ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 413 подписчиков, занимая 5 577 место в категории Религия и духовность и 2 192 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 413 подписчиков.

Согласно последним данным от 13 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 71, а за последние 24 часа — -3, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.53%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.38% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 933 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 446 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 23.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 14 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 413
Подписчики
-324 часа
+357 дней
+7130 день
Архив постов
✤✣✤ #በዓለ_ልደቱ_ለሐዲስ_ሐዋርያ_ፀሐይ_ማር_አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት #ታኅሣሥ_24_1196ዓም_በሰሜን_ሸዋ_ቡልጋ_ጽላልሽ_እቲሣ_ተወልደው_በአጠገቡ_በምትገኛወ_ደብረ_አጋዕዚት_ክርስትና_ተነሡ፡፡ #አባታቸው ቅዱስ ጸጋ ዘዓብና እናታቸው ቅድስት እግዚእ ኀረያ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሲያስተምሯቸው በአካባቢያቸው ደግሞ በዘመኑ የነበሩ ልጆች ይማሩ የነበረውን ፈረስ መጋለብን፣ ቀስት መወርወርን፣ እርሻንና አደንን አስተምረዋቸዋል፡፡ #በ7ት ዓመታቸው ከግብፃዊው ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ ዲቁናን ከተቀበሉ በኋላ እግዚአብሔር በክህነት ሕዝቡን እንዲያገለግሉ መረጣቸው፡፡ ከዮዲት ጉዲት በኋላ ሃገራችን ሰሜኑና ደቡቡ ተቆራርጧል፤ የሐሳብን ልዕልና የሚያመጣው የመንፈስ ልዕልና ተዳክሟል፡፡ ለዚህም ኢትዮጵያን የሚዋጅ ሐዲስ ሐዋርያ ያስፈልግ ነበርና አምላካችን አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ጠራ፡፡ #አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቅስናን ከአቡነ ቄርሎስ ተቀብለው በጽላልሽ አካባቢ በክህነት ከአባታቸው ጋር አገልግለዋል፡፡ አባታቸው ሲያርፉ በወንጌሉ ማንም ሊከተለኝ የሚወድድ ቢኖር ያለውን ሁሉ ትቶ መስቀሉን ተሸክሞ ይከተለኝ ያለውን በመከተል ሀብታቸውን ለድኾች መጽውተው በሸዋና በዳሞት በስብከተ ወንጌል አገለገሉ፡፡ ከዚያም፤ #በመጀመርያ ደቡብ ወሎ ቦረና ላይ ገዳማቸውን ደብረ ጎል ገድመው ወደሚገኙት ታላቁና ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን ወደኾኑት ጻድቅ አባት አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ገብተው ዐሥር ሁለት ዓመታት በትምህርትና በሥራ (በአርድእትነት) አሳልፈዋል፡፡ በዚያም ዋሻ ፈልፍለው አስደናቂ ሕንፃ ሠርተው ነበር፡፡ #በ1216 ዓ.ም. አካባቢ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ገሳም ገብተዋል፤ በዚሁ ገዳምም ከመመንኰሳቸው በፊት ሰባት ዓመት ከመነኰሱም በኋላ ሦስት ዓመት በድምሩ ለ10 ዓመታት በትምህርት፣ በእደ ጥበብ ሥራ፣ በአገልግሎትና ሥርዐተ ምንኵስናን እያጠኑ ቆይተዋል፡፡ #ከሐይቅ ወጥተው በዘመኑ በሥርዐተ ምንኵስናና በትምህርት ብሎም በጥበበ እድ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ወደ ነበረው ወደ ደብረ ዳሞ በመሄድ በየገዳሙ አበምኔት ከሆኑት ከአቡነ ዮሐኒ ዘንድ መንፈሳዊ ትምህርት፣ ሥርዐተ ምንኵስናና ጥበበ እድ ሲማሩ ለ12 ዓመታት ቆዩ፡፡ ያነጹት ፍልፍል ድንጋይ ዋሻ፣ መጻሕፍት ሲጽፉ ቀለማቸውን ያስቀምጡባቸው የነበሩትን ሽንቁሮች ዛሬም በደብረ ዳሞ ማየት ይቻላል፡፡ #በደብረ ዳሞ የነበራቸውን ቆይታ ጨርሰው በገመድ ሲወርዱ ሰይጣን በቅንዐት መጥቶ ገመዱን በጠሰባቸው እግዚአብሔር አምላክ በዚህ ወቅት የሚበሩበትን እንደ መላእክት ክንፍ ሰጣቸው፡፡ #ለአምስት ዓመታት #አኵስምን_ዋልድባን እንዲሁም ሎሎች የትግራይ ገዳማትን እየተዘዋወሩ ሲመለከቱ ቆዩ #ከሸዋ በወጡ በሃያ ሁለት ዓመት (እድሜያቸው ሃምሳ ሁለት ሲሆን) ለበለጠው ክብር እና ርእይ በግብጽ በኩል ወደ ኢየሩሳሌም ተሻገሩ፡፡ #ከኢየሩሳሌም ሲመለሱ በሐይቅ በኩል አድርገው ደብረ ጎልን ተሳልመው በሚዳ እና በመርሐ ቤቴ በኩል ወደ ሸዋ በመምጣት ከዮዲት ዘመን በኋላ በመንፈሳዊ ሕይወት የተጎዳውን ሸዋን እና ደቡብ ኢትዮጵያን በመዘዋወር ለዐሥር ዓመታት ያህል አስተምረዋል፡፡ #አቡነ ተክለ ሃይማኖት ተግተው በማስተማራቸው የተኛው ሁሉ ነቃ፣ የደከመው በረታ፣ የጠፋውም ተገኘ፡፡ ሐዋርያትን ለማፍራት እንዲችሉ አንድ ገዳም ለመመሥረትና ደቀ መዛሙርትን ለማስተማር አሰቡ፡፡ እናም ወደ ደብረ አስቦ ገዳም ገቡ፡፡ ቦታውን አስተካክለው እና ከደብረ ዳሞ እና ከሐይቅ የተከተሏቸውን ጥቂት ደቀ መዛሙርት ይዘው በደብረ ሊባኖስ ገዳም ልክ እንደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ሁሉ ሦስቱን ነገሮች ያካተተ አገልግሎት ጀመሩ፡፡ ምንኵስና፣ ትምህርትና ሥራ፡፡ መነኰሳቱ መንፈሳዊ ትምህርት ይማራሉ፤ በሕገ ገዳም ይመራሉ፤ ለራሳቸው እና ለአካባቢው ሕዝብ ርዳታ የሚሆን እርሻ ያርሳሉ፡፡ #ደቀ መዛሙርትን አፍርተው፣ ገዳማቸውን አደራጅተው፣ ስብከተ ወንጌልንም አስፋፍተው ካደላደሉ በኋላ በሕይወታቸው የመጨረሻ ዓመታት ወደ ደብረ አስቦ ዋሻ ገብተው በአንድ እግራቸው በጾም እና በጸሎት ተወሰኑ፡፡ #አገልግሎታቸውን ፈጽመው ነሐሴ 24 ቀን 1297 ዓ.ም. በ99 ዓመታቸው ዐረፉ፡፡ ጸሎትና በረከታቸው፤ ረድኤትና ምልጃቸው በመላው ሕዝበ ክርስቲያንና በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ሁሉ አድሮ ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን፡፡ /ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔዓለምና ደ.ት ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ/ ✤✤ #እቲሣ_ገዳም #በቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃና አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን የተመሠረተ፤ ሲመሠረትም በታቦተ ኢየሱስና አርባዕቱ እንስሳ ነው፤ #ሊቀ ካህናት አበይድላ ከአኵስም 300 ታቦታትና 300ካህናት ይዞ መጥቶ በጽላልሽ የተቀመጠባት ናት፤ #ፀሐይ አቡነ ተክለሃይማኖት የተወለዱባት (የተወለዱባት ጠፍጣፋ ደንጊያ አሁንም በቦታው አለች)፣ #አባታቸውና ጸጋ ዘአብና እናታቸው እግዚእኀረያ የተወለዱበት፤ ኋላም ክብሩ አጽማቸው ያረፈበት ነው፡፡ #ቅዱስ ያሬድ 3 ዓመት ጸልዮባታል፤ #ቅዱስ ላሊበላ 7 ዓመት ጸልዮባታል፤ #ተሰዓቱ ቅዱሳን 20 ዓመት የጸለዩበት፤ #ሐርቤ በሚባለው ቦታ ላይ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ 7 ዓመት ጸልየውበታል፤ #ታቦተ ጽዮን 12 ዓመት (ከ9ሺህ ሕዝብ) ጋር መጥታ ኖራበታለች፤ #በአምሳለ ሲዖል የተሠራ አስደናቂ የጨለማ ዋሻ ያለበት ነው፤ #ብዙ የታሪክ ቅርስ ያለበት ነው፤ #በቅዱስ ሚካኤልና ጸጋ ዘአብ ቤተ ክርቲያን ውስጥ ካየን በኋላ፤ እዚሁ ቦታ በሚገኘው ፈዋሽ ጠበል ተጠምቀንና ጠጥተን ጕዟችንን ወደ #ቦታው_ከአአ_በቅርብ_ርቀት_በደብረ_ብርሃን_መንገድ_አሌልቱ_ከተማ_ላይ_በመታጠፍ_ይገኛል፡፡ ✤✤ #በአዲስ አበባ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት በዓለ ልደት የሚከበርባቸው፤ 1.#በዳግማዊት ደብረ ሊባኖስ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም 2.#በመንበረ ክብር ደብረ ታቦር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም 4.#በጥንታዊው በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም 5.#በደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ #ሥርዐተ_ማኅሌቱን_እንደየደብራችሁ ይትበሃል እንድትጠቀሙበት በማሰብ ሁሉንም (በላይ ቤትና በታች ቤት) (#ዘአባጃሌ_ተክለ_ሃይማኖትና_ዘአደባባይ_ተክለሃይማኖት) አዘጋጅተነዋል፡፡

3ት ሰንበት ት/ቤቶችን ያጣመረ አዲስ ቴአትር #የደም_ደመወዝ>>፤ #ዛሬ_እሑድ_ታኅሣሥ_21_ቀን_በ9_ሰዐት * ድርሰት፤ ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት * ዝግጅት፤ የቀ.ደ.ሰ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ከኑብያ የቴአትር ጥበባት ጋራ በመተባበር * አስተባባሪ የመንበረ ክብር ደ/ታ ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ደብረ ታቦር ሰ/ት/ቤት ...ቦታ በቀ.ደ.ሰ ሰ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አዳራሽ፨

#ታኅሣሥ_፲፱ #በዓለ_ቅዱስ_ገብርኤል፤ #ወሥርዐተ_ማኅሌት፡፡ #ሊቀ_መላእክት_በመላእክት_ሁሉ_ላይ_የተሾመ_ነው_ሄኖክ_10፥14 #መልአከ_ራማ_ዘራማ_ልዑል_ነው፤ #አብሣሬ_ትስብእት_ነው፤ #መጋቤ_ሐዲስ_ነው፤ #የአርባብ_የ10ሩ_ነገደ_መላእክት_አለቃ_ነው #ከከበሩ_መላእክት_አንዱ_ነው_ሄኖክ_6፥7፤ #በእግዚአብሔር_ፊት_የሚቆም_መልአክ_ነው_ሉቃ_1፥19፤ #ለቅዱሳን_እውቀትን_የሚገልጽላቸውና_ከአላውያን_የሚታደጋቸው_ነው_ድርሳነ_ገብርኤል #መልአከ_ሰላሞሙ_ወመልአከ_ኪዳኖሙ_መልአከ_አድኅኖ_መልአከ_ኀይል_መልአከ_ፍስሐ #ናዛዜ_ኅዙናን_ያዘኑትን_የሚያጽናና_ መልአክ_ነው፨ ✤ ገብርኤል ማለት የእግዚአብሔር ልጅ ማለት ነው፤ የወልደ እግዚአብሔርን መወለድ አብሥሯልና፨ አንድም የሁለት ቃለት ጥምር ነው እነዚህም ገብር እና ኤል ሲሆኑ ትርጕማቸውም ገብር አገልጋይ ማለት ሲሆን ኤል ማለት ደግሞ አምላክ ማለት ነው፤ በተገኛኘ ገብርኤል ማለት የአምላክ አገልጋይ /የእግዚአብሔርን ልጅ የሚመስል የአምላክ አገልጋይ/ ማለት ነው። ✼ ነቢዩ ዳንኤል “ዐይኖቼንም አነሣሁ” አለና አስከትሎ “እነሆም በፍታ የለበሰውን ጥሩም የአፌዝን ወርቅ በወገቡ ላይ የታጠቀውን ሰው አየሁ፡፡ አካሉም እንደ ቢረሌ ይመስል ነበር፤ ፊቱም እንደ መብረቅ አምሳያ ነበረ፤ ዐይኖቹም እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ የቃሉም ድምፅ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነበረ፡፡… ይህንንም ታላቅ ራእይ አየሁ፤ ኃይልም አልቀረልኝም፤ ክብሬም ወደ ውርደት ተለወጠብኝ ኃይልም አጣሁ፡፡ የቃሉንም ድምፅ ሰማሁ፤ የቃሉን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ደንግጬ በምደር ላይ በግምባሬ ተደፋሁ” አለ፡፡(ዳን.10፥5-9) ነቢዩ ዳንኤል እንዲህ ብሎ የተናገረው የመላእክት አለቃ የቅዱስ ገብርኤልን አስፈሪ ግርማ በተመለከተ ጊዜ ነበር፡፡ ፠ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል “እነሆ ከዋነኞቹ አለቆች” አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ”(ዳን.10፥13) ብሎ በተናገረው ንግግሩ በመላእክት ላይ የተሾሙ ሌሎች አለቆች እንዳሉ ማስተዋል እንችላለን፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በቅዱሳን መላእክት ዘንድ ስላሉት ነገዶች ሲገልጽ “… በሰማይ ያለውን በምደር ያለውን የሚታየውንና የማይታየውን መናብርትም ቢሆኑ አጋእዝትም ቢሆኑ መኳንንትም ቢሆኑ ቀደምትም ቢሆኑ ሁሉም በእጁ ሆነ፤ ሁሉም በእርሱ ለእርሱ ተፈጠረ” (ቈላ.1፥16) በማለት ይዘረዝራቸዋል፡፡ ከዚህ ተነሥተን መላእክት በተለያዩ ዐበይት ነገዶች የተከፈሉና ለእያንዳንዱም ነገድ የራሱ የሆነ አለቃ እንዳለው ማስተዋል እንችላለን፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ከእነዚህ ዐበይት የመላእክት ነገዶች መካከል አንዱ በሆነው አርባብ በሚባለው ዐቢይ ነገድ ላይ የተሾመ ሲሆን ከ100ው ነገደ መላእክት መካከል ከበታቹ የሚመራቸው ዐሥር ነገደ መላእክት አሉት፤ ከተማቸውም በሰማየ ራማ ነው፡፡ ✼ ቅዱሳን መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ፊት አውራሪነት የሰው ልጆች ጠላት የሆነውን ዲያብሎስን ተዋግተው ድል ከመንሳታቸው አስቀድሞ ቅዱስ ገብርኤል፣ እንደ አምላክ ሊመለክ የወደደውን ሳጥናኤልን በመቃወም ‹‹ንቁም በበህላዌነ እስከ ንረክቦ ለአምላክነ - “አይዟችሁ ፈጣሪያችን እስክናገኘው፣ እስክናውቀው ድረስ በያለንበት ጸንተን እንቁም፡፡” (አክሲማሮስ ገጽ.35) በማለት መላእክትን ያረጋጋ መልአክ ነው፡፡ በተወዳጁ መልአክ በቅዱስ ሚካኤል መሪነት የሰው ልጆች ጠላት የሆነውን ዲያብሎስን ተዋግተው ድል እንዲያደርጉ ወደ ጥልቁ እንዲጣል አድርጓል ራእ12፥7፤ ነቢዩ ኢሳይያስ በሰማያት የሳጥናኤል ትዕቢትና ውድቀት ምን እንደሚመስል ሲጽፍልን “አንተ በንጋት የሚወጣ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! ወደ አሕዛብ መልእክትን የላክ አንተ ሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቀጠቀጥህ! አንተም በልብህ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደረጋለሁ፤… በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፡፡ ዛሬ ግን ወደ ሲኦል ትወድቃለህ፤ ወደ ምድር ጥልቅም ትወርዳለህ” (ኢሳ.14፥16) በማለት ገለጠልን፤ ወደ ምድር የጣሉት በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል መሪነት እነ ቅዱስ ገብርኤል ነበሩ፡፡ ✼ ቅዱስ ገብርኤል ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ከሊቃነ መላእክት አንዱና በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው ብሏል ሉቃ 1፥19፤ ታላቁ ነቢይ ሄኖክም ስለ ነገረ መላእክት በተናገረበት አንቀጽ እንዲህ ሲል መስክሯል ‹‹በአበቦች ላይ በገነትም በጻድቃን ላይ በኪሩቤልም ላይ የተሾሙ ከከበሩ መላእክት አንዱ ገብርኤል ነው፡፡›› ሄኖክ 6፥7፤ ‹‹በሦስተኛውም በመላእክት ሁሉ ላይ የተሾመ ቅዱስ ገብርኤል ነው››ሄኖክ 10፥14 እያለ የመልአኩን ክብር ተናግሯል፡፡ **ቅዱስ ገብርኤል ቅዱሳን ይሆኑ ዘንድ ለተጠሩት መንፈሳዊ እውቀቱን የሚያካፍላቸው መልአክ ብቻ አይደለም፤ ለእግዚአብሔር በመገዛታቸው ምክንያት ከአላውያን ገዢዎች ከሚደርስባቸው መከራም የሚታደጋቸው መልአክም ነው፡፡ ነገር ግን ያደረጋቸው ተዓምራቶች በመጽሐፍ ቅዱስ፣ በመልክኡ፣ በድርሳኑ፣ በገድሉ፣ በተዓምሩ የተጻፉ ቢሆንም ✤✼ ታኅሣሥ 19 ካደረጋቸው ተራዳኢነት ከብዙው በጥቂቱ እንደከሚተለው እናያለን፡- ፠ አናንያና(ሚሳቅ)፣ አዛርያ(ሲድራቅ) እና ሚሳኤል(አብደናጎ) ያዳናቸው ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ አናንያና(ሚሳቅ)፣ አዛርያ(ሲድራቅ) እና ሚሳኤል(አብደናጎ) የፋርስ ባቢሎን ንጉሥ የነበረው ናብከደነፆር በዱራ(አዱራን) በሚባል ስፍራ ላይ ላቆመው ጣዖት አንሰግድም በማለታቸው ወደ እቶን እሳት እንዲጣሉ አድርጓቸዋል፤ በመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት ግን ከእቶን እሳቱ የልብሳቸው ዘርፍ እንኳን እሳት ሳይነካው ድነዋል፡፡ ©/የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

✤ #አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_ዘገዳመ_ዋሊ፤ #ክቡር_መምህር፥ #የከበረ_መምህር፤ #መልአክ_ዘበምድር፥ #የምድር_መልአክ፤ #ካህን_ወድንግል፥ #ካህንና_ድንግል፤ #ፍጹም_ንጹሕ_ወልዑል፥ #ፍጹም_ንጹሕና_ልዑል፤ #ትጉህ_ወኅሩይ፥ #ትጉህና_ኅሩይ_የተመረጠ)፤ #ብእሴ_እግዚአብሔር፥ #የእግዚአብሔር_ሰው፤ #ለባሴ_ንጽሕና፥ #ንጽሕናን_የተላበሰ፤ #ወለብሰ_ብርሃናዌ፥ #ብርሃንን_የለበሰ፤ #ዘፈጸመ_ገድሎ_በሠናይ፨ #ገድሉን_በመልካም_ተጋድሎ የፈጸመ፨ #እናታቸው ዓመተ ማርያም በሕፃንነታቸው በሞተ ሥጋ ስትለያቸው ጌታችን ጣቶቹን ያጠባቸው ናቸው፨ <<መንኮብያቲሁ አጥበዎ ወልደ ማርያም ድንግል፤ ሳሙኤል፥ ሳሙኤል፥ ሳሙኤል ዘዋልድባ መነኮስ ኀያል>> እንዲል፨ #ታኅሣሥ ፲፪ በበዓለ ዕረፍታቸው ጊዜም፤ ሮም በጴጥሮስና በጳውሎስ ዕረፍት እንዳለቀሰች፤ ቅድስት ገዳማቸው ገዳመ ዋልድባ (ዋሊ) አልቅሳለች፨ <<በከየት ወለሀወት ገዳምከ በሞትከ ዮም፤ ሃሌ ሉያ፥ ሃሌ ሉያ፥ ሃሌ ሉያ፤ ምድረ ዋልድባ ቅድስት ሰሚዓ ዜና ሞትከ፤ እንዘ አንተ ሰብእ ምድራዊ ወመልአክ ተሠመይከ፤ ካህነ አርያም ሳሙኤል መንበረ ሥላሴ ዘአጠንከ፤ አንበሳ ወነምር ይሰግዱ ለከ፤ ወይልህሱ ጸበለ እግርከ፤ ዕንቆ ወዕጣነ ማርያም አምጽአት ለከ፤ በቅዳሴሃ ሶበ ጸለይከ፤ በከየት ወለሐወት ገዳምከ፥ በከየት ወለሐወት ገዳምከ።>> እንዲል፨

✤✤✤ #ፀሐይ_ማር_አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_ዘገዳመ_ዋሊ)፤ (ለኢትዮጵያ ርዕሰ ገዳማትና ምክኾን (መመኪያ) የኾነው፤ በሃገራችን በኢትዮጵያ ከሚገኙ ገዳማትና አድባራት በብቸኝነት በጌታችን የተመሠረተውና በ485ዓ.ም. በሸዋ አበው የተስፋፋው ገዳመ ዋልድባ፤ ኋላ በአሕዛብ ጠፍቶ ነበርና በ13ኛው ክፍል ዘመን እንደ መሶብ ከፍ አድርገው በ4ቱም አቅጣጭ በ4 ወንዞች (በሰሜን ተከዜ፥ በምሥራቅ እንስያ፥ በምዕራብ ዘሪማ ፥ በደቡብ እንዞና ወይቦ) ዙሪያውን ከልለውና አጥረው ያስባረኩ አባት ናቸው፡፡ ( አዲስ አበባንና አካባቢዋን ከ700ዓመታት በፊት በአንበሳ እየተጓጓዙ በስብከተ ወንጌል እርሻነት፥ በሥነ ምግባር ማለስለሻነት ያረሱ አባት ናቸው፡፡ ( ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን፣ ወላዴ መምህራን ወሊቃውንት የኾኑ ናቸው፤ ( አቡነ ሳሙኤልን ከቅዱሳን ሊቃውንት አንዱ የኾኑት ታላቁ አባት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በ40ቀን ዕረፍታቸው በመካነ መቃብራቸው ተገኝተው መልክአቸውን የደረሱላቸው፤ በርካታ ቅዱሳን ደራስያን በየድርሰታቸው ያነሷቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ( የከበረ መምህር፤ የምድር መልአክ፤ ካህንና ድንግል፤ ፍጹም ንጹሕና ልዑል፤ ትጉህና ኅሩይ(የተመረጠ)፤ ብእሴ እግዚአብሔር፤ ንጽሕናን የተላበሰ፤ ብርሃንን የለበሰ፤ ( እምቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዕንቊና ዕጣን የሰጠቻቸው ናቸው፤ ( ቅዳሴ ማርያምን ከተከዜ ወዲህ ያመጡና የቅዳሴ ትምህርትን በደብረ ዐባይ የጀመሩ ናቸው፡፡ ቅዳሴ ማርያን ሲደግሙ ከምድር ክንድ ከስንዘር ከፍ ብለው ይታዩ ነበር፡፡ ( ገባሬ ተዓምራት ወመንክራት የኾኑ፤ ⴲ ዝናብ በኾነ ጊዜ ዝሆኖች መጥተው አስጠልለውታል፤ ‹‹ሳሙኤል አቡነ ሠረገላ ጸሎት፤ ጊዜ ርደቶሙ ለዝናማት፤ ዘከለሉከ ነጌያት፡፡›› እንዳለ መጽሐፈ ሰዐታት፤ ⴲ ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር መንበረ ጸባዖትን ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ጋር አጥነዋል፤ ‹‹ሳሙኤል አቡነ ትሩፈ ምግባር፤ ዓምድ ጽኑዕ ፀወነ ሃገር፤ ወመልአክ ዘበምድር፡፡›› እንዲል መጽሐፈ ሰዐታት፣ ⴲ በዋልድባ ምድር ላይ ቀድሞ ውኃ የለም ነበርና፤ ፸ የሚጠጉ ምንጮችን በተለያዩ ቦታዎች አፍልቀዋል የምንኵስና ተወረዱም፤ አባት አባትን ሲወልድ፤ ገዳም ገዳምን ሲወልድ ነውና ቅሉ፤ የምንኵስና ተዋረዱም ርእሰ መነኰሳት አቡነ እንጦንስ አባ መቃርስን፤ አባ መቃርስ አባ ጳኵሚስን፤ አባ ጳኵሚስ አባ ቴዎድሮስን፤ አባ ቴዎድሮስ አቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞን፤ አቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ አባ ክርስቶስ ቤዛነነ፤ አባ ክርስቶስ ቤዛነ አባ መስቀል ሞዐን፤ አባ መስቀል ሞዐ አባ ዮሐኒን፤ አባ ዮሐኒ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን፤ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አቡነ መድኃኒነ እግዚእን፤ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ 7ቱን ከዋክብት /ፀሐይ አቡነ ሳሙኤልንና ሌሎች ቅዱሳንን/፤ ከ7ቱ ከዋክብት አንዱ ፀሐይ አቡነ ሳሙኤል ደግሞ ደቀ መዛሙርቶቻቸውን (አባ ተሥፋ ሐዋርያትን፥ አባ ዘሩፋኤልን፥ አባ ብንያሚን፥አባ በኪሞስን፥ አርሴማን (ሰማዕቷ አይደለችም)፥ …… ሌሎች እልፍ አእላፋት መነኰሳትን አምንኵሰዋል፣ ሊቃውንትን አስተምረዋል፤ መምህራንና ደራስያንን ተክተዋል ….፤ በዚህም ወላዴ አእላፍ አባ ሳሙኤል በመባልም ይታወቃሉ)፡፡ ፨ታሪኩንና ፎቶዎቹን ለሰበሰበልን ወንድማችን አምላከ አበው መድኀኔ ዓለም በረድኤት በበረከት ይጎብኝልን፨ /ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

#ታኅሣሥ_12_የአቡነ_ሳሙኤል_በዓለ_ዕረፍት_ከሚከበርባቸው_ቦታዎች_ዋናዎቹ፤ ✤✤1. በሁሉም የዋልድባ ገዳም ክፍልች (በውስጡ ባሉት 3ት ገዳማት፣ የተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት፣ ጸሎት/ስዕል/ ቤቶችን፣ የአትክልት ቦታዎችንና ሞፈር ቤቶች)፤ እነዚህም፡- 1.1. ዋልድባ አብረንታንት ገዳም (የአብረንታንት መድኀኔዓለም ገዳም) 1.2. ዋልድባ ዳልሽህ ገዳም (ዋልድባ ዳልሽህ አባ ሳሙኤል ቤ.ክ.) 1.3. ዋልድባ ሰቋር ገዳም (የኪዳነምሕረት፣ የቅዱስ ጊዮርጊስና የመድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያንን ያካተተ) 1.4. አቴና (መቃብረ ሳሙኤል)፤ ሌሊቱንና ቀኑን ሙሉ ገድላቸው እየተነበበ 1.5. አባ ናፃ የአቡነ ተሥፋ ሐዋርያት ገዳም 1.6. ደንደሮቃ ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ 1.7. ማይገባ ቅዱስ ሚካኤል ገዳም 1.8. ማይ ሃርገጽ ቅ/ጊርጊስ ቤ.ክ 19. ዕጣኖ ማርያም ቤ.ክ 1.10. ማይ ለበጣና ሌሎችም የስዕል ቤቶች፣ የአትክልት ቦታዎች ✤2. በተወለዱበት በርዕሰ አድባራት ወገዳማት አኵሱም ጽዮን ማርያም፤ ✤3. ምንኵስናን በተቀበሉበት በደብረ በንኰል አቡነ መድኀኒነ አግዚእ ገዳም ✤4. በቆብ ወንድማቸው በአባ ያሳይ መንዳባ መድኀኔ ዓለም ገዳም ✤ 5. በቆብ አያታቸው በአቡነ ተክለሃይማኖት ደብረ ሊባኖስ ገዳም በውዳሴና በቅዳሴ (ከጥንት ጀምሮ በደብረ ሊባኖስ ቅዳሴ በየቀኑ በማይቀደስበት ጊዜ በዓመት ውስጥ ጥቂት ቀናት በሚቀደሱበት ጊዜ የቅዳሴ ቀናቸው ከማይታጎሉ አንደኛውና ዋነኛው የአቡነ ሳሙኤል በዓለ ዕረፍት ነው) ✤✤5. 3. አቡነ ሳሙኤል በመሠረቷቸው ገዳማት፤ ✤5.3.1 በደብረ ዐባይ አቡነ ሳሙኤል ገዳም /ሽሬ አጠገብ/ ፣ እጅግ ደማቅ በኾነ ኹኔታ ✤5.3.2 በአብጠራ (አብጠራህ) አቡነ ሳሙኤል ገዳም /ደባርቅ/፣ ✤5.3.3 ደብረ ገነት አቡነ ሳሙኤል ገዳም /አዲስ አበባ አቃቂ አጠገብ/) በታላቅ ድምቀት ይከበራል፡፡ ✤5.3.4 ጎንደር አዘዞ አባ ሳሙኤል ✤✤5.4 በተጨማሪም በስማቸው በታነጹ አብያተ ክርስቲያናት ይከበራል፤ ለአብነትም፤ 5.4.1 በአዲስ አበባ ቦሌ ቡልቡላ አቡነ ሳሙኤል 5.4.2 በአዲስ አበባ ወረገኑ ቅዱስ ሚካኤል እና ጻድቁ አቡነ ሳሙኤል 5.4.3 በአዲስ አበባ ሲምሲ ሚካኤል (በድርብነት) 5.4.4 በታጠቅ በዓለ ወልድ ቤ.ክ (በድርብነት ይከብራል) ፤/ ወደ መናገሻ መንገድ ሲሄዱ) 5.4.5 ** በነቀምቴ አቡነ ሳሙኤል #ባርከኒ አባ እንሣእ በረከተከ በእንተ ሰላማ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን አባ ሳሙኤል/፫/ ባርከኒ እንሣእ በረከተከ፡፡ ፨ታሪኩንና ፎቶዎቹን ለሰበሰበልን ወንድማችን አምላከ አበው መድኀኔ ዓለም በረድኤት በበረከት ይጎብኝልን፨ /ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

#ጸልዩ_በእንተ_ሃገሪትነ_ቅድስት_ኢትዮጵያ፡፡ (ስለ ቅድስቲቱ ሃገራችን ኢትዮጵያ ጸልዩ፥ ጸልዩ፥ ጸልዩ!!!) #ጸልዩ_በእንተ_ሰላመ_ቤተ_ክርስቲያን_አሐቲ_ቅድስት_ጕባኤ_እንተ_ሐዋርያት_ርትዕት_በኀበ_እግዚአብሔር፡፡ (ሐዋርያት በሰበሰቧት በእግዚአብሔር ዘንድ ሰለቀናች፤ ክብርት ስለምትኾን አንዲት ቤተ ክርስቲያን ጸልዩ፡፡) #ጸልዩ_በእንተ_ሰላም_ፍጽምት_ወፍቅር_ተአምኁ_በበይናቲክሙ_በአምኃ_ቅድሳት፡፡ (ፍጽምት ስለምትኾን ሰላምና ፍቅር ጸልዩ፤ እርስ በእርሳችሁ በተለየች ሰላምታ እጅ ተነሳሱ፡፡) #አድኅነኒ_ወባልሐኒ_እምእዴሆሙ_ለደቂቀ_ነኪር_እለ_ከንቶ_ነበበ_አፉሆሙ_ወየማኖሙኒ_የማነ_ዐመፃ፡፡ (አድነኝ አፋቸውም ምናምን ከሚናገር ቀኛቸውም የሐሰት ቀኝ ከኾነ፤ ከባዕድ ልጆች እጅ አስጥለኝ፡፡) /#መዝ.፻፵፫፥፯/ #ኃዘና_ስምዒ_ወብካየ_ለሃገሪትነ_ኢትዮጵያ፡፡ (በፎቶ የምትመለከቷት የእመቤታችን ስዕል በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ. ብቻ የምትገኝ አስደናቂና ተዓምር አድራጊ ስዕል ስትኾን፤ የተሳለችውም ጠላት ሃገራችንን በወረረበት ወቅት በ፲፱፻፴ዓ.ም. በኢየሩሳሌም በሰዓሊና በወቅቱ ትልቅ ባለሥልጣን በነበሩት በኀይሌ ወልደ ሩፋኤል (ኃ.ወ.ሩ.) ነው፡፡)

ኦ እግዚኦ መሐራ ለነፍሰ መራሔ መንግሥትነ #ግርማ_ወልደ_ጊዮርጊስ፡፡ ኢትዮጵያን በርዕሰ ብሔርነት ለ12 ዓመታት (ከ1994 እስከ 2006 ዓ.ም.) ያገለገሉት ፕሬዚደንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ በ94 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡ በሃገራችን ታኅሣሥ 10 ብሔራዊ የሐዘን ቀን ኾኖ ታስቦ ይውላል፡፡ **በሕፃንንታቸው የአብነት ትምህርትን የተማሩት ርዕሰ ብሔራችን 6ት ቋንቋዎችንም የሚያውቁ ናቸው፡፡ #በሁለቱ_ቅዱስ_ሲኖዶስ_መካከል_እርቅ_እንዲወርድ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ ትልቅ ጥረት ያደረጉትንና ደብዳቤ የጻፉትን የሃገራችንም ኾነ የቤተ ክርስቲያናችን ታሪክ መቼውንም ቢኾን ሲያስታውሰው ይኖራል፡፡

#ታኅሣሥ_6_የአርሴማ_ቅድስት_ወሰማዕትና_የእርሷ_ማኅበርተኞች_ድል_አድራጊዎች_27_ሰማዕታት_ሥጋቸው_በክብር_የፈለሰበትና_ቤተ_ክርስቲያኗ_ቅዳሴ_ቤት_የተከበረበት_ዕለት ነው፡፡ 1ኛ. አርሴማ፤ ቅድስት ወሰማዕት ኃያል ተጋዳሊት 2ኛ. ኢያሚኖስ፤ ጸሎትን የሚያሳርግ ካህን 3ኛ. አፍጢኖስ፤ ከብዙዎች የተመረጠ 4ኛ. በርቲኖስ፤ ጻድቅና ቸር 5ኛ. ጢሞና፤ በመላላክ ሥራ አገልጋይ የኾነ 6ኛ. ጢሞዓና፤ ተአጋሽና ጸዋሚ 7ኛ. ዘኬዎስ፤ ከከበሩ የከበረ 8ኛ. እስጢፋኑ፤ ተጋዳይና የበደሉትን ይቅር ባይ 9ኛ. አርሞና፤ ከጎልማሶች ይልቅ ደም ግባቱና መልኩ ያማረ 10ኛ. ኪርያኮስ፤ ሥጋውን ያላረከሰ ንጹሕ 11ኛ. አንጥያኮስ፤ ቡሩክ የኾነ የአቡሪ ልጅ 12ኛ. ያዕቆብ፤ የእግዚአብሔር ታማኝ የኾነ 13ኛ. ቡራኬሌስ፤ በሰው ዘንድ ተወዳጅ የኾነ 14ኛ. አስቂርያቆስ፤ ክርስቶስን የሚወደው 15ኛ. አስኪርያኖስ፤ ባለሟል የኾነና ግርማው የሚያስፈራ 16ኛ. ሚርያኖስ፤ ፊቱና መልኩ ደስተኛ የኾነ 17ኛ. ትትግርጦስ፤ ወደ ንስሐ የተመለሰ 18ኛ. ያስቲኖስ፤ የሚፈርድና የሚበይን 19ኛ. ጥልያኖስ፤ ያላመኑ ሰዎችን የሚገስጽ 20ኛ. ዑልያኖስ፤ የዚህ ዓለም ጥበብ መምህር የኾነ 21ኛ. ጴርቅላስ፤ በስም አጠራርና በሽምግልና መልካም የኾነ 22ኛ. ኬብያኖስ፤ ተጋዳይ የኾነ 23ኛ. ጴጥሮስ፤ የጠራ የባሕርይ ዕንቊ 24ኛ. ጰኵንዮስ፤ የሮምያ ሹም 25ኛ. ሐናንያ፤ የዋህና ሽንገላ የሌለው 26ኛ. ሐሊባኖስ፤ ጾምና ጸሎትን የሚወድ 27ኛ. ኤስያኖስ፤ በመንፈስ ቅዱስ ጎልማሳ የኾነ 28ኛ. ኤልያብ፤ በረኛና የሰማዕት መጀመሪያ፡፡ ሰላም ለዘአዕረፉ ምስሌኪ ፳ወ፯ቱ ሰማዕታት፤ ረድኤቶሙ ትረድ ላዕሌየ ዘምስለ ብዙኅ ምሕረት፡፡ ወኀበ ሀለወ ስሞሙ ምስለ ስምኪ ቅድስት፤ ዓዲ ኢይቅረብ አርሴማ ሕማመ ብድብድ ወሞት፤ በኵሉ አዝማን ወበኵሉ ዓመታት፡፡

#ላልሰሙት_አሰሙ_Shareeeee_ለመጀመሪያ_ጊዜ_በኹሉም_የአዲስ_አበባ_አብያተ_ክርስቲያናት_የሚደረግ_ልዩ_ጕባኤ #ልዩ_ማሳሰቢያ_ከዛሬ_ዐርብ_ታኅሣሥ_5_እስከ_እሑድ_ታኅሣሥ_7_ለ3ት_ተከታታይ_ቀናት_በአዲስ_አበባ_በሚገኙ_አብያተ_ክርስቲያናት_ልዩ_የዐውደ_ምሕረት_የሠርክ_ጕባኤ_ስላለ_በሚቀርባችሁ_በማንኛውም_ቤተ_ክርስቲያን_እንድትሳተፉ_ቤተ_ክርስቲያናችን_ጥሪዋን_ታስታላልፋለች__መርሐ_ግብሩ_ኹሉን_ባቀፈ_መልኩ_ለመጀመሪያ_ጊዜ_በመኾኑ_እንዳያመልጣችሁ_፡፡ *ቃሌንም በአፉ አድርጋለሁ ያዘዝሁትንም ቃል ሁሉ ይነግራቸዋል፡፡ ዘዳ. ፲፰፥፲፰ **"ድምፃቸው ወደ ምድር ኹሉ፥ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ" መዝ ፲፰፥፬ ***‹‹የእግዚአብሔር ድምፅ ነው፤ …… የእግዚአብሔር ቃል ያድግና ይበዛ ነበር፡፡›› ሐዋ.፲፪፥፳፪