ru
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Открыть в Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Больше
2 271
Подписчики
+224 часа
+97 дней
+2130 день
Архив постов
ጥር ፳፯ /27/ በዚችም ዕለት የአዳም ልጅ ኄኖክን መላእክት ይዘው አሳረጉት። ይኸውም በመባርቅትና በነፋሳት ላይ ተጭኖ በመብረር ወደ ሰማይ ወስደው ከረቂቃን መላእክት ጋር አኖሩት የእግዚአብሔርም ት
ጥር ፳፯ /27/ በዚችም ዕለት የአዳም ልጅ ኄኖክን መላእክት ይዘው አሳረጉት። ይኸውም በመባርቅትና በነፋሳት ላይ ተጭኖ በመብረር ወደ ሰማይ ወስደው ከረቂቃን መላእክት ጋር አኖሩት የእግዚአብሔርም ትእዛዝ ጸሐፊ ተባለ። በደብር ቅዱስ ለነበሩ ለኃጢአት ለሚተጉ ለሴት ልጆች ይዘልፋቸው ዘንድ ቃል እንደጠራውና እንዳሳየው ተናገረ። በእሳት ቅጽርም የተሠራ በክብር ከሁሉ የሚበልጥ በውስጡም ከፍ ያለ የእግዚአብሔርን ዙፋን አየሁ መልኩም እንደ ውርጭ ነው አጎበሩም እንደሚያበራ ፀሐይ ነው። ከዙፋኑም በታች የኪሩቤል ድምፅ ይሰማል። በሰማይ ገጽ ስለሚመላለሱ ብርሃናት እንዲህ አለ አንዱም አንዱ በየወገናቸው በሠለጠኑበትና በተሠየሙበት ጸንተው ይኖራሉ ስለ ነፋሳትም መውጫዎች እንዲህ ብሎ ተናገረ ሦስቱ በሰማይ ገጽ ሦስቱ በምድር ገጽ ሦስቱ በቀኝ ሦስቱ በግራ ናቸው። ስለ አዳምም እንዲህ አለ እነሆ በሬ ከምድር ወጣ ፀዓዳም ሆነ ስለ ሔዋንም ደግሞ ሴት እምቦሳ ከርሱ ወጣች አለ። ስለ ምኵራብም ያንን አሮጌ ቤት እስከሚአሳንሰው ድረስ አየሁ አለ ምሰሶዎቹንም ከውስጡ አወጣ። ስለ ቤተክርስቲያንም ጌታ አዲስ የበጎች ቤት አምጥቶ እስቲሠራ ድረስ አየሁ ከቀድሞውም ቤት የበለጠ ነው በጎችም ሁሉ በውስጧ ይሠማራሉ አለ ። ስለ ምእመናንም የእሊህም በጎች ፀጕራቸው ንጹሕ ነጭ ነው የተበተኑትም ከአራዊት ጋራ ይሠማራሉ ሁሉም በአንድነት ተሰብስበው ገራሞች ሆነዋልና። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር

ቀሲስ ሄኖክ በአገልግሎት የገጠማቸውን አሳዛኝ ድርጊት እንዲህ ይናገራሉ!! በፂሜ ይቀኑብኛል ቀሲስ ሄኖክ!! ገንዘብና ትዳር ይኼንን ተጠንቀቁ!! #adonay https://youtu.be/DAEYtm5paOA

3ቱ አጋንንትና መናፍስት የሚጋለጥባቸውና የሚወጣባቸው መንገዶች!! በመቁጠሪያ በመፈተሽ አጋንንትን እንዴት መለየት ይቻላል? ከዓቢይ ጾም በፍት ይኼንን አድርጉ! https://youtu.be/gxMVZsYrUuA

በመተት የተዘጋን ዕድልና በረከት ለማስከፈት የሚጸለይ 7 የመዝሙረ ዳዊት ክፍሎች! https://youtu.be/hEqj7oVgLgE?si=Bi70avIM8F-Al1fy

ባልና ምስት አብራችሁ ጸልዩ የምንለው በዚህ ምክንያት ነው ውዶች! https://youtu.be/HY8hMu20yCI?si=t3x5HaGkyF5V2Tgn

ሰሞኑን የገጠመኝ ያልተለመደና አሳዛኙ ገጠመኝ ይጠቅማችኋልና አዳምጡኝ!! አጋዥ ወይም ሰራተኛ ስትቀጥሩ ይኼንን በደንብ አስተውሉ!! የጸሎት ቤት ወሳኝ ጥቅሞች! https://youtu.be/58Cf6e2SYuU

ከዚህ ቪዲዮ በኋላ ሕልማችሁንና ራዕያችሁን ለማንም አትናገሩም አስተውሉ!! ተንቀሳቃሽ ጣኦቶች በጴንጤዎች አለም ወገን እንንቃ!! ይኼንን የቅዱስ ገብርኤልን ተዓምር ተመልከቱ! https://youtu.be/rQo0Dm5Lvus?si=hcEsA8y228RE3_qy

"ይህችን ቤተክርስቲያን ኑ አብረን እንጨርስ የቻላችሁትን ያህል በማገዝ። ይኼ በዲላ ጌደኦ ዞን የሚገኘው የቅዱስ ራጉኤልና የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም ቤተክርስቲያን ነው። በዚህ አከባቢ ብዙዎቹ ፕሮተስታንቶች ያሉበት አከባቢ ነውና ቢያንስ በዚህ የበረከት ሥራ እንሳተፍ ውድ ቤተሰቦቼ። ለበለጠ መረጃ በዚህ ስልክ ደውላችሁ የቤተክርስቲያኗን አስተዳዳሪ በቀጥታ በዚህ ስልክ ማነጋገር ትችላላችሁ (0916508839) የንግድ ባንክ አካውንታቸው፥ 10003819096882 ከቻላችሁ ከላካችሁ በኋላ ርስቱን ላኩልኝ ከክርስትና ስማችሁ ጋር። መልካም ቀን ይሁንላችሁ። ቢያንስ አሁን 1000 ብሎኬት ይፈልጋሉ ይኼንን ተባብረን እንስራው ቤተሰቦቼ። የአንዱ ብሎኬት ዋጋ 40 ብር ነው ብለውኛል።

photo content

አስተርዮ ማርያም (እንኳን አደረሳችሁ!) በዘመነ አስተርዮ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ የሆነበትና የአምላካችን አንድነትና ሦስትነት የተገለጠበት ብቻም ሳይሆን በጥር ፳፩ የከበረች እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍት ቀን በመሆኑ “አስተርዮ ማርያም” በማለት በዓልን አናደርጋለን፡፡ የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር ላይ ፷፬ ዓመታትን ከኖረች በኋላ መንፈስ ቅዱስ ባስገነዘባት መሠረት በክብር ዐርፋለች፡፡ የዚህን ዓለም መከራና ሥቃይ ለሰዎች ድኅነት የተቀበለችው ክብርት እናታችን በሥጋ ብትሞትም እንደ ልጇ ደግሞ በትንሣኤዋ ተነሥታለች፤ ይህም የሆነው በተቀደሰች ዕለት ነሐሴ ፲፮ ነው፡፡ እመ ብርሃን ከእናትና ከአባቷ ጋር ሦስት ዓመት፣ በቤተ መቅደስ ፲፪ ዓመት፣ ከተወዳጁ ልጅዋ ጋር ፴፫ ዓመት ከሦስት ወር፣ ከጌታችን ዕርገት በኋላ ከወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ጋር ፲፭ ዓመት፣ በድምሩ ፷፬ ዓመት በዚህ በኃላፊው ዓለም ኖራ ጥር ፳፩ ቀን በ፵፱ ዓመተ ምሕረት በክብር ዐርፋለች፡፡ ክርስቲያኖች በሙሉ ይህንን በዓል ልናከብር ይገባልና ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓትን ሠርታልናለች፡፡ “አስተርዮ ማርያም” በሕዝበ ክርስቲያን ዘንድ የሚከበር በዓል በመሆኑ በሀገራችን ኢትዮጵያ እና በመላው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ማኅበረሰብ ዘንድ በድምቀት ይከበራል፡፡ በዓሉን የምናከብረውም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከዚህ ዓለም ድካም ማረፍ በማዘከር ብቻ ሳይሆን አማላጅነቷና ተረዳኢነቷን በማሰብና ተስፋ በማድረግ ነው፡፡ ስለዚህም እመ ብዙኃን እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዐሥራት ሀገሯን ኢትዮጵያን እንድታስባት፣ ለእኛም ለሕዝቦቿ ሰላምን፣ ፍቅርንና አንድነትን ታሰጠን እንዲሁም ለነፍሳችን ድኅነትን ትለምልን ዘንድ ዕረፍቷን መዘከር ይገባል፡፡ የአምላካችን እግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ አሜን!!! #ማህበረ_ቅዱሳን #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@walkinaddistv

እንዳይጸልይ እንዳይማር በመቃብር አፈር አፈዘዝነው አደነዘዝነው!! https://youtu.be/CbGG_yDibXA?si=fCUiSwkCDxC0u-P3

ቄስም ዲጄም የሆኑት አባት ይኼንን ጉድ ተመልከቱና ፍረዱ!! አራስ ልጇን በመተት ልታጣ የነበረች እናት የገጠማትና ያሳለፈችው አሳዛኝ ታርክ!! #መላዕክት #ንቁ https://youtu.be/BsAiOgKSSA0?si=VYlhMlJIAusMoGWv

ጥር ፲፱ /19/ በዚች ዕለት የከበሩ የአባ ዝሑራ የአባ ባሱራ የእናታቸውም የኔራ ሥጋቸው ተገኘ። እሊህ የከበሩ ተጋዳዮችም ጣዖት በሚመለክበት ዘመን ሳብሳ ከሚባል አገር በሰማዕትነት ሞቱ ሥጋዎቻቸውም
ጥር ፲፱ /19/ በዚች ዕለት የከበሩ የአባ ዝሑራ የአባ ባሱራ የእናታቸውም የኔራ ሥጋቸው ተገኘ። እሊህ የከበሩ ተጋዳዮችም ጣዖት በሚመለክበት ዘመን ሳብሳ ከሚባል አገር በሰማዕትነት ሞቱ ሥጋዎቻቸውም በሳብሳ አገር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚኖሩ ሆኑ ከንጹሐን ሰማዕታትም ዘመን ከ947 ዓመት በኋላ የአፍርንጊ ሠራዊት ግብጽን ከበቧት የድምያጥንም ከተማ ወስደው በዚያ ነገሡ ከርሷ ጋርም በዙሪያዋ ያሉ ታላላቅ ከተሞችን ያዙ። የኮሞል ንጉሥም ይህም የግብጽ ንጉሥ ነው አፍርንጊያውያንንም ይወጋቸው ዘንድ ከግብጽ ሀገር ሁሉ ብዙ ሠራዊትን ሰበሰበ ሠራዊቱም ሲጓዙ ብዙዎች አብያተ ክርስቲያናትን አፈረሱ ከፈረሱትም ውስጥ አንዲቷ የእሊህ ቅዱሳን ሰማዕታት ሥጋቸው በውስጧ ያለባት ናት ። ከሠራዊቱም አንዱ የቅዱሳን ሰማዕታት ሥጋ ያለበትን ሣጥን ወሰደ በውስጡ የሚደሰትበትን የዚህን ዓለም ገንዘብ እንደሚያገኝ አስቦ በከፈተው ጊዜ ከዕንቊ የከበረ የቅዱሳኑን ሥጋቸውን አገኘ ክብራቸውን ግን አላወቀም ከቤተ ክርስቲያኑ ግድግዳ ላይ ሥጋቸውን በትኖ ሣጥኑን ወስዶ ሸጠው። የቅዱሳኑን ሥጋቸውን ያ ሰው በበተናቸው ጊዜ የአንድ ቄስ ሚስት የሆነውን ትመለከት ነበር እስላሞችን ስለፈራች በመጎናጸፊያ ጠቅልላ በአንድ ስፍራ አኖረቻቸው። በዚያም ለ20ዓመት ቆዪ። እርሷም ከጊዜ ብዛት እረሳቻቸው። እግዚአብሔርም ይገልጣቸው ዘንድ በወደደ ጊዜ በዚያች ሴት ፊት ሌሎች ሰዎች አስታወሷቸው እርሷም በዚያን ጊዜ አስታወሰቻቸው ለካህናቱና ለምእመናኑ ነግራ ቦታቸውን አሳየቻቸው። ካህናቱም ገብተው ሥጋቸውን አነሡ ያማረች ሣጥንንም ሠርተው በውስጧ በክብር አኖሩዋቸው። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር

«ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የገዳማት መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ። ብፁዕነታቸው በሀገር ውስጥ እና በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳ
«ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የገዳማት መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ። ብፁዕነታቸው በሀገር ውስጥ እና በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳማት ሊቀ ጳጳስ በመሆን ሰፊ አገልግሎት አበርክተዋል።»

መምህር ተስፋዬ የሚፈራቸውና ሁላችንም ክርስቲያኖች መጠንቀቅ የሚገቡን 3 ነገሮች!! ግርማ ሞገሳችንና ውቤታችን በአጋንንት ሲቀማ ይኼንን ምልክት ታያላችሁ!! https://youtu.be/1CbGmnKKvvY?si=s9wO4XcqILsAvnzZ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ - Статистика и аналитика Telegram-канала @hailegebriel2021