ru
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Открыть в Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Больше
2 279
Подписчики
Нет данных24 часа
+47 дней
+2930 день
Архив постов
ጥያቄ 1፡ ከመላእክት መጋቤ ብሉይ ተብሎ የሚጠራው የቱ መልአክ ነው?
Anonymous voting

🛑ሰይፈ መለኮት ጸሎትን ከመቁጠሪያ ጋር እንዴት እንጠቀም ሰይፈ መለኮት ጸሎት መቁጠሪያ እና አጠቃቀሙ #ethiopia #orthodox #sibket 🙏🙄 https://youtu.be/nJAtrcOaZig

🛑የጸሎት አደራረግና የመናፍስት ዉጊያ አካሄዶች የመናፍስት ዉጊያ የጸሎት አደራረግ #ethiopia #orthodox #sibket || በማለዳ ንቁ 😰😭 https://youtu.be/BZZJVt_g11Y

🛑የጸሎት ቤት ስዕለ አድህኖ አቀማመጥ የጸሎት ቤት የጸሎት ቤት አዘገጃጀት #ethiopia #orthodox #sibket #በማለዳ_ንቁ_2023 🙏🙄 https://youtu.be/1mNC72EF6tA

"ለሰዎች የምትሰጠው ምንም ነገር ባይኖርህ.. ሞቅ ያለ ፈገግታ እና መልካም ቃልን ስጣቸው.. ፍቅርን ስጣቸው.. መልካምነትን ስጣቸው.. የማበረታቻ ቃልን ስጣቸው.. ልብህን ስጣቸው" [አቡነ ሽኖዳ]
"ለሰዎች የምትሰጠው ምንም ነገር ባይኖርህ.. ሞቅ ያለ ፈገግታ እና መልካም ቃልን ስጣቸው.. ፍቅርን ስጣቸው.. መልካምነትን ስጣቸው.. የማበረታቻ ቃልን ስጣቸው.. ልብህን ስጣቸው" [አቡነ ሽኖዳ] ሰዎችን በማሳዘን ፈንታ ሁሌም ይህንን ብናደርግ ኢየሱስ በእኛ እንዳለ ያኔ ይታወቃል.. #ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ! #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

🛑5ቱ የርኩሳን መናፍስትን አሳብ መቃወሚያ እና መከላከያ መንገዶች የቅጣት ስግደት የሕሊና ጸሎት የቅጣት መቁጠሪያ በርዕስ መቁረብ 🙏🙏🙄 https://youtu.be/jr39ZQbHdP8

🙏 የዛሬው የበረከት ሥራ ውሏችን ይሄን ይመስላል። ለሰጣችሁ በመሉ እግዚአብሔር አብዝቶ ጨምሮ ይስጣችሁ። በተለይም የመድኃኔዓለም የተለግራም ማህበራት በእውነት ተባረኩ። 🙏🙏🙏🙏
+2
🙏 የዛሬው የበረከት ሥራ ውሏችን ይሄን ይመስላል። ለሰጣችሁ በመሉ እግዚአብሔር አብዝቶ ጨምሮ ይስጣችሁ። በተለይም የመድኃኔዓለም የተለግራም ማህበራት በእውነት ተባረኩ። 🙏🙏🙏🙏

2.76 MB

ይሄው የእህታችን የሰብለ የበረከት ሥራ። ምርቃቱን ተቀበይ። እግዚአብሔር ለሁላችሁም አብዝቶ ይስጣችሁ። 🙏🙏

🙏 የመድኃኔዓለም የተለግራም ማህበር የበረከት ሥራ የእናታችንን የቤት ውስጥ ወጪና ለሎች ጉዳዮችን አሟልተናል። በዚህ ሥራ ለተሳተፋችሁ በሙሉ እግዚአብሔር ጨምሮ ጨምሮ ይስጣችሁ። ለሎቻችሁም እንዲሁ ተሳተፋ ብዙ የተቸገሩ ነገር ግን ወጥተው መለመን እና መጠየቅ የፈሩ ያለ አባት ቤትን፣ ልጆችን የሚያስተዳድሩ እናቶች እንዲሁም አባቶች አሉና እንርዳቸው። ስናያቸው የሞላቸው የሚመስሉ ነገር ግን ወደ ቤታቸው ስንጠጋ ብዙ ፈተናዎች እና ኑሮን ማሸነፍ የከበዳቸውን ቤቱ ይቁጠራቸው። እንረዳዳ 🙏🙏🙏 በዚህ በኩል አናግሩኝ @haile_gebriel_tube_bot

መዝሙረ ዳዊት 40 1፤ እግዚአብሔርን ቆይቼ ደጅ ጠናሁት፥ እርሱም ዘንበል አለልኝ ጩኽቴንም ሰማኝ። "ቆይቼ  ደጅ ጠናሁት" ማለት በትእግስት ብዙ ጠበክሁት ማለት ነው.. ስለዛ እግዚአብሔርን በትእግስት እንጠብቀው.. መልካሙን እግዚአብሔር ያድርግ እግዚአብሔር መልካም ነው

🛑የሚድንቅ ተሞክሮ! ክርስትና የመለወጥ ጉዞ እንጅ ጸድቆ የመጽናት ጉዞ አይደለም ተሞክሮ ክፍል 25 የብዙ ሰው ሕይወት ውስጥ ያለ እውነት ነው 😭😰🙏❤ https://youtu.be/-RvbAZTxT3s

+9
01 Memehir Girma' s message.mp373.26 MB

🛑[ክፍል 10] ከቤተሰብ የጣኦት አምልኮት ወጥታ ለቅዱስ ቁርባን የበቃች እናት ልዩ ገጠመኝ #በማለዳ_ንቁ_2023 | የአዳልሞቴና የውቃቢ መንፈስ ፈተና 🛑😱😱 https://youtu.be/PT5JOujnb1g

photo content
+1

የሚገርማችሁ ከ 10 ዓመት በኋላ ቦንብ ያፈነዳውን ሰውዬ እዛው ጻድቃኔ ማርም ታች ድልድዩ ስር ቀጭ ብሎ ሲለምን አገኘሁት። ሰላም አልኩትና "ትዝ ይልሃል ያኔ ቦንብ ያፈነዳህብኝ ነኝ" ስለው ቀና ብሎ በማፈር አየኝና "አዎ ንስሐ ገብቼበታለሁ" አለኝ። በጣም ተደሰትኩ። እመቤታችን ይቅር ያለችውን እኔስ ብለው ብዬ ጨብጬው ብር ሰጎጥ አደረኩለት። በነገራችን ላይ ለዚህ ሰው የጎጆ ቤቱ ባለቤት በራሱ ኪሳራ ስለፈረሰበት ተበሳጭቶ ለዚህ ምስኪን ሰው አምስት መቶ ብር ሰጥቶት ነው እነዚህን ቦምብ አፈንዳ ብሎ የላከው። ሰውዬውም እሺ ብሎ ሁለቱን ቦንብና ብር ተቀብሎ ፌውዙን ከቦንቦ ላይ እንደነቀለ እኔን ሲያገኘኝ ነው እግሬ ስር የጣለው። አጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ በኪነ ጥበባቸው፣ በተአምራታቸው፣ የጻድቃኔዋ ንግሥት፣ የአፄ ዘርአ ያዕቆብ እመቤት በምልጃዋ በጸሎቷ አዳኑኝ፡፡ ገዳሙም በዚህ በተፈጠረው ተአምራት ሁሌ በየወሩ በ 7 የሥላሴ ቀን ከዓመት እስከ ዓመት ለሱባኤተኛው ዳቤ ይዘክራሉ፡፡ ጻድቃኔ ማርያም ሄዳችሁ በሰባት የሥላሴ ቀን ዳቦ ንፍሮ ተዘክሯችሁ ከበላችሁ የሚዘከረው በዚህ ተአምር ነው። እኔምአጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ ከሞት አድነውኝ ዳግም የመኖር ዕድል ስለሰጡኝ በየወሩ እዘክራቸዋለሁ። የዓመት ሲሆኑ የጥር ሥላሴን ሦስት በሬ፣ የሐምሌ ሥላሴን ሦስት በሬ አርጄ በሰፊው እዘክራቸዋለሁ፡፡ እንግዲህ የአብረሃሙን ሥላሴ የምዘክርበት ምስጢር ይህ ነው፡፡ አጋዕዝተ ዓለም ሥላሴን አመስግኑልኝ፡፡ ምክንያቱም ከሞት ካዳኑኝ ዛሬ ድፍን ሃያ ዓመት ሞላኝ፡፡ #ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ! #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

◈ ህዳር 7 የዛሬ 20 ዓመት ጻድቃኔ ማርያም ከቦንብ የዳንኩበት ቀን 🙏 በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም ተወዳጆች ሆይ ቀኑ ወሩ ዓመቱ ዓመታቱ እንደ ዋዛ እንደ ፈጣን ባቡር እልም እያለ ይሄዳል ይነጉዳል፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች እየዳኑ ምስክርነታቸው ሰምቻለሁ አሰምቻለሁ፡፡ እስኪ እኔም የዛሬ 20 ዓመት አጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ ያደረጉልኝ፣ ከሞት የታደጉኙን እና ዳግም የመኖር ዕድል የሰጡኝን በእለተ ቀናቸው ልናገር፡፡ መቼን ጻድቃኔ ማርያምን የማያውቅ ኦርቶዶክሳዊ አለ ብዬ አላምንም፡፡ የተፈቀደላቸው የተቀደሰ ደጇን ረግጠው በሥጋም በነፍስም የተጠቀሙ ሚሊዮኖች ናቸው፡፡ ከእነዛ ውስጥ አንዱ እኔ ነኝ፡፡ እዚህ ለመድረሴ መሠረቴ ጻድቃኔ ማርያም ነች፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው ጻድኔ ማርያም አንድ ዓመት ተቀምጬ ሁለተኛ ዓመቴን እንዳገባደድኩ ልክ የዛሬዋ ቀን ህዳር 7 በ1996 ዓ.ም በርዕሱ የገለጽኩላችሁ ነገር ተፈጠረ፡፡ ጻደቃኔ ማርያም ገደም ውስጥ በተለይም ከኪዳን ማድረሻው ዋሻ አናቱ ላይ አንድ ትልቅ እና ሰፊ ጎጆ ቤት ነበር፡፡ በዚህች ጎጆ ቤት ከአዲስ አበባ እና ከለተያዩ ቦታዎች የሚመጡ የቦታው አፈር አይንካኝ፣ ደረቅ የሲሚንቶ አዳራሽ ውስጥ አታስተኙኝ የሚሉ የቀበጡ፣ ከመንፈሳዊ ሕይወት የወጡ፣ በገዳም ስለሚኖረው የሥጋ ፈተና እውቀት ያልጨበጡ፣ ሐብታም ጠብታም የሚጫወቱ መንፈሳዊ ቀለብ ሳይሆን ገንዘብ ያላቸው ሰዎች እየመጡ የደጇን እምነት እና ወለሉ ሲሚንቶ ሆኖ የሚቀዘቅዘውን አዳራሽ ሽሽት በዋሻው አናት ላይ በተሠራው ንብረትነቱ የአንድ ሰው ጎጆ ቤት ውስጥ በተለይ ለጾመ ለፍለሰታ ገንዘብ እየከፈሉ ያድራሉ፡፡ እኛ ደግሞ የሲሚንቶውን ቅዝቃዜ ችለን፣ አንድ ፎጣ ለብሰን እመቤታችንን ሙጥኝ ብለን ደጅ እንጸናለን፡፡ እንደ ነገርኳችሁ ጎጆ ቤቱ ከኪዳን ማድረሻው አናት ላይ ስላለ ከታች ሌሊት ሰዓታቱ ይቆማል፣ ጠዋት ኪዳን ይደረሳል፤ ከላይ ደግሞ ባለ ገንዘቦቹ ጎጆ ቤት የተከራዩት ኪዳን አያደርሱ ወሬ ሲለውሱ፣ ያለ ሰዓቱ እንደ ልባቸው ያገኙትን ሲያግበሰብሱ ይውላሉ፡፡ ይህ ብቻ አይደለም ቀንም ማታው ጨዋታ ሁካታ ያበዛሉ፡፡ ቦታው ደግሞ የአርምሞ፣ የጥሞና፣ የሱባኤ እና የጸሎት ቦታ ስለሆነ በቦታው ላይ ያሉት የተሰወሩት ቅዱሳን አዘኑ፣ እመቤታችንም አዘነች፡፡ በተለይ የተሰውሩት ቅዱሳን ለእመቤታችን መጸለይ አልቻልንም ጫጫታው በዛብን ብለው አመለከቱ፡፡ እመቤታችን ወትሮም ቅይም ብላቸው ስለነበር በሕልም እና በራዕይ በገዳሙ ላሉት እናቶች እና አባቶች ‹‹ቦታዬ የሳቅ የስላቅ፣ የጨዋታ የሆካታ ሆነ፡፡ ቅዱሳን ልጆቼም እኔም አዘንኩ፣ ከቤተ መቅደሴ አናት ላይ ሆነው ረበሹኝ›› ብላ መልእክት ተናገረች፡፡ ይህንን የእመቤታችንን መልእክት የሰሙት አባቶች እና እናቶች ለጎጆ ቤቱ ባለቤት ነገሩት አልሰማም፡፡ ‹‹ጎጆ ቤቱ ዋሻው አናት ላይ ስላለ የቤቱን ግምት እንስጥህ እና ይፍረስ ገዳሙም ቅዱሳኑም እየታወኩ ነው›› ተባለ፡፡ ሰውዬው እንቢኝ አሻፈረኝ አለ፡፡ በዚህ ጊዜ ገዳሙ ሰውየውን ፍርድ ቤት ከሰሰው፡፡ ፍርድ ቤቱም ጎጆ ቤቱ የተሠራው ገዳም ውስጥ ነው። ይባስ ብሎ የዋሻው አናት ላይ ነውና ጎጆ ቤትህ ይፍረስ አሥር ሺ ብር ካሳህን ጉረስ›› ብሎ በባለ ሙያ አስገምቶ ወሰነ፡፡ ሰውየውም እሺ ብሎ ተስማማ፡፡ ከፍርድ ቤት ከተመለሰ በኋላ ገዳሙን ‹‹አሥር ሺ ብር የጎጆ ቤቱ ካሳ ያንሰኛል አሥራ አራት ሺ ብር ካልከፈላችሁኝ አይፈርስም›› አለ፡፡ አስቡት የዛሬ 20 ዓመት አሥር ሺ ብር ያለውን የመግዛት ጉልበት! ጉዳዩ በድጋሚ ፍርድ ቤት ቀረበ፡፡ የሰላ ድንጋይ ፍርድ ቤትም ‹‹ህዳር 6 የማያፈርስ ከሆነ ህዳር 7 በራሱ ኪሳራ እናንተ አፍርሱት›› ብሎ ወሰነ፡፡ ይህንን ዜና ህዳር 6 ማታ ሰላም እለኪ አዳራሽ የገዳሙ አበ ምኔት መጥተው ነገሩን፡፡ ‹‹ዛሬ ህዳር 6 ስላላፈረሰ ነገ ጠዋት እናንተ ተባብራችሁ አፍርሱት›› ብለው ወጥተው ሄዱ፡፡ እኛም እመቤታችን አሥር ሺ ብር ካሳ ከፍላው እንዴት እንቢ ይላል፣ በዛ ላይ ገዳም ውስጥ፣ ይባስ ብሎ ዋሻዋ አናት ላይ ሠርቶ ብለን፣ በጠዋት ጎጆ ቤቷን ለማፍረስ ከሱባኤተኛው ጋር ቀጠሮ ይዘን ተኛን፡፡ ጠዋት እኔ አንድ ችግር ገጠኝ፡፡ ከማስታምማቸው ልጆች ውስጥ አንዱ ልብሱ ላይ ሽንቱን ሸንቶ ተጸዳድቶ አደረ፡፡ እሱን ሰውነቱን ላጥበው፣ ልብሱንም ልቀይርለት ወደ ወንዝ ይዤው ሄድኩኝ፡፡ አጣጥቤው ተመለስኩ እና እስኪ በረከቱ ይድረሰኝ ብዬ ወደ ጎጆዋ ስሄድ ሱባኤተኛው ጎጆ ቤቷን ከላይ ከታች እንደ ንብ ወረዋት በሞራል ያፈርሳሉ፡፡ ጎጆዋ ጋር እንደ ተጠጋሁ የቀኝ ተረከዜን የሆነ ነገር ሲመታኝ ታወቀኝ፡፡ ዞር ብዬ ስመለከት ቦምብ ነው፡፡ ችስስ … እያለ ተረከዜ ስር ይዞራል፡፡ በጣም ደነገጥቱ ወዴት እንደምሄድ ግራ ገባኝ፡፡ ቦምቡም ጊዜ አልሰጠኝም፡፡ እልም ብሎ ፈነዳ! ቦምቡ ከፈነዳ። በኃላ ምን እንደተፈጠረ፣ ምን እንደሆነ አላውቅም፡፡ ብቻ ስነቃ እኔ አዋራ ጠጥቼ፣ መሬቱ ላይ በጀርባዬ ተኝቼ፣ የማስታምመው ልጅ ደግሞ እኔ ላይ ወድቋል፣ ጆሮዬም በቦንቡ ፍንዳታ ተደናቁራል፡፡ አዋራው ይጨሳል፣ ጎጆ ቤቱን የሚያፈርሱት ሱባኤተኞች ጩኸታው ይሰማል፡፡ ደነገጥኩ ሕልምም ሰመለኝ ግን እውነታ ነው፡፡ የማስታምመውን ልጅ ከላዬ ላይ አንስቴ ምን እንደተፈጠረ ግራ ቀኝ ስቃኝ አንድ ሰው ከፊት ለፊቴ ወድቋል። ደሙ እንደ ጅረት ወንዝ ይፈሳል፡፡ ‹‹ኸረ ባካችሁ ሰው ወድቋል ሰው ሞቷል እያልኩ›› ስጮህ ሱባኤተኛው ግር ብሎ መጣ፡፡ በእውነትም የወደቀው ሰው በጀርባው ተኝቶ ደሙ በሥሩ ይፈሳል፡፡ ሰውየውን ለማንሳት እና ወደ ሕክምና ተቋል ለመውስድ ሰው ሲሯሯጥ ስማቸው ለጊዜው ይቅርና እንድ እማሆ ጠጋ በለው ‹‹እናንተ ቦምቡን ያፈነዳው ይሄው ሰውዬ ነው፣ ከቦንቡ ላይ የሆነ ነገር ነቅሎ ልጁ ላይ /እኔ ላይ/ ጥሎ እግሩ ሥር ሲወረውረው አይቻለሁ አታንሱት ፈትሹት›› አሉ፡፡ አንድ ወጣት ልጅ የወደቀውን ሰውዬ ከጨርቅ የተሰፋ ቦርሳውን ሲፈትሽ አንድ ያልፈነዳ ቦምብ አገኘ፡፡ ጉድ ተባለ፡፡ ወዲያው ፓሊስ መጣ የወደቀውን ሰውዬ አገላብጠው ሲያዩት ከጀርባው እስከ መቀመጫው ለሁለት ተሰንጥቋል፡፡ ለካ እኔ ላይ የወረወረው ቦንብ ሲፈነዳ እሱን ነው የመታው፡፡ ፖሊሱ ሲናገር እንደሰማሁት ቦንቡ እጅግ ገዳይ እና ብዙ ሜትሮችን የሚያካልልና ኤፍ ዋን ግሪናዴ/F1 grenade/ የሚባል ቦንብ ነው፡፡ እኔም የማስታምመው ልጅ ምንም አልሆንም። ፍንጣሪውም አልነካንም። የማስታምመው ልጅ ትንሽ ድንጋይ እግሩን በስቶታል፡፡ ወዳጆቼ እስከ ዛሬ ድረስ እንቆቅልሽ የሚሆንብኝ እና ሳስበው ድክም የሚለኝ ቦንቡ ሲፈነዳ ቆሜ ነበር። እራሴን ያገኘሁት ግን ቦንቡ ከፈነዳበት ቦታ ርቄ በጀርባዬ ተኝቼ ነው፡፡ በአየር ላይ ልሂድ፣ ልገልበጥ፣ ልንሳፈፍ አላውቅም፡፡ ይህ የሆነው ህዳር 7 በ1996 ዓ.ም የአጋዕዝተ ዓለም የሥላሴ ቀን የዛሬ ሃያ ዓመት ነው፡፡ ልክ ይሄ ነገር ሊፈጠር አንድ ቀን ሲቀረው አንዲት ልጅ ሱባኤ ግብታ ጨርሳ ልትወጣ ስትል እመቤታችን በሕልሟ ‹‹ዛሬ አንድ ተአምር በገዳሜ ላይ ታያለሽ ዛሬን ውለሽ ነገ ትሄጃለሽ ብላኝ ነበር ለካ ይሄንን ልታሳየኝ ነው›› ብላ ህዳር 7 ቀን እዛው ገዳም ምስክርነቷን ሰጥታለች፡፡