ru
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Открыть в Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Больше
2 280
Подписчики
Нет данных24 часа
+77 дней
+3930 день
Архив постов
ሰይጣን በገንዘብ ይገባል እንጂ በጭራሽ አይወጣም || የተደበቀ መተትን የሚያወጡ ደብተራዎች || የመምህር ተስፋዬ ትምህርት ቀየረኝ! | እኛና ቅዳሴያችን 💥😱🚩 https://youtu.be/rHv5VZnKUvY

አጋንንት የለብኝም ብላችሁ ለምትታበዩ አድምጡ እውነተኛ ጸሎትና አቀራረቡ በጸሎት ሰዓት የማይረሱ ነገሮች || ቀኙ በአጋንንት የተያዘበት ትውልድ 🚩😱💥 https://youtu.be/2toGGusfqvo

መዝሙር ተጋበዙ ውዶች! በያላችሁበት ሰዓት አቆጣጠር እንዴት አደራችሁ፣ እንዴት ዋላችሁ። የልጅነት ትውስታዎቻችን ሁለም የማንረሳቸው መዝሙሮች። ሰላሜ እግዚአብሔር ከሁላችሁ ጋር ይሁን። እንበርታ! 🙏🙏🙏

ለዘመናት ደም የለመዱ፤ የተሰገደላቸው መናፍስቶች አጋንንት አይራብም፥ ቢሮው አይዘጋም መናፍስትን ለምን እንቀጠቅጣለን? በማለዳ ንቁ 2024 #ebs 🚩 https://youtu.be/5PMtdkXHBm8

መዝሙር ተጋበዙልኝ ውዶች! እንዴት ናችሁ ሰላም ናችሁ! በያላችሁበት የእግዚአብሔር ሰላም ከሁላችሁ ጋር ይሁን። 🙏🙏🙏

photo content

◈ ሰይጣን የሰው ልጆችን የክፋት እስረኛ ከሚያደርግበት ዘዴው አንዱ ኃጢአትን "ኃጢአት" ብለን እንዳንጠራት ማለሳለስ ነው፤ ከዚያ ይልቅ መልካም በሚመስልና ቢሰማም ብዙ በማይቆረቁር ስም እንድንጠራው ያደርገናል። ለምሳሌ በትዳር ሳይወሰኑ እንዲሁ ከአገኙት ጋር በዝሙት መውደቅ "ነጻ ፍቅር" ("free love")፣ በሚስት እና በባል ላይ መሄድ ደግሞ "ባለጉዳይ"ነት (affair) ተሰኝተዋል፤ ይህን የሚያደርጉትም ኃጢአቱን ያለ ምንም መሳቀቅ መሥራት እንዲችሉ ስሙን ያሳምሩታል። ◈ ሰው የትኛውንም ኃጢአት ከመስራቱ በፊት ኃጢአቱን የሚጠራበት ስም ይለያል፤ ኃጢአትን የምንጀምረው በጎ ዓላማ እና ጥሩ ስም ያለው አስመስለን ነው፤ የሚሰክረው ከስካሩ በፊት ምን ልታደርግ ነው? ቢሉት "ልዝናና ነው" ይላል፤ የሚሳደበውና የሚራገመውም ከስድቡ በፊት ምን ልታደርግ ነው? ቢሉት "ልመክር" ወይም "እርማት ልሰጥ ነው" ይላል፤ ሌሎቹንም እንዲሁ፤ ጌታችን በመሰለው የጠፋው ልጅ ምሳሌ ላይ ያለውን ልጅ ከአባቱ ቤት ከመውጣቱ በፊት አግኝተን "ለምን ንብረት ተካፍለህ ከአባትህ ቤት ርቀህ ትሄዳለህ?" ብለን ብንጠይቀው፣ "ዓለምን ለማየት" ይላል እንጂ "ኃጢአት ስላማረኝ" እንደማይል ጥርጥር የለውም። ◈ ከኃጢአት መራቅ ትፈልጋለህ? እንግዲያስ ልታደርግ ያሰብከውን ክፋት በስሙ ጥራው፤ አታድበስብስ፣ አታለስልስ፤ በቃ ኃጢአት ነው፤ ስለዚህ አትጀምረው ገብተኽበትም እንደሆነ ስሙን እያሽሞነሞንክ ራስህን አትዋሸው፤ በደል እንደ ሆነ አምነህ በትክክለኛው ስሙ እስክት ጠራውና እስክትጋፈጠው ድረስ መድኃኒት የለህም፤ መዝሙረኛው ዳዊት በኦርዮ ሚስት ተሰነካክሎ ከወደቀ በኋላ ዳግመኛ የተነሣው "አንተን ብቻ በደልሁ፥ በፊትህም ክፋትን አደረግሁ" ብሎ መጸለየ በጀመረ ጊዜ ነው። (መዝ 51፥4) በዲያቆን አቤል ካሳሁን #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

photo content

«አስታውስ!» ◈ ደካማነትህን አስታውስ፣ ያንጊዜ በጣም ጠንቃቃ ትሆናለህ፣ ሊጎዱህ በሚችሉ በትምክህትና በውዳሴ ከንቱም አትሸነፍም፡፡ የተሰጠህን በፍቅር የተሞላ የእግዚአብሔርን ቸርነት አስታውስ፣ ይህም በምስጋና የተሞላ ሕይወት እንድትመራ ያደርግሃል፤ በእግዚአብሔር ፍቅርና ሥራ ላይ ስትታመን ፍጹም የሆነ እምነት በልብህ እያደገ ይመጣል፤ ከእግዚአብሔር ጋር ያሳለፍከው ጊዜ ደግሞ በእምነት እንድትኖር ያበረታታሃል፡፡ ◈ የሰዎችን ፍቅርና ካንተ ጋር ያሳለፉትን መልካም ጊዜ አስታውስ፤ የሰዎችን ቀናነት ትጠራጠር ዘንድ ወይም ያደረጉብህን ክፉ ነገር ታስብ ዘንድ ይገባሃልን? የቀደመ ፍቅራቸው ስለ እነርሱ ይማልዳል ያንተንም ቁጣ ያበርዳል፡፡ ሞት እንዳለ አስታውስ፣ እንዲሁ በዓለም ያለ ፈተናም እንደሚያልፍ "ሁሉ ከንቱ ነው፣ ነፋስንም እንደመከተል ነው፡፡" ማለትን ትረዳለህ፡፡ (መኬ 1፥14) ◈ በእግዚአብሔርፊት መቆምህንና እርሱም እንደሚመለከትህ አስታውስ፣ ያኔ ኃጢአት አትሰራም እግዚአብሔርን ታየዋለህና፡፡ ስለ አንተ የፈሰሰውን የክርስቶስን ክቡር ደም አስታውስ፤ በዚህም ሕይወትህ ያለውን ዋጋ በእርግጥ ታውቃለህ፤ በዓይኖችህ ፊት የከበረ ይሆናል፣ ስለዚህም በከንቱ በመኖር አታጠፋውም፣ "በዋጋ ተገዝታችኋልና"  እንዲል ቅዱስ ጳውሎስ፡፡ (1ኛ ቆሮ 6፥20) በወላጆችህ እምነት በተጠመቅህባት ቦታ ለእግዚአብሔር የገባኸውን ቃል አስታውስ፤ ዲያብሎስን፣ ሥራዎቹን ሁሉ፣ ሐሳቦቹንና ጥበቡን፣ ኃይሉንም ትክድ ዘንድ፡፡ በዚህ ዓለም እንግዳመሆንህንና ወደ ሰማያዊው ቤትህ እንደምትመለስ ዘወትር አስታውስ፤ ያን ጊዜ በዚህ ዓለምና በደስታው ተስፋ ማድረግን ትተዋለህ፡፡ ◈ በጠባቡ በር መጓዝ ወደ መንግስተ ሰማያት እንደሚያደርስህ አስታውስ፤ ሰፊው ደጅ ፊት ለፊትህ ተከፍቶ ብታየው፣ አልፈኸው ሂድ ከእሱም ራቅ፣ በእርሱ የሄዱ እንዳሉ አልቀዋልና፤ ዘላለማዊው ሕይወትህን አስታውስ፣ ሁልጊዜም ስለዚህ ትጋ፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህንና እርሱን መምሰል እንዳለብህ አስታውስ፤ እውነተኞች ከሆኑት ከእግዚአብሔር ልጆች ጋር አካሄድህን አስተካክል፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ መሆንህን አስታውስ፡፡ በውስጥህ ያለውንም ቅዱሱን የእግዚአብሔር መንፈስ አታሳዝን፤ ዘወትርም ቅዱስ የእግዚአብሔር ማደሪያ ሁን፡፡ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

የመስተፋቅር መዘዝ በአባ ገብረኪዳን የቅዳሴው ድንቅ ተዓምር ድግምት ስላክብን ተኝቶ መገኘት || መክሊት ቀባሪው አጋንንት | የመናፍቅ መንፈስ 😭💥🔥🚩 https://youtu.be/O7ZC3k7_aN4

photo content

◈ እግዚአብሔርን አምናለሁ አከብራለሁ የሚል አንድ ሰው ነበር ከእለታት በአንደኛው ቀን አንድ እንግዳ ወደቤቱ ይመጣል እሱም እንደ ክርስትናው ሥርዓት ጓዙን ተቀብሎ የሚበላውንና የሚጠጣውን የሚተኛበትንም አዘጋጅቶ ሲያብቃ እግሩን ያጥበው ጀመር፤ ይህ ደግ ሰው የእንግዳውን እግር እያጠበ "ዛሬ አንተን ወደ ቤቴ ያመጣልኝ እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይግባው" ይላል፤ እንግዳውም "እግዚርአብሔር ማነው?" ይለዋል በጥያቄው የደነገጠው እንግዳ ተቀባይ "ምን ማለትህ ነው እግዚአብሔርን አታውቀውምን?" ይለዋል "ኧረ በፍጹም ስሙንም ያለዛሬ ሰምቼ አላውቅም"ይላል እንግዳው፡፡ ◈ ለመሆኑ ስንት አመትህ ነው? ይላል የቤቱ ባለቤት፤ እንግዳውም (ስልሳ) ይላል የቤቱ ባለቤት በጣም በመደነቅ በመናደድም ጭምር የእንግዳውን እግር ማጠብ አቋርጦ "60 ዓመት እንዴት ሙሉ እግዚአብሔርን የማያውቅ ሰውማ እቤቴ አያድርም" ብሎ ያባርረዋል፤ የቤቱ ባለቤት እኩለ ለሊት ላይ ራእይ ያያል ልዑል እግዚአብሔር ተገልጾ "ዛሬ ውለህ አመሸህ?" ሲለው የቀኑን ውሎ ተናግሮ ሲያበቃ "60 ዓመት ሙሉ አንተን የማያውቅ እንግዳ በቤቴ ሊያድር ሲል እኔ ያንተ ባርያ አባርርኩት" አለ። ◈ እግዚአብሔርም ይህንን ስህተቱን ሊያርም ነበርና መምጣቱ "ወዳጄ ሆይ እኔ 60 ዓመት የታገስኩትን አንተ አንድ ሌሊት መታገስ አቃተህን?".....ብሎ መክሮት ተለየው። ብዙውን ጊዜ ሰው ከእግዚአብሔር ቀድሞ ፍርድ ለመስጠት ሲደክም ይታያል፤ እሱ እኛን በታገሰን ልክና መጠን ባይሆንም ምሳሌነቱን ወስደን ሰዎችን ይቅር ማለትና መታገስ አለብን። እስቲ እኛም ከዚህ ተምረን ለይቅርታ ለምህረት እራሳችንን እናዘጋጅ። ከሁሉም በላይ ደግሞ ፍረጃን እናቁም። በርቱ! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ጠንቋይ ቤት የሚሄደው ሲበዛ አያሳዝናችሁም | ከመዝሙር ይልቅ ዘፈን ሲወደድ | የዲያብሎስን ተንኮል ንቁበት | በሴት ዓይነጥላ ዕድላችን ሲወሰድ #ebs 🚩🔥💥😭 https://youtu.be/UEOLHjLhlSU?si=aV0LfgiS6Wh6Z1AE

«የምንለወጠው ምን ስናደርግ ነው?» ◈ በታመምህ ጊዜ ድካም ይሰማሃል፤ ብርታት ያንስሃል፤ ፊትህም ይገረጣል፤ የዕለት ተዕለት ሥራዎችህን በአግባቡ ማከናወን ይሳንሃል፤ በዚህ ጊዜም ሕመምህ ምን ያህል እንደ በረታ ሰዎች ያስተውላሉ፤ መታከም እንደሚገባህም ይነግሩሃል፤ ስለዚህ ወደ ሐኪም ትኼዳለህ ወደ ሐኪም የምትኼደው ግን ሐኪሙ ምን እንዲያደርግልህ ነው? አሁን ለሚሰሙህ ስሜቶች የሚሽሩ መድኃኒቶችን እንዲሰጥህ ነው፡፡ ኾኖም ይሰሙህ የነበሩ ስሜቶች ቢሻሉህም ሰውነትህ አሁንም እንደ ደከመ፣ ፊትህ እንደ ገረጣ ከቀረ፣ የዕለት ተዕለት ሥራዎችህንም በአግባቡ ማከናወን ከተሳነህ በተሰጠህ ሕክምና ደስተኛ ትኾናለህን? አትኾንም። ◈ “እውነታው ምንድን ነው?” ስንል ወደ ሐኪሙ የኼድከው የበሽታህን ምንጭ ለመታከም ሳይኾን የበሽታህን ምልክቶች ለማስታገሥ ስለኾነ ነው፤ በሌላ መልኩ ደግሞ የበሽታህ መንሥኤ እስካልታከመ ድረስ የበሽታህ ምልክቶች ለጊዜው ቢታገሡም ቅሉ ፈጽመው ሊወገዱ እንደ ማይችሉ ሐኪሙ በደንብ ያውቃል፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን፣ በወልድ ውሉድ፣ በመንፈስ ቅዱስም መንፈሳውያን የተባልን እኛም እግዚአብሔር መንፈሳዊ በሽታችንን እንዲያስወግድልን እንሻለን፤ እንደ እውነታው ግን ብዙዎቻችን ወደ እግዚአብሔር ቀርበን እንዲያስወግድልን የምንሻው ምልክቶቹን ነው፡፡ ለምሳሌ => ችግርን፣ ኀዘንን፣ ቀቢጸ ተስፋንና የመሳሰሉትን እንዲያርቅልን እንፈልጋለን። ◈ እግዚአብሔር ደግሞ ከዚህ በተቃራኒ የእነዚህ ምክንያት የኾነውንና ሥር የሰደደውን፣ ዋና ምክንያትም የኾነውን መንፈሳዊ በሽታችንን ሳይሽር እነዚህን ምልክቶች ሊያርቅልን አይፈልግም፤ ችግር የሚኾነውም ይህን ጊዜ ነው ምልክቶቹን እንዲያርቅልን ስንደክም ወደ ውሳጤያችን ገብቶ የችግሩን ምንጭ ሊያርቅልን የሚችለውን የእግዚአብሔርን ጸጋ (ኃይልን) አጥብቀን እንቃወማለንና፤ በውሳጤያችን የተሸሸገውን በሽታ ማስወገድ አንፈልግም፤ አመለካከታችን እንዲለወጥ አንፈቅድም፡፡ ◈ እውነተኛ ለውጥ የሚመጣውና አማን በአማን የምንታከመው ግን የልባችንን ውሳጤ ለእግዚአብሔር ስንከፍትለትና እርሱም በዚያ በመረቀዘው ቁስላችን ላይ ጽኑ መድኃኒት ሲያስርልን ነው፤ እንዲለወጡ የምንፈልጋቸው ምልክቶች በእርግጥም የሚለወጡት ይህ በልባችን ውስጥ የተደበቀው መንፈሳዊ በሽታችን ሲጠፋ ነው፡፡ "የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል" (ምሳ 1፥33) (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ብሮሽኤል አባድ፥ የዓመፃና የሞት መንፈስ ❗️ በማለዳ መያዝ ❗️ መምህር ግርማ ወንድሙ 2022 መምህር ተስፋዬ አበራ Pagumen Tube https://youtu.be/cVOh0ZIo3cA

የመንፈሱ የወንዝ ዳር ልጆች በማለዳ መያዝ ቁጥር 2 | በማለዳ ንቁ 2022 | በመምህር ግርማ ወንድሙ | መምህር ተስፋዬ አበራ | EOTC TV https://youtu.be/8TlC53rUCJg

የኩማኤል ርኩስ መንፈስ ጥፋት #በማለዳ_ንቁ_2022 #በማለዳ_መያዝ_ቁ.2 #መልክአ_ሳጥናኤል ትውልድ ገዳይ መናፍስት ማዋረሻ https://youtu.be/lUh4HRejSVY

በመንፈስ መቀ'ደስና መዳን እውነተኛ መዳን እንዴት ይገኛል 3ቱ የሰይጣን ሴራዎች || ብዙዎቻችን የማንቆርብበት ምክንያት #ebs #ethiopia 💥🔥🚩 https://youtu.be/y4QcTw6mw4E?si=crQCjO9n4_qgAAZG

photo content

◈ ሐምሌ ሰባት በዚች ቀን ሥሉስ ቅዱስ በአብርሃም ቤት የተገለጡበት ዕለት ነው! ◈ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በስም በአካል በግብር ሦስትነት በባሕርይ በሕልውናና በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ተገኙ፣ በዚህ ጊዜ ያልፋሉ አይባሉም መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና፡፡ ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት ‹‹ቅድስት ሥላሴ›› እንላቸዋለን፡፡ የሚጠላቸው (የማያምንባቸውን) አይጠሉም፡፡ የሚወዳቸውን ግን እጽፍ ድርብ ይወዱታል፣ በቤቱም መጥተው ያድራሉ፡፡ ◈ ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም፡፡ አባታችን ቅዱስ አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና በኬብሮን በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል፡፡ ◈ አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ ሥላሴን በድንኳናቸው አስተናገዱ፡፡ አብርሃም እግራቸውን አጠበ፡፡ በጀርባውም አዘላቸው፡፡ ምሳቸውንም አቀረበላቸው፡፡ እነርሱም እንደሚበሉ ሆኑለት፡፡ በዚያው ዕለትም የይስሃቅን መወለድ አበሠሩት፡፡ ◈ አብርሃም ከደግነቱና እንግዳ ከመውደዱ የተነሣ በተመሳቀለ ጎዳና ላይ ድንኳን ሠርቶ የወጣ የመረደውን፣ የመጣ የሄደውን ሁሉ እየተቀበለ እግዚአብሔርን እያገለገለ የሚኖር ጻድቅ ነበር፡፡ ለዚህም ነው አብርሃም በወይራ ግራር (በመምሬ) ዛፍ ሥር ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር አንድነቱን ሦስትነቱን የገለጠለት፡፡ (ዘፍ 18፡1-25፣ ሮሜ 4፡-3) ◈ ቀትር ሰዓት ላይ በድንኳኑ ደጅ ተቀምጦ እንግዳ ሲጠብቅ እግዚአብሔር ታየው ተነጋገረው፡፡ አንገቱን ቀና አድርጎ ዐይኑን አራምዶ በተመለከተ ጊዜ እነሆ ሦስት ሰዎች ከበላዩ ባለ ተራራ ላይ ቆመው አያቸው፣ ወደ እርሱም ሲወርዱ አይቶ ፈጥኖ ሄዶ ከሰግደላቸው በኋላ ‹‹አቤቱ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደሆነ ባሪያህን አትለፈኝ ብዬ እለምናለሁ፤ ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ እግራችሁን ታጠቡ…›› እያለ በትሕትና በመጋበዝ ወደ ድንኳኑ አስገብቶ በሚገባ ጋበዛቸው፡፡ ‹‹በፊትህስ ሞገ አግኝቼ›› ብሎ አንድነታቸውን፣ ‹‹ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ እግራችሁን ታጠቡ›› ብሎ የሦስትነታቸውን ምስጢር ገልጾአል፡፡ ◈ ያች ሥላሴ የገቡባት የአብርሃም ድንኳን የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡፡ ሥላሴ ወደ አብርሃም ድንኳን እንደገቡ ሁሉ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያምም አብ ለአጽንዖ፣ መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ፣ ወልድ በተለየ አካሉ ሥጋዋን ለመዋሐድ የማደራቸው ምሳሌ በመሆኑ አማናዊቷ የሥላሴ ማደሪያ የአብርሃም ድንኳን እመቤታችን ናት፡፡ (ሉቃ 1፡35) ◈ እግዚአብሔርም አብርሃምን የዛሬ ዓመት ልጅ እንደሚወልድ ነግሮት በዓመቱ ይስሐቅን ወልዷል፡፡ ሁለቱ ሰዎች ከአብርሃም ድንኳን ወጥተው ወደ ሰዶም ወደ ገሞራ ሄዱ፣ አብርሃምም ይሸኛቸው ዘንድ አብሯቸው ሄደ፡፡ የሄዱትም ሁለቱ ሰዎች አብና መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡ ነገር ግን አንዱ ወልድ በአብርሃም ቤት ቀርቷል ይኸውም ከቤተ አብርሃም ሰው እንደሚሆን ለማጠየቅ ነው፡፡ ◈ አብርሃምም ተመልሶ በእግዚአብሔር ፊት ቆመ፡፡ እግዚአብሔርም የሚሠራውን ሁሉ ከአብርሃም አይሠውርም ነበርና የሰዶምን የገሞራን ጥፋት ነገረው፡፡ አብርሃምም ይቅር እንዲላቸው አብዝቶ ለመነላቸው፡፡ ◈ ሥሉስ ቅዱስን በምግባር በሃይማኖት ሆነን እናገለግል ዘንድ የቅዱሳኑ ጸሎት ይርዳን! 🙏🏽 🙏🏽 🙏🏽 (ምንጭ #ስንክሳር_ዘወርኀ_ሐምሌ እና #ከገድላት_አንደበት) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube