ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 406 подписчиков, занимая 5 570 место в категории Религия и духовность и 2 189 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 406 подписчиков.

Согласно последним данным от 12 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 76, а за последние 24 часа — 7, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.12%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.38% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 871 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 446 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 23.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 13 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 406
Подписчики
+724 часа
+347 дней
+7630 день
Архив постов
ልዩ ሳምንታዊ የጸሎትና የትምህርት ጕባኤ፡፡ የመሐረነ አብ ጸሎት በዐቢይ ጾም ባካህናት ማዕጠንት ጭምር ይካሄዳል፡፡ ዘወትር ዐርብ ከ11፡45-2፡00ሰዐት፡፡ ሲሳያ ለነፍስ ቃለ እግዚአብሔር፡፡

ልዩ ሳምንታዊ የጸሎትና የትምህርት ጕባኤ፡፡ የመሐረነ አብ ጸሎት በዐቢይ ጾም ባካህናት ማዕጠንት ጭምር ይካሄዳል፡፡ ዘወትር ዐርብ ከ11፡45-2፡00ሰዐት፡፡ ሲሳያ ለነፍስ ቃለ እግዚአብሔር፡፡

ወተቀበልዎ መላእክት በስብሐት ወበማኅሌት፤ ወአብዕዎ ኢየሩሳሌም ሰማያዊተ አብዕዎ ገብረ ሕይወት፡፡ እንኳን #ለአቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ_በዓለ_ዕረፍት_በሰላምና_በጤና_አደረሳችሁ፡፡ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (አቦ፥ አቡዬ)፤ * እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ብርሃነ ዓለም የኾኑ፤ * እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ክብርን የተሞሉ፤ * ኰከበ ገዳም፥ መናኔ ዓለም፥ ምድራዊ መልአክ፤ * ስማቸውን ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ያወጣላቸው፤ * በአክናፈ መባርቅት ተጭነው የሚጓዙ፤ * 60 አናብስትና 60አናብርት ይታዘዙላቸው የነበሩ፤ የእግራቸው ትቢያ ለአራዊቶቹ ምግብ የኾነላቸው፤ * ለብዙ አእላፍ ቅዱሳን ወላዴ የኾኑና በረከትን የሰጡ ታላቅ አባት (ለአብነትም፤ ለቅዱስ ላሊበላ፥ ለአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ፥ ለአባ አንበስ ዘደብረ ሐዘሎ፥ ለአባ ብንያም ዘግብፅ) ፠፠፠ #ምድረ_ከብድ_፤ /ዝ_ምድር_ክቡድ_ውእቱ_/ ( ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ለመጀመሪያ ጊዜ ያረፉባት ቦታ ናት ቀጥሎ ወደ ደብር ቅዱስ #ዝቋላ (#ዝ_ቆላ) ለጸሎት ሂደው ለሃገራችን ኢትዮጵያና ለዓለማችን ምሕረትና በረከትን ከአምላካችን ለ100 ዓመታት በባሕር ውስጥ ሆነው ለምነዋል፤ ወደ ምድረ ከብድ ተመልሰው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል፤ ቊራም በሰይጣን ተመስሎ መጥቶ ዓይናቸውም ቢያጠፋውም ከ7 ሱባዔያት በኋላ ሊቀ መላእክት ሚካኤልና ገብርኤል ዓይናቸውን መልሰውላቸዋል፡፡ ወደ ዝቋላ በመመለስም አጋንንትም ከምድረ ዝቋላ አጥፍተዋል፤ ተመልሰው ወደ ምድረ ከብድ በነበሩበት ጊዜ ታላላቆቹና በአንበሳ ዘባን ላይ የሚሄዱት #አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ ፣ #አባ_አንበስ_ዘደብረ_ሐዘሎ_አፋር)፣ #አባ_ብንያም ዘግብፅ ከአባታችን ቡራኬ ለመቀበል መጡ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ተሰውረው ነበርና፤ የአቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ አናብስት የ3ቱን አባቶች አናብስት በሉባቸው፤ በ7ኛው ቀን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ተገልጠው የኾነውን ነገር በማየት የተበሉትን አናብስት እንዲመልሱ የራሳቸውን አናብስት አዘዟቸው መልሰውም እንደነበሩ በተዓምራት አስነስተው ሰጧቸው፤ በደመና ጠቅሰው ቅዱስ ፋኑኤል 3ት ሰማያዊ ኅብስትና 3ት ጽዋዕ ይዞ ለእንግዶቻቸው ይዘው ሠረገላ በሚባለው ዋሻ አመጡላቸውና ሰጥተው ሸኟቸው፤ እነዚህን ቅዱሳን በሸኙ በ7ኛው ቀን ወደ ተለያዩ ሃገራት ሄደው አስተምረዋል፤ በግብፅ 300ዓመታት፥ በኢትዮጵያ ምድር ላይ 262ዓመታት (በዋነኛነት በምድረ ከብድና በዝቋላ ቢኖሩም ሌሎችም የመሠረቷቸውና የኖሩባቸው ገዳማት አሉ፤ ለአብነትም ደቡብ ወሎ የሚገኘውን ገዘዛ አቦን መጥቀስ ይቻላል) ከኖሩ በኋላ በንጉሥ ሕዝብናኝ(እንድርያስ) ዘመነ መንግሥት፤ መጋቢት 5 ቀን ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ብዙ ቃል ኪዳንን ጌታችን ሰጣቸው፥ 12 አክሊላትንም አቀዳጃቸው፤ የነበሩባትም ምድረ ከብድ ገዳም ራደች፥ ተንቀጠቀጠች፥ በብርሃንም ተጥለቀለች፤ ዝቅ እያለችም መንሸራተት ጀመረች፤ ጌታችንም አንቺ መሬት ሆይ ጽኚ ይህንን ኹሉ ስለቻልሽ ምድር ክቡድ /ኋላ ምድረ ከባድ/ ትብለሽ ተጠሪ አላት የጻድቁም ነፍስ ከሥጋቸው ከሌሊቱ 6 ሰዓት ተለየች፡፡ ይህችውም ምድረ ከብድ ጻድቁ የኖሩባትና የቀደሱባት፥ የመሠረቷትና ያነፅዋት፣ ሠራዊተ መላአክት የከተሙባት፣ ታላላቅ አበው መጥተው በረከት ከአባታችን የተቀበሉባት፣ አርምሞና ጸጥታ የማይለያት፤ አጸዷና ቅጥሯ ልቡናን የሚመስጥ፤ ከአ.አ 125 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ናት፡፡ አምላከ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት፥ በረከትን ይክፈለን፡፡ (ሥርዐተ ማኅሌቱን የኢንተርኔት አቅርቦት በሌለባቸው ቦታዎች አድርሱልን፤ በተለይም ወደ ምድረ ከብድ፥ ዝቋላና ሌሎች የአባታችን ክብረ በዓል በሚከበርባቸው አድባራትና ገዳማት ያላችሁ አድርሱልን፡፡) /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

ኦ እግዚኦ መሐሮሙ (አዕርፍ) ለነፍሰ አግብርቲከ ወአእማቲከ እለ አዕረፉ አመ አሚሩ ለወርኃ መጋቢት በሃገረ ኢትዮጵያ በአድያሚሃ ለደብረ ዘይት፡፡ ‹‹የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ አየሁ፡፡›› /ትንቢተ ኤርሚያስ 3÷7/ ‹‹#ሞት_ትልቅ_መምህር_ነው_የሚያስተውል_ካለ_!!!_፡፡››

ቅድስት፤ ሁለተኛው የዐቢይ ጾም ሳምንት ሁለተኛው ሳምንት ቅድስት ይባላል፡፡ ‹‹ሰንበትየ ቅድስት›› የሚልና ይህን የመሰለ የሰንበትን ቅድስና የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡ በተጨማሪ ቅድስት የተባለበት ምክንያት ለ40 ቀን ጌታችን ጾም የጀመረበት ሳምንት ስለኾነም፤ ቅድስት ጾሙን ለማዘከር ቅድስት ተብሏል፡፡ ‹‹የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ፡፡›› ዘዳ 20፥8 ይህን ቃል እግዚአብሔር በሊቀ ነቢያት ሙሴ ላይ አድሮ ተናግሮታል፡፡ ‹‹ዕረፍባት›› ያለው እግዚአብሔር የፍጥረቱን አቅም ስለሚያውቅ ነው፡፡ ስናከብር ለነፍስ ዕረፍትና ፍስሐን፤ ለሥጋ በረከት ሊያሰጡ የሚችሉ ሃይማኖታዊ ተግባራትን በመፈጸም የሚከበር ነው፡፡ በቤተክርስቲያን በመሰባሰብ ቃለ እግዚአብሔርን በመስማት /በመማር/፣ ንሰሐ ገብቶ ቅዱስ ቁርባን በመቀበል፣ የተጣላ በማስታረቅ፣ ያዘነ የተከዘ በማረጋጋት በማጽናናት የታሰረን በመጠየቅ፣ በችግር የወደቁትን በመጎብኘት በአጠቃላይ በማቴ 25፥35-37 ላይ የተጠቀሱትን ምግባራት በመፈጸም ከተከበረ ከእግዚአብሔር ዘንድ የማያልቅ ዘላለማዊ በረከትን ያስገኛል፡፡ ኢሳ 56፡4-8 ይህችን ዕለት የናቁ ሰዎች በሞት ተቀጥተዋል፡፡ ዘኁ 15፡32-36፡፡ ሰንበትን እንደምናከብረው ኹሉ በየ49 ዓመታት ደግሞ እንኳን ሰው መሬትም ከሚያርሱባት እንድታርፍ ኢዮቤልዩ አድርጎ ሰጥቶናል፤ መሬትን ያለ እረፍት ከዘራንባት ፍሬ አትሰጥምና፡፡ በተጨማሪም በዚህ ሳምንት ቅዱስ ኾኖ ቅዱሳን ኹኑ ብሎ ያስተማረው የጌታችን ትምህርት የሚታሰብበት ሳምንትም ነው፡፡ የዕለተ ሰንበት ክብር፤ በብሉይ ኪዳን፤ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ፈጥሮ ከስራው ኹሉ አርፎበታል፡፡ ዘፍ 2፥3፣ ዘጸ. 20፥8 በሐዲስ ኪዳን፤ ጌታችን የተጸነሰባት፣ ትንሣኤውን የገለጠባት፣ ለሐዋርያት ጸጋ መንፈስ ቅድስ የሰጠባት፣ ዳግመኛ ለፍርድ የሚመጣባት....ወዘተ ናት፡፡ በአጠቃላይ ታላላቅ ሥራዎችን የሰራበት በመሆኗ ከሌሎች ቀናት ለይተን እናከብራታለን፡፡ ከምጽአት በኋላ ሌሎች ቀናት ሲያልፉ ዕለተ ሰንበት ባለማለፏ ለዘለዓለም ጸንታ በመኖሯ ነው፡፡ /ድርሳነ ሰንበት/ ምዕ 18፥3-7 በዕለተ ምጽዓት ከማያልፉ ነገሮች መካከል ቃሉ፣ ዕለተ ሰንበት፣ የሰው ልጅ ናቸው፡፡ ዛሬ ዛሬ የኀጢአት ሥራ ኹሉ ቀን ተለይቶ የሚፈጸመው (ዝሙት፣ ሴሰኝነቱ፣ መዳራቱ፣ ዘፈኑ) ወዘተ በዚች ቅድስት ዕለት ነው፡፡ ‹‹ይህን ኀጢአት ቅድስት በምትኾን በእለተ ሰንበት፣ በሰሞነ ሕማማት፣ የሚፈታም ወዮለት›› ይላል፡፡ /መጽሐፈ ፍትሐ ነገሥት/፤ የባልና ሚስት ሩካቤ ኃጢአት ባይሆንም በማይገባ ወቅት ይልቁንም በዕለተ ስንበት በሰሞነ ሕማማት በረቡዕና ዐርብ ከተፈጸመ ኃጢአት ነው፡፡ ኢሳ 58፥13-14 ‹‹ፈቃድህን በተቀደሰው ቀን ከማድረግ እግርህን በሰንበት ብትመልስ፣ የሰንበትንም ደስታ እግዚአብሔር የቀደሰው ክቡር ብትለው፣ የገዛ መንገድህን ከማግኘት ከንቱ ነገርንም ከመናገር ተከልክለህ ብታከብረው፣ በዚህ ጊዜ በእግዚአብሔር አፍ ተናግሯልና›› ሮሜ 14፡16 ‹‹ቀንን የሚያከብር ለጌታ ብሎ ያከብራል›› በማክበራችን ከእግዚአብሔር የምንቀበለው ዘላለማዊ ዋጋ ክብር አለና፡፡ ባለ ማክበራችን ደግሞ ቅጣት ጉዳት አለና ነው፡፡ ሰንበትን በሚገባ ለማክበር ቸሩ አምላክ ይርዳን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ (የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት)

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፱_ #የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችንን ሕዝቡን (በካህናት አንጻር)፤ ነገሥታት፥ መኳንንትና መሳፍንትን በምን እንደሚፈትናቸው፡፡ አባ ጳውሊ፤ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን በምን ሥራ ትዋጋቸዋለህ አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ክፉ ሥራችንን ይዘን ወደ ቤተክርስቲያን እንገባለን፡፡ በካህናት መካከል ጠብን እንፈጥራለን፡፡ ሳቅንና ስላቅን ዋዛ ፈዛዛን እንዲያበዙ እናደርጋለን፡፡ በማሕሌትና በቅዳሴ ጊዜ ኩራትን፥ ትምክህትን፥ ትዕቢትን፥ ማንቀላፋትን፥ #ክፉ ሐሳብን በልባቸው እንዲያሳድሩ፤ የቅዳሴ የማሕሌት አገልግሎታቸውን እንዲተዉ እናደርጋቸዋለን፡፡ በቅዳሴ ጊዜ ከቤተክርስቲያን እንዲሸሹ፥ እንዳያስቀድሱ፥ ከክብረ ምሥጢራት እንዳይሳተፉ እናደርጋቸዋለን፡፡ ይኸውም የመጨረሻ ዘለዓለማዊ ክብራቸውና ሕይወታቸው የሆነው የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው፡፡ አባ ጳውሊ፤ ይህንን የምታደርጉት ለምንድን ነው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ተስፋ ያደረጓትን መንግሥትና ስርየተ ኃጢአትን እንዳያገኙ ነው፡፡ #በቅዳሴ ጊዜ ኃጢአት የሚሰረይባትና ጸጋ የሚገኝባት ስለሆነ ፥ በሚቀድሱትና በሚያስቀድሱት ሁሉ ላይ ምሕረት ይወርዳልና፡፡ ስለዚህ ስለምንቀናባቸው ጥፋታቸውን እንጠባበቃለን ፣ እንሻለን ፤ ከመልካም ሐሳብ እንዲርቁ እናደርጋለን፡፡ በንጹሕ ልብ ሁነው የሚቀድሱ ካህናትና የሚያስቀድሱ ሁሉ በረከትን እንዳያገኙና የኃጢአት ስርየት እንዳይደረግላቸው እንጥራለን፡፡ በከንቱ ነገር እርስ በርሳቸው እንዲጣሉና በዚህ ምክንያት ቂም በቀል በልቡናቸው እንዲኖር እናደርጋለን፡፡ ተስፋ ያደረግዋትን ዘለዓለማዊ ሕይወትንም እንዲያጡና ሕይወታቸውም ኃጢአትና በደል የተሞላ ፍጻሜያቸውም ገሃነመ እሳት እንዲሆን እናደርጋለን፡፡ በልባቸው ውስጥ ቂምና ቅንዓትን ከአሳደርንባቸው በኋላ በዚህ ምክንያት ሥጋውንና ደሙንም እንዳይቀበሉ እናደርጋቸዋለን፡፡ ዘወትር በዚህ ምክንያት የኃጢአታቸውን ስርየት አያገኙም፡፡ ከእግዚአብሔር ምሕረትና ከዘለዓለም ጸጋና በረከት እናርቃቸዋለን፡፡ ከቤተ ክርስቲያን እንዳይደርሱ እንዳይገቡ የፈጣሪያቸውን ትእዛዝ እንዳይሰሙ እናደርጋቸዋለን፡፡ ዳግመኛም ጸሎታቸው ቁመታቸውና ድካማቸው ከንቱ እንዲሆን ሰዓታትና ማሕሌት በሚቆሙበትና በቅዳሴ ጊዜ አንዳቸው በአንዳቸው ላይ እንዲዘባበቱ ትምክሕትን ትዝርኅትን በልባቸው እናሳድራለን፡፡ ከካህናትና ከሕዝብ መካከል ክርስትናቸው እንዲሻር እንደ ዓላውያን ሥርዓት በሥራይና በጥንቆላ በውሃ እንዲታጠቡ እናደርጋቸዋለን፡፡ ክፉ ሥራቸውንም መልካም አስመስለን እያሳያቸዋለን፡፡ በውስጣቸው ብዙ ወጥመድ እናስቀምጣለን፡፡ ከአንዲቱ ቢያመልጡ በሌላይቱ እንዲያዙ እናደርጋለን፡፡ በማሕሌት በሰዓታት በቅዳሴ ጊዜ በእውቀት እኔ እበልጣለሁ ፡ እኔ ላመስግን ፡ እኔ ልቀድስ ፡ እኔ ልዘምር ፡ እኔ ላንብብ እንዲሉ እናደርጋቸዋለን፡፡ በዚህ ምክንያት እርስ በርሳቸው እንዲጣሉ እናደርጋቸዋለን፡፡ #ንጽሕና_ሳይኖራቸው_በድፍረት_እንዲያገለግሉ_እናደርጋቸዋለን፡፡ ቅንዓትና ሽንገላ ቂምና ትዕቢት በልባቸው እያለ ቅዳሴ እንዲገቡ እናደርጋለን፡፡ አንዱ በአንዱ ላይ እንዲዘባበትና እንዲታበይ እናደርጋለን፡፡ በክፉ ሥራቸው ያዩአቸውና የሰሙአቸው ሁሉ ተስፋ እንዲቆርጡ እናደርጋለን፡፡ ካህናትና ዲያቆናት ፣ ምዕመናንም በማይጠቅም ነገር እንዲጣሉ እናደርጋቸዋለን አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ አንተን ያልበደሉህን ሰዎች እንዲህ የምታደርገው ለምንድን ነው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ሃይማኖታቸው የቀና፥ ሥነ ምግባራቸው ያማረ ስለሆነ እንቀናባቸዋለን፡፡ ስለዚህ አሕዛብ ክፉ ሥራቸውን አይተው ሃይማኖታቸውን እንዲነቅፏት ለማድረግ ነው አለው፡፡ #ነገሥታት፥ መኳንንትና መሣፍንትን በምን እንደሚፈትናቸው… ክፍል ፲.… ይቀጥላል ሰኞይጠብቁን/ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/

ዛሬ የካቲት 27 በስሚዛ (በሰንሰል) ቤተ ክርስቲያኗ የታነጸውና የእባብ መርዝ በቦታዋ ኃያል እንዳይኖረው ቃል ኪዳን የተሰጣት ቅድስት ፍቅርስተ ክርስቶስ ዓመታዊ ክብረ በዓለሏ ነው፡፡

* በሠርፀ ድንግል የተሠራው ቤ/ክ ራሳቸውን አንሳር(አሸናፊዎች) በሚሉና የሱፊ እስልምና ተከታይ በሆኑት የሱዳን መሐዲስት ደርቡሾች በተደጋጋሚ 3ት ጊዜ ጥፋትን አደረሱበት፤ እነዚሁም -ከ1659-1674ዓ.ም. የመጀመሪያው ጥፋት፤ -በዐፄ ቴዎድሮስና በዐፄ ዮሐንስና ዘመን /በጥር 27 1877ዓ.ም. የጎንደርና የደምቢያውን ዘገረ ገዢ ዳኅና ፈንታን ገደሉ ገዳሙን አቃጠሉ፥ መነኰሳቱን ፈጁ/ -በ1880ዓ.ም. ጎንደር አካባቢ ያሉትን አብያተ ክርስቲያናት አቃጠሉ -ጥር 10 1880ዓ.ም. ከንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ጋር ተዋጉ፤ ልጃቸው ምንትዋብ ተማረከች አልሰልምም ብላ በረሃብ ሞተች፤ ባለቤቷ ደጃች ጀምበሬ ሞቱ፡፡ -ነሐሴ 23 1880ዓ.ም. ጎንደር ገብተው ከ44ቱ ደብራት 40ውን አቃጠሉ፤ -መስከረም 25 1881ዓ.ም. ጎንደርን አቃጠሉ፤ ቀሪዎቹን 3ት ደብራት ሠለስቱ ምዕትን ግምጃ ቤት ማርያምን አቃጠሉ፤ የግምጃ ቤት 9ኝ የመጻሕፍት መምህራንን (ዛሬ የምንገለገልበትን አንድምታ ከመምህር ኤስድሮስ በኋላ ያቀኑትን እነ መምህር ወልደ ሚካኤልን) በቤተክርስቲያኑ መውጫ በርላይ ከነተማሪዎቻቸው ሰየፏቸው፡፡ ጩጊ ማርያምንም አቃጠሉ፡፡ ….. ዐፄ ዮሐንስ እየመጡ መኾኑን ሲሰሙ ወደ መተማ ሸሹ፡፡ **ዐፄ ዮሐንስም ወደ ማኅበረ ሥላሴ በመግባት ገዳማውያኑን በማጽናናት፤ የብራና ተዓምረ ማርያምና ሌላም መብዓ በመስጠት በየካቲት 27/1881ዓ.ም ወደ መተማ ወርደው ተዋጉ፤ በውጊያው ግን ንጉሣችን ተመትተው ቆሰሉ፤ ጦሩም ንጉሡን ይዞ ወደ ማጠቢያ (ጻድቁ ልብስ ያጠቡበት በመሆኑ ይህን ስም አግኝቷል) ሸሸ፤ ጠላት ኃይሉን አጠናክሮ በመጋቢት 3/1881ዓ.ም. ደርሶ ንጉሣችንን ገደለ፤ ንጉሣችንን አናስነካም ያሉ በርካታ ካህናትና ምዕመናንም በሰማዕትነት አለፉ፡፡ **ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ /1929-1922ዓ.ም./ የተቃጠለውን ቤ.ክ. አሳነፁ፥ የውኃ ታንከር ከምድር በታች አስቆፍረው በደንጊያና በኖሩ አሠሩ፡፡ ከ8ት ዓመታት በኋላ ከሚያዝያ 13-15/ 1928ዓ.ም. ግን ጠላት ጣሊያን በጦር አውሮፕላን ሁኖ ገዳሙንና የውኃ ገንዳውን በቦንብ ደበደበ፥ 28 መነኰሳትንም ፈጀ (የቦንቡ ቀለሃ አሁንም በገዳሙ ወፍጮ ቤት ይገኛል)፡፡ ነገር ግን አውሮፕላኖቹ ጥቃቱን አድርሰው ሲመለሱ በአበው ጸሎት፥ በጻድቁ ዐምደ ሥላሴ ተዓምር አድራጊነት 2ቱን አውሮፕላኖች አንዱን ዋለንታ ላይ፤ ሁለተኛውን ማርዘነብ ላይ ከስክሰዋቸዋል፤ ስብርሪያቸው አሁንም ድረስ አለ፡፡ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/

... ስለ ማኅበረ ሥላሴ ገዳም የቀጠለ #የገዳሙ_አመሠራረት *ማኅበረ ሥላሴ ገዳም ከክርስቶስ ልደት በፊት እንደነ መልከጼዴቅና ነቢያት የክርስቶስን መወለድ የሚጠብቁ መናንያን የነበሩበት ነው፤ ለዚሁም ማስረጃ ክርስቶስ በተወለደ ዕለት ቶራ(ሚዳቋ) ‹‹ዮም ተወልደ ቤዛ ኵሉ ዓለም፥ ዮም ተወልደ ከሣቴ ብርሃን፥ ዮም ተወልደ መድኀኔ ዓለም›› (የብርሃን አምላክ ዛሬ ተወለደ) በማለት ስትቦርቅ የታየበት ነው፡፡ /የሰኞ ውዳሴ ማርያም አንድምታ/ *ይህ ገዳም በዚህ ሁኔታ የስውራንና የባሕታውያን መኖሪያ ሁኖ እስከ 4ኛው ክፍለ ዘመን ከቆየ በኋላ፤ በአብርሃ ወአጽብሃና በጳጳሱ ከሣቴ ብርሃን በአካባቢው በሚያልፉ ጊዜ (ቀድሞ ወደ ግብጽና ሱዳና የሚኬደው በዚሁ አካባቢ ተደርጎ ነበር)፤ ለጳጳሱ ድባ ተራራ ላይ (አሁን ገዳሙ የሚገኝበት ተራራ) ታላቅ የብርሃን ምሰሶ ዐምድ ሲወርድ፤ አወራረዱም ከላይ አንድ፥ ከታች ደግሞ ሦስት ሁኖ ያያሉ፤ ያትንም ለነገሥታቱ ነግረዋቸው ወደ ቦታው ያመራሉ፤ ከተራራው ግርጌ ሲደርሱ ይህ ቦታ መንፈሰ እግዚአብሔር የሰፈነበት የተቀደሰ ቦታ ነውና እኛም ጫማችንን ሠራዊቱም ትጥቃቸውን ፈትተው መግባት አለብን ብለው ለነገሥታቱ ነገሯቸው፤ ነገሥታቱም ከነሠራዊታቸው ጫማቸውን አውልቀው፥ ዝናርና ትጥቃቸውን ፈትተው፥ ጎራዴና ጦራቸውን አስቀምጠው፥ ባርኔጣቸውን አውልቀው፥ ከፈረስና ከበቅሎ ላይ ወርደው ወደ ተራረው ጕዞ ጀምረዋል፡፡ ይህ ቦታ ዛሬ ግዝት በር የሚባል ሲሆን (በየካቲት 27፣ ሐምሌ 27፣ ሰሙነ ሕማማትና፣ ቀብር ካልሆነ በቀር) 7ት ቀናት እዚሁ ቦታ ላይ ተቀምጦ ነገሥታቱ ከነሠራዊታቸው ያደረጉትን ሥርዐት (በባዶ እግር፣ ….) ነው ወደ ገዳሙ ተራራ ላይ የሚወጣው፡፡ ወደ ተራረውም እንደደረሱ ብርሃኑ ቢሰወርባቸው ለ7ት ቀን ሱባኤ ይዘው ምሥጢሩ ተገልጦላቸው ሚዳቋም ምልክት ሰጥታቸዋለች፤ ወዲያውም ቦታውን ባርከው፥ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑን አንጸው፥ ነዋሪ መነኰሳትን አስቀምጠው፥ ለገዳሙ መተዳደሪይ ርስት ጉልት ጎልተው፥ ዳሩ እሳት መሐሉ ገነት ብለው ገድመው፥ የብርሃን ዐምድ ያዩበት ነውና የገዳሙን ስም ‹‹ምቅዋመ ሥላሴ›› ብለው ሰይመው ተመልሰዋል፤ ኋላ ግን ገዳሙ ስሙ ‹‹መካነ ሥላሴ›› በሚል ስያሜም ሲጠራ ቆይቷል፡ በ14ኛው ክፍለ ዘመን የጌታችን መስቀል የቅዱሳን አእፅምትና ሌሎችም ንዋያተ ቅድሳት ለ3ት ቀናት ውለው አድረውበታል፤ የብርሃን ነጸብራቅም ታይቷል፡፡ **በ17ኛው ክፍለ ዘመን የተነሡት ጻድቁ ዓምደ ሥላሴ ደግሞ በተለያየ ዘመን ጠፍ የነበረውን ይህንን ገዳም አስፋፍተውና እንደ መሶብ አስባርከው እስካሁን ድረስ ሥርዐቱን እንደጠበቀ ቆይቷል፡፡ እርሳቸውም 104ዓመታትን ከኖሩ በኋላ የካቲት 27 ዐርፈው በዚሁ በገዳማቸው አጽማቸው በክብር አርፏል፡፡ **ይህ ገዳም የትምህርትና የጥበብ ማዕከልም በመኾኑ ከሕዝብ እስከ ካህናት፤ ከመሳፍንት እስከ ነገሥታት፤ ከመነኰሳት እስከ ጳጳሳት፤ ቅዱሳንና ጻድቃን መናኻሪያቸው አድርገውታል፤ (ለአብነትም ከነገሥታት ዐፄ ፋሲል፤ ዐፄ ቴዎድሮስ ዳግማዊ ይጠቀሳሉ) *** ዐፄ ቴዎድሮስ የተወለዱት በማኅበረ ሥላሴ አካባቢ ዳዋ በሚባል መንደር ሲሆን፤ በሕፃንነታቸው ቸንከር ተክለ ሃይማኖት ገብተው ሲማሩ እስላሞች ቤተ ክርስቲያኑን አቃጥለውና ተማሪዎቹን ሲገድሉ እርሳቸው አምልጠው፤ ወደ ታላቁ ገዳም ገብተው ከታለቁ ምሁር ባሕታዊ ከአባ ገብረ መሢሕ (በኢየሩሳሌምና በግብጽ ገዳማት የኖሩና ዐረብኛና ፈረንሣይኛን የሚያውቁ) ዘንድ ተማሩ፤ በዘመነ መሳፍንት ደጃዝማች ማሩና ደጃዝማች ይማም ሲዋጉ የገዳሙ 48 ተማሪዎችና መነኰሳት ሞቱ፤ ዐፄ ቴዎድሮስ ግን ተረፉ፡፡ የአባታቸው ልጅ የደንቢያ ቋራና መተማ ገዢ ደጃዝማች ክንፉ ጸሎት በአባቶች ሊያስደርጉ ወደ ማኅበረ ሥላሴ ሲመጡ ዐፄ ቴዎድሮስም ጸሎተ ማርያም አስደርሰው ‹‹ስሞት ግን ዐፅሜን ከዐፅማችሁ ጋር ደምሩልኝ›› ብለው ገዳሙን ለቀው ደጃች ክንፉን ተከትለዋቸው ሄዱ፤ …… ሚያዝያ 5/1860ዓ.ም. ዐፄ ቴዎድሮስ መቅደላ ላይ ካረፉ በኋላና በመቅደላ መድኀኔ ዓለም ተቀብረው 3ት ዐመት ከተቈጠረ በኋላ በኑዛዜያቸው መሠረት ልጃቸው ራስ መሸሻና የመቅደላ ካህናትና ሕዝብ የንጉሣችንን የዐፄ ቴዎድሮስን ዐፅም በታላቁ ማኅበረ ሥላሴ አምጠተው በክብር አሳረፉ፡፡ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/ #የገዳሙ_መነኰሳት_ሥርዐት *** ገዳሙ ሥርዐተ አበው እጅጉን የሚጠበቅበት፥ ፍቅር እንደ ሸማ የተለበሰበት፥ ምግባረ ትሩፋት የሚዘወተርበት ገዳም ነው፡፡ ለአብነትም፤ **በገዳሙ የሚገኙ መነኰሳት እንደ ዮሐንስ ወገባቸውን በዝናር የሚታጠቁና በዚያ በበርሐ እያረሱና ከፍተኛ ቊጥር ያላቸውን ከብቶች እየጠበቁ፤ ነፍሳቸውን ለሥላሴ አደራ ሰጥተው የሚኖሩ ናቸው፡፡ *የገዳሙ መደበኛ (ከዓመት እስከ ዓመት) ምግብ ከብዙ እህሎች የተቀያየጠው ‹‹መኰሬታ›› (ዳቤ) ሲሆን፤ በተለያዩ ሃገራችን ከምናውቀው መኰሬታ (ዳቤ) ይለያል፤ መኰሬታው የሚጋገረው በድንጋይ ወፍጮ በእጅ በክርትፉ ደቅቆ ሲሆን ፈጽሞ ዱቄት ያልሆነ፥ ያልላመና ወፍጮ ያልነካው ነው፡፡ በዓለም ለሚኖር ሰው ለመመገብ ይከብዳል፡፡ **መጠጣቸው ውኃ ሲሆን አልፎ አልፎ በበዓላ ከኑግ(ከሱፍ) የሚሠራ ጭልቃን ይጠጣሉ፡፡ አብዛኞች የሚመገቡትና የሚጠጡት በቀን ውሎ አንዴ ነው፡፡ ***ሥጋ ትህርምት ነው (ፈጽሞ አይበላም)፤ በዓመት 3ት ቀን (ልደት ጥምቀትና ትንሣኤ) ብቻ ነው የሚበላው፡፡ የመገርመው ግን ገዳሙ ሰፊ መሬት ስላለው በከብት ብዛት (በሃገራችን ግንባር ቀደም ነው)፡፡ እንጀራ መብላት የሚፈልግና የታመመ መነኰስ ካለ ከገዳሙ ጋር አንድነት ወዳለው ወደ ዋታሆ አቦ በመሄድ ነው እንጀራ የሚበላው፡፡ * መነኰሳቱ ለዓመት ከሚሰጣቸው ልብስ ውጪ በራሳቸው አሰፍተውና ገዝተው መልበስ አይችሉም፤ * ቁሪት (የግል ንብረት) አይፈቀድም፤ ማለትም መነኰሳቱ ከሚቆነንላቸው (ከሚሰጣቸው) መኮሪታና ጭልቃ ውጭ ማንኛውንም ተጨማሪ ምግብና መጠጥ (የሚወርድ ውኃም ቢኾን) መመገብና መጠጣት፤ በቤታቸው መርፌም ቢኾን ያለ መጋቢው ፈቃድ ማስቀመጥም ኾነ መጠቀም አይፈቀድም፤ * ማንኛውም ወደ ገዳሙ የሚሄድ ሰው (በየካቲት 27 በጻድቁ ዓምደ ሥላሴ፣ በጥርና በሐምሌ 7 የቅድስት ሥለሴ ክብረ በዓል ቀንና ለቀብር ካልኾነ በስተቀር) ለ፯ት ቀናት የግዝት በር ላይ ደጅ መጥናት ግድ ይለዋል፡፡ **በማኅበረ ሥላሴ እንኳን ሰዉ ከብቱ ሥርዐት ያለው ስለሆነ፤ ወገን፥ ወገን፤ ተለይ፥ ተለይ፤ አጎዶ፥ አጎዶ፤ ጉዞ፥ ጉዞ፤ ሰፈር፥ ሰፈር ሲባሉ በየወገኑና በየጾታው እንዲሁም ወደ ሚታዘዙበት ቦታ ይሄዳሉ፡፡ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/ #የገዳሙ_መፍለስ_መነሳት_መጥፋት_መልማት -ገዳሙ በጠረፍ አካባቢ ከመኖሩ ጋር በተያያዘ ፤ለበርካታ ጊዜያት በየዘመናቱ መቃጠል፣ መዘረፍና የቦንብ ድብደባ ደርሶበታል፤ መናኞች በሰይፍ ተሰይፈውበታል፡፡ ዋና ዋናዎቹን ብናነሣ፤ *አብርሐ ወአጽብሐ ያሠሩትን ቤ/ክ ዮዲት ጉዲት (842-888ዓ.ም.) አቃጠለችው፥ ንዋያተ ቅድሳቱንና ንብረቱን ዘረፈች፡፡ **ዮዲት ያፈረሰችውን በንጉሥ ዐምደ ጽዮን(1268-1277ዓ.ም.) ቤ/ክ መልሶ ተሠራ፡፡ *በእስላም የቱርክ መንግሥት ይረዳ በነበረው ወራሪው አሕመድ ግራኝ /1541-1545ዓ.ም./ ብዙ መነኰሳት ተጨፈጨፉ፥ ቅርሶች ተዘረፉ፡፡ እንደገና በዐፄ ሠርፀ ድንግል /1553-1587ዓ.ም./ ተቋቋመ፡፡ *በዘመነ መሳፍንት ደጃዝማች ማሩና ደጃዝማች ይማም ሲዋጉ የገዳሙ 48 ተማሪዎችና መነኰሳት ሞቱ፡፡ /ዐፄ ቴዎድሮስ ግን ተረፉ) *በዐፄ ቴዎድሮስ ዘመን እንግሊዞች የገዳሙን ንብረት መዘበሩ፡፡

#ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳምና_ጻድቁ_ዐምደ_ሥላሴ #ታቦቱ_ሥላሴ፥ #ጻድቁ_ዐምደ_ሥላሴ፥ #የገዳሙ_ስም_ማኅበረ_ሥላሴ፡፡ #በየቀኑ_በሁሉም_ቤክ_በቅዳሴ_ላይ_ስሙ_የሚነሳው_ገናናው_ገዳም (ብዙዎች ግን የማያውቁት)፡፡ #እንኳን_ሰዉ_ከብቱ_ሥርዐት_ያለው_ድንቅና_ዕፁብ_ገዳም፡፡ #ገዳሙን_ያጠፉ_አውሮፕላኖችን_በጸሎት_የከሰከሱ_አባቶች_የሚገኙበት #የበርካታ_ትምህቶችና_የጥበብ_ማዕክል፤ …. ኢትዮጵያውያን ሁሉ ቢያንስ አንዴ ሊያዩት የሚገባ ዕፁብ ድንቅ የኾነ ገዳም!!!፡፡  በዚህች በየካቲት 27 እለት ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን ወመነኰሳት (ለአቡነ ክፍለ ማርያም፥ ለአቡነ ገብረ ክርስቶስ ዘቋራ፥ ለ፯ቱ ዘሥላሴ በመባል ለሚጠሩ ቅዱሳን፣ ለዐርከ ሥሉስ /የአርኬና የመልክአ ቊርባን ደራሲ/፤ ….) የኾኑትና ፤ ጽድቃቸውና ቃልኪዳናቸው እንደ ምድር አሸዋ የበዛው፥ እንደ ሰማይ ከዋክብት ለመቊጠር የሚያስቸግረው ጻድቁ ዐምደ ሥላሴ ዘማኅበረ ሥላሴ ልደታቸውም እረፍታቸውም ነው፡፡ - እኒህ ጻድቅ የተወለዱት በጎጃም(ሸዋም የሚሉ አሉ) ሲኾን፤ የተወለዱትም ሆነ 104ዓመታት ከኖሩ በኋላ ያረፉበት ቀን በመድኀኔ ዓለም ወርኀዊ በዓል በየካቲት 27 ነው፡፡ - ጻድቁ በተለያዩ ገዳማት በአርድእትነትና ሥርዐተ አበው በማጥናትና በመተግበር ከቆዩ በኋላ፤ ምንኩስናን ከአቡነ ተንሥአ ክርስቶስ ዘትግራይ ተቀብለዋል፤ ኋላም ወደ ታላቁ ገዳም ገዳመ ዋሊ (ገዳመ ዋልድባ) ገብተው ከቆዩ በኋላ ወደ ገዳመ አስቄጥስ በመሄድ ለ18 ዓመታት ከቆዩ በኋላ በስተመጨረሻ ምናኔያቸውን በማኅበረ ሥላሴ አድርገዋል፡፡ * በ1616ዓ.ም. ሱስንዮስ 8,000 ክርስቲያኖችን የካቶሊክን ካልተቀበላችሁ ብሎ ጠዳ ላይ በሰየፈ ጊዜ ሳይፈሩና ሳይፍሩ ለሃይማኖታቸው ከተከራከሩና ጠበቃ ከኾኑት መካከል ግንባር ቀደሙ ናቸው፡፡ (ሌሎችም ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ፣ እኅተ ጴጥሮስ፣ ፍቅርተ ጴጥሮስ፣ ሐራ ድንግል ምዕመነ ድንግል አብረው ይጠቀሳሉ)፡፡ እነዚህም ቅዱሳን ሐዘናቸውን ወደ ፈጣሪያቸው በማድረሳቸው ሱስንዮስ ምላሱ ተጎልጉሎ ወጣ (ተቀሰፈ)፡፡ - የሱስንዮስ ልጅ ፋሲልም አባቴን ይፈውሱልኝ ብሎ መልእክትን ላከ፤ ጻድቁ ዐምደ ሥላሴና አባ ምዕመነ ድንግል ዘጩጊ ማርያም ተገኝተው ካቶሊክነቱን ከተወ እሺ ብለው 3ት ሱባኤ ጸልየው ፈወሱት፤ ሱስንዮስም ንሥሐ ገብቶ ቅዱስ ቊርባንን ተቀበለ፡፡ በሰኔ 21 1624ዓ.ም. ‹‹የእስክንድርያ ሃይማኖት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ይመለስ፥ የሮም ካቶሊክ ሃይማኖት ይፍለስ፥ ልጄ ፋሲል ይንገሥ›› ብለው አዋጅ ነገሩ፤ ልጃቸው ፋሲልንም ጻድቁ ዐምደ ሥላሴ ቅብዓ መንግሥት (አፈዋተ መንግሥት) ቀብተው አነገሡት፤ ንጉሡም ለገዳሙ የእርሻ መሬት የሚሆን ጣቁሳ ላይ 44ት ጉልት ጐለተ፥ የገዳሙንም ስም ‹‹ማኅበረ ሥላሴ›› ብሎ ሰየመው፡፡ - ታላቁ ማኅበረ ሥላሴ ገዳም ቀድሞም ከእርሳቸው በፊት የነበረ ቢኾንም፤ በተለያዩ ዘመናት በጠላት የጠፋ ስለነበረ ዳግመኛ ያስፋፉትና እንደ መሶብ ያስባረኩት ናቸው፤ - ከወለዷቸው አንዱ ዐርከ ሥሉስ ከደረሳቸው አንዱ በኾነው በመልክአ ቊርባን ላይ፤ ‹‹ሰላም ለክሙ ጻድቃነ ዛቲ ዕለት ኵልክሙ፤ ዕድ ወአንስት በበአስማቲክሙ፡፡ ቅዱሳነ ሰማይ ወምድር ማኅበረ ሥላሴ አንትሙ፤ ዝክሩነ በጸሎትክሙ በእንተ ማርያም እሙ፤ ተማኅጸነ ለክርስቶስ ሥጋሁ ወደሙ፡፡ በማለት የደረሱለት ሲኾን፤ በዚህም በየቀኑ በቅዳሴ ላይ ከቊርባን በፊት የማኅበሩን ስም የማይጠራ ቤተ ክርስቲያን የለም፡፡  ብፁዕ አባ አቡነ ዓምደ ሥላሴ ንብረቱ ገዳም ውስተ ሀቌሁ ቅንአቱ ዘአዲም ያስተጋብእ ጽድቀ ዘእምኵሎሙ ቅዱሳን በጾም ወበጸሎት ሀለወ በክብር ወበሰላም፡፡ /መሐረነ አብ/ /#ዋልድባ_ዋሊ_ገጽ/ #የማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም፤ (#የሺዎች_ማኅበር)፤ #ምቅዋመ_ሥላሴ፡፡ #ስለ_ገዳሙ_አጠቃላይ_ሁኔታ፤ *ገዳሙ የሚገኘው በሀገራችን በመተማ በረሃ ደቡባዊ ክፍል፥ ከጎንደር በስተምዕራብ አቅጣጫ (132 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ) ሲሆን፤ ከአ.አ. 901ኪ.ሜ. ርቀት ላይ፤ ከደረቅ ዐባይ ቀበሌ በ4ት ሰዓት የእግር ጕዞ ይገኛል፡፡ የጣቁሳ የቋራና የሱዳን በረሓማው አከባቢዎችም ያዋስኑታል፡፡ *ከፀሐዩ ሐሩር ማየልና ከቆላነቱ የተነሣ ‹‹በደንጊያው ላይ ተልባ ያስቆላል›› እየተባለ የሚነገርለት ነው፡፡ የተለያዩ ዕፅዋትና አራዊት የሚገኙበትም ሲሆን ቦታው በብሔራዊ ደረጃ ጥብቅ ደን ነው፡፡ * የገዳሙ ይዞታ ከ19ሺህ 186 ሄክታር በላይ የሚሸፍን ሲሆን፤ በቦታ ስፋት የሚመስለው ዋልድባ (ዋሊ) ብቻ ነው፡፡ በዚህም ከሃገራችን ገዳማት 2ቱ ታላላቅ ገዳማት እጅግ በጣም ሰፋፊ ይዞታ ያላቸው ገዳማት ናቸው፡፡ * ገዳሙ በ፪ት ትላልቅ ወንዞች (በገንዳ ውኃና ሸንፋ ወንዝ) የተከበበ ነው፡፡ *ገዳሙ በሚገኝበት በረሃ ውስጥ 4ት ተራሮች(አምባዎች) ይገኛሉ፡፡ እነርሱም፤ ድባ(የማኅበረ ሥላሴ ገዳም ያለበት)፣ ከርከመች፣ ኩክቢና ጎርማስ ይባላሉ፡፡ *ገዳሙን በርቀት ሆነው የሚያዋስኑት ታላላቅ ገዳማትም፤ በሰሜን አቅጣጫ ደምጫ፥ በደቡብ ጋንጫ(ዋታሆ አቦ) ናቸው፡፡ *በገዳሙና በአካባቢው ከሚገኙት የተለያዩ ዕጽዋት መካከል (ሰርኪን፥ ሲና፥ የዕጣን ዛፍ/ዋልያ/፥ መቀር፥ ወርካ፥ ክርክራ፥ ሽመል) እና ሌሎችም ልዩ ልዩ ዕጽዋት የሚገኙበት ሲኾን፤ ከዱር አራዊት መካከልም (አንበሳ፥ ነብር፥ አጋዘን፥ ቶራ/ሚዳቋ/፥ ድኩላ፥ አሳማ፥ ጉሬዛ፥ ዝንጀሮ፥ ቀይ ጦጣ፥ የተለያዩ የእባብና የዘንዶ ዝርያዎች) ይገኙበታል፡፡

የዐቢይ ጾም የሱባኤ መርሐ ግብራት፤ ከሰኞ የካ. 25 - ዐርብ የካ. 29፤ ጠዋት ጠዋት ከ12-1ሰዐት (ጸሎት)፣ ማታ ማታ ከ12-2 (ጸሎትና ትምህርት) እንደተለመደው አለ፡፡