ru
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Открыть в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 382 подписчиков, занимая 5 568 место в категории Религия и духовность и 2 195 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 382 подписчиков.

Согласно последним данным от 04 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 23, а за последние 24 часа — -1, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 22.11%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.42% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 401 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 449 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 20.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 05 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

15 382
Подписчики
-124 часа
-107 дней
+2330 день
Архив постов
ቅዱሱ አባ ዮሐኒም ከአራዊትና አባ አበይዶን ከመሰሉ አባቶች ጋር ኖረ፡፡ ከንጽሕናውም የተነሳ ቅዱሳን መላእክት ያነጋግሩት ነበር፤ በእንዲህ ያለ አኗኗር 12 ዓመታት ከኖረ በኋላ፤ ስም አጠራሩ በመላዋ ሃገሪቱ ሲሰማ ወላጅ እናቱ በሕይወት ነበረችና ሰማች፤ ልታየውም የወንድ ልብስ ለብሳ ወዳለበት ተራራ ገሰገሰች፡፡ ኅዳር 5 ቀን ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት እንደ ልማዱ ተራራ ላይ ወጥቶ ሳለ፤ ወደ ተራራው ደርሳ ስትጠራው ቅዱሱ ተመለከታት፤ አንተ ማነህ? አለ፤ እናቱም በክርስትና ስሟ አኔ ‹ዓመተ መንፈስ ቅዱስ ነኝ› አለችውና ወደ እርሱ ቀረበች፤ በቀረበች ጊዜም ሴት መኾኗን ተመለከተ፤ አባቱ አሞኒ የነገረውን (ሴት ስታይ ሩጥ ያለውን) ወዲያውኑ አስታውሶ፤ መጽሐፉንና የቀለም መጻፊያ ብዕሩን አንስቶ በሩጫ ወደ ገደሉ /በፎቶ ላይ ወደ ምታዩት እጅግ እጅግ በጣም ረጅም ገደል/ ተወረወረ፤ አባ አበይዶ እያየው በክንዶቹ ግራና ቀኝ ክንፍን አውጥቶ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከእርሱ ጋር ሁኖ መንፈስ ቅዱስ እየመራው ሞትን ሳይቀምስ ሔኖክና ኤልያስ ሌሎችም አባቶች ወዳሉበት ወደ ብሔረ ሕያዋን በ32 ዓመቱ ገባ፡፡ ደቀ መዝሙሩም አባ አበይዶም ኅዳር 4 በደብረ ዓሣ በሰላም አረፈ፡፡ *ወደ ገደል መወርወሩ፤ እንደ ሞትና መቃብር፡፡ *ክንፍ አውጥቶ ብሔረ ሕያዋን መግባቱ፤ እንደ ትንሣኤ ሙታን ነው፡፡ ለኢትዮጵያውያን ብሩክ ኮከብና ገባሬ ተአምር የሆነው አባ ዮሐኒ ይህ ኹሉ ተዓምራት የሚፈጸመው እመቤታችን (አበባ፥ ፍሬ) በወለደችው መድኀኔዓለም ክርስቶስ (ጽጌ) ነው፤ ይህንንም በማስመልከት የተለያዩ ሊቃውንት የተለያዩ ድርሰቶችን ደርሰዋል፤ ከእነዚህም መካከል አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌተ ጽጌ ድርሰታቸው፥ አባታችን አርከ ሥሉስ በስንክሳር (በአርኬ) ድርሰታቸው፥ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በኆኅተ ቅዱሳን ድርሰታቸው፥ ቅዱስ ያሬድ በመጽሐፈ ድጓው የሚከተለውን ደርሰውላቸዋል፤ ፩. #ስለ_አባ_ዮሐኒ_ ፠ ሊቁ ቅዱስ ያሬድም በመጽሐፈ ድጓ ላይ የአባ ዮሐኒን ወደ ብሔረ ሕያዋን መሰወሩን በተመለከተ፤ ‹‹አባ ዮሐኒ ጸገየ ሕይወተ፤ ፈረየ ሠላሳ ወስሳ ወምእተ፤ ብሔረ ሕያዋን ተመሥጠ ግብተ፤ ዘዐይን ኢርዕየ ነሥአ ዕሤተ፡፡ (አባ ዮሐኒ ሕይወትን አብቦ፤ ሠላሳ፥ ስሳንና፥ መቶን አፈራ፤ ወደ ሕያዋን ሀገር በድንገት ተነጥቆ ዐይን ያላየውን ዋጋ አገኘ) ፠ አባ አርከ ሥሉስ ቅዱስ በመጽሐፈ ስንክሳር አርኬው ላይ የአባ ዮሐኒን መሰወር በተመለከተ፤ ‹‹ሰላም ዕብል ለዘኮነ ሱቱፈ፤ ምስለ እለ ገብሩ ሰብእ ብሔረ ሕያዋን ምዕራፈ፡፡ እምሥርዓተ መላእክት ዮሐኒ ምንትኒ ኢያትረፈ፤ ከመ ሕይወቶሙ ሕይወተ ተጸገወ ዘልፈ፤ ወከመ ክንፎሙ አብቈለ አክናፈ፡፡›› (አርኬ) (ብሔረ ሕያዋንን ማረፊያን ካደረጉ ሰዎች ጋር ኅብረትን ያደረገ ለኾነ ሰላም እላለኊ፤ ዮሐኒ ከመላእክት ሥርዐት ምንም ምን አላስቀረም፤ እንደ ሕይወታቸው ሕይወትን ተቀበለ ፥ ተቸረ፤ እንደ ክንፋቸውም ክንፎችን አበቀለ) ፠ አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌተ ጽጌ ድርሰቱ የአባ ዮሐኒን ታሪክና በጽጌና በፍሬ የተመሰሉ እናትና ልጇን አመሳትሮ እንዲህ ደርሶታል፤ ‹‹ሶበ ዴገነኪ አርዌ በሊዓ ሕፃንኪ ዘኀለየ፤ በዘትሠርሪ ገዳመ ወታፈጥኒ ጐይየ፡፡ እንተ ጸገይኪ አክናፈ ከመ ዮሐኒ ጸገየ፤ ብእሲተ ሰማይ ማርያም ዘትለብሲ ፀሐየ፤ ተአምረኪ ጸሐፈ ዮሐንስ ዘርእየ:: /አባ ጽጌ ድንግል፣ ማሕሌተ ጽጌ/ ፠ አባቶቻችን በወርኃ ጽጌ በመጽሐፈ ወረባቸው እንዲህ ብለውታል፤ ———- ወረብ፤ ብእሲተ ሰማይ ማርያም ፀሐየ ዘትለብሲ፤ ተአምረኪ ጸሐፈ ዮሐንስ ዘርእየ/፪/ ተአምረኪ፡፡ ———- ወረብ፤ አመ/፪/ ጸገይኪ አክናፈ ከመ ዮሐኒ ተአምረኪ ጸሐፈ ዮሐንስ ዘርእየ/፪/ተአምረኪ፨ ———- ፠ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ የአባ ዮሐኒን ክብር እንዲህ ገልጾታል፤ ‹‹ሰላም ለአባ ዮሐኒ ከመ ንህብ ዘተመሰለ፤ እምኲሎሙ ቅዱሳን ዘአስተጋብአ ገድለ፡፡›› (እንደ ንህብ የተመሰለ ኾኖ ከቅዱሳን ኹሉ ገድልን የሰበሰበ ለኾነ ለአባ ዮሐኒ ሰላምታ ይገባል) ፪. #ስለ_አባ_አበይዶ_ ፠ አባ አርከ ሥሉስ በመጽሐ ስንክሳር አርኬው ላይ የዚኽን ዓለም ሥራ ትቶ የአባ ዮሐኒ ደቀ መዝሙር ስለነበረው ስለ አባ አበይዶ በኅዳር ፬ ዐርኬው ላይ እንዲህ ብሎ የክብሩን ታላቅነት መስክሯል፤ ‹‹ሰላም ለአበይዶ ዘመጠነ ዮሐኒ መጠኑ፤ እስመ ውእቱ ረድኡ ወውስተ ኲሉ ምእመኑ፡፡ ለዝ ጻማዊ ወፈጻሜ መልእክት ዘበበበይኑ፤ ጼና አልባሲሁ ከመ ጼና ስኂን ይጼኑ፤ ወይበርህ እምፀሓይ ምስብዒተ ሥኑ፡፡›› (የማዕርጉ መጠን እንደ ዮሐኒ ማዕርግ መጠን ለኾነ ለአበይዶ ሰላምታ ለርሱ አገልጋዩና በኹሉም ውስጥ ታማኙ ነውና፤ በየወገኑ አገልግሎትን ለሚፈጽምና ለዚኽ ትጉህ ለኾነ ሰው የልብሶቹ ሽታ እንደ ዕጣን መዐዛ ይሸታል፤ የልብሱ ሽታ እንደ ዕጣን ጢስ ይሸታሉ፤ ደም ግባቱም ከፀሓይ ሰባት እጅ ይበራል)፡፡ ፠ ቅዱስ ያሬድም በመጽሐፈ ድጓ ላይ የአባ አበይዶን ተጋድሎ በተመለከተ እንዲህ ብሏል፤ ‹‹ብፁዕ ውእቱ አባ አበይዶ ረድአ ዘኮኖ ለአባ ዮሐኒ ብፁዕ ብእሲ በትዕግሥቱ ዘፈጸመ ገድሎ፤ (ለአባ ዮሐኒ አገልጋይ የኾነው አባ አበይዶ ንኡድ ፥ ክቡር ነው፤ ተጋድሎውን በትዕግሥቱ የፈጸመ የኾነ ርሱም ንኡድ ክቡር ነው)፡፡ ፠ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ የአባ አበይዶን ክብር እንዲህ ገልጾታል፤ ‹‹ሰላም ለአባ አበይዶ፤ ለጸላኢ ዘኬዶ፡፡›› (ጠላትን የረገጠው ለኾነ አባ አበይዶ ሰላምታ ይገባል)፨ (ምንጭ፤ የገዳሙ አባቶች የቃል አስረጅ፣ ገድለ አቡነ ዮሐኒ፣ የአስቴር (ዮሐኒ) የጕዞ ማስታወሻ) (ታሪኩን ከቦታው ድረስ ሄዶ፤ አባቶችን ጠይቆ፤ መጻሕፍትን አገላብጦ ለዘገበልን ወንድማችን አምላከ አቡነ አሞኒ፥ ዮሐኒ ወአበይዶ በበረከት ይጎብኝልን፡፡) /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

ኅዳር 4ና5፤ #አባ_ዮሐኒ_ወአሞኒ_ወአበይዶ_፤ #ዘገዳመ_ዓሣ(ይ)፥#ቆላ_ተንቤን፡፡ ፠አባ አሞኒ ፥ ዮሐኒ ፥ አበይዶ፤ አያት፣ አባትና የልጅ ልጅ፡፡ ፠አባ አሞኒና ዮሐኒ ታሪካቸው ከቅድስት እንባ መሪና ጋር የሚመሳሰልና ብዙ ትምህርት የሚገኝበት #የሚመስጥ_ታሪክ_ስለሆነ_እስከ_መጨረሻው_ያንብቡት_፤ ፠ምንኵስና በተሰዓቱ ቅዱሳን ከመግባቱ በፊት የምነና ሕይወት በኢትየጵያ ለመኖሩ አስረጅ የሆኑ ቅዱሳን፤ ፠ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናቸው ከ1600 ዓመታት በላይን ያስቈጠረና አሁንም ያለ እጅግ በጣም ጥንታዊ ገዳም፡፡ አባ ዮሐኒ በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መግቢያ ላይ በትግራይ ተንቤን አውራጃ በሀገረ ሰላም ቀበሌ የተወለደ ቅዱስ ነው፡፡ በዚያን ዘመን ሥርዓተ ምንኵስና ወደ ኢትዮጵያ ባይገባም አበው በምናኔ በበረሃ ይኖሩ ነበር፡፡ ከ4ኛው መ/ክ/ዘ በፊት (ሥርዓተ ምንኵስና ወደ ሀገራችን የገባው በኢትዮጵያ በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ /ከአባ መቃርስ ወደ አባ ጳኵሚስ፤ ከአባ ጳኵሚስ ወደ አባ ቴዎድሮስ፤ ከአባ ቴዎድሮስ ወደ አባ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ) ቢሆንም የብሕትውና ኑሮ ግን በሀገራችን ከዚያም ቀድሞ እንደነበረ ከሚጠቁሙን ዋነኛ ነገሮች አንዱ የገዳመ ዓሣ/ይ/ ታላላቆች የኾኑ ቅዱሳን አባቶቻችን ቅዱሳን አባ አሞኒ እና አባ ዮሐኒ ዋነኞቹ ናቸው፡፡ #ገዳመ_ዓሣ(ይ) ገዳሙ ከ1600-1800ዓመታትን ያስቈጠረ ውቅር(ፍልፍል) ቤተክርስቲያኝ ሲኾን፤ ገዳሙ የሚገኝበት ተራራ ብቻውን ከ20ደቂቃ በላይ ያስጕዛል፤ እንደ ደረጃ ያሉ፥ ሠርጥ የኾኑና አንድ ድልድይን ካለፉ በኋላ ገዳመ ዓሣን እንዲኹም ወደ ላይ ተጨማሪ የ5 ደቂቃ ተራራ ሲወጡ አባ ዮሐኒ በሕፃንነታቸው (ከተወለዱባት እለት ጀምሮ እስከ 3 ዓመት እስከሚሞላቸው) ያደጉባትን ትንሽ ዋሻ ያገኛሉ፤ የአባ አሞኒና የአባ ዮሐኒ ታሪክም ከአባ መሪና ጋር በተወሰነ መልኩ ይመሳሰላል፤ ………. ለማንኛውም ከዚህ በታች ታሪኩ ይተረካል………፡፡ አባ ዮሐኒ ከመወለዱ በፊት፤ የእናቱ ባል የተንቤን ሹም ስለበር ለዘመቻም /ለንግድም/ ይላሉ ኖባና ላባ ወደሚባል አገር ሔዶ ለሰባት ወር ያህል ዘገየ፤ ታናሽ ወንድሙም የወንድሙን ሚስት ወንድሜ ዘገየ ከእንግዲህ ወዲህ አይመለስም /ሞቷልም ይላሉ/ ስለዚህ ሚስት ትሆኚኝ ዘንድ ነዪ ቃል ኪዳን እንግባ አላት፤ እሷም የባሏ ታናሽ ወንድምና በቤቷ ውስጥ ያሳደገችው ነበረና እንዴት ደፈርከኝ ብላ ተቆጣች፤ እርሱም ተቆጥቶ ደረሰባትና ጸንሳ ወንድ ልጅ ወለደች፡፡ በወለደችበት ቀንም ከብዙ ምርኮ ጋር ባሏ ወደ አገሩ ተመለሰ፤ ወደ ቤቱም በገባ ጊዜ ሚስቱ ከቤት የለችም ነበርና ሚስቴ ወዴት ሔደች ብሎ ጠየቀ፡፡ በቤቱ ውስጥ ያለ አንድ ሕፃን ባለቤትህ ታማለች አለው፤ ባለቤቷም በሽታዋ ምንድን ነው አለው? ያ ሕፃንም ዛሬ ልጅ ወለደች ብሎ መለሰለት፡፡ ይህንንም በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ተቆጣ፤ ያ ሕፃንም እየመራው ሚስቱ ወዳለችበት ገባሕ ይደበድባትም ጀመር፡፡ ደብረ ዓሣይ (በቆላ ተንቤን የሚገኝ) በሚባል ገዳም ስሙ አባ አሞኒ ዘናሕሶ የተባለ ገዳማዊ ነበር፤ በዚያ ገዳምም ለሃያ ዓመታት ያህል የቆየ ነው፡፡ የእግዚአብሔር መልአክም አባ አሞኒን ተነስተህ የተንቤን ሹም ወደ ሆነው ሰው ቤት ሂድ ከዚያም እግዚአብሔር የወደደውን ነገር ታገኛለህ አለው፤ አባ አሞኒም የእግዚአብሔር መልአክ እንዳዘዘው ከተራራው(ከገዳሙ) ወርዶ ወደ ተንቤን ሹም ቤት ደረሰ፤ ሚስቱም በቤቷ በር ፊት ለፊት አባ አሞኒን ባየችው ጊዜ ውስጡ ጥበበ እግዚአብሔር ነውና፤ ለባሏ የጸነስኩት ከዚህ መነኵሴ ነው አለችው፡፡ ያን ጊዜም ባሏ በቁጣ ወጥቶ አባ አሞኒን መታው፥ ደበደበው፤ ልጅህን ይዘህ ሒድ ብሎ ሕፃኑን ለአባ አሞኒ ሰጠው፡፡ አባ አሞኒም ሕፃኑ በተወለደበት ቀን በልብሱ አቀፈው፤ ወደ ገዳሙ (ደብረ ዓሣይ) ወስዶ እኔ ጡት የለኝ! ብሎ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ ከተራራው ከገደሉ ጀርባ እንደ መቃብር አስመስሎ ምድርን ቆፈረና፤ ለሕፃኑ የሰሌን ቅጠልን አንጥፎ በዚያ አስቀመጠው፥ ድንጋይም ከደነ፤ እግዚአብሔር ከወደደ ያድንህ፣ ይህቺ ጉድጓድ እናትህ ትሁን፤ ብሎ ከዚያ ትቶት ወደ በዓቱ ሔደ፡፡ በነጋውም ማልዶ ወደዚያ ሕፃን ገሠገሠ፤ ፌቆ/ሚዳቋ የምትመስል/ ከጉድጓዱ ድንጋዩን አስወግዳ ተንበርክካ ስታጠባው አያት፤ ፌቆዋም አባ አሞኒን ባየችው ጊዜ ከጉድጓዱ ውስጥ ሸሸች፤ አባ አሞኒም ያን ሕፃን ደስተኛ ሆኖ ዓይኖቹን ባየ ጊዜ የተደነቀው ቅዱስ አሞኒ ሕፃኑን "ዮሐኒ" ሲል ስም አወጣለት፤ ትርጕሙም ወላጆችህ ወይም አሳዳጊዎችህ አራዊት ናቸው እንደ ማለት ነው፡፡ አባ አሞኒም ይህን ዕፁብ ድንቅ ሥራ ያሳየኸኝ እግዚአብሔር ስምህ ይመስገን አለና ወደ ገዳሙ ተመለሰ፡፡ አባ አሞኒም ሕፃኑን ጠዋትና ማታ እየጎበኘው፤ ፌቆ እንደ እናቱ እያጠባችው ሦስት ዓመት ኖረ፤ እንዳይበርደውም ዝንጀሮ/አሞራም/ ያቅፈው ነበር፡፡ ሕፃኑም ከሦስት ዓመት በኋላ የፌቆዋን ጡት መጥባትን ተወ፤ አባ አሞኒም ወደ ገዳሙ ወስዶ እስከ ሰባት ዓመት ድረስ በዚያ አሳደገው፤ ከሰባት ዓመቱ ጀምሮ የዳዊትን መዝሙር፣ የነቢያትንና የሐዋርያትን መጻሕፍት እስከ ትርጓሜያቸው አስተማረው፤ ሕፃኑም ዐሥራ ሁለት ዓመት በኾነው ጊዜ፤ አባ አሞኒ ይህ ልጄ ትምህርትን ጨረሰ ዲያቆን ይኾን ዘንድ ወደ ጳጳስ ልውሰደው ብሎ መንገድ (ለጕዞ) ተነሡ፡፡ የስድስት ሰዓት መንገድንም ተጓዙ፤ አባ ዮሐኒ መንገድ ላይም ዐሥር ወጣት ሴቶች ውኃን በእንስራ ተሸክመው (ተሰባስበው ሲጫወቱ) ከልብሳቸው ተራቁተው አየ፤ አባ ዮሐኒም ከዚህ በፊት የሴት መልክን አይቶ አያውቅም ነበረና አባቴ ሆይ እነዚህ ጸጕራቸው የረዘመ፣ ደረታቸው ወደፊት የወጣ ፍጥረቶች ምንድን ናቸው? ሲል ጠየቀው፤ አባ አሞኒም ልጄ ዮሐኒ ሆይ እነዚህ ሴቶች ናቸው፤ ግን እንደ እኔና ላንተ ላሉ የበርሃ ሰዎች አይሆኑምና አትቅረባቸው አለው፡፡ አባ ዮሐኒ መልሶ አባቴ! ድንገት ቢመጡብኝ ምን ላድርግ? ሲል ጠየቀው፡፡ አባ አሞኒም ልጄ! ከዘለዓለም ርስት ከምትነቀል ሩጠህ ብታመልጥ ይሻላል አለው፡፡ ከዚህ በኋላ ወደ ገዳማቸው ተመለሱ፡፡ #አባ_አበይዶ_ አባ አበይዶ የሚባል መነኵሴም የተጋድሎ ዜናቸውን ሰምቶ ረድዕ (አገልጋይ) ለመኾን ወደ ገዳማቸው መጥቶ ተጨመረ፡፡ ለምግባቸውና ለልብሳቸው አባ አሞኒና ልጁ አባ ዮሐኒ መጻሕፍትን እየጻፉ፤ አባ አበይዶ እየሸጠ እንዲህ ኾነው በብሕትውና ሲኖሩ፤ አባ አሞኒ አርባ ዓመት በገዳም ኑሮ (አባ ዮሐኒ በተወለደ ሃያ ዓመት ሲሞላው) ኅዳር 5 አረፈ በገዳማቸውም ቀበሩት፡፡

✤✤ #ደብረ_ወገግ_፤ ፠ ‹‹ደብረ ወገግ›› ከ2-5 ዓ.ም. እመቤታችን ከነልጇ ስተሰደድ ለ6 ወር የተቀመጠችበት ሲኾን፤ ደብረ ወገግ የሚለው ስያሜ የተገኘው ከመላእክት ነው፡፡ ድርሳነ ዑራኤል በሰፊው እንደሚያትተው ቅዱስ ዑራኤል በ34ዓ.ም. የጌታችንን ደም በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ ዓለምን እየረጨ ሲቀድሳት የያዘውን ጽዋ በደብረ ወገግ ላይ ቆሞ ሳለ ነው ጨልጦ ያንጠፈጠፈው፡፡ ያንጊዜም ደብረ ወገግን የብርሃን ውጋገን ሲያጥለቀልቀው በመታየቱ መላእክትም ቦታውን ‹‹ደብረ ወገግ›› (የብርሃን ተራራ) ብለው ሰይመውታል፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ‹‹ወደፊት ፈጣሪውን የሚያገለግል ታላቅ ጻድቅ ይወጣባታልና ይህችን ቦታ ባርካት›› ብሎ ቅዱስ ዑራኤልን በነገረው መሠረት ባርኳት አርጓል፡፡ ፠ በደብረ ወገግ ቦታ ላይ ብዙ ጊዜ የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ መታየቱን የበቁ ገዳማውያን ብቻ ሳይሆኑ በከተማ ያሉና ለመሳለም ወደ ቦታው የሄዱ ደገኛ ሰዎችም በዐይናቸው ያዩትን ይናገራሉ፡፡ በገዳሙ ዙሪያ እጅግ በጣም ብዙ ስውራን ቅዱሳን እንዳሉ በግልጽ ይታወቃል፡፡ ፠ ገዳሙ በግራኝ ወረራ ወቅት ከጠፋ በኋላ እንደገና መልሶ የቀናው በ1911ዓ.ም. በታላቁ ሊቅና መናኝ በአለቃ ገብረ መድኅን ነው (ለአፄ ኀይለ ሥላሴ በማሳሰብ)፡፡ በ1912 ዓ.ም. የአቡነ ሳሙኤልን ቤተ ክርስቲያንን በሣር ክዳን ሠሩ፤ በዓመቱ በ1918 ዓ.ም. ደግሞ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያንን መሥራት ጀምረው ፍጻሜውን ሳያዩ እርሳቸው ቢያርፉም፤ በ1919 ዓ.ም. የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ ሥራ ተጠናቋል፡፡ በ1929 ዓ.ም. በሶማልያ በኩል በገባው የፋሽስት ኢጣልያ ጦር ገዳሙ ተዘርፏል፥ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያንም ፈርሷል፡፡ በወቅቱ በገዳሙ ከነበሩት ከ500 በላይ መነኰሳት መካከል ከፊሉ ታቦቱን ይዘው ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ሲሸሹ ከፊሎቹ ደግሞ ወደ ሞቃዲሾ ተወስደው ታስረዋል፡፡ ከጣሊያን ወረራ በኋላ መነኰሳቱ በ1936 ዓ.ም. ተሰባስበው ወደ አሰቦት መጡ፡፡ ከ22 ዓመት በኋላ ደግሞ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ትእዛዝ በ1952 ዓ.ም. ተሠራ፡፡ በደርግ ዘመነ መንግሥት ሶማሊያ ኢትጵያን ስትወርር ገዳሙ ላይ አደጋ ለመጣል የመጡ ጠላቶች በተአምራት ያለቁበት ነበር፤ የጃራ ጦር የሚባሉ ገዳሙን ለማጥፋትም መጡ ጠላቶች እንዲሁ በተአምራት አብደው የተመለሱበት ታላቅ ገዳም ነው፡፡ ግንቦት 16 ቀን 1984 ዓ.ም. በአክራሪ ኃይል የገዳሙን መነኰሳትና የአካባቢው ምዕመናን ላይ የከፋ አደጋ ጥሏል፤ ብዙዎችም ሰማዕት ሁነዋል፡፡ በአሰቦት ደብረ ወገግ ገዳም ውስጥ የተሰወሩ እጅግ በርካታ ቅዱሳን ስለመኖራቸው በገድለ አቡነ ሳሙኤል መቅድም ውስጥ በሰፊው ተጠቅሷል፡፡ አሁንም ሆነ ወደፊት በቦታው ላይ የተሰወሩት ቅዱሳን ለገዳማውያኑም ሆነ በዓለም ለሚኖሩ ምግባርን ከሃይማኖት አስተባብረው ለያዙ ሰዎች እየተገለጡላቸው ይታዩዋቸዋል፣ መልእክትም ይነግሯቸዋል፡፡ እንዲሁም ስውራኑ ባሉበት ቦታ የከበሮ ድምጽ ይሰማል፣ ዕጣን ይሸታል፣ ቀንና ሌሊት አራዊት ሲሰግዱበትና ሲጠብቁት ይታያል፡፡ ለአብነትም በ1972ዓ.ም. ሐምሌ 7 ብዙ ሰው እያያቸው አባ መዘምር የተሠወሩበት ታለቅ ገዳም ነው፡፡ /ታሪኩን ለዘገበልን ወንድማችን አምላከ አቡነ ሳሙኤል በረድኤት በበረከት በጤና ይጠብቅልን፡፡/ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool

ጥቅምት 29 | አርፍደን ጻፍንላቹህ ታላቁ ገዳማችን አሰቦት ደብረ ወገግንና ደብረ ኪሩብን ለመሠረቱት ለአባታችን ለአቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ በዓለ ዕረፍት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ ✤✤ #አቡነ_ሳሙኤል-ዘደብረ_ወገግ፡፡ ፠ በታላቁ አባት አቡነ ተክለሃይማኖት ‹እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ፥ ጣዖታትን የሚሰብር፣ የሚያጠፋ፣ አጋንንትን በጸሎቱ የሚያርቅ፣ ሕዝብን ከኀጢአት በሽታ የሚያድን፣ ፈጣሪውን የሚያስደስት ደግ ልጅ› ተብሎ በተነገረለት ትንቢታዊ ብሥራት ከደጋግና ከበቁ አባታቸው እንድርያስና ከእናታቸው አርሶንያ ሐምሌ 10 ቀን 1248 ዓ.ም. በቡልጋ (በኢቲሳ ደብረ ጽላልሽ ገዳም) ተወለዱ፤ ሲወለዱም መልካቸው በአራት ልዩ ልዩ ሕብረ መልክ እየተለዋወጠ አንድ ጊዜ እንደ በረዶ፣ አንድ ጊዜ እንደ እሳት፣ አንድ ጊዜ እንደ ልምላሜና ቢጫ ሆነው ታይተዋል፡፡ ፠ስማቸውን ሳሙኤል ብለው የሰየሟቸውና ክርስትናም ያነሷቸው፤ ኋላም መዓርገ ምንኵስናን በደብረ ሊባኖስ የሰጧቸው አቡነ ተክለሃይማኖት ናቸው፡፡ ፠ ብዙ ጻድቃንን (አቡነ ተክለሃይማኖትን፣ ታዴዎስ ዘደብረ ድኁኃን፣ ሮማኖስ ዘደብረ ዋምን፣ አቡነ አኖሬዎስ ዕንቈ ባሕርይ ዘመረግድ ወመስተጋድል ወምግባር ንጹሕን) በሥጋ የሚዛመዱ ናቸው፡፡ ፠ ሃይማኖቱ የቀና ደግ ጻድቅ ንጉሥ ዳዊት በነገሠ ጊዜ አባታችን ሳሙኤል ዘወገግን አገኘውና አባቱ ዓምደ ጽዮን ለሠራው ክፉ ሥራ ‹‹መማጸኛ እንዲሆነኝ በእንድርያስ መቃብር ላይ ቤተክርስቲያን ሥራልኝ›› ብሎ ለመነውና የሩፋኤልን ቤተ ክርስቲያን ሠራለት፡፡ የእንድርያስንም አጽም ከመቅደሱ ስር አኖረው፡፡ ንጉሡም በዚያ በእንደግብጦን አውራጃ ሁሉ ላይ ፓትርያርክ አድርጎ ሾመው፡፡ ፠፠ አቡነ ተክለሃይማኖት ትንቢት እንደተናገሩላቸው አቡነ ሳሙኤል፤ * በሰዎች፣ በባሕርና በዛፍ ላይ እያደሩ ይመለኩ የነበሩ በጣም ብዙ አጋንንትን አጠፏቸው፡፡ * ጠንቋዮችንም በውስጣቸው ካደረባቸው ሰይጣን እያላቀቁ የእግዚአብሔር አገልጋይ ያደርጓቸውና ያመነኩሷቸው ነበር፡፡ * ወንጌልን ዞረው በማስተማር ሐዋርያትን መሰሉ፥ * ከዓላውያን ጋር ለመዋጋት ሰውነታቸውን ለሞት በመስጠት ሰማዕታትን መሰሉ፥ * በጾም በጸሎት በስግደት በተጋድሎ ቅዱሳን ጻድቃንን መሰሉ፥ * ይህን ኀላፊና ጠፊ ዓለም ንቀው በመተው ባሕታውያንን መሰሉ፥ * በደልንና ኃጢአትን በማስተሠረይ ካህናትን መሰሉ፥ * በጽሕናና በቅድስና መላእክትን መሰሉ፤ * ብዙ አስደናቂ ተአምራትንም በማድረግም ይታወቃሉ፤ ከእነዚህም ጥቂቶቹ በትእምርተ መስቀል አድርገው እንደሙሴ ባሕርን ለሁለት ከፍለዋል፣ እንደ ኢያሱ በጸሎታቸው ፀሐይን አቁመዋል፡፡ አቡነ ሳሙኤል ተጋድሏቸውን ፈጽመው ከጌታችን ታላቅ ቃኪዳን ተቀብለው በዚህች ዕለት (በጥቅምት 29) በኦጋዴን ዘርዘር በተባለ ቦታ በሰላም አርፈዋል፤ ከ7 ወራት በኋላ ሠምረ ክርስቶስ የተባለ ልጃቸው ሥጋቸውን አፍልሶ በደብረ ወገግ በክብር አሳርፎታል፡፡ ፠ አቡነ ሳሙኤል የአሰቦት ደብረ ወገግን (ምዕራብ ሐረርጌ) ና ደብረ ኪሩብ (አፋር) ገዳምን ያቀኑ፥ ለብዙ አእላፍ ቅዱሳን ወላዴ የኾኑና፤ የመሠረቱት ገዳም የምሥጢርና የብዙ ስውራን መኖሪያ የኾነላቸው፥ ምስራቅ ኢትዮጵያን እስከ ሞቃድሾ ድረስ በወንጌል ያረሱ፥ አረማውያንን ያጠመቁ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ፠ ከአቡነ ተክለሃይማኖት በኋላ ከተሾሙት 12ቱ ንቡራነ ዕድ አንዱ ናቸው፤ ሃገረ ስብከታቸውም ሐረርና ሱማሌ ነው፡፡ የአቡነ ሳሙኤል ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡ ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘፍቅዳቲሁ ራብዕ፤ ውእቱ ልኩእ ዲበ ረቀ ሰማይ ሳብዕ፡፡ ሊቀ ካህናት ሳሙኤል ዘደብተራ ሐዲ ምሥዋዕ፤ አስተስሪ ኀጣውእየ በደመ ነቢብ በግዕ፤ ለቤዛ ሙታን ዘሞተ በግፍዕ፡፡ (ሳሙኤል ሆይ ቊጥሩ ዐራት ለኾነ በሰባተኛው የሰማይ ብራና(ወረቀት) ለተጻፈ ስም አጠራርህ ሰላምታ ይገባል፤ የሐዲስ መሠዊያ አገልጋይ፥ የካህናት አለቃ ሳሙኤል ሆይ፤ ለሰዎች ቤዛ ለመኾን በግፍ በሞተ በነባቢ ክርስቶስ ደም ኀጢአቴን አስተሥርይ፡፡) /ታሪኩን ለዘገበልን ወንድማችን አምላከ አቡነ ሳሙኤል በረድኤት ፥ በበረከት ፥ በጤና ይጠብቅልን፡፡/ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

ሥርዓተ ማኀሌት ዘወርኀ ጽጌ ‹‹ዘላይ ወዘታች››ቤት ፫ኛ ዙር ዓመተ ፤፭ኛ ሳምንት፣ ጥቅምት ፳፱ በዓለ ወልድ

ወረብ | ብፁአን አበዊነ አረጋዊ .. | በደብረሰላም ሊቃውንት ዝማሜ ※ጥቅምት14፤2013 ዓ.ም በዓለ አቡነ አረጋዊ ወገብረክርሰቶስ ወሙሴ ብእሴ በዩቲዩብ ገጻችን ላይ ይመልከቱ https://youtu.be/3o4wj7Qqcaw

※ጥቅምት14፤2013 ዓ.ም | በዓለ አቡነ አረጋዊ ወገብረክርሰቶስ ወሙሴ ብእሴ ከፎቶ ማሕደራችን
+6
※ጥቅምት14፤2013 ዓ.ም | በዓለ አቡነ አረጋዊ ወገብረክርሰቶስ ወሙሴ ብእሴ ከፎቶ ማሕደራችን

---------- ዝማሜ | ዘእምደብረ ደናግል |በፍኖተ ሕይወት | በሕፃናት ክፍል| ※ጥቅምት14፤2013 ዓ.ም | በዓለ አቡነ አረጋዊ ወገብረክርሰቶስ ወሙሴ ብእሴ በዩቲዩብ ገጻችን ላይ ይመልከቱ https://youtu.be/8TaHMwbZ-KQ

※ጥቅምት14፤2013 ዓ.ም | በዓለ አቡነ አረጋዊ ወገብረክርሰቶስ ወሙሴ ብእሴ ከፎቶ ማሕደራችን
+5
※ጥቅምት14፤2013 ዓ.ም | በዓለ አቡነ አረጋዊ ወገብረክርሰቶስ ወሙሴ ብእሴ ከፎቶ ማሕደራችን

ሥርዓተ ማኀሌት ዘወርኀ ጽጌ ‹‹ዘላይ ወዘታች››ቤት ፫ኛ ዙር ዓመተ ፤፭ኛ ሳምንት፣ ጥቅምት ፳፱ በዓለ ወልድ ሙሉውን ሥርዓተ ማኀሌት ለማግኝት ወደ facebook ገጻችን (like page) 👇 ይሂዱ
ሥርዓተ ማኀሌት ዘወርኀ ጽጌ ‹‹ዘላይ ወዘታች››ቤት ፫ኛ ዙር ዓመተ ፤፭ኛ ሳምንት፣ ጥቅምት ፳፱ በዓለ ወልድ ሙሉውን ሥርዓተ ማኀሌት ለማግኝት ወደ facebook ገጻችን (like page) 👇 ይሂዱ https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool