰሪያ ገመዳችን መሆኑን የሚገልጽ ሀቅ ስለሆነ ነው፡፡ ብሔራዊ ገዥ ትርክት ልክ እንደ ዓድዋ ድል ሁሉም ኢትዮጵያዊያን በሀገራቸው ጉዳይ እኩል ተሳትፎና ተጠቃሚነት እንዲኖራቸው የሚያስችል ሲሆን ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ በተሰናሰለ የብሔር-ብሔረሰቦች ላብ እና ደም ድምር ውጤት የተገነባችና በወል ጥረቶቻቸው የምትበለጽግ ሀገር ናት።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ በሚገኘው 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በምክር ቤቱ አባላት አስተያየቶች እና ጥ
+1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ በሚገኘው 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በምክር ቤቱ አባላት አስተያየቶች እና ጥያቄዎች እያቀረቡ ነው፡፡ በዚሁ መሠረት፡- 👉 የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች የመልካም አሥተዳደር ችግር ወደ መሆን እየተሸጋገሩ በመሆኑ በልዩ ሁኔታ የሚጠናቀቁበት አቅጣጫ ቢሰጥ፣ 👉 ኢትዮጵያ የዕዳ ጫናን ለመቀነስ እየተከናወኑ ስላሉ ተግባራት ማብራሪያ ቢሰጥ፣ 👉 ሕገ-ወጥ የማዳበሪያ ዝውውር (ንግድ) እና በወቅቱ ለአርሶ አደሩ ከማድረስ አኳያ በተለይም በአማራ ክልል ችግር እንዳለ ይነሳል፤ መንግሥት በዚህ ጉዳይ ላይ ምን እየሠራ ነው? 👉የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦላቸው ወደ ግንባታ ያልገቡ እና ተጀምረው እየተጓተቱ ያሉ የልማት ሥራዎች በልዩ ትኩረት እንዲከናወኑ ቢደረግ? 👉 በአንዳንድ አካባቢዎች ከተስተዋለው ድርቅ ጋር በተያያዘ መንግሥት የዜጎችን ሕይወት ለመታደግ እየሠራ ስላለው ሥራ ማብራሪያ ቢሰጥ? 👉 የስፖርት ጨዋታወች ውርርድ (ቤቲንግ) ከሚያስከትለው አሉታዊ ተጽዕኖ አንጻር በመንግሥት በኩል የታሰበ ነገር ካለ ቢገለጽ? 👉 በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከአዲስነቱ ጋር በተያያዘ ያለው የልማት ፍላጎት ከፍተኛ በመሆኑ የፌዴራል መንግሥት በዚህ ጉዳይ ላይ ምን አስተያየት አለው? የሚሉና ሌሎች የባህር በር ጉዳይ፣ የሰላምና ጸጥታ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎች ቀርበዋል።

photo content

ሀገራችን ኢትዮጵያ ከፍተኛ የመልማት የበልፀግ አቅም ያላት ሀገር ናት። ኢትዮጵያ ትናንት ያላትን አቅም በቅጡ ተረድቶ እና ለይቶ መጠቀም ባለመቻል ዜጎቿ ሲራቡ ነበር። አቅሟ እጅግ በጣም ትልቅ ነው አለም ላይ ካሉ የአፈር አይነቶች 25 አካባቢ የሚሆኑትን በጉያዋ ይዛለች። ይህም ማለት ተዘርቶ የማይበቅል የሰብል አይነት፣ ተተክሎ የማይፀድቅ የችግኝ አይነት የለም ማለት ነው። ደጋ፣ ወይና ደጋ፣ ቆላማ የአይር ንብረቶችም እንድሁ አሏት። ችግር የነበረው ያለንን አቅም ለይቶ መጠቀም ነበር። ባለራዕይ መሪ ሲኖር አይኑን ገልጦ በማየት ያለንን አቅም ያለንን ሀብት አይናችንን ገልጠን እንድናይ ያደርጋል። ሰርቶ በማሳየት ውጤት አምጥቶ ህዝቡ እንድከተለው ያደርጋል። ጠቅላይ ሚኒስተራችን ዶ/ር አብይ አህመድ የሀገራችንን የመበልፀግ አቅም እንድናይ እንድንረዳ እና በተሰማራንበት ሁሉ ውጤት እንድናስመዘግብ ቀን ሌት የሚታትሩ መሪ ናቸው። ከተማ ላይ ማምረት ብሎም ራስን መመገብ ይቻላል በማለታቸው አዲስ አበባ ላይ በዶሮ እርባታ ከራስ አልፈው ሚሊየነር የሆኑ ወጣቶች ክ/ከተማችን ላይ ጭምር አሉ። የጓሮ አትክልት ከራስ ፍጆታ ተርፈው ለገበያ ያቀረቡ በርካቶች ናቸው። በአጭር ጊዜ በትንሽ ቦታ፣ በእቃ ላይ ማምረት ይቻላል የሚለው ከራዕይ ከእቅድ ተሻግሮ ውጤት ተመዝግቦበታል። ለዚህ ውጤት መመዝገብ ምክንያት ደግሞ የጠቅላይ ሚኒስትራችን የሌማት ትሩፋት ፕሮግራም መጀመር ነው። ትናንት አፋር ላይ ስንዴ ይመረታል ብሎ ማሰብና መገመት የማይታሰብ ጉዳይ ነበር። ዛሬ ግን አፋር የስንዴ ምርት ብቻ ሳይሆን የሙዝ ምርትም ሌሎችም መመረት የሚችልበት አካባቢ መሆኑን አይን ያስገለጡት ጠቅላይ ሚኒስትራችን ናቸው። ሶማሌ፣ አፋር ላይ የስንዴ፣ ጅማ ላይ የሩዝ ምርት፣ አዲስ አበባ ከተማ ላይ ዶሮ፣ እንቁላል፣ ወተት እናመርታለን ቢባል ትናንት ቀልድ ሊመስል ይችል ነበር። ዛሬ ግን እውን ሆኖ አለም የሸለመው ተግባር ሆኗል። ስራ ሲሰራ የሚጮኸው ሰነፍ ሊበዛ ይችላል። ሊያደናቅፍ የሚጥረው ጠላት ይበዛ ይሆናል። ራዕይ የሌላቸው ምን እየተፈጠረ እንደሆነ ላይረዱ ይችላሉ። ቁም ነገሩ ለሀገር ለመጥቀም ሁሉንም ንቆ ራዕይን መከተል ነው። ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር አብይ አህመድ አቧራውን ትተው አሻራ በማሳረፋቸው፣ በምግብ ዋስትና እና በተመጣጠነ ምግብ ላሳዩት የአመራር ቁርጠኝነትና ተግቶ መስራት አለም ሸለማቸው። ኢትዮጵያንም ስሟን በክብር በአለም ላይ ከኢትዮጵያ የተሻገረ አቅም እንዳላት አሳይተው አስጠሯት። ስራን ተግቶ ለራዕይ መስራት መቻል ከራስ የተሻገረ ለአለም ይጠቅማል። አለምም ለተሰራላት ስራ ሁሉ ታመሰግናለች። ኢትዮጵያ በየዘመናቱ በልጆቿ ኮርታለች። ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድም ሀገራችንን በአለም አደባባይ ደጋግሞ ስሟ ከፍ ብሎ እንድጠራ ተግተው በመስራት ደጋግመው ከፍታዋን በማሳየት አኩርተዋታል። ሁላችንም በተሰጠን ኃላፊነት፣ በተሰማራንበት ቦታ ሁሉ ውጤት በማስመዝገብ ለሀገራችን አሻራ እናሳርፍ። #መልካም_ቀን_ይሁንለዎ ! #Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !

ሚዲያው ትርክትን አስተካክሎ ታሪክ ለመስራት ያግዛል፡፡ ኢትዮጵያ የነበራትን የዳበረ የወንድማማችን/ እህትማማችነትን፣ የአብሮነትን፣ የእንግዳ ተቀባይነትን እሴት የትርክቷ ማጠንጠኛ አድርጋ በመስራት ላይ ትገኛለች፡፡ ትናንት የትርክት ወጥነት በማጣታችን የነበሩን እሴቶች መደብዘዝ እንድገጥማቸው ሆኖ ቆይቷል፡፡ ባለፉት ጊዚያት ሚዲያውን በአግባቡ ባለመጠቀማችን ከታሪክ ሰሪነት ይልቅ በታሪኩ ላይ የማይግባባ በታሪኩ ላይ አለመግባባት ብቻ ሳይሆን የሚጨቃጨቁ ልጆች እንድኖራት አድርጎታል፡፡ ታሪካችንን በአግባቡ እንዳንጠቀም ሚዲያዎቻችንን በአግባቡ ሳንሰራባቸው ቀርተናል፡፡ ማህበራዊ ሚዲያ፣ መጽሐፍ፣ መፅሄት፣ ቴሌቪዥን፣ ራድዮ፣ ፊልም፣ ጋዜጣ፣ ተረት፣ አፈ ታሪክ፣ ስርዓተ ትምህርት የመሳሰሉት ሁሉ በተጠና መንገድ ለትውልዳችን የሚጠቅሙ ትርክታችንን ወጥነት እንድኖረው የሚሰራባቸው ማድረግ ግድ ይላል፡፡ ሚዲያው ትርክትን የመፍጠር በፈለግነው ልክ ፈጥሮ የምንፈልገው ቦታ የማድረስ አቅም አለው፡፡ የፈጠርነው ትርክት ሰው ዘንድ መድረሻ መንገዱ ሚዲያ ነው፡፡ ህንድን ስናነሳ ቦሊውድ በሰው አእምሮ ውስጥ እንድትታተም ባህሏን አኗኗሯን እምነቷን ሁሉ ነገሯን ለማስተዋወቅ እድል ሰትቷል፡፡ ሚዲያው አሜሪካን በምንም መንገድ የመጨረሻ ችግር ውስጥ እንኳን ብትሆን መውጣት የምትችል ሀገር አድርጎ መሳል የቻለው ሚዲያው ነው፡፡ በሚዲያ የተፈጠረ ትርክት ወደ ተግባር ተቀይሮ ታሪክ መሆኑ አይቀሬ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ሁኔታ አሁን ላይ ታሪክ ሰሪ ትውልድ እየተፈጠረ ነው፡፡ የትርክት ወጥነት እንዲፈጠር የሚሰሩ ስራዎችም በርካታ ናቸው፡፡ የትርክታችን ማጠንጠኛ የትናንት ወረታችን ነው፡፡ ወረታችን ደግሞ የህዝባችን የአብሮነት መሰረት የሆነው ወንድማማችነት/ እህትማማችነት ነበር፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን የጋራ ድል ያለን በጋራ ታሪክ የሰራን ድንቅ ህዝብም ነን፡፡ አሁን ላይ እየመጣ ያለውን የብልፅግና ጉዞ ማፍጠን የሚቻለው በተባበረ ክንድ ነው፡፡ ሁላችንም አብሮነታችንን አጠናክረን የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ይገባናል፡፡ የምንሰራው ስራ በሁሉም ተሳትፎ እንዲሆን ሚዲያውን መጠቀም ይገባል፡፡ ይህን ለማድረግ በተሰማራንበት ሁሉ ኃላፊነታችንን በአግባቡ እንወጣ፡፡ መልካም ቀን ይሁንለዎ! #Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና

ኢትዮጵያ የወንድማማችነት/ እህትማማችነት አሴት ላይ ቆማ አንድነቷን ያጠናከረች ሀገር ናት። ብዙ የመከፋፈል፣ ብዙ አንድነትን የሚጎዱ ስራዎ ቢሰሩም የህዝባችን አንድነት እየጠነከረ ቀጥሏል። ኢትዮጵያውያን የአንድነታችን መሠረት ወንድማማችነት/ እህትማማችነት ነው። ትውልዱ ላይ ለብዙ ጊዜ አንድነት ሳይሆን ተፈጥሯዊ ልዮነቱን ወደ አንድ አይነትነት ለማምጣት በርካታ ስህተቶች ተሰርተዋል። ህዝባችንም አንድ ላይ ሆኖ አንድ አይነትነትን ታግሎ ቀይሮታል። በርግጥ ታግሎ የቀየሰው እሳቤ መልሶ የአጠፋ ትርክቱን ይዞ ፍፁም ልዮነት ላይ ብቻ በመስራት በአንድ ላይ የሰራቸውን የጋራ ታሪኮቹን ሳይቀር በመነጣጠቅ መንፈስ እንዲያቸው አድርጓል። የጋራ ድል ነው ብሎ ከፍ አድርጎ ከመያዝ ይልቅ የእኔ ብቻ ነው የሚል በአንድ በኩል ሲፈጠር በሌላ ጫፍ ደግሞ ድሉ ድል ቢሆን እንኳን የማንኳሰስ ችግርን ፈጥሮ አልፏል። ፓርቲያችን ብልፅግና እነዚህ እና ሌሎችም የትናንት እዳ እና ስብራቶቻችንን ከስር መሠረቱ በመለየት የመፍትሄ መጠገኛ መንገድኑ አምጥቷል። አንዱ የአንድነታችን መሠረት የቆየው የህዝባችን በወንድማማችነት/ እህትማማችነት ላይ የተገነባው አንድነት ነው። ኢትዮጵያ በብዝሃነት የተዋበች የብዝሃነት ማሳያ ሀገር ስትሆን ብዝሃነቷ በመተሳሰብ በመፈቃቀር በወንድማማችነት ላይ መሰረት ያደረገ ውብ መሠናሰል የፈጠረ ነው። አንዳይነትነትም ሆነ ፍፁማዊ ልዮነት በኢትዮጵያ ውስጥ ዋጋ ቢስ እሳቤዎች ከመሆናቸው ባሻገር ህዝብ የጎዱ ጭምር ናቸው። በመሆኑም በወንድማማችነት/ እህትማማችነት ላይ ማዕከል ያደረገ ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ማጠናከር የኢትዮጵያ ብልፅግናን ለማሳካትም ሆነ የህዝባችንን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው። በወንድማማችነት/ እህትማማችነት ላይ ተመስርተን አብሮነታችንን እናጠናክር። #መልካም_ቀን_ይሁንለዎ ! #Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !

የአድዋ ድል ለኢትዮጵያ የድል ታሪክ ለመላው የአለም ጭቁን ህዝብ የእኩልነት ፋና ወጊ ድል ነው። አድዋ አልገዛ ባይነት፣ ጀግንነት፣ እየተገዙ ላሉ የነፃነት ትግል ፋና ወጊነት ነው። ኢትዮጵያ ለሁሉም ነገር ፋና ወጊ ናት። ምንም እንኳን ልጆቿ የተጀመረውን አሳድጎ ከማስቀጠል ይልቅ አንድ እርምጃ ወደ ፊት ሶስት ወደ ኋላ የሚጎትት ድርጊት የፈፀሙበት ታሪክ ቢኖረንም የተሰሩ በደማቅ ቀለም ታሪክ የፃፋቸው ታሪኮች አሉን። የአድዋ ድልን ጀግኖች አርበኞቻችን በስጦታ ለአለም በአበረከቱበት ወቅት አለም ጥቁር እና ነጭ፣ ሴት እና ወንድ፣ የመሳሰሉትን ተፈጥሯዊ ልዮነቶች መሠረት አድርጋ የበላይ የበታች የሚኮንበት ወቅት ነበር። በአድዋ ላይ ግን ነጮችም የሚሸነፉ ሰዎች መሆናቸውን ከጥቁር በምንም የማይበልጡ፣ ጥቁሮችም ከነጮች በምንም እንደማያንሱ ያሳየ ታሪክ ነው የተፃፈው። ነጮችንም ማሸነፍ አይቻልም የሚለው በጊዜው የታመነበት እሳቤ ተረት ተረት ሆኖ እንድቀር ያደረገችው ኢትዮጵያ ነች። ተረት ተረት ሆኖ እንድቀር የተደረገወም በአድዋ ተራሮች ላይ ነው። የሴት ብልሃት የሴት እኩልነት ውጤታማ መሪነትንም ያየነው ዛሬ አልነበረም በአድዋ ድል ላይ በነበረ የጦር ታክቲክ ነድፈው ስኬት ሲያስመዘግቡ ጦርነቱ ላይ አሸናፊ የሚያደርግ ስልት ሲነድፉ የነበሩ ሴቶች በመሪነት አዋግቶ ድል ማድረግ የሚችሉ ከወንዶች እኩል መሆናቸውን በተግባር ያሳዩበት ነበር። አድዋ የኢትዮጵያ ታሪክ ብቻ አልነበረም የአፍሪካ ብቻም ሆኖ አልተገደበም በወቱ አትችሉም ከእኛ ታንሳላችሁ ለተባሉት ሁሉ ቢሆን እንጂ። አሁን ላይ የሴተቶች እኩልነት፣ ሴቶች ይችላሉ የሚሉት ሀሳቦች ሁሉ በአድዋ ተራራ ላይ ግን ከወንዱ እኩል ተግባራዊ ስምሪት ሰጥተው የሚታይ ውጤት አምጥተው ያረጋገጡበትን ታሪክ ማውሳት በቂ ነው። አድዋ ትናንት አባቶቻችን ለአለም እኩልነትን በተግባር አበረከቱ፤ ኢፍትሃዊነትን በተግባር በፍትሃዊነት ሻሩት። ቅኝ ገዥነት ከጉልበት ከመቻል ባሻገር ኢፍትሀዊነት ስለነበር በፍትህ የተተካው በአድዋ ነበር። ዛሬ አዲስ አበባ አባቶቻችን እናቶቻችን ለመዝመት ከጠነሰሱበት ከመነሻው ከፒያሳ ላይ የአድዋ ድል መታሰቢያን ገንብታ ለኢትዮጵያውያን አበርክታለች። የአድዋ ድል መታሰቢያ እኛ ኢትዮጵያውያን አሸናፊዎች መሆናችንን ብቻ አይደለም ለፍትህ ስንል የምንዋደቅ መሆናችንን ጭምር እንጂ። እኛ ኢትዮጵያውያን ድል አድራጊነታችንን ብቻ አይደለም እኩልነትን ሳይደርሱብን አለመድረስን ፍትህ ለሚያጓድሉ ፍትሃዊነትን የምናስተምር እንጂ። ኢትዮጵያ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያራምዷት ልጆች ሲኖሯት ሶስት አራት ወደ ኋላ የሚጎትቷት ባንዳዎችም አሉባት። የአድዋ ድል ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ብሎም ፍትህ ለተጓደለባቸው የአለም ህዝብ መነሳሳትን ፍትህ መስፈንን የተሳሳተው እሳቤ መቃናትን ያስተማርንበት የጀግንነት ታሪክ ትናንት የሚያነሳው የሚያወሳው ለመማሪያነት የሚሰበስበው ባለመኖሩ ሳንጠቀምበት ቆይተናል። እሱ ደግሞ የዛሬ አርበኞች እንዳይፈጠሩ አድርጓል፣ የወል ታሪካችን፣ የጋራ ድላችን ወረት እንዳይኖረው የትውልድ ጅረት ላይ ቋጥኝ እየሆነ መቆራረጥ ፈጥሯል። ለዚህም ነው የትውልድ ጅረት ላይ ቋጥኝ ተቀምጦ እንዳያሰናክለን የአድዋ ድል የወል ታሪክ የጋራ ድል መሆኑን የሚያሳይ የአድዋ ድል መታሰቢያ ከመነሻው መገንባታችን። በየዘመኑ የሚጠበቅብንን መወጣት ስንችል ኢትዮጵያ ቀና ብላ ትቀጥላለች። ለአለምም ስልጣኔን መሪነትን፣ ፍትሃዊነትን፣ እኩልነትን፣ ሰጥቶ መቀበልን እያስተማረች ትቀጥላለች። አድዋ የኢትዮጵያውያን የወል ታሪካችን የጋራ ድላችን ነው። የጋራ ድሎቻችንን ጠብቀን ተንከባክበን የወል ማንነታችንን በማይነቃነቅ አለት ላይ እየገነባን ለአለም ማበርከት ያለብንን እያበረከትን እንቀጥላለን። ሁላችንም የሚጠበቅብንን ተወጥተን የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ! #መልካም_ቀን_ይሁንለዎ ! #Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !

ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጥምቀቱ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። መልካም በዓል! #Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና