ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 380 подписчиков, занимая 5 588 место в категории Религия и духовность и 2 193 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 380 подписчиков.

Согласно последним данным от 10 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 43, а за последние 24 часа — -3, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 23.36%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.42% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 592 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 449 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 23.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 11 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 380
Подписчики
-324 часа
-27 дней
+4330 день
Архив постов
እንደ መድኀኔ ዓለም ፈቃድ፤ ልዩ መርሐ ግብር ስለሚኖር እንዳያመልጥዎ፤ የጽጌ ሥርዐተ ማኅሌት እንደተለመደው በጕባኤው ላይ ይታደላል፡፡ #የዐርብ_ጕባኤ_፻፵፯ኛ_ሳምንት #መስከረም_፴/፳፻፲፪ዓ.ም. ከ፲
እንደ መድኀኔ ዓለም ፈቃድ፤ ልዩ መርሐ ግብር ስለሚኖር እንዳያመልጥዎ፤ የጽጌ ሥርዐተ ማኅሌት እንደተለመደው በጕባኤው ላይ ይታደላል፡፡ #የዐርብ_ጕባኤ_፻፵፯ኛ_ሳምንት #መስከረም_፴/፳፻፲፪ዓ.ም. ከ፲፪-፪ ሰዓት፤ #በሰዐቱ_ይገኙ!!!!!!!! እንዳያመልጥዎ!! በታላላቅ ገዳማት የሚጸለየው #የመሐረነ_አብ ጸሎት ይደርሳል፡፡ ላልሰሙት ያሰሙ፤ <<Like, Share>> በማድረግ ይተባበሩ /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት፡፡/

#ነግሥ_ነግሥ_ነግሥ እንኳን ለወርኃ ጽጌ በሰላምና በጤና አደረሰን፥ አደረሳችሁ፡፡ በማንኛውም ወርኀዊና ዓመታዊ ክብረ በዓላት ላይ ማኅሌተ ጽጌን ጨምሮ ማኅሌት ሲቆም፤ መጀመሪያ የሚባለውን ነግሥንና የ
+6
#ነግሥ_ነግሥ_ነግሥ እንኳን ለወርኃ ጽጌ በሰላምና በጤና አደረሰን፥ አደረሳችሁ፡፡ በማንኛውም ወርኀዊና ዓመታዊ ክብረ በዓላት ላይ ማኅሌተ ጽጌን ጨምሮ ማኅሌት ሲቆም፤ መጀመሪያ የሚባለውን ነግሥንና የነግሥ መቅድምን እነሆ፡፡ *ነግሥ ምን ማለት ነው *ዚቅ ምን ማለት ነው *የነግሥ መቅድምና ነግሥ ቀመረ መረግድ፤ (ማንኛውም ማኅሌት ሲቆም ባለ 5 መስመር ግጥም ሲሆን እያንዳንዱ መስመር 28ት ጊዜ በከበሮና በጸናጽል ይመረገዳል ፤ የአመረጋገዱን ቅደም ተከተል እንዲቀላችሁ በማሰብ በቀመር (በቊጥር አስቀምጠንላችኋል፡፡) ….. ከጽሑፉ ያገኟቸዋል፡፡ ይህን ነግሥ በሁሉም ማኅሌት መጀመሪያ የሚባል እንደመሆኑ መጠን በቃላችሁ አጥኑት፡፡ /ፎቶ፤ HYPERLINK "https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/" የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

እንኳን ለቅድስት አርሴማ ዓመታዊ ክብረ በዓል (በዓለ ዕረፈት) አደረሰን፥ አደረሳችሁ፡፡ በዚህች በመስከረም 29 ቀን አርሴማ ቅድስት ወሰማዕት እና የእርሷ ማኅበርተኞች ድል አድራጊዎች 27 ሰማዕታት በሰማዕትነት ያረፉባት ዕለት ነች፡፡ እግዚአብሔር ከእነዚህ ቅዱሳን ሰማዕታት ረድኤት በረከታቸውን ይክፈለን፡፡ እነዚህም ቅዱሳን፤ 1ኛ. #አርሴማ፤ #ቅድስት_ወሰማዕት_ኃያል_ተጋዳሊት_ 2ኛ. ኢያሚኖስ፤ ጸሎትን የሚያሳርግ ካህን 3ኛ. አፍጢኖስ፤ ከብዙዎች የተመረጠ 4ኛ. በርቲኖስ፤ ጻድቅና ቸር 5ኛ. ጢሞና፤ በመላላክ ሥራ አገልጋይ የኾነ 6ኛ. ጢሞዓና፤ ተአጋሽና ጸዋሚ 7ኛ. ዘኬዎስ፤ ከከበሩ የከበረ 8ኛ. እስጢፋኑ፤ ተጋዳይና የበደሉትን ይቅር ባይ 9ኛ. አርሞና፤ ከጎልማሶች ይልቅ ደም ግባቱና መልኩ ያማረ 10ኛ. ኪርያኮስ፤ ሥጋውን ያላረከሰ ንጹሕ 11ኛ. አንጥያኮስ፤ ቡሩክ የኾነ የአቡሪ ልጅ 12ኛ. ያዕቆብ፤ የእግዚአብሔር ታማኝ የኾነ 13ኛ. ቡራኬሌስ፤ በሰው ዘንድ ተወዳጅ የኾነ 14ኛ. አስቂርያቆስ፤ ክርስቶስን የሚወደው 15ኛ. አስኪርያኖስ፤ ባለሟል የኾነና ግርማው የሚያስፈራ 16ኛ. ሚርያኖስ፤ ፊቱና መልኩ ደስተኛ የኾነ 17ኛ. ትትግርጦስ፤ ወደ ንስሐ የተመለሰ 18ኛ. ያስቲኖስ፤ የሚፈርድና የሚበይን 19ኛ. ጥልያኖስ፤ ያላመኑ ሰዎችን የሚገስጽ 20ኛ. ዑልያኖስ፤ የዚህ ዓለም ጥበብ መምህር የኾነ 21ኛ. ጴርቅላስ፤ በስም አጠራርና በሽምግልና መልካም የኾነ 22ኛ. ኬብያኖስ፤ ተጋዳይ የኾነ 23ኛ. ጴጥሮስ፤ የጠራ የባሕርይ ዕንቊ 24ኛ. ጰኵንዮስ፤ የሮምያ ሹም 25ኛ. ሐናንያ፤ የዋህና ሽንገላ የሌለው 26ኛ. ሐሊባኖስ፤ ጾምና ጸሎትን የሚወድ 27ኛ. ኤስያኖስ፤ በመንፈስ ቅዱስ ጎልማሳ የኾነ 28ኛ. ኤልያብ፤ በረኛና የሰማዕት መጀመሪያ፡፡ ሰላም ለፀዐተ ነፍስኪ በጊዜ ኃለፈ ሰይፍ፤ መንገለ ክሣድኪ ድኑን ለአምሳለ መሥዋዕት ውኩፍ፡፡ እስእለኪ አርሴማ በከናፍር ወአፍ፤ ረድኤትኪ ትሩፍ በላዕሌየ ያንጸፈጽፍ፤ እስመ አርአየኒ ዘንተ ሞትኪ ትሩፍ፡፡ ሰላም ለዘአዕረፉ ምስሌኪ ፳ወ፯ቱ ሰማዕታት፤ ረድኤቶሙ ትረድ ላዕሌየ ዘምስለ ብዙኅ ምሕረት፡፡ ወኀበ ሀለወ ስሞሙ ምስለ ስምኪ ቅድስት፤ ዓዲ ኢይቅረብ አርሴማ ሕማመ ብድብድ ወሞት፤ በኵሉ አዝማን ወበኵሉ ዓመታት፡፡ /ፎቶ፤ HYPERLINK "https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/" የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

መድኀኔዓለም ተወከፍ እንተ አቅረብኩ ንስቲተ፤ ዘሰተይከ በእንቲአየ ከርቤ ወሐሞተ፤ በሞተ ዚአከ ከመ ትቅትል ሞተ፡፡ ትርጕም፤ ፈጣሪዬ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ሆይ ፤ በሞትህ ሞትን ታጠፋው ዘንድ ከርቤ
+3
መድኀኔዓለም ተወከፍ እንተ አቅረብኩ ንስቲተ፤ ዘሰተይከ በእንቲአየ ከርቤ ወሐሞተ፤ በሞተ ዚአከ ከመ ትቅትል ሞተ፡፡ ትርጕም፤ ፈጣሪዬ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ሆይ ፤ በሞትህ ሞትን ታጠፋው ዘንድ ከርቤ የተቀላቀለበትን መራራ ሐሞትን ስለኔ ሕይወት የጠጣህ የአቀረብኳትን አነስተኛ የምስጋና መባ በቸርነትህ ተቀበል፡፡ (መልክአ መድኀኔ ዓለም ለዝክረ ስምከ) ፎቶዎቹ፤ ፩ኛ) መ.መ.መ. (መንበረ መንግሥት መድኀኔ ዓለም /ጎንደር/) ፪ኛ) ደ.ቀ.መ. (ደብረ ቀራንዮ መድኀኔ ዓለም) ፫ኛ) ቀ.ደ.ሰ. (ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም) /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

✤✣✤#ገዳመ_ጽጌ_ድግል_፤ የአቡነ ጽጌ ድንግል ገዳም በ14ኛው ክፍለ ዘመን የተመሠረተው በታላቁ አባት በአቡነ ጽጌ ድንግል ሲኾን፤ እኝህ ታላቅ አባት እጅግ ሰፊ ኾኖ የሚያምረውንና ዕጹብ ድንቅ የሚያሰኘውን ባለሦስት ክፍል (ቅኔ ማሕሌት፣ ቅድስትና መቅደስ) ያለውን የገዳመ ጽጌን ውቅር ዋሻ ቤተክርስቲያን ያነጹ፣ ከሰባቱ ቅዱሳን ዘጋሥጫ (አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ዘደብረ ጎል፥ አቡነ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፥ አቡነ ያዕቆብ ዘቀዳሚት ግሸን ደብረ ከርቤ፥ አቡነ ገብረ እንድርያስ ዘደብረ ቆዘት፥ አቡነ ዘካርያስ ዘወለቃ፥ አቡነ ዮሴፍ ዘወለቃ፥ የዝቋላው አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዘምስካበ ቅዱሳን ገዘዛ) አንዱ የኾኑና የወርቃማ ዘመን ወርቃማ ደራሲ የኾኑ በዚህም በቤተክርስቲያናችን ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፮ የምንጸልይበትንና የምናመሰግንበትን ማሕሌተ ጽጌን ባለ ፭ት አርኬና እንደ መዝሙረ ዳዊት በ፻፶ መዝሙር ልክ አድርገው የደረሱና ጸሐፊያቸው በኾኑ ጓደኛቸው አቡነ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሐንታ አጽፈው ለትውልድ ያስተላለፉ፤ እንዲሁም ሰቈቃወ ድንግልን ከጓደኛቸው አቡነ ገብረ ኢየሱስ ዘገዳመ መጕና ጋር አብረው የደረሱ ቅዱስ አባት ናቸው፤ እንዲሁም በዘመናቸው ከነበሩት ከጓደኛቸው ከታላቁ አባት አቡነ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ጋር ብዙ ገቢረ ተዓምራትን የሠሩ (የወለቃ ወንዝ ድልድይን ጨምሮ ያነጹ)፥ አሁንም ብዙ ገቢረ ተዓምራትን የሚሠሩ አባት ናቸው፡፡ ገዳሙ የሚገኘው በደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ በወግዲ ወረዳ ልዩ ስሙ ደብረ (ገዳመ) ጽጌ ጫቀታ በሚባል ቦታ፤ ለዐባይ ወንዝ ገባሮች ከኾኑትና በበረሀ ውስጥ ከሚጓዙት አንዱ በኾነው በወለቃ ወንዝ አቅራቢያ ነው፡፡ ገዳሙ ለታላቁ አባት በተሰጠው ቃል ኪዳን መሠረትም አኹንም ድረስ ፈውሰ ሥጋ፥ ፈውሰ ነፍስ እየሰጠ ይገኛል፤ የገዳሙ ፍየሎችና ከብቶችም በአካባቢው ከሚገኙት ነብሮች ጋር አብረው ያለምንም አደጋ ይኖራሉ፡፡ ገዳሙ በግራኝ መሐመድ ወረራ ወቅት 500 መነኰሳት በሰማዕትነት የተሰየፉበት ሲኾን ከዚህ ጀምሮ እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ተዘግቶ ቆይቶ በልዑል ራስ ካሣ ኀይሉ አማካይነት ተከፍቶ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፤ በድጋሚ በጣሊያን ወረራ ወቅት አደጋ ደርሶበታል፤ በደርግ ዘመንም የገዳሙ 84 ጋሻ መሬት ስለተወሰደበት እንደገና እስከ ከ1995ዓ.ም. ገዳሙ ዘግቷል፤ ነገር ግን በ1995ዓ.ም. በበጎ አድራጊ ምዕመናን ድጋሚ ሊከፈት ችሏል፡፡ ማሕሌተ ጽጌ የተደረሰበት ይህ ገዳም እስከ 2008ዓ.ም. ማሕሌቱ ሳይቆምበት ቆይቶ ከ2009 ዓ.ም. ጀምሮ ማሕሌቱ እየተቆመ ይገኛል፡፡ ለበርካታ ዓመታት የሊቁ የአባ ጽጌ ድንግል በዓለ ዕረፍት መስከረም 27 መከበር አቁሞም ነበር፤ እንደ አምላከ አበው ፈቃድ ከ2011 ዓ.ም. ጀምሮ ክብረ በዓሉ በገዳም ሥርዐት እየተከበረ ይገኛል፡፡ ወደ ገዳሙ ለመሄድ ለሚፈለጉ ምዕመናን፤ (በተለይ ወደ ግሸን ደብረ ከርቤ የተጓዛችሁ በዛው ለመሄድ ቅርብ ነው፡፡) 1ኛ) ከደሴ ከተማ ለምትነሱ ወግዲ በሚል መኪና ከተሳፈሩ በኋላ ከተወሰኑ የእግር ጕዞ በኋላ ይገኛል፤ 2ኛ) ከጎጃም በመካነ ሰላም ለምትነሱ ወግዲ በሚል መኪና ከተሳፈሩ በኋላ ከተወሰኑ የእግር ጕዞ በኋላ ይገኛል፤ 3ኛ) በመርሐ ቤቴ በሚዳ ለምትነሱ ወግዲ በሚል መኪና ከተሳፈሩ በኋላ ከተወሰኑ የእግር ጕዞ በኋላ ይገኛል፡፡ † በዚሁ አጋጣሚ የታለቁ ሊቅ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በዓለ ጽንሰታቸውም ጥቅምት 3 ስለሚከበር አብሮ ማክበር ይቻላል፡፡ /ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/ (የገዳሙን ኹኔታ የዘገበልንን ወንድማችንን አምላከ አባ ጽጌ ድንግል ወጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ይስጥልን፤ በረድኤት በበረከት ቅዱሳን ሊቃውንቱ ይጎብኙልን፡፡)

✤✤#መስከረም_27_ሊቁ_አባ_ጽጌ_ድንግል (#ጽጌ_ብርሃን)፤ #የማኅሌተ_ጽጌ_ደራሲ¬ ✤✤ የተወለደው በ14ኛው መ.ክ.ዘ. በሰሜን ሸዋ በይፋት(ዊፋት) አውራጃ ውስጥ ሲሆን፤ ነገዱ ታቦተ ጽዮንን ይዘው ከመጡት ከ318 ሌዋውያን ነው፡፡ የቀድሞ እምነቱ አይሁዳዊ ሲኾን ስሙም ዮሐኒ ይባል ነበር፡፡ በወጣትነት ዕድሜው አውሬ ለማደን በይፋት አውራጃ በምትገኝ ልዩ ስሟ ገዳመ ደነስ ወደሚባል ዱር (ጫካ) ሄደ፤ በጫካዋ ውስጥም ፊቷ በጽጌረዳ አበባ የተከበበና ያጌጠ፣ እጅግም ደስ የምታሰኝ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ሥዕል አይቶ በሥዕሏ ውበት እየተደነቀ ሲመለከት እንደ እርሱ ያልተጠመቀ አይሁዳዊ ጓደኛው መጥቶ፣ ‹‹ምን እየፈለግህ ነው? የክርስቲያኖችን ሥዕል ነውን?›› ብሎ ለድንግል ማርያም ምስጋና ይግባትና በያዘው በትር ሥዕሏን ሲመታት ወዲያው ተቀሥፎ ሞተ፣ ከዚህ በኋላ ቅዱስ ሩፋኤል በነጭ ወፍ ተመስሎ አንድ መነኵሴ እሰኪመጣ ድረስ፣ ይህችን ሥዕል ጠብቃት ብሎ በሰው አነጋገር ነግሮት ተሠወረ፣ አቡነ ዜና ማርቆስ ደብረ ብስራት ከሚባለው ገዳሙ ወደ ይፋት መጥቶ ከነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት በምዕ. 11፥1 ‹‹ትወጽእ በትር እምሥርወ እሴይ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ (ከዕሤይ ግንድ በትር ትወጣለች /ትገኛለች/ ከሥሩም ቁጥቋጦ ያፈራል››) እያለ ሲያነብ አባ ጽጌ ድንግል በሰማ ጊዜ አባቶቼ አይሁድ የነቢያትን ትንቢት ንባቡን አስተምረውኛል አውቀዋለሁ፤ ትርጕሙን ግን አላውቀውምና ተርጕምልኝ አለው፡፡ አቡነ ዜና ማርቆስም ሲተረጕምለት እንዲህ አለ፤ ፠ትወጽእ በትር እምሥርወ እሴይ፣ የሚለው ከእሴይ ነገድ የሕይወት በትር የኾነች ድንግል ማርያም ትወለዳለች፡፡ ፠ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ የሚለው ንባብ ደግሞ፤ ከእመቤታችን ጌታችን በድንግልና ይወለዳል፤ ጌታችንም ተወልዶ ትንቢቱ ተፈጽሟል ብሎ ተረጐመለት፡፡ ኢሳ. 7፥14፣ ማቴ. 18፥24፡፡ ይህ ሰውም (አባ ጽጌ ድንግልም) በዚህ ትርጕም ደስ ተሰኝቶ አባት ሆይ በመልካም ሁኔታ ተረጐምከው አለውና፣ ሥዕሏ ወዳለችበት ቦታ ወስዶ ታሪኩ ከላይ የተገለጸውን ሁሉ ነገረው፣ አቡነ ዜና ማርቆስም ከሥዕሏ የተደረገውን ተአምር ሰምቶ፣ እጅግ ደስ አለውና አስተምሮ አጥምቆ #ጽጌ_ብርሃን_ ብሎ ሰየመው፡፡ ከዚህ በኋላ ሥዕሏን ከገዳመ ደንስ ደብረ ብሥራት ወደሚባል ገዳሙ ወስዶ በዘመነ ጽጌ ጥቅምት አንድ ቀን በክብር አስቀመጣት የምትከብርትንም ቀን ጥቅምት 3 እና ሰኔ 8 ቀን አደረገ፡፡ አቡነ ዜና ማርቆስም ጽጌ ብርሃንን ለመዓርገ ምንኵስና አበቃው፤ አባ ጽጌ ድንግል ምንም እንኳን አስቀድሞ ብሉያትን ቢማርም ከአቡነ ዜና ማርቆስ ዘንድ ብሉያትንና ሐዲሳትን ንባባቸውን ከነትርጓሜያቸው ተማረ፡፡ አባ ጽጌ ድንግል ከሰባቱ ቅዱሳን ዘጋሥጫ (አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ዘደብረ ጎል፥ አቡነ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፥ አቡነ ያዕቆብ ዘቀዳሚት ግሸን ደብረ ከርቤ፥ አቡነ ገብረ እንድርያስ ዘደብረ ቆዘት፥ አቡነ ዘካርያስ ዘወለቃ፥ አቡነ ዮሴፍ ዘወለቃ) አንዱ የኾኑና ገባሬ ተዓምራት ወመንክራት የኾኑ የወርቃማ ዘመን ወርቃማ ደራሲ ናቸው፡፡ በወርቃማ ደራሲነታቸው ማኅሌተ ጽጌንና ሰቈቃወ ድንግልን ደርሰዋል፡፡ ሊቁ ሲደርሱም ዋርማ (ሽክና) ሙሉ እንባን እያነቡ ባነቡት እንባ ቀለም እየበጠበጡ እርሳቸው እየደረሱ፤ ጸሓፊያቸውና ጓደኛቸው የኾኑት አባ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሐንታ ደግሞ እየጻፉ ነው፡፡ #ማኅሌተ_ጽጌ_ እመቤታችንንና ፈጣሪ ልጇን በጎ፥ በጎ መዓዛ ባላቸው አበባዎችና ፍሬዎች እየመሰለ የሚያመሰግን ሲኾን፣ በአባቷ በዳዊት መዝሙር መጠን 150 አድርጎ ደረሶታል፤ ፍሬ ከአበባ አበባም ከፍሬ እንደሚገኝ ኹሉ በማኅሌተ ጽጌ እመቤታችንን በአበባ፥ ጌታችን በፍሬ፤ ወይም እመቤታችንን በፍሬ፥ ጌታችንን በአበባ እየመሰለ እጅግ አስደናቂ የሆኑ ታሪኮችን እያጣቀሰ ደርሶታል፡፡ ዘመነ ጽጌ ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 5 ድረስ 40 ቀናት ሲኾን በዚህ ወቅት የሚጾመው ጾም ጾመ ጽጌ ሲባል ጾሙ የፈቃድ ነው፡፡ #ሰቈቃወ_ድንግል፤ ማለት እመቤታችን ከልጇ ከመድኀኔዓለም፥ ከአረጋዊ ዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር በስደቷ ወቅት ያየችውን መከራ፥ ልቅሶ፥ ዋይታ የሚዘከርበት የማኅሌተ ጽጌ አርኬ ነው፡፡ የሰቈቃወ ድንግልን ደራሲ በተመለከተ አባ ጽጌ ድንግል ደረሱት የሚሉ አሉ፤ በሌላ በኩል ደግሞ አባ ገብረ ኢየሱስ ዘገዳመ መጕና ወይም /አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ/ ወይም /አባ አርከ ሥሉስ/ ነው የደረሱት የሚሉም አሉ፡፡ በገቢረ ተዓምራት አድራጊነታቸውም እንደ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በአየር ላይ የሚጓጓዙት በክነፈ ነፋስ፥ በሠረገላ እሳት፥ በደመናት፥ በመባርቅትና በነጐድጓድ ሲኾን በምድር ላይ ደግሞ በአንበሳና በነብር ተጭነው እንዲሄዱ ጸጋው ተሰጥቷቸው ነበር፡፡ በዘመናቸው ከነበሩት ከጓደኛቸው ከታላቁ አባት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ጋር ብዙ ገቢረ ተዓምራትን የሠሩ ሲኾን የእግዜር ድልድይ (የወለቃ ወንዝ ድልድይን) ያነጹ፥ ብዙ ድውያንና ሙታንን አብረው ያስነሱ ናቸው፤ አሁንም ብዙ ገቢረ ተዓምራትን የሚሠሩ አባትም ናቸው፡፡ ገዳሙ የተመሠረተው በአባ ጽጌ ድንግል ሲኾን፤ እጅግ ሰፊ ኾኖ የሚያምረና ዕጹብ ድንቅ የሚያሰኝ ባለአራት ክፍል (ቅኔ ማኅሌት፣ ቅድስትና መቅደስ፣ አጽመ ቅዱሳን ማረፊያ) ያለው ነው፡፡ የሚገኘውም በደቡብ ወሎ ወግዲ ወረዳ ነው፡፡ /ምንጭ ገዳሙ ካሳተመው ታሪክና ከቀ.ደ.ሰ. መድኀኔ ዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡/ /የቀ.ደ.ሰ. መድኀኔ ዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት፡፡/

#ዘመኑን_የዋጀ_ተከታታይ_መንፈሳዊ_ትምህርት_ (Course)፤ ለወጣቶች (በቀንና በማታ) እና ለሕፃናት (በቀን)፤ ለምትፈልጉ ምዕመናን በሙሉ፤ ሰ/ት/ቤታችን የቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ/ት/ቅ/ገብር
+2
#ዘመኑን_የዋጀ_ተከታታይ_መንፈሳዊ_ትምህርት_ (Course)፤ ለወጣቶች (በቀንና በማታ) እና ለሕፃናት (በቀን)፤ ለምትፈልጉ ምዕመናን በሙሉ፤ ሰ/ት/ቤታችን የቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ/ት/ቅ/ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ለወጣቶችና ሕፃናት ምዕመናን በ2012ዓ.ም. ልዩ ተከታታይ ትምህርቶችን አዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል፡፡ የትምህርቶቹ ዓይነቶች፤ በወጣት ክፍል የሚሰጡ፤ ✤ #በቀዳማይ፤ * ትምህርተ ሃይማኖት (መግቢያ ሥነ ፍጥረትና አእማድ) * የቤተ ክርስቲያን ታሪክ መግቢያና በዓለም መድረክ * የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መግቢያና አዋልድ ቅዱሳት መጻሕፍት * ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ✤ #በካልዓይ፤ * ነገረ ማርያም ወነገረ ቅዱሳን * የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ (የቤ.ክ ታሪክ በኢትዮጵያ) * ብሉይ ኪዳን * ተግባራዊ ክርስትና (ክርስቲያናዊ ሕይወት) ✤ #በሣልሳይ * ነገረ ክርስቶስ ወነገረ ድኅነት * ልሳነ ግእዝ * ሐዲስ ኪዳን * ሥርዐት ወምሥጢራተ ቤ.ክ እንዲሁም በሕፃናት ክፍል የአብነት ትምህርትን ጨምሮ የተለያዩ ትምርቶች ይሰጣሉ፡፡ ትምህርቱ የሚሰጠው፤ * ለወጣቶች በቀን (ቅዳሜ ከ9-11 ና እሑድ ከ4፡30-6፡30) * ለወጣቶች በማታ (ሰኞ፣ ረቡዕና ዐርብ ከ12-2)፤ ለ6 ወራት * ለሕፃናት በቀን (ቅዳሜ ከ6፡30-8፡30 ና እሑድ ከ6፡30-8፡30) ✣✣ መመዝገቢያ፤ በሰ/ት/ቤቱ ጽሕፈት ቤትና ትምህርት ክፍል ✣ ከአኀት ሰንብት ትምህርት ቤቶችና ከግቢ ጕባኤ ለመማር የምትመጡ የተማራችኋቸውን ትምህርቶች የሚገልጽ ደብዳቤ (ምስክር ወረቀት /ካርድ (Certeficet)/ ማምጣት ይጠበቅባችኋል፡፡ ✤✤ ትምህርቱ ጥቅምት 1 ይጀመራል፡፡ ‹‹የነፍስ ምግቧ የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡›› ለበለጠ መረጃ፤ 0922 85 13 74 /0921 05 60 56/

እንኳን ለዘመነ ጽጌ (ከመስከረም ፳፮ - ኅዳር ፭) በሰላምና በጤና አደረሰን ፥ አደረሳችሁ፡፡ ኀለፈ ክረምት ቆመ በረከት፣ ተሠርገወት ምድር በሥነ ጽጌያት፡፡ ትርጕም፤ የክረምት ዘመን (ከሰኔ 26 -
+3
እንኳን ለዘመነ ጽጌ (ከመስከረም ፳፮ - ኅዳር ፭) በሰላምና በጤና አደረሰን ፥ አደረሳችሁ፡፡ ኀለፈ ክረምት ቆመ በረከት፣ ተሠርገወት ምድር በሥነ ጽጌያት፡፡ ትርጕም፤ የክረምት ዘመን (ከሰኔ 26 - መስከረም 25) አለፈ፥ ሄደ /መኃ.2 11/፡፡ የጽጌ ዘመን (ከመስከረም 26 - ኅዳር 5) ተተካ፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት፡፡/

#የዐርብ_ጕባኤ_፻፵፮ኛ_ሳምንት #መስከረም_፳፫/፳፻፲፪ዓ.ም. ከ፲፪-፪ ሰዓት፤ #በሰዐቱ_ይገኙ!!!!!!!! እንዳያመልጥዎ!! በታላላቅ ገዳማት የሚጸለየው #የመሐረነ_አብ ጸሎት ይደርሳል፡፡ ላልሰሙት
+1
#የዐርብ_ጕባኤ_፻፵፮ኛ_ሳምንት #መስከረም_፳፫/፳፻፲፪ዓ.ም. ከ፲፪-፪ ሰዓት፤ #በሰዐቱ_ይገኙ!!!!!!!! እንዳያመልጥዎ!! በታላላቅ ገዳማት የሚጸለየው #የመሐረነ_አብ ጸሎት ይደርሳል፡፡ ላልሰሙት ያሰሙ፤ <<Like, Share>> በማድረግ ይተባበሩ /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት፡፡/

በአዲስ አበባ በዋነኛነት የመስከረም 21 (የብዙኃን ማርያም) ክብረ በዓል የሚከበርባት፤ ግማደ መስቀሉ ለተወሰኑ ጊዜያት ያረፈበት፥ ለጥቂት ዓመታት የሃገራችን ኢትዮጵያ ርዕሰ መዲና የሆነችው፤ ርዕሰ
+1
በአዲስ አበባ በዋነኛነት የመስከረም 21 (የብዙኃን ማርያም) ክብረ በዓል የሚከበርባት፤ ግማደ መስቀሉ ለተወሰኑ ጊዜያት ያረፈበት፥ ለጥቂት ዓመታት የሃገራችን ኢትዮጵያ ርዕሰ መዲና የሆነችው፤ ርዕሰ አድባራት መንበረ ፀሐይ እንጦጦ ማርያም፡፡ ሌሊቱን በማኅሌት አሸብርቃ አድራለች፤ በእንጦጦ ብቻ ከሚወረቡ ወረቦች መካከልም፤ እትአመን ባቲ እስመ አርአያ መስቀል ይእቲ፤(፪) አክሊለ ተቀጺላ ታንሶሱ፡፡(፪) የሚለውን ወረብ ልቡናን በሚመሰጥ አወራረብ ሲወረብ አድሯል፡፡ የአዲስ አበባና የሱሉልታ ምዕመን በቤቱ አለ ወይ? በሰፈሩስ ቀርቷል ወይ በሚያስብል ሁኔታ ሁሉም ወደ እንጦጦ በእግር በመኪና በፈረስ ሳይቀር ይተምማል? /መልካም በዓል/

#ዛሬ_በአሁኑ_ሰዐት_ክብረ_በዓሉ_በግሸን_ደብረ_ከርቤ_ይህን_ይመስላል፡፡ በክብረ በዓሉም ላይ ከ3 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ይገኛል ተብሎ ይገመታል፡፡ ፠ በዐውደ ምሕረቱ ላይም የግሸን ደብረ ከርቤና ከኢት
+6
#ዛሬ_በአሁኑ_ሰዐት_ክብረ_በዓሉ_በግሸን_ደብረ_ከርቤ_ይህን_ይመስላል፡፡ በክብረ በዓሉም ላይ ከ3 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ይገኛል ተብሎ ይገመታል፡፡ ፠ በዐውደ ምሕረቱ ላይም የግሸን ደብረ ከርቤና ከኢትዮጵያና ከመላው ዓለማት የተውጣጡ ሊቃውንት ከዚህ በታች ያሉውን ወረብ እየወረቡ ገኛሉ፡፡ ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ (፪) ወረከበ ደብረ ከርቤ ዕፀ መስቀሉ ለክርስቶስ፡፡(፪) ትርጕም፤ እውነት በእውነት የክርስቶስ ዕፀ መስቀሉ በደብረ ከርቤ ተቀመጠ፡፡ ፠ ቀጥለውም ከጌታችን ዕፀ መስቀል ጋር አብረው በግሸን በክብር ከተቀመጡት ንዋያተ ቅድሳት መካከል አይሁድለ ለጌታችን ያለበሱትን ከለሜዳ (ቀይ ግምጃ ልብስ) ወጥቶ ሕዝቡን እየባረከ ይገኛል፡፡ ሊቃውንቱም ለዚሁ ተስማሚ የሆነውን ከዚህ በታች ያለውን ወረብ እየዘመሩ ይገኛሉ፡፡ ዘአልበስዎ አይሁድ ከሌሜዳ ዘለይ፤ (፪) ከለሜዳ ዘለይ፡፡ (፫) ትርጕም፤ አይሁድ ከሌማዳና ዘለይ /ለመድኀኔዓለም ክርስቶስ/ አለበሱት፡፡ ፠ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላትም የሚከተለውን ወረብ እየወረቡ ይገኛል፤ አይ ይእቲ ዛቲ ደብረ ከርቤ መድኀኒት እንተ ኀሠሥዋ ወዖድዋ ነቢያት፤ (፪) እትአመን ባቲ (፪) እስመ አርአያ መስቀል ይእቲ፡፡ (፪) ****ትመስል ኢየሩሳሌም በአርአያ ልዑል ፤ ደብረ ከርቤ ግሸን ማርያም፡፡ ፠፠ አሁን ደግሞ ጸሎተ ምሕላ እየደረሰ ነው ቀጥሎ ትምህርት ይኖራል፡፡ ፎቶዎቹ፤ አይሁድ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስን ያለበሱት ከሌዳ ዘለይ የሚባለው ቀይ ግምጃ ልብስ፤ በክብረ በዓሉ ከተገኙ ሕዝቦች በጨረፍታና፤ ሊቃውንቱና ሰ/ት/ቤት ተማሪዎች ወረብ ሲያቀርቡ፡፡

✤እንኳን ለመስከረም 21፤ #ብዙኃን_ሊቃውንት_ሌሰበሰቡበት_ብዙኃን_ማርያም_፤ #ክቡር_መስቀሉና_ሌሎችም_ንዋያተ_ቅድሳት-በግሸን_ደብረ_ከርቤ_አምባ_ላይ_በክብር_ላረፉበት_ዕለት፤( …….ዝረዝርሩን በስተመጨረሻ ይመልከቱ)፤ #ለቅዱስ_ቆጵርያኖስ_(ኃይለኛ ሥራየኛ ጠንቋይ የነበረውና በኋላም አምኖ ለክርስቶስ ምስክር ሆኖ አንገቱን የተሰየፈው )ና ፡ ቆጵርያኖስን ያሳመነችውና ስሟ በተጠራበት ቦታ ሰይጣናት እንደ ትቢያ በነው የጠፉት ታላቋ ቅድስት ድንግሊቱ ዮስቴና በሰማዕትነት ላረፉበት ዕለት፤ #ሃይማኖታቸው_ለቀና_ለ318ቱ_አበው_ሊቃውንት (#በ325 ዓ.ም #አርዮስን_አስተምረው_ለመመለስ_በኒቅያ_የተሰበሰቡባት_ዕለት )፣ /የጉባኤውም ፍጻሜ ኅዳር ዘጠኝ ነው/ እንዲሁም #ከ72ቱ_አርድእት_አንዱ_ለሆነው_ለሐዋርያው_ቅዱስ_ጢባርዮስ_ዕረፍት በሰላምና በጤና አምላከ አበው መድኀኔዓለም አደረሳችሁ አደረሰን፡፡ ፠፠፠ #ብዙኃን_ማርያም፤ /ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት ባጭሩ የተወሰደ፡፡/ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓሏ መስከረም ፳፩ ቀን መከበሩ ስለ ሁለት ነገር ነው፡፡ ፠1ኛ) አንዱ ጉባኤ ኒቅያን ይመለከታል፤ ለ፲፰ኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ ለተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስ ካሉት ደቀ መዛሙርት መካከል አርዮስ፣ አኪላስና እለእስክንድሮስ የሚባሉት ዋነኞቹ ነበሩ፡፡ አርዮስ እውቀቱ በመምህሩ የተመሠከረለት ሊቅ ነበር፡፡ ነገር ግን “እጅግ ጥበብ ያደርሳል ከሞት” እንዳለ ሰሎሞን የተጻፈውን ትቶ ባልተጻፈው ላይ ፍልስፍና ጀመረ፡፡ በምሳ. ፰÷፳፪ ላይ ያለውን ቃል በተሳሳተ መንገድ ፈታው፤ ነገር ግን ተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስ ጠርቶ ቢመክረው ቢገስጸው እንቢ በማለት የክህደት ትምህርቱን ቢቀጥልበት ከሹመቱ አውርዶ አወገዘው፡፡ ተፈጻሜተ ሰማዕት ከደቀመዛሙርቱ መካከል አኪላስን ተክቶ ኅዳር ፲፱ ቀን በሰማዕትነት አረፈ፡፡ አኪላስም የጓደኝነት ፍቅር አድልቶበት አርዮስን ከውግዘት ቢፈታው በመቅሠፍት ሞት ሞተ፡፡ በመንበሩም እለእስክንድሮስ ተተካ፡፡ በዚህ ጊዜ የአርዮስ የክህደት ትምህርት በሀገሪቱ ሞላ፡፡ ይህ ነገርም እየተባባሰ በመሔዱ በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ዘንድ ተሰማ፡፡ ንጉስ ቈስጠንጢኖስም ይህን ሲሰማ ለአርዮስ ጥያቄ መልስ ይሠጥበት ዘንድ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ጕባኤ እንዲደረግ ሰኔ ፳፩ ቀን አዋጅ አስነገረ፡፡ ይህንን አዋጅ የሰሙት ሊቃውንት ሁሉ መስከረም ፳፩ ቀን የእመቤታችን እለት ተሰባሰቡ፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ “ለምን ቈስጠንጢኖስ መልዕክት ከላከበት ጊዜ በኋላ ወዲያውኑ ለምን አልመጡም? ለምን ዘገዩ?” የሚለው ጥያቄ ይነሳል፡፡ ምክንያቱም፤ *አንደኛ መጓጓዣ ችግር ስለነበር፤ *ሁለተኛ ሁሉም ሊቃውንት አስተማሪዎች በመሆናቸው ለምዕመናኑ (ለተማሪዎቻው) ሌላ መምህር ማዘጋጀት ስለነበረባቸው፤ *ሦስተኛ ደግሞ በእድሜ የገፉ ስለነበሩ አንድም ሊቃውንቱ ሲያስተምሩ በአላውያን ነገሥታት ባላመኑ ሰዎች ግፍ ይድርስባቸው ስለነበር ነው፡፡ ለምሳሌ ቶማስ ዘመርዓስ በእነዚህ ሰዎች በግፍ እግሩና እጁ ተቆርጦ ስለነበር ለማስተማር በቅርጫት ይዘውት ነበር የሚጓዘው፡፡ ወደ ጕባኤውም ሲመጣ ደቀ መዛውርቱ ያመጡት በቅርጫት ይዘውት ነበር፡፡ ከዚህ በኋላ 2,340 ሊቃውንት መስከረም ፳፩ ቀን ተሠባሰቡ፡፡ ከእነዚህ መካከል ግን 318ቱ ሊቃውንት ‹‹ዘእሩይ ምስለ አብ በመለኮቱ ›› በማለት በሃይማኖታቸው የጸኑ ነበሩ፡፡ ጉባኤውን ከመጀመራቸው በፊት አርባ (፵) ቀን ሱባኤ እስከ ኅዳር ዘጠኝ (፱) ቀን ይዘውና ጕባኤውን አድርገው በአንዲት ቀን ያንን ታላቅ መናፍቅ አርዮስን ድል ነሥተውታል፡፡ ከዚህ ጋር አያይዘውም የኃይማኖታችን መሠረት የሆነውን ጸሎተ ሃይማኖትን አዘጋጅተዋል፡፡ #ብዙኃን_ማርያም_የተባለበት_ምክንያት_ብዙኃን_ሊቃውንት_የተገኙበት_እለት_በመሆኑ_ነው፡፡ ፠፠ 2ኛ) መስከረም ፳፩ የምናከብርበት ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ መስቀልን አስመልክቶ ነው፡፡ መስቀሉ በመስቀልኛ ቦታ በግሸን ደብረ ከርቤ በክብር ያረፈበት ዕለት ነው፡፡ ለዚህም በቂ ማብራሪያ በመስከረም 17 (የመስቀል ክብረ በዓለት የሚለውን ገጽ ይመለከቱ)፡፡ ከበዓሉ ረድኤት በረከት ይክፈለን እመቤታችን ጣዕሟን ፍቅሯን ታሳድርብን አሜን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር (በሁሉም የእመቤታችን አብያተ ክርስቲያናት በላይ ቤትና በታች ቤት ይትበሃል የሚቆመውን ሥርዐተ ማኅሌቱን አቅርበንላችኋል፡፡ ላልደረሰው በ Facebook, twitter, instagram, telegram, Email, Viber, Xender, whatsup, imo, Bluetooth, ….. በማድረስ ይተባበሩ፡፡) መልካም ማኅሌት፡፡ የቤ/ኑ ፎቶዎቹ፤ ግማደ መስቀሉ ካረፈባቸው ቅዱሳን መካናት የ3ቱ (የመናገሻ አምባ ማርያም፣ የእንጦጦ ማርያምና የግሸን ማርያም) ናቸው፡፡

#ፎቶ_ክምችት_11፤ የደመራ በዓል በአፍሪካ (በኡጋንዳ፣ በግብጽ)፣ በኢየሩሳሌም፣ በዱባይ፡፡
+5
#ፎቶ_ክምችት_11፤ የደመራ በዓል በአፍሪካ (በኡጋንዳ፣ በግብጽ)፣ በኢየሩሳሌም፣ በዱባይ፡፡