HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Открыть в Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Больше2 276
Подписчики
+524 часа
+117 дней
+3430 день
Архив постов
» “God gave you eyes, but you reshape them; He gave you skin, but you stain it; He gave you form, but you alter it. Are you not ungrateful to the Creator?” => "እግዚአብሔር ዓይንን ሰጠህ፣ አንተ ግን ቅርጹን ትለውጣለህ፤ ቆዳ ሰጠህ፣ አንተ ግን ትቀባዋለህ፤ መልክ ሰጠህ፣ አንተ ግን ታዛባዋለህ። ፈጣሪህን የማታመሰግን አይደለህምን?"
» “Women who are so concerned with cosmetics and perfume become ministers of Satan's deceit. They lead others to destruction—and will share in their punishment.” => “በመኳኳያና በሽቶ ይህን ያህል የሚጨነቁ ሴቶች የሰይጣን የማታለል አገልጋዮች ይሆናሉ። ሌሎችን ወደ ጥፋት ይመራሉ—በቅጣታቸውም ይካፈላሉ።”
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው!
» St. Cyprian of Carthage: “Those who dye their hair, paint their faces, or enhance their looks deny the handiwork of God.” "ጸጉራቸውን የሚቀቡ፣ ፊታቸውን የሚቀባቡ ወይም መልካቸውን የሚያሳምሩ የእግዚአብሔርን የእጅ ሥራ ይክዳሉ።"
» St. Clement of Alexandria: “The use of rouge and eyeshadow is evidence of a soul sick with vanity.” "የቀለምና የኩል አጠቃቀም በከንቱ ውዳሴ የታመመችን ነፍስ ያመለክታል።"
የዕለቱን ወንጌል እናንብብ! ሰኔ 20
+++ እንዲህም አለ። እውነት እላችኋለሁ፥ ነቢይ በገዛ አገሩ ከቶ አይወደድም። ነገር ግን እውነት እላችኋለሁ፥ በኤልያስ ዘመን ሦስት ዓመት ከስድስት ወር ሰማይ ተዘግቶ ሳለ በምድር ሁሉ ብርቱ ራብ በነበረ ጊዜ፥ በእስራኤል ብዙ መበለቶች ነበሩ፤ ኤልያስም በሲዶና አገር ወዳለች ወደ ሰራፕታ ወደ አንዲት መበለት እንጂ ከእነርሱ ወደ አንዲቱ አልተላከም። በነቢዩ በኤልሳዕ ዘመንም በእስራኤል ብዙ ለምጻሞች ነበሩ፥ ከሶርያዊው ከንዕማን በቀር ከእነርሱ አንድ ስንኳ አልነጻም። በምኵራብም የነበሩ ሁሉ ይህን ሰምተው ቍጣ ሞላባቸው፥ ተነሥተውም ከከተማ ወደ ውጭ አወጡት፥ ይጥሉትም ዘንድ ከተማቸው ተሠርታባት ወደ ነበረች ወደ ተራራው አፋፍ ወሰዱት፤ እርሱ ግን በመካከላቸው አልፎ ሄደ። ወደ ገሊላ ከተማም ወደ ቅፍርናሆም ወረደ። በሰንበትም ያስተምራቸው ነበር፤ ቃሉ በሥልጣን ነበርና በትምህርቱ ተገረሙ። በምኵራብም የርኵስ ጋኔን መንፈስ ያደረበት ሰው ነበረ፥ በታላቅ ድምፅም ጮኾ። ተው፥ የናዝሬቱ ኢየሱስ ሆይ፥ ከአንተ ጋር ምን አለን? ልታጠፋን መጣህን? ማን እንደ ሆንህ አውቄሃለሁ፥ አንተ የእግዚአብሔር ቅዱሱ አለ። ኢየሱስም። ዝም በል ከእርሱም ውጣ ብሎ ገሠጸው። ጋኔኑም በመካከላቸው ጥሎት ሳይጐዳው ከእርሱ ወጣ። ሁሉንም መደነቅ ያዛቸው፥ እርስ በርሳቸውም። ይህ ቃል ምንድር ነው? በሥልጣንና በኃይል ርኵሳን መናፍስትን ያዝዛልና፥ ይወጡማል ብለው ተነጋገሩ። ዝናም በዙሪያው ባለች አገር ወደ ስፍራው ሁሉ ስለ እርሱ ወጣ። በምኵራብም ተነሥቶ ወደ ስምዖን ቤት ገባ። የስምዖንም አማት በብርቱ ንዳድ ታማ ነበር ስለ እርስዋም ለመኑት።
(የሉቃስ ወንጌል 4፡24-38)
ዶክተሯ ያጋለጠችው ከባድ ምስጥር!! በማሕጸን ካንሰርና ልጅ በማጣት የምትቸገሩ አዳምጡ!! የመናፍስት ውጊያ የገባት ዶክተር!! መምህር ተስፋዬ አበራ #ጸሎት https://youtu.be/pYAh-yWOacY?si=K8M38pv7U4dJdILt
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ! ሰኔ 19»
+++ እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው። በዚያን ጊዜ ለመከራ አሳልፈው ይሰጡአችኋል ይገድሉአችሁማል፥ ስለ ስሜም በአሕዛብ ሁሉ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ። በዚያን ጊዜም ብዙዎች ይሰናከላሉ እርስ በርሳቸውም አሳልፈው ይሰጣጣሉ እርስ በርሳቸውም ይጣላሉ፤ ብዙ ሐሰተኞች ነቢያትም ይነሣሉ ብዙዎችንም ያስታሉ፤ ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች። እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል። (የማቴዎስ ወንጌል 24፡8-13)
“ቤታቸውን በጸሎት፣ በትሕትናና በጋራ ፍቅር የሚባርኩ ባልና ሚስት፣ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት እንደተለኮሱ ሁለት ሻማዎች ናቸው — ብርሃናቸው ጨለማን ይገፋል፤ ለራሳቸው ብቻ ሳይሆን፣ ወደ ቤታቸው ለሚገቡ ሁሉ ሰላምን ያመጣል።” የኦርቶዶክስ ገዳማዊ አባባል
“A husband and wife who bless their home through prayer, humility, and mutual love are like two candles before the throne of God — their light dispels darkness and brings peace not only to themselves, but to all who enter their home.” – Orthodox Monastic Saying
“የትዳር ጓደኛችሁን ስትሉ ራሳችሁን ዝቅ ባደረጋችሁ ቁጥር፣ ክርስቶስ ወደ እናንተ ይቀርባል። በፍቅር በጠረጋችሁት እንባ ሁሉ፣ መላእክት ይደሰታሉ።” “In every moment that you humble yourself for your spouse’s sake, Christ draws near. And in every tear wiped in love, angels rejoice.”
“አንድ ቤት ጠንካራ የሚሆነው በድንጋይ ስለተሠራ ሳይሆን፣ በጸሎት ላይ ስለታነጸ ነው።” – ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ
“A house is strong not because it is built of stone, but because it is built on prayer.”
"ሰይጣን ሺህ መነኮሳትን ከመፍራት ይልቅ የሚጸልዩና የሚዋደዱ ጥንዶችን አብልጦ ይፈራል።" – የኦርቶዶክስ ገዳማዊ አባባል
"The devil fears a praying, loving couple more than a thousand monks." – Orthodox monastic saying
ሰኔ ፲፱ /19/በዚች ዕለት ሰማዕት በመሆን አባ ብሶይ አኖብ አረፈ ትርጓሜውም የጠራ ወርቅ ማለት ነው። ይህም ቅዱስ ከድምያጥ አውራጃ ስሟ ባኖስ ከሚባል አገርከአቅራብ መኰንን ከቆጵርያኖስ ጭፍሮች ውስጥ ከከተማዋ ታላላቅ ሰዎች ልጆች ወገን ነበር ። በዚህም ቅዱስ በመኰንኑ ዘንድ ነገር ሠሩበት። ቅዱሱም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም በፊቱ ታመነ። ወደ አንዴናውም ወሰዱት በመኰንኑ አርያኖስም ፊት ቁሞ በጌታችን ታመነ አርያኖስም በእርሱ ላይ ተቆጣ ለአማልክትም ሠዋ አለው አልታዘዘለትም ሥቃዩንም አልፈራም መኰንኑም ወስዶ ጽኑዕ ሥቃይ አሠቃየው ከዚያም ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡት አዘዘ ወደሚገድሉበት ቦታም ሊወስዱት አወጡት ብዙ ሕዝብም ይከተሉት ነበር እነሆ ከዚያም የአርያኖስ መኰንን አንበሶች ነበሩ። የሚጠብቃቸውም ሰው ነበር እነርሱም በብረት ሰንሰለት ታሥረው ነበር ከእነርሱም አንዱ አንበሳ የብረት ሰንሰለቱን በጥሶ ሩጦ ወደ ቅዱሱ ደረሰ። የእግዚአብሔርም መልአክ ቅዱሱን በአንበሳው ጀርባ ላይአወጣውና ዐይነ ፀሐይ ወደሚባል አገር እስከሚያደርሰው በረረበት ቅዱሱ ግን ዐይኑን ሸፍኖ ስለ ነበረ ወዴት እንዳለ አላወቀም በዚያም ራሱን በሰይፍ ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
መናፍስት እንደተያዙና እንደተሸኙ እንዴት ማወቅ እንችላለን?? የቁርባን ጋብቻ ልፈርስ ይችላል ወይ? ሰይፉ ሾው ከባድ ቅሬታ ቀረበበት!! ገዳሙን ልቀቁ ይሉናል! https://youtu.be/JH59iqmX_AI
“The husband is to love his wife as Christ loved the Church—ready to die for her, to suffer for her, to live for her.” ባል ሚስቱን ሊወድ የሚገባው ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን እንደወደዳት ነው፤ ይህም ለእርሷ ለመሞት፣ መከራን ለመቀበልና ለመኖር ዝግጁ መሆንን ይጠይቃል። (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
“A husband and wife should be like the hand and the eye. When one hurts, the other should weep. When one weeps, the other should wipe away the tears.” ባልና ሚስት እንደ እጅና አይን መሆን አለባቸው። እጅ ሲጎዳ አይን ታለቅሳለች፤ አይን ስታለቅስ ደግሞ እጅ እንባዋን ታብሳለች።
ሰኔ ፲፰ /18/በዚች ቀን ከአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ቁጥር አርባ አምስተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ድምያኖስ አረፈ። ይህም አባት በአስቄጥስ በአባ ዮሐንስ ሐጺር ገዳም ከታናሽነቱ ጀምሮ መነኰሰ ዓሥራ ሰባት ዓመት ያህልም እየታጋደለ ኑሮ ዲቁና ተሾመ። ከእርሱ አስቀድሞ የነበረው አባ ጴጥሮስም ሊቀ ጵጵስና በተሾመ ጊዜ በሊቀ ጵጵስናው ሥራ የሚራዳውና በሥራው ሁሉ የሚአማክረው ስለ ቤተ ክርስቲያን ጥበቃ አዋቂ ሰው ፈለገና አባ ድምያኖስን አማካሪው አደረገው። አባ ጴጥሮስም በአረፈ ጊዜ ኤጲስቆጶሳትና አዋቂዎች ሊቃውንት በአንድ ምክር ተስማምተው በእስክንድርያ ከተማ ይህን አባ ድምያኖስን ሊቀ ጵጵስና ሾሙት ለአገልግሎትም ፅሙድ ሆነ በመልካም ሥራ ሁሉ ጸንቶ ኖረ። ሁልጊዜም ድርሰቶችንና መልእክቶችን እየጻፈ ወደ ሀገሩ ሁሉና ወደ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ይልክ ነበር። በአስቄጥስም ገዳም በአባ መቃርስ ደብር ከነጣቂው ከሀዲ ወገን የሆኑ አርሲሳን የሚሉአቸው መናፍቃን ነበሩ። ይህም አባት አባ ድምያኖስ ስሕተታቸውን ገለጠላቸው ከእርሳቸውም ውስጥ ከስሕተታቸው ተመልሰው ንስሐ የገቡና የታዘዙለት አሉ ያልተመለሱትን ግን አውግዞ ከምእመናን አንድነት ለይቶ አባረራቸው። ይህም አባት ድምያኖስ በተግሳጾቹና በመልእክቶቹ መንጋውን እየጠበቀ አርባ ሦስት ዓመታት ያህል ከኖረና ወደ በጎ እርጅና ከደረሰ እግዚአብሔርንም ከአገለገለ በኋላ በሰላም አረፈ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ! ሰኔ 18»
+++ ወንድምህም ቢበድልህ፥ ሄደህ አንተና እርሱ ብቻችሁን ሆናችሁ ውቀሰው። ቢሰማህ፥ ወንድምህን ገንዘብ አደረግኸው፤ ባይሰማህ ግን፥ በሁለት ወይም በሦስት ምስክር አፍ ነገር ሁሉ እንዲጸና፥ ዳግመኛ አንድ ወይም ሁለት ከአንተ ጋር ውሰድ፤ እነርሱንም ባይሰማ፥ ለቤተ ክርስቲያን ንገራት፤ ደግሞም ቤተ ክርስቲያንን ባይሰማት፥ እንደ አረመኔና እንደ ቀራጭ ይሁንልህ። እውነት እላችኋለሁ፥ በምድር የምታስሩት ሁሉ በሰማይ የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈቱት ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሆናል። ደግሞ እላችኋለሁ፥ ከእናንተ ሁለቱ በምድር በማናቸውም በሚለምኑት ነገር ሁሉ ቢስማሙ በሰማያት ካለው ከአባቴ ዘንድ ይደረግላቸዋል።
(የማቴዎስ ወንጌል 18፡15-19)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
"He who leaves the world behind for the sake of God has already begun to repent," his life declares.
"ስለ እግዚአብሔር ብሎ ዓለምን የካደ ሰው፣ ንስሐ መግባት ጀምሯል’ ስትል ሕይወቱ ትመሰክራለች።"
ከድብርትና ከጭንቀት መንፈስ ለመላቀቅ ይኼንን ዘወትር እናድርግ!! የፀራሞና ደራሞ የድባተና የጭንቀት መንፈሶች!! QUITE DEPRESSION & ANXIETY! https://youtu.be/J7UX5VSLVt0
“He who loves God purely cannot sin with the body.” — St. Maximos the Confessor
“Give your body work to do, or it will work against you.” — St. John Cassian
“Do not be ashamed to get up each time you fall. The victory is not in never falling, but in never giving up.” — St. John Chrysostom
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
