ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 382 подписчиков, занимая 5 582 место в категории Религия и духовность и 2 195 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 382 подписчиков.

Согласно последним данным от 07 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 40, а за последние 24 часа — 9, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 22.55%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.50% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 469 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 461 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 20.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 08 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 382
Подписчики
+924 часа
-177 дней
+4030 день
Архив постов
#የማንቂያ_ደውል #የማንቂያ_ደውል #የማንቂያ_ደውል #የማንቂያ_ደውል #የማንቂያ_ደውል (በደቡብ ሸዋ፣ በድሬደዋና በደቡብ ኢትዮጵያ እንገናኝ) Sharereeeeee ‹‹#የእግዚአብሔር_ድምፅ_ከተማይቱን
+3
#የማንቂያ_ደውል #የማንቂያ_ደውል #የማንቂያ_ደውል #የማንቂያ_ደውል #የማንቂያ_ደውል (በደቡብ ሸዋ፣ በድሬደዋና በደቡብ ኢትዮጵያ እንገናኝ) Sharereeeeee ‹‹#የእግዚአብሔር_ድምፅ_ከተማይቱን_ይጠራታል_ስምህን_መፍራት_ጥበብ_ነው_፡፡›› /ትንቢተ ሚክያስ 6፥9/ ፠ ኀሙስ የካቲት 12፤ በድሬደዋ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል፡፡ ፠ የካቲት 13፤ በናዝሬት (አዳማ) ቅድስት ማርያም፡፡ ፠ ከየካቲት 13-15፤ በሐዋሳ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፡፡ #ይቀጥላል ~ ጎንደር ፥ ጂጂጋ ፥ አርባምንጭ ፥ ጂንካ ፥ ቡታጅራ ፥ ደሴ ፥ ባሕርዳር ፥ አሶሳ ፥ አዳማ ፥ ጋምቤላ፥ ሆሳዕና ..... ፠፠፠ የአቤልን የግፍ ሞት፤ የዘካርያስን በግፍ መገደል የተበቀለ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በቤተ ክርስቲያናችንና በምዕመኗ ላይ የደረሰውን ግፍ፣ ቅትለት (ግድያ)፣ ማስፈራሪያ፣ ዛቻ፣ ሥልጣንን ተገን በማድረግ የሚሠራ ደባ፣ ሙስና፣ ……. እርሱ ይበቀልልን፤ እርሱ ፍርዱን ይስጥ፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

/ከትናንቱ የቀጠለ……/ #ክፍል_፬.፬ #ለየካቲት_12_የሰማዕታት_ቀን_መዳረሻ፥ #ለየካቲት_23_የአድዋ_ድል_መነሻ፥ #ለሚያዝያ_27_የድል_ቀን_ማስታወሻ_ ፠ ‹‹ህየንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ፡፡
+9
/ከትናንቱ የቀጠለ……/ #ክፍል_፬.፬ #ለየካቲት_12_የሰማዕታት_ቀን_መዳረሻ፥ #ለየካቲት_23_የአድዋ_ድል_መነሻ፥ #ለሚያዝያ_27_የድል_ቀን_ማስታወሻ_ ፠ ‹‹ህየንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ፡፡ (#በአባቶችሽ_ፈንታ_ልጆች_ተወለዱልሽ) ፠ የዘንድሮ የካቲት 12/2012 ዓ.ም. በዓል በአባቶቻችን እግር ሥር የተተኩ ሕፃናትና ወጣቶች (የአርበኞች ትምህርት ቤት፣ የኢትዮጵያ ስካውት ማኅበር፣ ብሉ በርድ ትምህርት ቤት፣ ሒል ሣድ ትምህርት ቤት፣ ድራማና ዝማሬና ሽለላ ልክ በወቅቱ ያለ አስመስለው አቡነ ጴጥሮስንም አስመስለው የሚያቀርቡ ማኅበራትና ሌሎችም ተሳትፈዋል፡፡) በዕለቱም ከተጻፉ ጥቅሶች መካከል ጥቂቶቹ፤ #ሀገሬ_እኔ_ብለህ_የምትኖርባት_እኛ_ብለህ_የምትሞትላት_ጣፋጭ_ቅኔ_ናት፡፡ ፠ ለዘለዓለማዊ የሰው ልጅ ሞቱ ነፍሱ ከሥጋው መለየቱ ሳይሆን ነጻነትን አለማወቁ ነው፡፡ #ከሰብዐዊነት_ዘር_ይበልጣልን? ፠ እኛ የሞትነው መወለድ ግብሯ የሆነውን ኢትዮጵያን ልንወልድ ነው፡፡ #ኢትዮጵያ_በክፋት_የነካትን_የምታቃጥል_እሳት_ናት፡፡ ፠ አገሩን በሰላም ወጋግራ አቁሞ ለማለፍ ሰው ከአባቱ ገዳይ ጋር በቅርታ ይፋቀራል፡፡ #ኢትዮጵያን_የምታክል_ሃገር_እንዴት_ለባርነት_እናስረክባለን፡፡ ፠ ለራስህ ከርስ ብለህ ለመጪው ትውልድ ባርነትንና ምድራዊ ገሃነምን እንደምን ታወርሰዋለህ!!፡፡

/ከትናንቱ የቀጠለ……/ #ክፍል_፬.፫ #ለየካቲት_12_የሰማዕታት_ቀን_መዳረሻ፥ #ለየካቲት_23_የአድዋ_ድል_መነሻ፥ #ለሚያዝያ_27_የድል_ቀን_ማስታወሻ_ ፠ የዘንድሮ የካቲት 12/2012 ዓ.ም. በዓ
+3
/ከትናንቱ የቀጠለ……/ #ክፍል_፬.፫ #ለየካቲት_12_የሰማዕታት_ቀን_መዳረሻ፥ #ለየካቲት_23_የአድዋ_ድል_መነሻ፥ #ለሚያዝያ_27_የድል_ቀን_ማስታወሻ_ ፠ የዘንድሮ የካቲት 12/2012 ዓ.ም. በዓል የአባቶቻችንና የእናቶቻችን አርበኞች ሰማዕታት ውሎ በከፊል፡፡

/ከትናንቱ የቀጠለ……/ #ክፍል_፬.፪ #ለየካቲት_12_የሰማዕታት_ቀን_መዳረሻ፥ #ለየካቲት_23_የአድዋ_ድል_መነሻ፥ #ለሚያዝያ_27_የድል_ቀን_ማስታወሻ_ (የዘንድሮ የካቲት 12/2012 ዓ.ም. በዓልና ጸሎተ ፍትሐት በ6ኪሎና በ4 ኪሎ ሥላሴ ምን እንደሚመስል ፎቶውን ይመልከቱ፡፡) ‹‹#የአካፋው_ሚካኤል››፤ #የካቲት_12/1929ዓ.ም. (#የሰማዕታት_ቀን) (#30_ #ሺህ_ኢትዮጵያውያን_ሰማዕታት_) ፠ ዐጤ ኀይለ ሥላሴ ወደ ሃገራቸው ከተመለሱ በኋላ በ6 ኪሎ ለሰማዕታቱ ሐውልት ቆመ መጀመሪያ የተሠራው አነስተኛ በመሆኑ ኋላ አሁን ያለው ትልቅ ተደርጎ ተሠርቷል፡፡ ፠ ቀኑ እንዳይረሳም #ቤተ_ሳይዳ ተብሎ ይጠራ የነበረው ሐኪም ቤት #የካቲት_12_ሆስፒታል ተባለ፡፡ ፠ በጀግንነት ለተዋጉት አርበኞች በ1934ዓ.ም. በአዲስ አበባ ‹‹የአርበኞት ትምህርት ቤት›› ተሠራ፡፡ ፠ በ1923 ዓ.ም. ተመሥርቶ የነበረውና በእቴጌ መነን ይጠራ የነበረው ትምህርት ቤትም ቆይቶ የካቲት 12 ትምህርት ቤት በመባል ተሠየመ፡፡ ፠ ከ8 ዓመት በኋላም (ጥቅምት 23 በ1937 ዓ.ም.) የሰማዕታቱ ዐፅም ተሰብስቦና ፈልሶ በ4ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በክብር እንዲያርፍና መቃብር ቤት እንዲሠራለት ተደረገ፡፡ (በነገራችን ላይ የዛሬን አያድርገውና /በስመ ታዋቂና ባለሀብት እየተባለ ሆነ እንጂ/ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ጀግኖች አርበኞች የሚቀበሩበት ቤተ ክርስቲያን ነበር)፡፡ በሐውልቱ ላይ ያለው ጽሑፍና ግጥም እንዲህ ይነበባል፤ #‹‹ዝንቱ ውእቱ ምዕራፈ አዕጽምቲሆሙ ለብዙኃን ኢትዮጵያውያን እለ ተቀትሉ በግፍዕ በእደዊሆሙ ለሕዝበ ኢጣሊያ ፋሽስታውያን አመ ፲ወ፪ ለየካቲት በ፲ወ፱፻፳ወ፱ ዓ.ም.፤ ወተቀትሎቶሙኒ ኮኑ በውግረተ አእባን ወበአብትር፥ በመክርይ ወበመስኤ፥ በመሕፄ ወበዕፀው፥ በመብረቀ ሐፂን ወበፀዓዕ፥ ወበውዕየተ እሳት ውስተ ቤቶሙ፡፡ ወበራብዕ ዓመት እምዘኮነ ዝንቱ ነገረ ግፍዕ ተመይጠ እግዚእነ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ እም ሀገረ ብሪታንያ በግርማ መዊዕ፤ ወአቲዎ ብሔሮሙ ሠረዎሙ ለጸላእትነ ወአቀመ ትእምርተ ግዕዛንነ፡፡ ወእምድኅረዝ አዘዞሙ ለኅሩያኒሁ ከመ ያስተጋብኡ አዕጽምቲሆሙ ለእሉ እለ ተቀትሉ በግፍዕ ወያንብርዎሙ ውስተ ዝንቱ መካን ቅዱስ ዘሕኑፅ ለዝክረ ነገር ወለዝክረ ስሙ፤ ወኮነ በዓለ ፍልሰቶሙ ወተጋብኦቶሙ ለእሙንቱ አዕጽምተ ምውታን በ፲ወ፬ ዓመተ በዓለ ንግሡ ለቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትየጵያ አመ ፳ወ፫ ለጥቅምት በዕለተ ኀሙስ በ፲ወ፱፻፴ወ፯ዓ.ም.፡፡›› ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

‹‹#የአካፋው_ሚካኤል››፤ #የካቲት_12/1929ዓ.ም. (#የሰማዕታት_ቀን) (#30_ #ሺህ_ኢትዮጵያውያን_ሰማዕታት_) ፠ ውለታን የማትረሳ ቤተ ክርስቲያናችን እነዚህን ሰማዕታት በአዲስ አበባ 6 ኪሎ
+3
‹‹#የአካፋው_ሚካኤል››፤ #የካቲት_12/1929ዓ.ም. (#የሰማዕታት_ቀን) (#30_ #ሺህ_ኢትዮጵያውያን_ሰማዕታት_) ፠ ውለታን የማትረሳ ቤተ ክርስቲያናችን እነዚህን ሰማዕታት በአዲስ አበባ 6 ኪሎ መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ቀድሞም ይከበራል፤ ከ2ት ዓመት ወዲህ ደግሞ ከአዲስ አበባ ዩነቨርሲቲ የተገኘው የቅዱስ ሚካኤልም አብሮ ወጥቶ ይከበራል፡፡

ዝክረ ቅዱስ ያሬድ ዘየካቲት እንደተለመደው በተለያዩ መርሐ ግብሮች የሚዘከር በመሆኑ እንዳያመልጥዎ፡፡ ቀንና ሰዓቱ፤ ረቡዕ የካቲት 11 በ12 ሰዓት ፠ ቅዱስ ያሬድን ያልዘከረ ምኑን ካህን ኾነ? ፠ ቅ
+1
ዝክረ ቅዱስ ያሬድ ዘየካቲት እንደተለመደው በተለያዩ መርሐ ግብሮች የሚዘከር በመሆኑ እንዳያመልጥዎ፡፡ ቀንና ሰዓቱ፤ ረቡዕ የካቲት 11 በ12 ሰዓት ፠ ቅዱስ ያሬድን ያልዘከረ ምኑን ካህን ኾነ? ፠ ቅዱስ ያሬድን ያልዘከረ ሰንበት ተማሪ ምኑን ሰንበት ተማሪ ኾነ? ፠ ቅዱስ ያሬድን ያልዘከረ ክርስቲያን ምኑን ክርስቲያን ኾነ? ፠ ቅዱስ ያሬድን ያልዘከረ ኢትዮጵያዊ ምኑን ኢትዮጵያዊ ኾነ? የፍኖተ ሕይወት ሰ/ትቤት

#ሰበር_ዜና_ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ራሱን “የኦሮምያ ቤተ ክህነት” አደራጅ አድርጎ የነበረው ቡድን ሦስት አመራሮች ክህነታቸው እንዲያዝ እና ከማንኛውም መንፈሳዊ አገልግሎት እንዲታገዱ፣ በየአካባቢው የከፈቷቸው ጽሕፈት ቤቶች እንዲዘጉ እና በሕግ እንዲጠየቁ ውሳኔ አስተላለፈ። ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

/ከትናንቱ የቀጠለ……/ #ክፍል_፬ #ለየካቲት_12_የሰማዕታት_ቀን_መዳረሻ፥ #ለየካቲት_23_የአድዋ_ድል_መነሻ፥ #ለሚያዝያ_27_የድል_ቀን_ማስታወሻ_ #የካቲት_12 (#30_ #ሺህ_ኢትዮጵያውያን_ሰማዕታት_) (‹‹#የአካፋው_ሚካኤል››፤) ለሁለተኛ ጊዜ ሃገራችንን ልተወር በመጣችው የጣሊያን የጦር ሹም የነበረው ግራዚያኒን ለመግደል ጀግኖቹ አብርሃም ደቦጭና ሞገስ አስገዶም በጣሉት አደጋ ግራዚያኒ በመቁሰሉና አመራሮቹ በመሞታቸው የተቆጣው የጣሊያን ጦር በአዲስ አባባ በየካቲት 12/1929ዓ.ም. ለቅ/ሚካኤል ወርኋዊ በዓል በየቤተ ክርስቲያኑ የተገኙትን (ሔሮድስ ምጽዋት አደርጋለሁ ብሎ እንደሰበሰበው ጣሊያንም ለምጽዋት የተሰበሰቡትን ኢትዮጵያውያን ጨምሮ)ና በየቤቱ በመግባት 30 ሺህ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያንን በአሰቃቂ ሁኔታ በአካፋ ጭምር እንደ ቅጠል አረገፏቸው፤ 30ሺህ ሰማዕታት በመባልም ይታወቃሉ፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላም የደብረ ሊባኖስ ገዳም መነኰሳትን አርበኞችን ደብቃችኋል በሚል በተቀደሰው ስፍራ ተረሸኑ፡፡ በዚህም ምክንያት ጣሊያን ይህን አሰቃቂ ግፍ በአካፋ ጭምር ስትሠራና የሰማዕታቱን የከበረ አካል በአካፋ በመሰብሰቧ ‹‹#የአካፋው_ሚካኤል_›› በሚል መጠሪያ ይጠራል፡፡ በተለይም በ6 ኪሎ በመንበረ ልዑል ቅ/ማርቆስ የቅ/ሚካኤል ታቦተ ሕግ ወጥቶ በልዩ ሁኔታ ይከበራል፡፡ (እናት ቤ/ክ መቼውንም ቢሆን የሃገርና የቤ/ክ ባለውለታዎችን አትዘነጋምና!!!!) (እናቶቻችንና አባቶቻችን እንደነገሩን ከ6 ኪሎ የደብራችን አጥቢያ ምዕመን በቅርብ ርቀት የሚገኙ በመሆኑ፤ አያቶቻችን የተሠዉ እናዳሉና ግማሾቹም ይህንን ዜና ሲሰሙ ወደ 6 ኪሎ እየሄዱ ሳለ ሲሰሙ ከመንገድ የተመለሱ እንዳሉም ልብ ይሏል፡፡) ዐጤ ኀይለ ሥላሴም ወደ ሃገራቸው ከተመለሱ በኋላ በ6 ኪሎ ለሰማዕታቱ ሐውልት ቆመ መጀመሪያ የተሠራው አነስተኛ በመሆኑ ኋላ አሁን ያለው ትልቅ ተደርጎ ተሠርቷል፡፡ ቀኑ እንዳይረሳም #ቤተ_ሳይዳ ተብሎ ይጠራ የነበረው የካቲት 12 ሆስፒታል ተባለ፡፡ ቆይቶ ደግሞ በእቴጌ መነን ይጠራ የነበረው ትምህርት ቤትም የካቲት 12 ትምህርት ቤት በመባል ተሠየመ፡፡ ከ8 ዓመት በኋላም የሰማዕታቱንም ዐፅም ሰብስበውና አፍልሰው በ4ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በክብር እንዲያርፍና መቃብር ቤት እንዲሠራለት ተደረገ፡፡ በሐውልቱ ላይ ያለው ጽሑፍና ግጥም እንዲህ ይነበባል፤ #‹‹ዝንቱ ውእቱ ምዕራፈ አዕጽምቲሆሙ ለብዙኃን ኢትዮጵያውያን እለ ተቀትሉ በግፍዕ በእደዊሆሙ ለሕዝበ ኢጣሊያ ፋሽስታውያን አመ ፲ወ፪ ለየካቲት በ፲ወ፱፻፳ወ፱ ዓ.ም.፤ ወተቀትሎቶሙኒ ኮኑ በውግረተ አእባን ወበአብትር፥ በመክርይ ወበመስኤ፥ በመሕፄ ወበዕፀው፥ በመብረቀ ሐፂን ወበፀዓዕ፥ ወበውዕየተ እሳት ውስተ ቤቶሙ፡፡ ወበራብዕ ዓመት እምዘኮነ ዝንቱ ነገረ ግፍዕ ተመይጠ እግዚእነ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ እም ሀገረ ብሪታንያ በግርማ መዊዕ፤ ወአቲዎ ብሔሮሙ ሠረዎሙ ለጸላእትነ ወአቀመ ትእምርተ ግዕዛንነ፡፡ ወእምድኅረዝ አዘዞሙ ለኅሩያኒሁ ከመ ያስተጋብኡ አዕጽምቲሆሙ ለእሉ እለ ተቀትሉ በግፍዕ ወያንብርዎሙ ውስተ ዝንቱ መካን ቅዱስ ዘሕኑፅ ለዝክረ ነገር ወለዝክረ ስሙ፤ ወኮነ በዓለ ፍልሰቶሙ ወተጋብኦቶሙ ለእሙንቱ አዕጽምተ ምውታን በ፲ወ፬ ዓመተ በዓለ ንግሡ ለቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትየጵያ አመ ፳ወ፫ ለጥቅምት በዕለተ ኀሙስ በ፲ወ፱፻፴ወ፯ዓ.ም.፡፡›› #ራስን ካንገት ላይ ቈራርጦ እየጣለ፤ በችንካር ቸንክሮ ሰው እየገደለ፤ ሰውን ከነቤቱ አብሮ እያቃጠለ፤ ማነው እንደ ፋሽስት በሰው ግፍ የዋለ?፡፡ ሥጋችንን ገድለው ሳይቀብሩ እየጣሉ፤ ስማችንን ገድለው ሊቀብሩት ከጀሉ፡፡ በዚህ ያልነበሩ ሐሰት እንዳይሉ፤ እሊህ አስከሬኖች ይመሰክራሉ፡፡ ይህን ታላቅ ስቃይ መከራና ግፍ፤ ሲያስታውስ ይኖራል የታሪክ መጽሐፍ፡፡ አትርሱት አንርሳው ያስታውሰው ዘራችን፤ ኢጣሊያ መሆኗን መርዛም ጠላታችን፡፡ እናንት አእጽምቶች ዕድለኞች ናችሁ፤ በኃይለ ሥላሴ ትንሣኤ አገኛችሁ፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

/ከትናንቱ የቀጠለ……/ #ክፍል_፫ #ለየካቲት_12_የሰማዕታት_ቀን_መዳረሻ፥ #ለየካቲት_23_የአድዋ_ድል_መነሻ፥ #ለሚያዝያ_27_የድል_ቀን_ማስታወሻ_ (ከ1878-1888ዓ.ም.) #ከዓድዋ_በፊት_የነበሩ_8ቱ_አድዋዎች_፤ 2ኛ) ደጃች ደበብ፤ #ሰገነይቲ ላይ የተደረገ ውጊያ 3ኛ) ደጃች ባሕታ ሀጐስና ወንድማቸው አዝማች ሰንጋል፤ ከጄነራል ሳጎናይቲና ከተከታዩ ታንቲ ጋር ያደረጉት ውጊያ፡፡ ቀጥሎም ደጃች ባሕታና ዘመዳቸው ባሻይ ምስጉን የተሰዉበት #የሐላይ_መንደር_ ውጊያ፡፡ 4ኛ) ራስ መንገሻ ዮሐንስ #በኰዓቲት_ ከጥር 13-15 የተዋጉበት፤ ጦርነቱ የተራዘመና በርካታ ኢትዮጵያውያን የተሰዉበት፤ የሟች ቊጥር በመበርከቱ አሸናፊና ተሸናፊው ሳይለይ፤ የራስ መንገሻ ጦር ወደ ሰነዓፌ የተበተነበት፡፡ 5ኛ) የራስ መንገሻ ዮሐንስ የጦር አዝማቾች (እነ ተስፋይ ህንጣሎ አጋሜ፥ ወልደ ማርያም፥ ቀኛዝማች ኃይለማርያም ወምበርታ፥ ቀኛዝማች አብርሃ፥ ደጃች ረዳ አባ ጉብራ /የራስ አርአያ ልጅ/) መሪያችንን ራስ መንገሻን አናስነካም ብለው #በደብረ_አላ_ ላይ የተዋጉት ውጊያ፡፡ 6ኛ) ልዑል ራስ መኰንን (የኢትዮጵያ ጠቅላይ ጦር አዛዥና የሐረርጌ ገዥ /የአፄ ኃይለ ሥላሴ አባት/)፤ #አምባ_አላጌ ላይ ጣሊያንን እንደ ንብ ወረው ትልቅ ጀብድ የሠሩበትና ለአድዋውም ወኔ ቀስቃሽ ውጊያ፡፡ 7ኛ) ልዑል ራስ መኰንን፤ መቀሌ #እንዳ_ኢየሱስ (ዛሬ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ኢንጂነሪንግ ግቢ የሚገኝበት) ላይ፤ ቀድሞ በቦታው ላይ ጠላት ሸምቆ ስለበረ ዙሪያውን ከበው ስንቅ በማሳጣት መሪው ማጆር ጋሊያኖ ማሩኝ ለጄነራሌ ለባራታሪ ሂጄ ዕርቅ ይሆናል አስማማለሁ፤ ብሎ በዕርቅ ያለቀበት፡፡ (ኋላ ግን ማጆር ጋሊያኖ ቃሉን በማጠፉና ጣሊያንን ለጦርነት በማነሳሳቱ የአድዋ ጦር ሁኗል፡፡) 8ኛ) ራስ ስብሐትና ደጃች ሐጐስ ተፈሪ (ቀድሞ ባንዳ ነበሩ) ማጆር ጋሊያኖ ለጄነራሉ ከማስማማት ይልቅ ጠብን በመምከሩና የጣሊያን ጦር በእንትጮ በኩል ከኢትዮጵያ ጋራ ሊዋጋ ሲገሰግስ የአካለ ጉዛይን ባላሃገር በማስተባበር #እንትጮ ላይ ደጀን ሁነው መክተው የተዋጉት ውጊያ፡፡ 9ኛ) #አድዋ፥ #ሶሎዳ፡፡ (በየካቲት 23 ይጠብቁ) ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

/ከትናንቱ የቀጠለ……/ #ክፍል_፪ (ከ1878-1888ዓ.ም.) #ከዓድዋ_በፊት_የነበሩ_8ቱ_አድዋዎች_፤ ፩ኛ) #ራስ_አሉላ_ነጋ_ (የዐፄ ዮሐንስ ጦር አበጋዝና የሐማሴን ባላባት)፤ #ዶጋሊ_ ላይ ጠላትን ድባቅ በመምታት ወደ ምጽዋ የመለሰበት፡፡ #ለየካቲት_12_የሰማዕታት_ቀን_መዳረሻ፥ #ለየካቲት_23_የአድዋ_ድል_መነሻ፥ #ለሚያዝያ_27_የድል_ቀን_ማስታወሻ_ #የአውሮፓውያን_አፍሪካን_መቃራመት፡፡ የአውሮፓ ኃያላን ሃገር ነን ብለው ራሳቸውን የሰየሙ አፍሪካን ሊቀራመቱ በተስማሙት መሠረት ጣሊያን ኢትዮጵያን ልትቀራመት ወሰኑ፡፡ ለዚህም ውሳኔ ያደረሳቸው ከሚስዮኖቿ አንዱና ተኩላው አባ ማስያስን (የጣሊያ ንጉሥ የቪክቶሪ ንስሐ አባትን ቀድሞ በትንሹ ራስ ዐሊ ዘመን ወደ ኢትዮጵያ የገባው) በአፄ ቴዎድሮስ ተባሮ፤ እንደገና በአፄ ዮሐንስ ዘመን ወደ ሃገራችን ገብቶ ነበር፤ አሁንም መልሰው አፄ ዮሐንስ ሲያብርሩት ለጣሊያን መንግሥት የኢትዮጵያን ልዩ መልክአ ምድሮችና በዓለም ላይ ልዩ ሃገር መሆኗን 2ት መጻሕፍት ጽፎ ለጣሊያን መንግሥት በማስረከቡ በዚሁ መሠረት ጣሊያኖች በመቋመጣቸው ነው፡፡ #የጣሊያን_የመጀመሪያው_ወረራና_ጦርነት ጣሊያን መጀመሪያ በ1861ዓ.ም. እግሯን ወደ ኢትዮጵያ በአሰብ በኩል አስገባች፤ በ17ዓመታት ቆይታ (እስከ 1878ዓ.ም.) ምጽዋን፣ የዳህላክ ደሴቶችንና የኤርትራን ቀይ ባሕር ያዘች፡፡ ምጽዋን በያዘች በ3ት ዓመታት ኤርትራን ያዘች፤ ኤርትራን በያዘች በ7 ዓመት መረብን ተሻግራ ወደ ሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች በመግባት ጦርነት ከፈተች፡፡ ከኤርትራ ሲሻገሩ መጀመሪያ ጦርነት ያደረጉት በ1887ዓ.ም. በወርኃ ጥር በዶጋሊ ከአጼ ዮሐንስ ጦር አበጋዝና ከሐማሴኑ ባላባት ከጀግናው #ራስ_አሉላ_አባ_ነጋ ጋር ነው፡፡ ጀግናው ራስ አሉላ አባ ነጋም ጠላትን ድል በማድረግ ወደ ምጽዋ መልሰውታል፡፡ ፠ ለራስ አሉላ አባ ነጋም እንዲህ ተብሎ ተግጠሞላቸዋል፡፡ ‹‹የአሉላ ፈረስ የረገጣቸው፤ እስካሁን ድረስ አለ ቊስላቸው፡፡ የአሉላ ፈረስ ተስቦ ወርዶ፤ ያንን ነጭ ገብስ አረገው ነዶ፡፡›› ይህ አልሆን ሲላቸው በተወካያቸው በአንቶኔሊ በሚያዝያ 25/1881ዓ.ም. በውጫሌ (ወሎ ቦሩ ሜዳ የምትገኝ) ላይ የተፈረመውን የውል ስምምንት አንቀጽ 17 በአማርኛና በጣሊያንኛ ቅጂው የተሳሳተ (የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ከውጭ ሃገራት ጋር የሚያደርገውን ግንኙነት በኢጣልያ በኩል ማድረግ ይገባዋል!!፡፡›› አድርገው አንቀጹን አሰፈሩ፡፡ በየካቲት 1885ዓ.ም. ዐጤ ምኒልክ የውጫሌ ውል እንደማይሠራ ለአውሮፓ መንግሥታት ደብዳቤ ጻፉ፡፡ በዶጋሊ የተሸነፉትና በውጫሌ ውል አልሆን ያላቸው ጣሊያን በኅዳር 29/1888ዓ.ም. ጦርነት ከፈቱ ጀግኖች ኢትዮጵያኖችም ሻለቃ ቶዘሊንና ሌሎች ፋሽስቶችን እንደ ነፋስ ትቢያ አድርጎ በተናቸው፡፡ ቀጥለውም በየካቲት 23/1888ዓ.ም. ጠዋት 12 ሰዐት አመሻሽ 12 ሰዐት ባለቀው፤ እንኳን ለኢትዮጵያውያን ይቅርና ለአፍሪካውያን ኩራትና የጀግንነት ተምሳሌት የሆነው የአድዋ /የሶሎዳ ተራራ/ ጦርነት በጀግናው መሪ በዐጤ ምኒልክ ድል አድራጊት ተጠናቀቀ፤ ጣሊያንም የሽነፈት ጽዋዋን ጠጥታ ተመለሰች፡፡ ዐጤ ምኒልክም ሚያዝያ 15/1889ዓ.ም. ወደ መናገሻ ከተማቸው ሲመለሱ የማረኳቸወን ጣሊያኖች ዛሬ ‹‹ጣሊያን ሰፈር›› በሚባለው ቦታ አኖሯቸው፡፡ ‹‹የአዲስ አበባ ውል›› ተብሎ በሚጠራው በኢትዮጵያና በጣሊያን በተደረገው ስምምነት ኢትዮጵያ ምርኮኞቹን እንድትፈታ፤ የውጫሌ ውል መሠረዙና፣ ኢጣሊያ በኢትዮጵያ ላይ ጣልቅ እንዳትገባ፤ የኤርትራ ድበር እስኪከለል ጣሊያን ከጦርነቱ በፊት ባለችበት እንድትረጋ በሚል ተከናወነ፡፡ (ስለ አድዋ ድል ዝርዝሩን በየካቲት 23 እንዘግበዋለን) /ክፍል ፫ትን ለነገ ይጠብቁ፡፡/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

ሰኞ የካቲት 9 የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትና ብፁዓን ወቅዱሳን ፓትርያርኮች የሚያደርጉትን የሲኖዶስ ስብሰባ፤ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ እንደ ቸርነቱ በመልካሙ መንገድ እንዲመራቸው፤ መልካሙንም እንዲያሰማን፤ ሁላችንም በየአጥቢያችን በሚገኙ ገዳማትና አድባራት ጸሎት እንድናደርስ ይሁን።

#ዐርብ_የካቲት_6፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት #የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፲፡፡ Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡ ፠ ለምን እንፈተናለን፤ ፠ ፈተናዎች ለምንና እንዴት ይመጣሉ፤ ፠ ፈተናዎችን እንዴት አድርገን ድል እናድርጋቸው፤ …. ፠ ……እንዳያመልጣችሁ፤ በሌሎችም ርዕሶች ዙሪያ በብዙ ጕባኤያት ላይ ያልተዳሰሱ ርዕሶች የሚዳሰሱበት ጕባኤ ስለሆነ እንዳያመልጣችሁ፤ #ደግመን_እንላለን_ይህ_ትምህርት_በፍጹም_እንዳያመልጣችሁ!!!!! ለተከታታይ ሳምንታት፤ ትምህርቱ ተከታታይነት ስላለው መቅረትና ማርፈድ አይመከርም!!፡፡ (፻፷ኛ ሳምንት የዐርብ ጕባኤ) #ዐርብ_የካቲት_፮፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት አሁንም በድጋሚ እንላለን ለሕይወታችን ወሳኝና በብዙ የትምህርት ጕባኤያት ላይ የማይዳሰሱ ትምህርቶች ስለሆኑ እንዳያመልጣችሁ!!!! የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ለየካቲት_12_የሰማዕታት_ቀን_መዳረሻ፥ #ለየካቲት_23_የአድዋ_ድል_መነሻ፥ #ለሚያዝያ_27_የድል_ቀን_ማስታወሻ_ ክፍል ፩ (ውድ ተከታታዮቻችን ከዛሬ ጀምሮ ለ7ት ቀናት በ7ት ክፍሎች የየካቲት 12
+6
#ለየካቲት_12_የሰማዕታት_ቀን_መዳረሻ፥ #ለየካቲት_23_የአድዋ_ድል_መነሻ፥ #ለሚያዝያ_27_የድል_ቀን_ማስታወሻ_ ክፍል ፩ (ውድ ተከታታዮቻችን ከዛሬ ጀምሮ ለ7ት ቀናት በ7ት ክፍሎች የየካቲት 12ትንና ተያያዥ ታሪኮችን እናቀርብላችኋለን) ‹‹#የአካፋው_ሚካኤል››፤ #የካቲት_12 (#30 #ሺህ_ኢትዮጵያውያን_ሰማዕታት_) ለሁለተኛ ጊዜ ሃገራችንን ልተወር በመጣችው የጣሊያን የጦር ሹም የነበረው ግራዚያኒን ለመግደል ጀግኖቹ አብርሃም ደቦጭና ሞገስ አስገዶም በጣሉት አደጋ ግራዚያኒ በመቁሰሉና አመራሮቹ በመሞታቸው የተቆጣው የጣሊያን ጦር በአዲስ አባባ በየካቲት 12/1929ዓ.ም. ለቅ/ሚካኤል ወርኋዊ በዓል በየቤተ ክርስቲያኑ የተገኙትን (ሔሮድስ ምጽዋት አደርጋለሁ ብሎ እንደሰበሰበው ጣሊያንም ለምጽዋት የተሰበሰቡትን ኢትዮጵያውያን ጨምሮ)ና በየቤቱ በመግባት 30 ሺህ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያንን በአሰቃቂ ሁኔታ በአካፋ ጭምር እንደ ቅጠል አረገፏቸው፤ 30ሺህ ሰማዕታት በመባልም ይታወቃሉ፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላም የደብረ ሊባኖስ ገዳም መነኰሳትን አርበኞችን ደብቃችኋል በሚል በተቀደሰው ስፍራ ተረሸኑ፡፡ በዚህም ምክንያት ጣሊያን ይህን አሰቃቂ ግፍ በአካፋ ጭምር ስትሠራና የሰማዕታቱን የከበረ አካል በአካፋ በመሰብሰቧ ‹‹#የአካፋው_ሚካኤል_›› በሚል መጠሪያ ይጠራል፡፡ በተለይም በ6 ኪሎ በመንበረ ልዑል ቅ/ማርቆስ የቅ/ሚካኤል ታቦተ ሕግ ወጥቶ በልዩ ሁኔታ ይከበራል፡፡ (እናት ቤ/ክ መቼውንም ቢሆን የሃገርና የቤ/ክ ባለውለታዎችን አትዘነጋምና!!!!) (እናቶቻችንና አባቶቻችን እንደነገሩን ከ6 ኪሎ የደብራችን አጥቢያ ምዕመን በቅርብ ርቀት የሚገኙ በመሆኑ፤ አያቶቻችን የተሠዉ እናዳሉና ግማሾቹም ይህንን ዜና ሲሰሙ ወደ 6 ኪሎ እየሄዱ ሳለ ሲሰሙ ከመንገድ የተመለሱ እንዳሉም ልብ ይሏል፡፡) /ክፍል ፪ትን ለነገ ይጠብቁ፡፡/

ልዩ ጕባኤ ፤ በተባበሩት ዐረብ ኢምሬትስ ይኖሩ የነበሩ ምዕመናን በኢትዮጵያ የማኅበር ምሥረታ፡፡ ቦታ፤ በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን፡፡ ቀን፤ እሑድ የካቲት ዓ.ም. ከጠዋቱ ሰዐት ጀምሮ
+2
ልዩ ጕባኤ ፤ በተባበሩት ዐረብ ኢምሬትስ ይኖሩ የነበሩ ምዕመናን በኢትዮጵያ የማኅበር ምሥረታ፡፡ ቦታ፤ በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን፡፡ ቀን፤ እሑድ የካቲት ዓ.ም. ከጠዋቱ ሰዐት ጀምሮ፡፡ ለበለጠ መረጃ፤ 0933 316729 /0904 132782/ 0910 293447