የስንኝ ቋጠሮ
رفتن به کانال در Telegram
የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!
نمایش بیشتر2 046
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
2 046
ምሽት ላይ ለሚኖረን የግጥም ውድድር ግጥሞቻችሁን @mogea፣@Abebekasu ላኩልን።
ክረምቱ ስንኞቻችሁን ይሻል።በክረምት ያላችሁን የትዝታ፣የናፍቆት፣የፍቅር፣የልጅነት ስሜቶቻችሁን አጋሩን።
ሌሎች ወዳጆቻችሁንም ወደ ቻናሉ ጋብዙ።
@gitmv
2 046
ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች የግጥም ውድድር ሀሙስ ምሽት ለማሰናዳት አስበናል።ስለዚህም ለዛ የሚሆን ግጥም ብትልኩልን እንደምንቀበል ለማሳወቅ እንወዳለን።
1.የግጥሙ ሀሳብ በክረምት ውስጥ ስለሚያልፍ ጊዜ የሚያትቱ ስንኞች ይሆኑ ዘንድ እንሻለን።
👉እስኪ ክረምትን በስንኞቻችሁ ግለፁልን።
ምናልባት "ክረምት እና ናፍቆት"፣"ክረምት እና ልጅነት"፣"ክረምት እና ትዝታ"፣"ክረምት እና ፍቅር" እና መሰል የግጥም ሀሳቦችን የያዙ ስንኞችን @mogea እና @Abebekasu ላይ ላኩልን።
2 046
*አትምጪ*
አለመምጣትሽን ልቤ ይከጅለዋል
ጠብቄሽ መቅረትሽን ውስጤ ይሽተዋል
የመጣሽ እንደሆን 'መሄድሽ ነው' እያልኩ ሰዓቱን እያየሁ
ከመቅረትሽ ይባስ በሃሳብ እዋኛለሁ
ናፍቆት ያጎበጠው፤ድካም የተጫነው ልብ እና አካሌን
መምጣትሽ አይደለም እቅፍሽም እንዲሁ መዳኛ 'ሚሆነው
በዛው መቅረትሽ ነው ከደዌ 'ሚያርቀው።
✍Ab
17/11/2014
2 046
ሆያ ሆዬ
ድቅን አለ ፊቴ ሳስበው በድንገት፣
ሆያ ሆዬ ስንል ያኔ በልጅነት፡፡
የሙልሙሉ ዳቦ የኩበቱ ሽታ፣
መቼም አይረሳም የቡሄ ትዝታ፡፡
ሆያ ሆዬ ሆ ሆያ ሆዬ፣
ሙልሙሊቷን ስጡኝ እባኮ ጌታዬ፡፡
እዛ ማዶ ሆ አንድ ስንደዶ፣
እዚ ማዶ ሆ አንድ ስንደዶ፣
የዚ ቤት ጌታ ጥርሰ በረዶ፣
"እንለው ነበረ"
ጥርሱ ግን ወላልቆ ቢሆንም ባዶ፡፡
ድቅን አለ ፊቴ ሳስበው በድንገት፣
ጆሮዬን ተሠማው የጅራፉ ጩኸት፣
ተሠማኝ ሙቀቱ የችቦውም እሳት፡፡
ሆያ ሆዬ ሆ ሆያ ሆዬ፣
ሙልሙሊቷን ስጡኝ እባኮ ጌታዬ፡
እዛ ማዶ ሆ አንድ እረኛ፣
እዚ ማዶ ሆ አንድ እረኛ፣
የዚ ቤት ጌታ የኢትዮጵያ አርበኛ፣
" እንለው ነበረ"
ለራሱም ቢያስፈልግ ጠባቂ ዘበኛ፡፡
ዳቦውም ይበላል ችቦው ይለኮሳል፣
ሆያ ሆዬ ተብሎ ቡሄ ይከበራል፡፡
እጅጉን ደነቀኝ ገረመኝ ሳስበው፣
ሆያ ሆዬ ማለት ራሡ ጥበብ ነው፡፡
©Afe.Z.eth @gitmv
2 046
የጥቅምት መስክ ነኝ !!
(በእውቀቱ ስዩም)
ሰው ለሰው ይፈርዳል
ልብን ዘልቆ ሳያይ
ላልቃሽ እያዘነ
በፈካ ገፅ ውስጥ ያደፈጠን ስቃይ
-ማነው የመዘነ?
የይስሙላም ይሁን: ከልብ ያለቀሰ
አያጣም አይዞህ ባይ
ካንጀት ይሁን ካንገት : እንባ ላፈሰሰ
አይጠፋም ከምንገድ : መሀረብ አቀባይ
ይብላኝ ላሳሳች ፊት: አፅናኝ ለማይጋብዝ
አንዳንድ ሀዘን አለ
ከላይ ተሰውሮ : ልብ የሚበዘብዝ
የጥቅምት ብሩህ መስክ: አደይ የለበሰ
ስንቱን ጉድ አዝሎታል: ስሩ ከተማሰ!!
የጥቅምት መስክ ነኝ : አደይ ያደመቀው
ፈገግታ ቢውጠው: ዘበት ቢደብቀው
የኔን ብቻ ህመም: እኔው ነኝ የማውቀው::
(ተከፍተው የተከፉ ለማይመስሉ)
2 046
ለግጥም አፍቃሪዎች
፧
ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን የስነ ግጥም ቻናሉን join ብለው እንዲቀላቀሉ እጋብዛለሁ።
በብዙ ይዝናኑበታል ያተርፉበታልም።
join👇👇👇
@lij_werkneh_gitm
@lij_werkneh_gitm
@lij_werkneh_gitm
2 046
*የማይድን...*
ምን ብንታገል ከሆድ የማናወጣው
በጊዜ ሂደት እንርሳው ብንል የማንረሳው
ስንት ህመም አለን
ሰርክ የሚያደማን
'እህህ' ብለን የማይወጣልን
በሚመሽ እድሜ የማይመሽልን
እልፍ ህመም አለን
ከቀን እስከሌት ከዘመን ዘመን
ከጉያችን ስር 'ሚበረታብን።
✍Ab
07/11/2014
2 046
ልብህ ነው
እግርማ ታዛዢ ነዉ..ከላከዉ ሚደርስዉ
እግርህን ላሰርዉ.....ልብህን ጠይቀዉ
እንዳደርስ ላርገህ...... ተራራውን መስሎ
ሳትይዝ ያሳጣህ........ በፍራት ጠቅልሎ
le comment @Amen122119 @gitmv
