ru
Feedback
የስንኝ ቋጠሮ

የስንኝ ቋጠሮ

Открыть в Telegram

የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!

Больше
2 046
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней
Архив постов
አደራ ለቡሄ ክረምቱ ዝናቡን ያለልክ ሲያፈሰው በቤቱ ሲታደም ጉብል አዋቂው ሰው ናና በፉጨትህ ጥራኝ እወጣለሁ አረማ ጉልጉሎ ወይ እንጨት ለቀማ በወጣሁኝ ቁጥር ባንተ ከምታማ አንተ ብቅብለህ ድምፅን አሰማ አባባ ሳይሰማ እማማም ሳታየኝ አንዴ ብቅ ብለህ አይንህን አሳየኝ ይህ ሁሉ ካልሆነ አንዱም ካልተሳካ ፎቶህን ስደደው አቅፌው ልተኛ ይሄም ካልሆነልህ ከጠፋህ መፍትሔ ያው ነሀሴም አይደል እንዳትቀር ለቡሄ የምትወደውን ሙልሙሉ ስለምሰራ እንዳትቀርብኝ አንተ ልጅ አደራ ሆያ ሆየ እያልክ የመጣህልኝ እለት አይኖቼ ይበራሉ አገኛለሁ ጉልበት ሽንሽኔን ለብሼ ደር እና አምባሬን አጌጥበታለሁ ሆያያ ሆየ እያልክ ና እጠብቅሃለሁ ቡሄ ምክንያቴ ነው እኔ አንተን ለማየት ሳላይህ እንዳይልፍ እንዳይልቅ ክረምት እመጣለሁ ወንዙን ተራራው ባህሩን አልፌ ለፍቅራችን ስል ውዴ ተንሰፍስፌ እኔም ናፍቀሽኛል አይንሽን አያለሁ ሆያሆየ ብየ እመጣልሻለሁ አባታሽ ሳያዩኝ ወንድምሽ ሳይገለኝ ላንቺ የምነግርሽ አንድ መልክት አለኝ ግን አሁን አይሆንም ያኔ እነግሻለሁ የኔ አለም ጠብቂኝ ሆ ብየ እመጣለሁ የጌቶች ጌታየን ፍቃድ ጠይቂያለሁ ገና ሳትነግሪኝ መንገድ ጀምሪያለሁ ሆያሆየ ብየ እመጣልሻለሁ ✍ .... @nitsuti1419

ውድድራችንን ለመጀመር የተወሰኑ ደቂቃዎች ይቀሩናል።አሁንም ወዳጆቻችሁን ወደ ቻነሉ መቀላቀል አትርሱ። @gitmv

የቀድሞው ህጋችን እንደተጠበቀ ነው።ቅድሚያ 60 ላይክ ለሚደርስ ተወዳዳሪ የ 25 ብር ካርድ፣ሁለተኛ 15 ብር እንዲሁም ለሶስተኛ 10 ብር ካርድ የምንሸልም ይሆናል። ውድድሩን ምሽት 3:00 እንጀምራለን።እስከ 2 ሰዓት ድረስ ግጥሞቻችሁን ላኩልን። @gitmv

ምሽት ላይ ለሚኖረን የግጥም ውድድር ግጥሞቻችሁን @mogea@Abebekasu ላኩልን። ክረምቱ ስንኞቻችሁን ይሻል።በክረምት ያላችሁን የትዝታ፣የናፍቆት፣የፍቅር፣የልጅነት ስሜቶቻችሁን አጋሩን። ሌሎች ወዳጆቻችሁንም ወደ ቻናሉ ጋብዙ። @gitmv

ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች የግጥም ውድድር ሀሙስ ምሽት ለማሰናዳት አስበናል።ስለዚህም ለዛ የሚሆን ግጥም ብትልኩልን እንደምንቀበል ለማሳወቅ እንወዳለን። 1.የግጥሙ ሀሳብ በክረምት ውስጥ ስለሚያልፍ ጊዜ የሚያትቱ ስንኞች ይሆኑ ዘንድ እንሻለን። 👉እስኪ ክረምትን በስንኞቻችሁ ግለፁልን። ምናልባት "ክረምት እና ናፍቆት"፣"ክረምት እና ልጅነት"፣"ክረምት እና ትዝታ"፣"ክረምት እና ፍቅር" እና መሰል የግጥም ሀሳቦችን የያዙ ስንኞችን @mogea እና @Abebekasu ላይ ላኩልን።

*አትምጪ* አለመምጣትሽን ልቤ ይከጅለዋል ጠብቄሽ መቅረትሽን ውስጤ ይሽተዋል የመጣሽ እንደሆን 'መሄድሽ ነው' እያልኩ ሰዓቱን እያየሁ ከመቅረትሽ ይባስ በሃሳብ እዋኛለሁ ናፍቆት ያጎበጠው፤ድካም የተጫነው ልብ እና አካሌን መምጣትሽ አይደለም እቅፍሽም እንዲሁ መዳኛ 'ሚሆነው በዛው መቅረትሽ ነው ከደዌ 'ሚያርቀው። ✍Ab 17/11/2014

ሆያ ሆዬ ድቅን አለ ፊቴ ሳስበው በድንገት፣ ሆያ ሆዬ ስንል ያኔ በልጅነት፡፡ የሙልሙሉ ዳቦ የኩበቱ ሽታ፣ መቼም አይረሳም የቡሄ ትዝታ፡፡ ሆያ ሆዬ ሆ ሆያ ሆዬ፣ ሙልሙሊቷን ስጡኝ እባኮ ጌታዬ፡፡ እዛ ማዶ ሆ አንድ ስንደዶ፣ እዚ ማዶ ሆ አንድ ስንደዶ፣ የዚ ቤት ጌታ ጥርሰ በረዶ፣ "እንለው ነበረ" ጥርሱ ግን ወላልቆ ቢሆንም ባዶ፡፡ ድቅን አለ ፊቴ ሳስበው በድንገት፣ ጆሮዬን ተሠማው የጅራፉ ጩኸት፣ ተሠማኝ ሙቀቱ የችቦውም እሳት፡፡ ሆያ ሆዬ ሆ ሆያ ሆዬ፣ ሙልሙሊቷን ስጡኝ እባኮ ጌታዬ፡ እዛ ማዶ ሆ አንድ እረኛ፣ እዚ ማዶ ሆ አንድ እረኛ፣ የዚ ቤት ጌታ የኢትዮጵያ አርበኛ፣ " እንለው ነበረ" ለራሱም ቢያስፈልግ ጠባቂ ዘበኛ፡፡ ዳቦውም ይበላል ችቦው ይለኮሳል፣ ሆያ ሆዬ ተብሎ ቡሄ ይከበራል፡፡ እጅጉን ደነቀኝ ገረመኝ ሳስበው፣ ሆያ ሆዬ ማለት ራሡ ጥበብ ነው፡፡ ©Afe.Z.eth @gitmv

የጥቅምት መስክ ነኝ !! (በእውቀቱ ስዩም) ሰው ለሰው ይፈርዳል ልብን ዘልቆ ሳያይ ላልቃሽ እያዘነ በፈካ ገፅ ውስጥ ያደፈጠን ስቃይ -ማነው የመዘነ? የይስሙላም ይሁን: ከልብ ያለቀሰ አያጣም አይዞህ ባይ ካንጀት ይሁን ካንገት : እንባ ላፈሰሰ አይጠፋም ከምንገድ : መሀረብ አቀባይ ይብላኝ ላሳሳች ፊት: አፅናኝ ለማይጋብዝ አንዳንድ ሀዘን አለ ከላይ ተሰውሮ : ልብ የሚበዘብዝ የጥቅምት ብሩህ መስክ: አደይ የለበሰ ስንቱን ጉድ አዝሎታል: ስሩ ከተማሰ!! የጥቅምት መስክ ነኝ : አደይ ያደመቀው ፈገግታ ቢውጠው: ዘበት ቢደብቀው የኔን ብቻ ህመም: እኔው ነኝ የማውቀው:: (ተከፍተው የተከፉ ለማይመስሉ)

ለግጥም አፍቃሪዎች ፧ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን የስነ ግጥም ቻናሉን join ብለው እንዲቀላቀሉ እጋብዛለሁ። በብዙ ይዝናኑበታል ያተርፉበታልም። join👇👇👇 @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm @lij_werkneh_gitm

*የማይድን...* ምን ብንታገል ከሆድ የማናወጣው በጊዜ ሂደት እንርሳው ብንል የማንረሳው ስንት ህመም አለን ሰርክ የሚያደማን 'እህህ' ብለን የማይወጣልን በሚመሽ እድሜ የማይመሽልን እልፍ ህመም አለን ከቀን እስከሌት ከዘመን ዘመን ከጉያችን ስር 'ሚበረታብን። ✍Ab 07/11/2014

አክሊሉን ሸልመነዋል ሁለተኛ የወጣ ሰው የለም እንሸልመዋለን ብለን ነበር የጠበቅነው ሶስተኛም የለም። @gitmv

ዛሬ ማታ አክሊሉን እንሸልመዋለን!! ውድድር በ ስንኝ ቋጠሮ ብቻ!! @gitmv

የሀገሬ እንግልት ልፋቷና አሳሯ ምነው እንደ አንዲት ሴት ዘጠኝ ብቻ ቢሆን የእርግዝና ወሯ ደሟ ሳይፈስባት ምጧ ሳይበረታ ከጥበበኛ ሰው አዋልዳት ነበር በፍቅር በደስታ። @gitmv ✍በአክሊሉ

አንደኛ 🏆

በዚህ ውድድር ፖስት ከተደረጉ ግጥሞች በጣም የወደዳችሁትን ግጥም inbox አድርጉልኝ መልካም ውድድር አክሊሉ እየመራ ነው!!

ፒን እንዲደረግላችሁ ምትፈልጉ ቢያንስ ሶስት ሰው ወደ ቻናሉ አቀላቅሉ ከዛን በውስጥ መስመር አናግሩኝ

ልብህ ነው እግርማ ታዛዢ ነዉ..ከላከዉ ሚደርስዉ እግርህን ላሰርዉ.....ልብህን ጠይቀዉ እንዳደርስ ላርገህ...... ተራራውን መስሎ ሳትይዝ ያሳጣህ........ በፍራት ጠቅልሎ le comment @Amen122119 @gitmv

አመሏን አውቃለሁ ሰው አልምዳ አታውቅም ተረተረት እጂ ሀሳብ ህልም የላትም ስለወደፊቷ ትንሽ ብትረዳ፣ ተስፋ ቢኖራትም አላሚዋን ጥላ ህልመኛዋን ጥላ ፣ የትም አትሄድም @gitmv @hashuya

ፒን እንዲደረግላችሁ ምትፈልጉ ቢያንስ ሶስት ሰው ወደ ቻናሉ አቀላቅሉ