ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 380 подписчиков, занимая 5 573 место в категории Религия и духовность и 2 194 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 380 подписчиков.

Согласно последним данным от 06 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 32, а за последние 24 часа — -4, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 22.44%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.50% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 449 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 461 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 20.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 07 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 380
Подписчики
-424 часа
-257 дней
+3230 день
Архив постов
ስምዕዋ ለዝንቱ ምክር እምጥንታ እስከ ተፍጻሜታ፤ (ይህችን ምክር ከመጀመሪያዋ እስከ መጨረሻዋ አድምጧት፡፡) #የሐበሻ_ፒኮክ_!!!??? (ወቅታዊ ጉዳይ) https://www.youtube.com/watch?v=q4nGwAZeNIA * ዘዳ. 30፥11፤ ‹‹ …… ታደርገው ዘንድ ቃሉ ለአንተ እጅግ ቅርብ ነው……. ፡፡›› * ምሳ. 22፥28፤ ‹‹አባቶችህ የሠሩትን የቀድሞውን ድንበር፥ ምልክት አታፍርስ፡፡›› ፠ ትውልድ ሆይ የት ነበርክ!?፤ /ምን ያልተለወጠ ነገር አለና ነው፣ ….. ኡኡታ እሪታ በቤተ መንግሥት ስለተሠራው ፒኮክ ብቻ ነው እንዴ? የአባቶቻችን ድንበር ማፍረስ የተጀመረው በ1966 ዓ.ም. ጀምሮ ነው፡፡ ፠ ትውልድ ሆይ እወቅ፤ ፠ ትውልድ ሆይ ወደ ልብህ ተመለስ፤ ፠ ትውልድ ሆይ ለአንበሳው ምስል ብቻ ሳይሆን፤ ለአንበሳዊ አስተዳደር ዘብ ልትቆም ያስፈልጋል፤ ፠ አንበሳው ተነሥቶ የፒኮክ ሐውልት መደረጉ ብቻ አይደለም ሊያስቆጨን የሚገባው፤ የአንበሳውም ታሪክ በመጥፋቱ ነው፡፡ ስለአንበሳው ታሪክ፤ አንበሳውን ያስቀመጠው ማነው፤ ማነውስ ያራቀው የሚለውን ታሪክ ነው ማወቅ የሚገባን፡፡ # አንበሳዊ፣ ዘውዳዊ፣ አሐዳዊ … አስተዳደር፥ ግዛት ምን ማለት ነው #ሞዐ_አንበሳ_ዘእምነገደ_ይሁዳ_ማለት_ምን_ማለት_ነው?፤ የአፄ ኀይለ ሥላሴ፣ የአፄ ምኒልክ፣…… የሌሎችም ነገሥታት አስተዳደር ማለት ነውን??? መነሻውስ ምንድን ነው??? ፠ በዋናነት አስተዳደሩ ሲከበር፤ የአንበሳውም ምልክት ይከበራል፡፡ ፠ ለሙሴ የተሰጠውን ትዕዛዘ ኦሪት እንቀበላለንን? እውን እየተቀበልነው ነውን??? * ከ1966-አሁን ….. የተሠራ ምን መልካም ነገር አለ? *** የፈረንጅን ጋዜጣ ብቻ ያነበቡ፥ የኢትዮጵያን ታሪክ ያልጠነቀቁ፥ በፈረንጅ ትምህርት ጥርሳቸውን ሸርፈው ያደጉ ስለ ኢትዮጵያ ታሪክስ ምስክር መሆን ይችላሉን? የወረቀት ላይ ሕግ፤ የአፈ ቀላጤ አስተዳደር፤ … ምን ያመጣው ነገር አለ፡፡ ፠ በጥንታውያን መጻሕፍት (በወንጌል) በሐረጋት፣ በሥርዐተ በኑባሬ፣ በሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ዐምድ ላይ የተሣለችው እውን ፒኮክ ናትን??? አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌስ ጣዖስ ብለው የገለጿትስ የኢትዮጵያን መቄ፥ ዋርዴ፥ ዋርድዬ ነውን? **** መቄ፥ ዋርዴ፥ ዋርድዬና ፒኮክን ምን አገናኛቸው፡፡ ፠ ሶራ ምንድን ነው፤ የሶራ ላይ ወፌ የተባለችውስ ፒኮክ ናትን?? *** ጃንሜዳ ገበያ ቦታ መሆኑስ ተገቢ ነውን፡፡ *** የሃይማኖትና የምግባር ኪሳራ ምን ማለት ነው፡፡ በተገለጸው ሊንክ ላይ ገብተው ያድምጡ፡፡

‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በሚያዝያ ፳፪/፳፻፲፪ ዓ.ም
+1
‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በሚያዝያ ፳፪/፳፻፲፪ ዓ.ም በቀ/ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ ጋብቻህን የፈጸምከው የሰ/ት/ቤታችን አባል ወንድማችን፤ #ተክሌ_ሰይፉ_ከመቅደስ_ ጋር የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤ የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፥ ያጣምራችሁ፥ ያዋሕዳችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡ ✤ ‹‹ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንዲሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡›› ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፖሊካርፐስ በላከው መልእክቱ ✤ ከተጋባችሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአያዕቆብ፡፡ /ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

#ሚያዝያ_23_በዓለ_ክላሌሁ_ለሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ፡፡ ኦ ፍጡነ ረድኤት … ብለን እኛ ኢትዮጵያውያን በእምነት ኾነው ስንጠራው፤ ከዐይን ጥቅሻና ከዐውሎ ነፋስ ይልቅ ፈጥኖ የሚደርስልን የሊቀ
+5
#ሚያዝያ_23_በዓለ_ክላሌሁ_ለሊቀ_ሰማዕታት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ፡፡ ኦ ፍጡነ ረድኤት … ብለን እኛ ኢትዮጵያውያን በእምነት ኾነው ስንጠራው፤ ከዐይን ጥቅሻና ከዐውሎ ነፋስ ይልቅ ፈጥኖ የሚደርስልን የሊቀ ሰማዕታት የቅዱስ ጊዮርጊስ የበዓለ ዕረፍቱ ክብረ በዓል ነው፡፡ #ኮከበ ክብር፥ *ሊቀ ሰማዕታት፥ *መክብበ ሰማዕታት፥ *የፋርስና የቤሩት ኮከብ፥ *የልዳ ፀሐይ፥ *የኢትዮጵያ ገበዝ፥ *ባለ ፀዓዳ ፈረስ፥ *፸ ነገሥታትን ድል ያደረገ፥ *በሕይወቱ ክርስትናን ያስፋፋ፥ በዕረፍቱ ክርስቶስን የሰበከ፥ ከዕረፍቱ በኋላ ዛሬን ጨምሮ ፈጥኖ የሚራዳ፥ *፫ት ጊዜ ሞቶ ፫ት ጊዜ የተነሣ፥ *፯ት አክሊላትን የተቀናጀ፤ *እመቤታችንን በጣም ስለሚወድ ስሙ ከስሟ፥ ዝክሩ ከዝክሯ፥ ፍልሰቱ ከፍልሰቷ ጋር የተባበረ እንዲኾን ያደረገችለት፤ #የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስን በዓለ ክላሌ (ሚያዝያ 23) ከዋይዜማው ጀምሮ በመላው ሃገራችን የሚቆመውን ሙሉውን ሥርዐተ ማኅሌት አቅርበንላችኋል፡፡ #አማን በአማን፥ አማን በአማን፤ ኮከበ ልዳ፥ ፀሐየ ፋርስ፡፡ #በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፤ ዘአንበሩ ብየ አክሊለ ሞገስ፤ መዘምረ እኩን ለጊዮርጊስ፡፡ #ኀያል መስተጋድል ኀያል ኮከበ ክብር፤ ኀያል ገባሬ ተአምር፤ ጊዮርጊስ ቅዱስ ለእግዚአብሔር፡፡ #በእንተ ጊዮርጊስ ፍቁርከ (ሰማዕትከ፥ ምዕመንከ)፤ ምህላነ ስማዕ በዕዝንከ፡፡ #ሥርዐተ ማኅሌቱን ሌሎችም እንዲደርሳቸው ከዚህ በታች የሰፈረውን ገጾችንን LIKE, SHARE, INVITE, SUBSCRIBE ያድርጉ፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihan

#የ፯ኛ #ዓመት_መታሰቢያ ****(የወንድማችን ብርሃነ መስቀል (ስለሺ ብርሃኑ) 7ኛ ዓመት በማስመልከት #የምትፈልጉትን_ጥያቄዎች_ጠይቁ፡፡ ሊቃውንትን ጠይቀን፤ መጻሕፍን አገላብጠን የምንመልስ መሆኑን እንገልጻለን፡፡) እስመ ተሀጥኦ መምህርሰ እኩይ ግብር ውእቱ፡፡ (የመምህር መታጣቱ ይጎዳል)፡፡ /ቅ.ዮሐ.አፈ./ ፠ #ስለሺ ወንድሜ በነበረህ ለዛ፣ በሚጥመው ቃልህ በስብከት (በትምህርት) መዐዛ፣ ቀና በል ተናገር ዝምታ አታብዛ፣ ሁሉም ያልፋልና ድንገት እንደዋዛ፡፡ ፠ ሚያዝያ 22/2012ዓ.ም. ወንድማችን ስለሺ ብርሃኑ (ብርሃነ መስቀል) በሥጋ ከተለየን 7ኛ ዓመቱ ኾነ፤ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ነፍሱን ከቅዱሳኑ ጋር ይደምርልን፥ ነፍስ ይማርልን፡፡ #መሐራ_እግዚኦ_ለነፍሰ_እኁነ_ብርሃነ_መስቀል፡፡ ‹‹ #ያገለገለህን_ሰው_ሞት_ቸል_አትበል_፡፡›› ሲራክ 38፥26 ‹‹ የሞተ ሰውስ ዐረፈ፤ ነገር ግን ነፍሱ ታርፍ ዘንድ ተዝካሩን አውጣለት፤ ከዚያ በኋላ ልቅሶህን ተው፡፡›› ሢራክ ፴፷፥፳፫ #ያረፈበት_ቀንም፤ * ዓለም ከተፈጠረ፥ ዘመን ከተቈጠረ በ7506 ዓመት (በፀሐይ)፤ * በ2006 ዓመተ ምሕረት (በፀሐይ)፤ * በ58 ዐውደ ቀመር፤ * በወንጌላዊ ማርቆስ፤ * በ1 ጥንተ ዮን፥ በ6 እንድክትዮን፥ * በአልቦ አበቅቴ፤ * በሚያዝያ ወር በ22ኛ ቀን (በፀሐይ)፤ ** በ26 ሠርቀ ሌሊት፤ *በ1730 ዓመተ ሰማዕታት ነው፡፡ #በዕለቱ_ከቀረቡ_ግጥሞችና_ቅኔዎች የተወሰኑትን እነሆ ብለናችኋል፡፡ (ግጥሞቹና ቅኔዎቹ ከሕይወቱ ታሪክ ጋር /በፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አገልጋይ ከመኾኑ ጋር፣ 2ት ሕንፃ ቤተ ክርስቲያንን ከማሠራቱ ጋር፣ በእንጦጦ ዳግማዊት ስሪንቃ ቅድስት አርሴማ ጠበል ቦታ ከማገልገሉ ጋር ….. የተመሳጠሩ ድንቅ፥ ድንቅ የሆኑ ግጥምና ቅኔዎች ናቸው)፡፡ ፠ #ስለሺ ወንድሜ በነበረህ ለዛ፣ በሚጥመው ቃልህ በስብከት መዐዛ፣ ቀና በል ተናገር ዝምታ አታብዛ፣ ሁሉም ያልፋልና ድንገት እንደዋዛ፡፡ ፠ #ክፉ ሰው ሞት በሰው ላይ ነገረ ሠሪ፣ ለምድር አሽከርካሪ ለሰማይ አብራሪ፣ ደኅና ሰውን መስሎ የቅርብ ዘመድ መካሪ፣ ደርሶ የሚያጣላ ፍጡርን ከፈጣሪ፣ ክፉ ሰው ሞት በሰው ላይ ነገረ ሠሪ፣ ዛሬ ምን በደለው ስለሺ የብዙዎች(የብዙኃን) አስተማሪ፡፡ ፠ #በነገረ ሠሪ ኅልፈት ክፉ መሃለኛ፣ ከፊትህ ብትርቅ ድንገት ሕይወት ወረተኛ፣ የነበረው ቀርቶ ብትሆንም ብቸኛ፣ ብቸኛ ነኝ አትበል ስለሺ በሠራኸው ሥራ ነህና ዝነኛ፡፡ ፠ #ስለሺ ለብዙዎች ብሎ የጸለየው ጸሎት ተግቶ፣ በማርያም ምልጃ ከእግዚአብሔር ተሰምቶ፣ ሲሻው የነበረ እንዲሰጥ ጽዋ ሞት ተቀድቶ፣ ተቀበለ ዛሬ ከቅዱስ ዑራኤል እጅ ነስቶ፡፡ ፠ #ሥጋም በምድር ላይ መከራን ታገሺ ነፍስም በሰማይ ላይ በገነት ንገሺ፣ ክርስቶስ በዳግም ትንሣኤ እስኪነግስ ስለሺ፡፡ #ጕባኤ_ቃና_ቅኔ ……. ቃልየ አጽምዕ እግዚኦ ወለቡ ጽራሕየ ……. በሕማም ወጸዕር ሶበ ወጽአት ለብርሃነ መስቀል ነፍሱ፤ እጼ ወዝኅር አዝማዱ ንብረተ ሥጋሁ ወረሱ፡፡ #ሥላሴ_ቅኔ …….. ይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አበዊነ …….. ብርሃነ መስቀል በአዕይንቲሁ ወኢይርዓይ መልክዐ ብእሲት ዓለም አበሳ ዘብዙሃነ ፈተነ፤ ሥጋ ሰብእ ዓይነ እንቲአሁ በልብሱ ከደነ፤ በቃለ ሐዲስ ወንጌል እምንእሱ እስመ አእመረ ወኮነ፤ ወበዝ ዓለም እስከ ሀለውነ፤ ኢርዕዮተ ዓለም ብእሲት ዘገብሮ እኁነ፣ ለኵልነ ትምህርተ ይኵነነ፡፡ #መወድስ_ቅኔ ……. ፍትሃ ሊተ እግዚኦ ወተበቀል በቀልየ ………. እንበለ ኢምንት ፍጥረተ ኀበ ተኀሰበ በዓይነ አብዕልት ሕዝብ ወበእግረ ንዑስ ወዐቢይ፤ ዘይትከየድ ዘልፈ መቃብረ ሥጋ ነዳይ፤ ሞተ አቤል ወርኅ ጊዜ አንገሦ፤ በዓለም ተፈጥሮተ ሥጋ ዘብዙኅ ጌጋይ፤ ይቀውም ከመ ቆሙ ዲበ ዘገፍዕዎ ቅድመ ገበርተ ዓመጻ ወእከይ፤ ንሕነኒ ይደልወነ ከመ ንጸልይ፤ ጸሎተ ንስሓ መንገሌሁ ለአምላከ ምድር ወሰማይ፤ ሊቀ ካህናት ክርስቶስ እምነ አእላፍ ኅሩይ፤ በኢያእምሮ ዘአበስናሁ ወዘጌጋይ ናሁ ከመ ይሥረይ፨ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#በተለያዩ_ምክንያቶች_የቤተ_ክርስቲያንን_ይዞታዎችና_መብት_መዳፈር_ይቁም፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደርን፤ የጠቅላይ ሚንስቴር ጽ/ቤትንና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትን በጽኑ እንቃወማለን፡፡ አዲስ አበባ አሁን ባለችበት ሁኔታ ስትቈረቈር፤ ፠ ለመስቀል አደባባይነት ከግል ቦታቸው ላይ ከፍለው የሰጡት ራስ ብሩ ወልደአረጋይ ናቸው፡፡ ፠ ጃን ሜዳ (ጃንሆይ ሜዳ) በዓለ ጥምቀት መከበር የጀመረው ከ1887 ዓ.ም. በአፄ ምኒልክና በእቴጌ ጣይቱ ፈቃድ ነው፡፡ ይህ ሜዳ የጃንሆይ ሜዳ የተባለበት ምክንያት፤ * ነገሥታት ለመሾም ለመሻር፣ ዳኝነት ለመስጠት፣ ሊቃውንትን ለመሾምና፣ ዐዋጅ ሲያስነግሩ በቤተ መንግሥታቸው አቅራቢያ በሚገኝ ሜዳ ላይ የጃኖ ድንኳን ተክለው ያስነግራሉና * አፄ ምኒልክ ለጥምቀተ ባሕር የሰጡት ቦታ በመሆኑ፤ * ልጅ ኢያሱ አልጋ ወራሽ መሆናቸው በግንቦት 10 ቀን 1901ዓ.ም. ዐዋጅ ያስነገሩበት በመሆኑ፤ * ‹‹ንሥረ ተፈሪ›› የተባለው የመጀመሪያው አውሮፕላንም በ12921ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ያረፈውም በዚሁ ሜዳ በመሆኑ ጭምር ነው፡፡ ፠ሃገራችንና ዓለማችን በኮሮና፣ በረሃብ፣ በአንበጣ መንጋ በምትሸበርበት ዘመን #የ2.5 ቢሊዮን (ልብ በሉ ሚሊዮን አይደለም ቢሊዮን ብር ነው) ፕሮጀክት አደባባይን አፍርሶ መገንባት ምን ይሉታል??? * ይህ በር በርካታ ቬንትሌተሮችን ይገዛልል * ይህ ብር ለበርካታ ለተራቡና ለተጎዱ ሰዎች ይሆናል * ይህ ብር ለዐባይ ግድብ ማስፈጸሚያ ይሆናል * ይህ ብር ለትውልድ የሚተላለፍ ብድር ከምንበደር ይልቅ ለተለያዩ ነገሮች መሆን ይችላል፤ ፠ ….. ነገሩ … ከምርጫ በፊት እኛ እያለን ያልተገነቡ ግንባታዎች መቼም አይገነቡም ይመስላል፡፡ ….. በዚህ መንገድ ያሉ ጥቂት አመራሮችና አማካሪዎቻቸው ‹‹ሮም በአንዴ አልተገነባችም!!!!!›› የሚለውን ብሂል ያስተዋሉ አይመስሉም፡፡ ፠ #የአዲስ_አበባ_ከተማ_አስተዳደር፤ በርካታ ቦታዎች (የራሱን የመስተዳደሩን ግቢ፣ ጃንሜዳ አጠገብ የሚገኘው የመከላከያ ሠራዊት ግቢ፣ ……..) እያሉት የቤተ ክርስቲያን ይዞታ ላይ ባለቤቷን ሳያስፈቅድ በምንአለብኝነት በጊዜያዊነት ስም መውሰዱ ተገቢ አይደለም እየተጓዘ ያለበት መንገድም እንዲሁ የተሳሳተ ነው፤ ፠ #የጠቅላይ_ሚንስትር_ጽ/ቤት የመስቀል አደባባይ ፓርክ፣ የእንጦጦ ፓርክ፣ የቤተ መንግሥት ፓርክ፣ የሸገር ፓርክ፤ …… እያለ መቅደም ያለባቸውን ነገሮች ሳያስቀድም መሯሯጡ (ሲሮጡ የታጠቁት…) ሆኗል ነገሩ፤ የይዞታ ባለቤቷን ቤተ ክርስቲያንን እንዲሁም የሃገሪቱ ሕዝቦችና ባለሙያዎች ባልመከሩበት፣ የከተማ መስተዳደሩ ባወጣው የማስተር ፕላን ላይ ባልተካተተበት፤ እንደ ….. ብድግ ብሎ ለግንባታ መነሣቱ ያሳዝናል፡፡ በአንድ በኩል ድሃ ሀገር ነች ተብሎ ከብዙ ሃገራት ተተኪ ትውልድ እንኳን ከፍሎ የሚጨርሰው የማይመስል ዕድና ብድር ይቀበላል፤ በሌላ በኩል 2.5 ቢሊየን ብር ካላፈሰስኩ እያለ ይሮጣል፡፡ ፠ #የሕዝብ_ተወካዮች_ምክር)ቤት፤ መቼ ሊነቁ ነው፤ ከተለያዩ የመንግሥት አመራርና አካላት የሚመጣለቸውን ረቂቆች (ያውም የ2.5 ቢሊየን ፕሮጀከት፣ ያውም የይዞታዋ ባለቤት ባለተጠየቀችበትና ይሁንታዋን ባለሰጠችበት፣ ያውም በዘመነ ኮሮና (ቬንትሌተር የለንም፣ ሳኒታይዘር አልኮል ….. ምናምን የለንም እያልን እጃችንን ለእርዳታ እየዘረጋን ባለንበት ወቅት) የ2.5 ቢሊየን ብር ፕሮጀከት ማጽደቃቻው እንዴት ይሆን፤ መቼ ይሆን የምትነቁት፡፡ (ወይ ስሜን መልስ ወይ ተግባሬን ሥራ ብሏል እስክንድር ጠቢብ ፤ ወይ የሕዝብ ተወካይ አባላት የሚለውን ስም ልቀቁ፤ ወይ የሕዝብ ተወካይነትን ተግባር በአግባቡ ሥሩ፡፡ ****ስለ መስቀል አደባባይ ገና መፍረስ ሲጀምር የጻፍነውን ጽሑፍ በሚያዝያ 5 ላይ ጽፈነዋል፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

፠ በዐረብ ሃገራት ያላችሁ ወገኖቻችን ያለባችሁን ችግሮች በተመለከተ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባል በሆነው በሊቀ ልሳናት ዘማሪ ቸርነት ሠናይ ውይይት እየተደረገ ስለሆነ፤ እኅቶቻችን በዚህ የዋስትአ
+1
፠ በዐረብ ሃገራት ያላችሁ ወገኖቻችን ያለባችሁን ችግሮች በተመለከተ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባል በሆነው በሊቀ ልሳናት ዘማሪ ቸርነት ሠናይ ውይይት እየተደረገ ስለሆነ፤ እኅቶቻችን በዚህ የዋስትአፕ ቊጥር በመደወል የውይይቱ ተካፋይ ይሁኑ፡፡ 2024468035-whats app ደውሉ፡፡ +++ በዐረብ ሃገራት …. በአጋጣሚ የኮሮና ቫይረስ በሽታ የተያዙ ካሉ በአቅራቢያችሁ በቤይሩት የሚገኘውን የቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን እምነት አሻሿቸው (ጠበሉን አጠጧቸው፡፡) ፠ ሁለት ልብሶች ያሉት ከማብዛት ልብስን፤ ለሌለው ያድለው ሁለተኛውን፡፡ ፠ እርስ በእርሳችሁ ተረዳዱ፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#አስደሳች_ዜና_ ፠ ከ1000-1400 ዓመታት ዕድሜን ያስቈጠረው ደብረ ጊዮርጊስ (ጊዮርጊስ ገዳም) በቁፋሮ ተገኘ፡፡ ፠ በዋርሶው ዩኒቨርስቲ የፖላንድ የሥነ ቁፋሮ ሳይንስ ማዕከል በDr. Michela
+1
#አስደሳች_ዜና_ ፠ ከ1000-1400 ዓመታት ዕድሜን ያስቈጠረው ደብረ ጊዮርጊስ (ጊዮርጊስ ገዳም) በቁፋሮ ተገኘ፡፡ ፠ በዋርሶው ዩኒቨርስቲ የፖላንድ የሥነ ቁፋሮ ሳይንስ ማዕከል በDr. Michela Gaudiello በሚመራ ባለሞያዎች ረጅም ቁመት ያላቸውና በርካታ ምሰሶዎች ያሉት የመካከለኛው ዘመን ቅርስ በቁፋሮ መገኘቱ ተገለጸ፡፡ ፠ ‹‹ሰማያት ደስ ይበላቸው፥ ምድርም ሐሴትን ታድርግ፤ በአሕዛብም መካከ፤ እግዚአብሔር ነገሠ በሉ፤ ባሕርና ሞላዋ ትናወጥ፤ በረሀ በእርሷም ያሉ ሁሉ ሐሤትን ያድርጉ።›› ፩ኛ ዜና ፲፮፥ ፴፩- ፴፪ ምንጭ፤ http://scienceinpoland.pap.pl/en/news/news,81911,polish-scientists-discover-1000-year-old-church-walls-ethiopia.html

በአሜሪካ ሜሪላንድ የወይዘሮ ወገኔ ደበሌ ሥርዐተ ቀብር ይሄን ይመስላል፡፡ ባሏ ብቻውን ባልተቤቱን የሸኘበት ሥርዐት፡፡ ውስተ ሃገሪትነ ኢትዮጵያ ህየ ነበርነ ወበከይነ፤ በከመ ርኢነ በነጽሮተ መክስተ
+1
በአሜሪካ ሜሪላንድ የወይዘሮ ወገኔ ደበሌ ሥርዐተ ቀብር ይሄን ይመስላል፡፡ ባሏ ብቻውን ባልተቤቱን የሸኘበት ሥርዐት፡፡ ውስተ ሃገሪትነ ኢትዮጵያ ህየ ነበርነ ወበከይነ፤ በከመ ርኢነ በነጽሮተ መክስተ ርዕይ ዘተገብረ በሃገረ አሜሪካ፡፡ ከመዝ ተናገርነ…. (በሃገራችን ኢትዮጵያ ሆነን በአሜሪካ ሃገር የሆነውን ነገር ባየን ጊዜ አለቀስን፡፡ እንዲህ አልን፤ ፠ ይህ በሽታ ለጊዜው ከማንኛውም ወገን መድኀኒት አልተገኘለትም፤ ምክንያቱም፤ + ብዙዎቻችን አሁንም በኅሊናችን ጓዳ፥ በአእምሯችን ሰሌዳ መጥፎ መጥፎ ነገሮችን ከማመላለስ አልተከለከልንምና፤ ልቡናችን ክፉ ከማሰብ፥ አንደበታችንም ክፉ ከመናገር አለታቀቡምና፡፡ + ብዙዎቻችን ኮሮና ቢጠፋ ከአሁኑ ልንሠራ የምናስባቸው ነገሮች መጥፎ ነገሮችንና በእግዚአብሔር ዘንድ አስጸያፊ ነገሮችን ነውና፡፡ ፠ እንዲህ ያለውን ልቅሶ፤ በሰው ቃል ማጽናናት አይቻልም፥ በእግዚአብሔር ቃል ግን ማጽናናት ይቻላል፡፡ + ሞት ሀገር መለወጥ ነው (ሀገር ለውጦ ወደ ሰማያዊ ሀገር መሄድ ነው)፤ ብንኖር ለእግዚአብሔር ብንሞት ለእግዚአብሔር እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ፡፡ + በሞት አጠገብ ሕይወት፥ በመቃብር አጠገብ ትንሣኤ አለን፡፡ ‹‹በምድር ያለው ምድራዊ ቤታችን ቢፈርስም በሰማይ በእግዚአብሔር ዘንድ የሰው እጅ ያልሠራው ዘለዓለማዊ ቤት እንዳለን እናውቃለን፡፡›››› እንዲል ፪ኛ፡ቆሮ፡፭፥፩፡፡ ‹‹ኃዘና ስምዒ ወብካያ ለሃገረ አሜሪካ፡፡›› አምላከ አበው መድኀኔ ዓለም ነፍስ ይማርልን፤ ከደጋጎቹ ከአብርሃም ከይስሐቅና ከያዕቆብ ጋራ ያኑርልን፡፡ የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-

ጎንደር አቡን ቤት ቅዱስ ገብርኤል፡፡ ፎቶ፤ በቀ.ደ.ሰ. ፍኖተ ሕይወት፡፡
+1
ጎንደር አቡን ቤት ቅዱስ ገብርኤል፡፡ ፎቶ፤ በቀ.ደ.ሰ. ፍኖተ ሕይወት፡፡

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤ #ክፍል#፬_ (#ሰይጣን_የቅዱሳን_መላእክትን_ቃል_ምሥጢር_እንደሚሰማና_ #የሰማው_ከመደረጉ_በፊት_ለሰዎች_በመናገር_እንደሚያስት፤ #ሰይጣን_ከተፈጠረ_ጀምሮ_በዘመን_ብዛት_ሰውን_ያሚያስትበት_ብዙ_ጥበብ_እንዳለው፤ #የክርስቶስ_ሰው_መሆን_ከሰይጣን_የተሰወረ_እንደነበር) +አባ ጳውሊ፤ ወደ ሰማይ ወጥታችሁ የመላእክትን ቃል ትሰማላችሁን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ፈጽመን አንወጣም አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ ስለምንድነው የማትወጡት? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ከክብራችን ከተዋረድን በኋላ በቧለሟልነት ሥልጣን ወደዚያ እንቀርብ ዘንድ አይፈቀድልንም አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ሰዎች እናንተ ወደ ሰማይ እንደምትወጡና ከመላእክት ጋር እንደምትነጋገሩ የሚናገሩት ዋሽተው ነውን? አለው፡፡ ሰይጣን፤ መላእክት ከምስጋና በቀር አይናገሩምና አዎን ዋሽተው ነው አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ እንግዲያ ከመደረጉ በፊት አስቀድመህ ለሳኦል ምሥጢር የገለጥክለት በምን አውቀህ ነው? አለው፡፡ /፩ሳሙ.፳፰፥፲፯/ ዲያብሎስ፤ እግዚአብሔር ለሳሙኤል ሲነግረው ሰምቼ ነው አለው፡፡ /፩ሳሙ.፲፮፥፩) እግዚአብሔር ለመላእክቶቹ ምሥጢር ሲነግራቸው እኛም ባለንበት ሆነን እንሰማለን፡፡ ያን ጊዜ ፈጥነን ሄደን ከመደረጉ በፊት ለሰዎች እንነግራቸዋለን፡፡ ሰዎች ሁሉ በየሀገሩ እኛ የነገርናቸውንና በሕልም ያሳየናቸውን ይናገራሉ አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ሰዎች ነገርህን እንደምን አምነው ይቀበሉሃል? የመልክህን ክፋት የመዓዛህን ክርፋት አያውቁምን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ሰዎች ሁሉ እንደ አንተ ክፉ መሰሉህ? ለአንተ ክፉ መስዬ እታይሃለሁ እንጂ በዚህ ዓለም መዓዛዬን ለማሽተትና መልኬን ለማየት እኔን የሚሹ ብዙ ሰዎች እንዳሉ እነግርሃለሁ፡፡ እነርሱ ወደ እኔ መጥተው እገለጽላቸው ዘንድ ይለምኑኛል እንጂ እኔ ወደ እነርሱ አልሔድም አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ ሰዎች ስለምን ይወዱሃል? ይህ የሚሆነው ለምንድን ነው? ዲያብሎስ፤ እኔን ለማየት በሚፈልጉት መልክ ተመስዬ በመገለጽ ስለማስደስታቸው ነው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ መልክህን መለወጥ እንደምን ይቻልሃል አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ይህ የሚያስደንቅ አይደለም ሰይጣን የብርሃን መልአክን ይመስላል ብሎ ጳውሎስ የተናገረውን አልሰማህምን፡፡ /፪ቆሮ.፲፩፥፲፬/ ++አባ ጳውሊ፤ የማታውቀውን ምሥጢር ማስመሰል እንደምን ይቻልሃል አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ #ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ በዘመን ብዛት የሰበሰብኩትና የማውቀው ብዙ ጥበብ አለኝ፡፡ #ነገር ግን የክርስቶስ ሰው መሆን ብቻ ተሰወረብኝ እንጂ አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ የክርስቶስ ሰው መሆን ስለምን ተሰወረብህ? ዲያብሎስ፤ ከእኔ የተሰወረበትን ምክንያት አላውቅም፡፡ ነገር ግን አውቄስ ቢሆን ክፉና በጎ ለይተው ያላወቁ ብዙ ሕፃናትን በሄሮድስ አድሬ ባላስገደልኩም ነበር አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ በገዳመ ቆሮንቶስ አንተ ፈትነኸዋልና አላውቅም አትበል አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ በሰውነቱ ስለሚሠራው ሥራ እንደ ነቢይ፥ እንደ ንጉሥ ይመስለኝ ነበርና ባውቅም እጠራጠር ነበር፡፡ ስለዚህ እፈትነው ዘንድ በእርሱ ላይ ተነሳሁ አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ እርሱ በእውነት አምላክ መሆኑን ያወቅኸው መቼ ነው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ኃይሌን እስከሚያደክመው ድረስ አላወቅሁም ነበር፡፡ መላእክት ሲያመሰግኑት፥ ሙታን ሲነሡ፥ ምድር ሲነዋወጥ፥ ፀሐይ ሲጨልም አየሁ፤ ያን ጊዜ የዓለም ብርሃን፥ የፍጥረታት ፈጣሪ እርሱ በመስቀል ላይ እንደተሰቀለ አወቅሁ አለው፡፡ #የሰይጣናት_አለቃና_ታዛዥ_እንዳላቸው፤ #ገሃነም_ስለመኖሩና_ዲያብሎስ_ለምን_ንስሐ_እንደማይገባ) #ክፍል_፭.…#ይቀጥላል_ይጠብቁን/ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

አዳም ኀሙስ፡፡ ሉቃ. ፳፬፥፳፭-፵፱ ለአዳም ዘአግብዖ ውስተ ገነት፤ ወለፈያታዊ ኀረዮ በቅጽበት፡፡ (አዳምን ወደ ገነት ያስገባው፤ ፈያታዊ ዘየማን ጥጥስንም በቅጽበት መረጠው፡፡)
አዳም ኀሙስ፡፡ ሉቃ. ፳፬፥፳፭-፵፱ ለአዳም ዘአግብዖ ውስተ ገነት፤ ወለፈያታዊ ኀረዮ በቅጽበት፡፡ (አዳምን ወደ ገነት ያስገባው፤ ፈያታዊ ዘየማን ጥጥስንም በቅጽበት መረጠው፡፡)

አዳም ኀሙስ፡፡ ሉቃ. ፳፬፥፳፭-፵፱ ለአዳም ዘአግብዖ ውስተ ገነት፤ ወለፈያታዊ ኀረዮ በቅጽበት፡፡ (አዳምን ወደ ገነት አስገባው፤ ፈያታዊ ዘየማን ጥጥስንም በቅጽበት መረጠው፡፡)

የቀ.ደ.ሰ. መድኀኔ ዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት የበዓለ ትንሣኤ እንኳን አደረሳችሁ መልእክት፤ በሚከተለው የዩቲዩብ ገጻችን ያገኛሉ፡፡ https://www.youtube.com/watch?v=F25FXo_nx_M&feature=youtu.be

#ሰሙነ_ፋሲካ (#ከትንሣኤ_እስከ_ዳግም_ትንሣኤ) (ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ) ከትንሣኤ እሑድ ቀጥለው ያሉት ዕለታት ሰሙነ ፋሲካ ወይም ትንሣኤ እየተባሉ የየራሳቸው ምሥጢራዊ ስያሜ አላቸው፡፡ ይኸውም፡- ✞ #ሰኞ፤ #ማዕዶት ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡ ጌታችን በሞትና ትንሣኤው ነፍሳትን ከሲኦል አውጥቶ ወደ ገነት አሻግሮ ለማስገባቱ መታሰቢያ ሆና «ፀአተ ሲኦል ማዕዶት» ትባላለች፡፡ ዮሐ. 19-18 ሮሜ. 5-10-17 የዳግም ትንሣኤው ማግሥት ያለችው ግን ገበሬው፤ ወንዶቹ እርሻ ቁፋሮውን፣ ንግዱን፣ ተግባረ እዱን ሁሉ ሴቶቹ ወፍጮውን፣ ፈትሉን፣ ስፌቱን የሚጀምሩባት ዕለት ስለሆነች «እጅ ማሟሻ» ሰኞ ትባላለች፡፡ ✞ #ማክሰኞ፤ #ቶማስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29 የትንሣኤው ዕለት እሑድ ማታ ጌታችን በዝግ ቤት ገብቶ ለሐዋርያት ሲገለጽ ቶማስ ሐዋርያ አልነበረም ኋላ ከሔደበት ሲመጣ ሌሎቹ ሐዋርያት ትንሣኤውን ቢነግሩት እኔ ሳላይ አላምንም በማለቱ በዚህ ጥያቄው መሠረት በሳምንቱ ጌታችን በድጋሚ ስለተገለጸ ለዚህ መገለጹ መታሰቢያ ሆና ዕለቲቱ «በቶማስ» ተሰየመች፡፡ ዮሐ. 20-24-30 ✞ #ረቡዕ፤ #አልአዛር ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡ ከሞተና ከተቀበረ አራት ቀን በኋላ ከመቃብር ጠርቶ ላሥነሣው፣ አላዓዛር መታሰቢያ የእርሱንም ተነሥቶ በማየት በጌታችን ብዙ ሕዝብ ስለአመነበት ቀኒቱ «አላዓዛር» ተብላ ትታሰባለች፡፡ ዮሐ. 11-38-46 ✞ #ኀሙስ፤ #አዳም ሐሙስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡ የአዳም ተስፋው ተፈጽሞለት ከነልጅ ልጆቹ ወደቀደመ የገነት ክብሩ ለመግባቱ መታሰቢያ ሆና «የአዳም ኀሙስ» ተብላ ይኸው ትከበራለች፡፡ ሉቃ. 24-25-49 ✞ #ዐርብ፤ #ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በክርስቶስ ደም ተዋጅታ በተመሠረተችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታላቅ መታሰቢያ በመሆኗ በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ዐርብ «ቤተ ክርስቲያን» ተብላ ትጠራለች፡፡ ማቴ. 26-26-29 የሐ. ሥራ. 20-28 በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡ ✞ #ቅዳሜ፤ #ቅዱሳት አንስት ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡ በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ቀዳሚት ሕዝቡ ከአንዳንዱ በስተቀር ገበያ እንኳን ስለማይገበይባት «የቁራ ገበያ» የገበያ ጥፊያ ስትባል በቤተ ክርስቲያን ግን በዘመነ ሥጋዌው በገንዘባቸውና ጉልበታቸው ለአገለገሉት በስቅለቱ ዋይ ዋይ እያሉ እስከ ቀራንዮ ለተከተሉት፣ የትንሣኤው ዕለት ገና ከሌሊቱ ወደ መቃብሩ ሽቱና አበባ ይዘው በመገሥገሣቸው ትንሣኤው ከሁሉ ቀድሞ ለተገለጸላቸው ቅዱሳት አእንስት መልካም መታሰቢያ ሆና «አእንስት» ተብላ ትጠራለች፡፡ ሉቃ. 23-27-33፣ 24-1-01፣ ማቴ. 25-1-11 ✞ #እሑድ፤ #ዳግም ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡ (የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ሰሌዳ መጽሔት) + + + መልካም በዓል!!! + + + ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ክብ_ቀስተ_ደመና (የማርያም መቀነት) በባህርዳርና አካባቢዋ ላይ ዛሬ፤ *በቀን አቈጣጠር ሚያዝያ 11/2012 ዓ.ም. (በሌሊት አቈጣጠር በ21፤ በጨረቃ በ25ኛው፤ አበቅቴ 6 በሆነበት) በዕለተ እሑ
+2
#ክብ_ቀስተ_ደመና (የማርያም መቀነት) በባህርዳርና አካባቢዋ ላይ ዛሬ፤ *በቀን አቈጣጠር ሚያዝያ 11/2012 ዓ.ም. (በሌሊት አቈጣጠር በ21፤ በጨረቃ በ25ኛው፤ አበቅቴ 6 በሆነበት) በዕለተ እሑድ፥ በበዓለ ትንሣኤ ቀን ላይ ታይቷል፡፡ ፠ #እሠይም_ቀስትየ_በውስተ_ደመና_ ‹‹ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች፤ በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ መካከል ሁሉ ያለውን የዘለዓለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ።›› /ዘፍ .፱፥፲፮/ ፠ ‹‹ምልክትንም ለመልካም ከእኔ ጋር አድርግ የሚጠሉኝ ይዩ ይፈሩም፥ አቤቱ፥ አንተ ረድተኸኛልና፥ አጽንተኸኛልምና።›› /መዝሙር 86፥17/ ፠ ‹‹እግዚአብሔር መልካም ነው፤ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል›› /ትንቢተ ናሆም 1፥7/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w