ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 389 подписчиков, занимая 5 582 место в категории Религия и духовность и 2 199 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 389 подписчиков.

Согласно последним данным от 02 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 23, а за последние 24 часа — -3, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 21.38%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 10.20% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 290 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 569 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 17.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 03 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 389
Подписчики
-324 часа
+207 дней
+2330 день
Архив постов
#_ግንቦት_26_ለዓለም ብርሃን የሆኑ #ኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_አቡነ_ሀብተ_ማርያም_ልደታቸው_ነው፡፡ በመብረቅ፣ በቸነፈር፣ በረሃብ፣ በወረርሽኝ፣ በእሳት ቃጠሎ ላይ ቃል ኪዳን የተሰጣቸውን የእኒህን ጻድቅ #ታሪካቸውን_መልክአቸውና_በ ቃሌ ተራራ ደብረ መድኀኒት አቡነ ሀብተማርያም ገዳም( አዲስ አበባ ከዊንጌት ትምህርት ቤት አጠገብ) የሚቆመውን ሥርዓተ ማኀሌት እንሆ ብለናል፡፡ #share ፠፠በማዕጠንታቸው የታወቁ፤ ፠፠በጽድቅ ሥራቸው የተደነቁ፤ ፠፠5ት መቅሰፍቶችን የሚያርቁ፨ ፠በመራ ውዕይ (ሸዋ ፥ ቡልጋ) ከአባታቸው #ፍሬ ቡሩክና ከእናታቸው ቅድስት #ዮስቴና ነው የተወለዱት፡፡ ወላጆቹ በተለይም እናቱ ከማግባቷ በፊት መንና ነበር፡፡ ጻድቁን እንደምትወልድ በበቃ ባሕታዊ ተነግሯት ጻድቁን ወልዳ በጽድቅ ኑሮ ኑራ #7_አክሊላትን ተቀብላ በክብር አርፋለች፡፡ ፠አቡነ ሀብተማርያም በሕፃንነታቸው ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ ‹‹እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ›› ሲባል ይሰማሉ፤ በሕፃን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ ‹‹ማረን እባክህን›› እያሉ ይሰግዱ ነበር፡፡ ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ፡፡ ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል፤ ጓደኞቻቸው የሌላ ሰው እሸት እየነቀሉ ሲበሉ እርሳቸው ግን አይበሉም ነበር፡፡ የፈጣሪውን ስም ያቃለለውን አንድ እረኛም በአየር ላይ ሰቅለው አውለውታል፡፡ ፠ወደ ት/ቤት ገብተው ትምህርትን ከቀሰሙ በኋላ ለአካለ መጠን ሲደርሱ ቤተ ሰቦቻቸው ሚስት አጩለት፤ እርሱ ግን ወደ አፋር ከአባ ሳሙኤል ዘንድ ሂዶ ለ12 ዓመታት ረድዕ ሆኖ ተቀመጠ፡፡ ከአፋርም ወደ ምኔት ወደሚባል ቦታ መጥቶ በታላቁ አባት በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሰ፤ ከአፋር ወደ ይነውፋ፥ ከይነውፋ ወደ ጉሐርብ ወደሚባል ሃገር ሂዶ ምናኔን፣ ትሩፋትንና ተጋድሎን ሠራ፡፡ ለአብነትም፤ ባሕር ውስጥ ሰጥሞ 500 ጊዜ ይሰግዳል፤ በየቀኑ 4ቱን ወንጌልንና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያል፤ በ40 ቀናት ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባል፤ ምግቡ ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው፤ በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋል፤ ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላል፥ ክቡር ደሙን ይጠጣል፤ በልቡ ውስጥ በፍጹም ቂምን፣ መከፋትን አያሳድርም፡፡ የብረት ሰንሰለት በወገቡ ታጥቆ ይሰግዳል ይጸልያልም፡፡ "ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሀብተ ማርያም" T የተባለላቸው ታላቅ አባታችን ናቸው ፡፡ ፠ዲቁናን ከጳጳሱ አቡነ ይስሐቅ ዘንድ ተቀበሎ ወደ በዓቱ ተመለሰ፡፡ ፠ኋላ ቆይቶም እንደገና ከአቡነ ይስሐቅ ዘንድ ቅስናን ተቀበለ፡፡ ወደ ጓና ወደ ምትባል ሀገርም ሂዶ ተቀመጠ፡፡ ቀጥሎም ጐላጐት ወደ ምትባል አገር ሂዶ ተቀመጠ፡፡ *የአፄ ናዖድ የንስሐ አባት ነበረና ንጉሡን ያስተምረውና ይገስጸውም ነበር፡፡ ፠ጌታችንም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቶት በዚያ እየበረረ ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ተለያዩ ቦታዎች ይሔድ ነበር፡፡ ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በኋላም የክብር ባለቤት መድኀኒታችን ክርስቶስ አእላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ እንዲህ አላቸው:: "*ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ: *ስለ ምናኔሕ: *ስለ ተባረከ ምንኩስናህ: *ስለ ንጹሕ ድንግልናህ: *ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ: *ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ: *ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ::" "በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን: 500 የዕንቊ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ: በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ በርእስየ' ብዬሃለሁ" አላቸው:: +ቅዱሳን መላእክትም "ሀብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው:: ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች:: መላእክትም ዝማሬም ወሰዷት::  ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ሥልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነርሱም፤ ፩ኛ. #መብረቅ፣ ፪ኛ. #ቸነፈር፣ ፫ኛ. #ረሃብ፣ ፬ኛ. #ወረርሽኝ፣ ፭ኛ. #የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡ ፨በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ ቦታውን ሲባርክ ሦስት አጋንንት በጸሎቱ ሥልጣን የታሠሩለት ታላቅ ጻድቅ ነው፡፡ በግንቦት 26 ተወልዶ፤ በ1490 ዓ.ም. በወርኀ ኅዳር 26 ባረፈ ጊዜም፤ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው በዝማሬ በማኅሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት አጽም ጋር በደብረ ሊባኖስ ቀበሩት፡፡ (ከወርቅ ንፁህ ከብርም የጠራ ከሁሉ የሚበልጥ የተመረጠ ሃብተማርያም መልአክ ዘበምድር ነው መልካሙ ዜናው እስከ አጽናፍ ተሰማ፡፡) ክብርት በሆነችው ጸሎቱና ምልጃው ይማርን ይጠብቀን፡፡ #ሰላም_ለጽንሰትከ_እማኅፀነ_ቅድስት_ዮስቴና፤ #በብሥራተ_ጻድቅ_ባሕታዊ_ሠናየ_ዜና፡፡ #ሀብተማርያም_ጴጥሮስ_ሐዋርያ_ወልደ_ዮና፤ #መሐረኒ_ምግባረ_ጽድቅ_ወጸግወኒ_ልቡና፤ #አፍቅሮ_ቢጽ_እኅሥሥ_ዘምስለ_ፍጽመት_ትሕትና፡፡ ፎቶ ላይ የሚታዩት ገዳሞቹ፤ ፨ ብሔረ ብፁዓን ደበረ ይሰበይ አቡነ ሀብተ ማርያም ገዳም፤ ደብረ ሊባኖስ አጠገብ ፨ ቃሌ ተራራ ደብረ መድኀኒት አቡነ ሀብተማርያም ገዳም፤ አዲስ አበባ አስኮ ........ለመሄድ የአስኮን ታክሲ ይዞ ካውጄጄ ጋር መውረድ፡፡ #share ꔰ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

ተፈሥሂ #ፍቁረ_እግዚእ ወንትፌሣህ ብኪ፤ እስመ ዮም ተከበረ በዓለ ክብርኪ ፡፡ የ53ኛ ዓመት የምስረታ በዓላችሁን በእመቤታችን በዓል ዕለት(21/09/2013 ዓ.ም) ላጠናቀቃችሁት ለእህት ሰንበት ት/ቤታችን #ፍቁረ እግዚእ አገልጋዮች ፤ እንኳን አደረሳቹህ ፡፡ #ፍቂረ_እግዚእ 53 ዓመት ያደረገችው አገልግሎት ለብዙዎች ምሳሌ የሆነ እና የቅድስት ቤተክርስቲያንን አገልግሎት ዘርፈ ብዙ ያደረገ እና የወንጌል ተደራሽነትን የጨመረ ነው፡፡ ሰንበት ት/ቤቱ ለሚያሰራው የመማርያ ቦታ እና የአጥቢያችን ዕንቁ የሆነችውን የእመቤታችንን ሕንጻ ቤተክርስቲያን ተሰርቶ እስኪጠናቀቅ ለምታደርጉት አገልግሎት ሁሉ ከጎናቹህ መሆናችንን ልናሳውቅ እንወዳለን፡፡ ፍኖተ ሕይወት 55ኛ ዓመቷን እንዲሁ በማክበር ላይ ነች :: አገልግሎታችን ከአጥቢያችን ምዕምናንና ወጣቶች አልፎ ለዓለም እንዲሆን መድኀኔዓለም ከፊታችን እየመራን ቀሪው የአገልግሎት ጊዜያችን እንዲባረክ ደግሞ የአባታችን የፍቂረ እግዚእ ዮሐንስ ርትዕት የሆነች ምልጃና ጸሎቱ ከእኛ ጋር ትሁን፡፡ መልካም አገልግሎት ꔰ ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

የገርጂ ኆኅተ ብርሃን ማርያም ቤ/ክ ቅዳሴ ቤት ቅዳሜ #ግንቦት# 21/2013 ዓ.ም. ከዋዜማው ጀምሮ ይከበራል፡፡ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ ሥርዓተ ማኀሌት ዘሕንጸተ ቤተክርስቲያን ከዕለቱ በ
+3
የገርጂ ኆኅተ ብርሃን ማርያም ቤ/ክ ቅዳሴ ቤት ቅዳሜ #ግንቦት# 21/2013 ዓ.ም. ከዋዜማው ጀምሮ ይከበራል፡፡ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ ሥርዓተ ማኀሌት ዘሕንጸተ ቤተክርስቲያን ከዕለቱ በዓል ( ደብረ ምጥማቅ ማርያም ) ሥርዓተ ማኅሌት ጋር አስማምታቹህ ተጠቀሙ ፡፡ ꔰ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

#ግንቦት_21_ደብረ_ምጥማቅ_ማርያም ሥርዐተ_ማኅሌት_ዘግንቦት_21፡፡ ደብረ_ምጥማቅ_ማርያም የምናከብርበት ምክንያት #ግብጻውያን ክርስቲያኖች ከግንቦት 21 እስከ 25 የእመቤታችንን በዓል (ምሰሶ አቁመው፥ አጎበር ጥለው፥ ድንኳን ተክለው፥ ድባብ ዘርግተው ያከብራሉ፤ እመቤታችንም ከቅዱሳን ጋር በመገኘት ትባርካቸዋለች፡፡) እነዚህ 5ት ቀናትም #ከእመቤታችን 33ቱ በዓላት 5ቱን ከተ.ቊ 25ኛ እስከ 29ኛ ያለውን ይይዛሉ፡፡ እነርሱም፤ ፠25ኛና 26ኛ፤ ግንቦት #21 ና 22 ቀን በግብጽ ሃገር ደብረ ምጥማቅ በተባለ ቤተክርስቲያን ለተሰበሰቡት ምዕመናን በግልጽ የታየችበት ነው፡፡ ፠27ኛ፤ ግንቦት 23 ቀን ደብረ ምጥማቅ በተባለች ቦታ የታየችበት ነው፡፡ ፠28ኛ፤ ግንቦት 24 ተሰዳ ግብጽ የገባችበት ነው፤ /ኢሣ.1 9፥11፣ ማቴ.2፥13-15/ ፠29ኛ፤ ግንቦት 25 ልጇ መድኀኔዓለም ክርስቶስ የደረቁ በትሮችን ተክሎ ያለመለመበት በዓል ነው፡፡ እነዚህ ከላይ ያየናቸውን የደብረ ምጥማቅ በዓላት (ከግንቦት 21-25) በአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመን በግብፅ ተነሥቶ የነበረው ንጉሥ የግብጽ ክርስቲያኖች በዓሉን እንዳያከብሩ በመከልከሉ፤ ኢትዮጵያውያንም ይህንን በዓል ለማክበር ወደ ግብፅ ይሄዱ ነበርና ፤ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ለመጽናኛ እንዲሆን በሃገራችን የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያምን መሠረተ፤ እመቤታችንም ብዙ ቃል ኪዳንን ሰጠችው፤ ይኸው ቃል ኪዳኗ ሳይታጠፍ በጻድቃኔ ማርያም ዛሬ ድረስ ስፍር ቊጥር የሌለው ብዙ ተዓምራትና የምሕረት ሥራ የሚፈጸምባት ቅዱስ ቦታ ኾና ትገኛለች፡፡ እስካሁን ባለን መረጃ በሃገራችን ግንቦት 21 የደብረ ምጥማቅ ክብረ በዓል በስሟ ተሰይሞ ! በዋነኛነት የሚከበርባቸው ቦታዎች የሚከተሉት ናቸው፤ *1ኛ) #ደብረ_ምጥማቅ_ጻድቃኔ_ማርያም_ገዳም /ሰሜን ሸዋ/ *2ኛ) ሐመረ ብርሃን ደብረ ምጥማቅ ቤተ ክርስቲያን /ጎንደር ከተማ/ *3ኛ) ደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም /አዲስ አበባ/ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #ግንቦት_24_በዓተ_ግብጽ_፤ እመቤታችን እመ አምላክ ድንግል ማርያም ከልጇና ከአረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ ጋር ለ3 ዓመት ከ6 ወር ከተሰደዱ በኋላ ወደ ግብጽ ሃገር ገብታ በሰላም ያረፈችበት ቀን ነው፡፡ #ግንቦት_24_በዓተ_ግብጽ *በአዲስ አበባ ታቦተ ሕጉ የሚነግሥባቸው ቦታዎች፤ ፠እንጦጦ መንበረ ንግሥት ቅድስት ቊስቋም ማርያም፡፡ (365ት ቀናት ሙሉ ዝክር በማኅበረ መድኀኔ ዓለም አዳራሽ የሚዘከርባት ቤ/ክ) ፠ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ቤተ ክርስቲያን፡፡ (የቤ/ክርስቲያኑ ዐጸድ እጅጉን ልብን የሚገዛና የሚማርክ) ፠ ቃሊቲ ደብረ ቊስቋም ማርያም፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ኦ አበው ወእማት አኃው ወአኃት ኢትርስዑነ በጸሎተክሙ (በዘጸለይክዋ በዝንቱ ሥርዐተ ማኅሌት) ለትምህርተ ቤትነ ቀ.ደ.ሰ.መድኀኔዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት፡፡ ꔰ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

እስከዛሬ_ድረስ #በላስታ_ተራራ_ጭላዳ_እህል_እንዳይበላ_ለገዘቱት #በጎንደር_ከተማ_ጅብ_እንስሳቶችን_እንዳይበላ_ለገዘቱት፡፡ ለታላላቆቹ አባቶች ለአቡነ ዓቢየ እግዚእና ለአቡነ ዮሴፍ ዓመታዊ በዓል (ግንቦት 19) በሰላምና በጤና አደሳችሁ፡፡ /#በጻድቃን_ተዓምራት_ማድረግ_ለምትጠራጠሩ፤/ #ጻድቃን_ከበዓለ_ዕረፍታቸው_በኋላ_ዛሬም_ከማማለድም_አልፈው_በቃልኪዳናቸው_ተዓምራት_እንደሚያደርጉ_ኑና_እዩ_ተመልከቱ፡፡ ተዓምራትን ማየት ለምትፈልጉ ኹሉ ሂዳችሁ እዩ!!!!!)፡፡ ፠ ክብረ በዓላቸው ✍️ የአቡነ ዓቢየ እግዚእ በተንቤን መረታ ደብረ መድኃኒት፣ በጎንደር ከተማ ጥንታዊ በኾነው በዓቢየ እግዚእ ኪዳነምሕረት፣ በመቀሌ እንዳ ገብርኤል /እንዳ አቡነ ዓቢየ እግዚእ/፣ በአዲስ አበባ ሞጆ አካባቢ ባለው ቤ.ክ በድምት ይከበራል፡፡) እንዲሁም ✍️ (የአቡነ ዮሴፍ በላስታ ላሊበላ በቅርብ ርቀት በሚገኘውና ወደ ላለበላ የሚጓዝ ኹሉ ሊያየው በሚችል በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘውና በኢትዮጵያ በከፍታ ከራስ ደጀን ተራራ ቀጥሎ በሚገኘው የዋሻ ገዳማቸው ይከበራል)፡፡ ሁለቱም ቅዱሳን አስካሁን ጊዜ ድረስ የሚታይ ባለ አስደናቂ የቃልኪዳን ተዓምራት አላቸው፤ አቡነ ዮሴፍ ከላሊበላ በቅርብ ርቀት በሚገኝ ገዳማቸው #ጭላዳ_እህል_ጠባቂ_ሳያሻው_እህል_እንዳይበላ_ገዝተውታል፤ አቡነ ዐቢየ እግዚእ ቃል ኪዳን በተሰጣቸው ቦታ (ለምሳሌ በጎንደር ከተማ) አሁንም ድረስ #ጅብ_እንስሳቶችን_እንዳይበላ_ገዝተዋል፡፡ #አቡነ_ዮሴፍ_ዘእንጂፋቱ * በወሎ ላስታ ሰውንና ዝንጀሮን በቃል ኪዳን ያስተሳሰሩ #እስከዛሬ_ድረስ_ዝንጀሮ_እህል_እንዳይበላ_የገዘቱ፤ * እመቤታችን ዕጣን እየሰጠቻቸው፤ * ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር የሥላሴን መንበር ያጠኑ (እንደ አቡነ ተክለሃይማኖት፣ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባና አቡነ ዘርዓ ቡሩክ) ናቸው፤ * ወደ ደብረ ሐዊ በመሄድ ሱባዔ ገብተው ቅዱስ ያሬድን በተሰወረበት የተመለከቱ፤ * ገዳማቸው በላሊበላ በቅርበት አቡነ ዮሴፍ ተራራ ተብሎ በሚጠራ ተራራ ቦታ ላይ የሚገኝ የዋሻ ቤ.ክ አላቸው፡፡ #አባ_ዓቢየ_እግዚእ_፤ * አባ ዓቢየ እግዚእ የተወለዱት በ14ኛው መቶ ክ/ዘመን ትግራይ ተንቤን (መረታ) ውስጥ ነው:: የተባረኩ ወላጆቻቸው ያፍቅረነ እግዚእ እና ጽርሐ ቅድሳት ይባላሉ፡፡ * አጥምቀው 'ዓቢየ እግዚእ' ሲሉ ስም ያወጡላቸው የወቅቱ ዻዻስ ሰላማ መተርጕመ መጻሕፍት ናቸው:: ትርጉሙም "በጌታ ዘንድ ታላቅ ሰው" ማለት ነው:: * በሕፃንነታቸው ሌሊት ሌሊት ባሕር ውስጥ ሰጥመው ሲጸልዩ አድረው ቀን ቀን እየተማሩ ብሉይ ከሐዲስ ጠነቀቁ፡፡ * ገና በወጣትነታቸው ወደ ታላቁ መነኰስ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ደብረ በንኮል ሔደው መንኵሰዋል፡፡ * በደብረ በንኰል ገዳም በጾም በጸሎትና በስግደት ተወስነው ከኖሩ በኋላ ወደ ዋልድባ ሔደው የተሰወረች ቤተ ክርስቲያንን አግኝተዋል፤ በጊዜው በ40 ቀን አንዲት ቅጠል ብቻ ለቁመተ ሥጋ ይበሉ ነበር፡፡ ከዚያም ወደ ሃገራቸው ተንቤን ተመልሰው ዛሬም ድረስ ድንቅ ሆኖ የሚታየውን ገዳም መሥርተው ብዙ መናንያንን አፍርተዋል፡፡ * ዓቢየ እግዚእ ገዳማዊና ጻድቅ ብቻ ሳይሆን ሐዋርያዊ አባትም ነበሩ፡፡ ከትግራይ እስከ ደንቢያ ሃገረ ስብከታቸው ነው:: * አንድ ጊዜ ደቀ መዛሙርትን አስከትለው ለስብከት ሲንቀሳቀሱ ተከዜ ወንዝ አካባቢ ደረሱ፤ ቀኑ ነሐሴ 10 ነውና ተከዜ እስከ ገደፉ ሞልቶ ለ3 ቀናት ባለመጉደሉ ከ1,000 በላይ ሰዎች ሲያለቅሱ ደረሱ፤ ጻድቁ ባካባቢው የነበሩት ኢ-አማንያን (አሕዛብ) ቢሆኑም ራርተዋልና "አምላከ ሙሴ" ብለው ጸልየው ወደ ጥልቁ ውስጥ ገቡ፡፡ ቅዱስ ሚካኤል አብሯቸው ነበርና ተከዜ ግራና ቀኝ ተከፍሎ መሃሉ የብስ ሆነ፤ ይህን ድንቅ ያዩ ከ1,000 በላይ አሕዛብም አምነው በጻድቁ እጅ ተጠምቀዋል፤ ይህም ዘወትር ነሐሴ 10 ቀን በቤተ ክርስቲያናቸው (ጐንደር) ይከበራል:: * ከዚያም እያስተማሩ ጐንደር ደረሱ፤ ያኔ ጐንደር በቀሃና አንገረብ ወንዞች የታጠረች አንዲት መንደር ነበረች፤ ጻድቁ ቀን ቀን እየሰበኩ፥ ማታ ዛሬ ቤተ ክርስቲያናቸው የታነጸበት ሥፍራ ላይ ሲጸልዩ ያድሩ ነበር፤ በዚያ ዘመን ጐንደር ውስጥ ጅብ፥ እባብና መሰል አራዊት ገብተው ሕዝቡን ጨረሱት፤ ይህንን የተመለከቱት አባ ዓቢየ እግዚእ ወደ እግዚአብሔር አለቀሱ፤ በፍጹም ልባቸውም ስለ ሕዝቡ ለመኑ፡፡ የለመኑትን የማይነሳ ጌታ ወደ ጻድቁ ቀርቦ ‹‹በስምህ የተማጸኑ፥ በቃል ኪዳንህ ያመኑ፥ በምድር አራዊት አይሠለጥኑባቸውም፤ በሰማይም እሳትን አያዩም፤ ጐንደርንም አራዊት ገብተው ሰውን አይጐዱም፡፡›› ብሏቸው አርጓል፡፡ ጻድቁም የወንጌል አገልግሎታቸውን ፈጽመው ወደ ገዳማቸው ተንቤን ተመልሰዋል፡፡ ዛሬም ድረስ ከብቶችን ጅብና መሰል አውሬ እየበላ የሚያስቸግራቸው ምዕመናን ገድላቸውን ሲያስነብቡ ይርቃሉ፡፡ * አባ ዓቢየ እግዚእ በገዳማቸው ተንቤን ለብዙ ዘመናት በቅድስና ኑረው፥ 3 ሙታንን አስነስተው፥ ብዙ ድውያንን ፈውሰው፥ ብሔረ ብጹዓንን ጎብኝተው፥ የድኅነት ቃል ኪዳንም ተቀብለው፥ በ140 ዓመታቸው ግንቦት 19 ቀን አርፈዋል፡፡ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

#ለ5ኛ_ጊዜ_ደብሩ_ለሰ/ት/ቤቱ የቀድሞውን የሰ/ት/ቤቱን ቦታ እንዲሰጥ ከአ.አ ሐገረ ስብከት በብጹዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ አመራር ሰጪነት መምህር አካለወልድ ተሰማ ውሳኔ አስተላለፉ፡፡ ከዚህ በፊት በብ
#ለ5ኛ_ጊዜ_ደብሩ_ለሰ/ት/ቤቱ የቀድሞውን የሰ/ት/ቤቱን ቦታ እንዲሰጥ ከአ.አ ሐገረ ስብከት በብጹዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ አመራር ሰጪነት መምህር አካለወልድ ተሰማ ውሳኔ አስተላለፉ፡፡ ከዚህ በፊት በብጹዕነታቸው ለደብራችን የተላከውን ደብዳቤ ተከትሎ የደብራችን አስተዳደር የተወሰነውን ውሳኔ ከህግ አንጻር ማስፈጸም አልችልም በማለት በደብዳቤ ቁጥር 6033/13/2013 በቀን 18/08/2013 ዓ.ም ለአ.አ ሐገረ ስብከት አቤቱታ ያቀረበ ሲሆን አቤቱታውንም ተከትሎ በዛሬው እለት ለ5ኛ ጊዜ ውሳኔው እንደጸና ደብዳቤ ለደብራችን አስተዳደር ተልኳል፡፡ በደብዳቤውም መሰረት ውሉ አሁን እንዲቋረጥ ወይም እንዲሻሻል እና በዚህ ዓመት የትምህርት መጨረሻ ድረስ የመዋዕለ ህጻናት ተማሪዎች እንዲማሩ የተወሰነውን ውሳኔ ያጸና ነው፡፡ ሰንበት ት/ት ቤታችን ምንም እንኳን በበርካታ ፈተናዎች ውስጥ ያለ ቢሆንም ነገር ግን መድኃኔዓለም እየቀደመ ፈተናዎቹን እያስወገደ በሰከነ እና በበሰለ መንገድ እየሄደ በገዳማውያን አባቶቻችን እና በሕጻናቱ ጸሎት እዚህ ደርሷል፡፡ የደብራችን አስተዳደር አሁንስ ለ5ኛ ጊዜ የመጣውን ውሳኔ ይፈጽም ይሆን? ደብራችንስ ወደ ቀደመ ሰላሙ ይመልስልን ይሆን? ወይስ ከእንደገና አቤቱታ ለሀገረ ስብከቱ ያቀርብ ይሆን ? ስለሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን!!!