የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Открыть в Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Больше2 634
Подписчики
+124 часа
+227 дней
+5430 день
Архив постов
መጋቢት - 27
መድኃኔዓለም
መጋቢት ሃያ ሰባት በዚችም ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዓለም ድኅነት በሥጋ ተሰቀለ። ፈጣሪዋ በእንጨት መስቀል ላይ ተዘርግቶ ተሰቅሎ በአየችው ጊዜ ፀሐይ ጨለመች እርሱም ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የነሣትን ለባዊት ነባቢት የሆነች ነፍሱን ከሥጋው ለያት ሐዋርያ ጴጥሮስ በሥጋ ምውት ሲሆን በመለኮት ሕያው ነው እንዳለ ነፍሱ ከመለኮት ሳትለይ ከሥጋ ተለየች በዚያ ጊዜ ሥጋ ከመለኮት ሳትለይ በዕንጨት መስቀል ላይ ተሰቅሎ ነበር። እንዲሁም ነፍስ ከመለኮት ጋራ አንድ ሁና እሥረኞች ነፍሳትን ትፈታቸው ዘንድ ወደ ሲኦል ወረደች።
መድኃኔዓለም ክርስቶስ ስለ ዓለም ሁሉ ድኅነት በሥጋ ተሰቅሏልና ሞቱን በአንክሮ እናዘክር ዘንድ የልቡናችን ዐይን ወደ ቀራንዮ እናንሳ! እነሆ ክፉዎች አይሁድ ሰይጣን ልባቸውን አስቶታልና እንደ ወረንጦና እንደ ወስፌ እንደመርፌም ያለ 300 እሾህ ያለው ስረወጽ አድርገው አክሊል ሠርተው ከፍላት አግብተው በጉጠት አንስተው ‹ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሥ ነህ ዘውድ ይገባሃል› ብለው በራሱ ላይ ደፉበት፡፡ ለአክሊለ ሦኩም 73 ስቁረት ነበረው፡፡ እራሳቸው እንደ መሮ፣ ወርዳቸው እንደ ሞረድ 4 ማዕዘን አሠርተው ቁመታቸውን ክንድ ከስንዝር፣ ስለታቸውን እንደ ወስፌ አድርገው 73 ችንካር ሠርተው በ73ቱ ስቁረት አግብተው በጌታችን በራሱ ላይ ቢመቱበት ሥጋ ለሥጋ ገብቶ መሐል ልቡን ወጋው፡፡ አክሊለ ሦኩን በራሱ ላይ አድርገው ሲያበቁ ከቤት ወደ አደባባይ እያመላለሱ ‹‹ንጉሥ ሆይ!...›› እያሉ ምራቃቸውን እየተፉበት ተዘባበቱበት፡፡ መስቀል አሸክመው ከሊቶስጥራ እስከ ቀራኒዮ ድረስ እያዳፉ ሲወስዱት 136 ጊዜ በምድር ላይ ጣሉት፡፡ ከኋላ ያሉት ‹‹ፍጠን›› እያሉ ገፍትረው ይጥሉታል፣ ከፊት ያሉት ደግሞ ‹‹ምን ያስቸኩልሃል?›› እያሉ መልሰው ገፍትረው ይጥሉታል፡፡ ከዚህ በኋላ ክፉዎች አይሁድ ቁመታቸውን ክንድ ከስንዝር ስለታቸው ደግሞ እንደ ወስፌ የሆኑ 5 ችንካሮችን ሠርተው ሳዶር በሚባለው ችንካር ቀኝ እጁን፣ በአላዶር ግራ እጁን፣ በዳናት ሁለት እግሮቹን፣ በአዴራ መሐል ልቡንና በሮዳስ ደረቱን ቸንክረው የአዳም ራስ ቅል ባለበት ቀራኒዮ አደባባይ ላይ ሰቅለውታል፡፡
ክፉዎች አይሁዶች መድኃኒታችንን በሁለት ግንዶች መካከል አድርገው 65 ጊዜ ከግንዱ ጋር አጋጩት፡፡ ቀያፋ በሚመረምረው ጊዜ ጌታችን ‹‹አምላክነቴን አንተው ራስህ ተናገርኽ›› ቢለው አይሁድ በእጃቸው ሲመቱት እጃቸውን ቢያማቸው ድንጋይ ጨብጠው 120 ጊዜ ፊቱን ጸፉት፡፡ አይሁድ ወደ ጲላጦስ ዘንድ ሲወስዱት ‹‹ምናልባት ጲላጦስ ባይፈርድበት እንኳ እንዳይቆጨን›› ብለው 305 ጊዜ በሽመል ደብድበውታል፡፡ በአምላክነቱ ቻለው እንጂ የአንዱ ምት ብቻ በገደለው ነበር፡፡
ሰይጣን ልባቸውን ለክፋት ያስጨከናቸው ክፉዎች አይሁድ በጲላጦስ አደባባይ የጌታችንን ፂሙን 80 ጊዜ ነጭተውታል፡፡ ጲላጦስ እንደ ሕጋቸው 41 ብቻ ገርፈው እንዲለቁት ቢያዝም ክፉዎች አይሁድ ግን ጌታችንን ሲገርፉት ‹‹አሠቃቂ ግርፋቱን አይተን ልባችን እንዳይራራ›› ብለው ሰንጠረዥ ገበጣ ሰርተው ሲጫወቱ አንዱ ተነስቶ እስከ 60 እና 70 ድረስ ይገርፍና ሲደክመው ‹‹ቆጠራችሁን?›› ብሎ ይጠይቃል፡፡ ‹‹አልቆጠርንም›› ሲሉት ከድካሙ የተነሣ ‹‹እኔው ልግረፍ እንደገና እኔው ልቁጠር›› ብሎ ትቶት ሲቀመጥ ሌላኛው ይነሣና እንደዛኛው ሁሉ በተራው 60 እና 70 ይገርፈዋል፡፡ ሁሉም እንዲህ እያሳሳቱ የራሳቸውን ሕግ እየተላለፉ አይሁድ ጌታችንን ሥጋው አልቆ አጥንቱ እንደበረዶ ነጭ ሆኖ እስኪታይ ድረስ 6666 ጊዜ ጽኑ ግርፋትን ገረፉት፡፡ በእነዚህ ሁሉ ግርፋቱ ወቅት 366 ጊዜ ሥጋው ተቆርሶ መሬት ላይ ወድቋል፡፡
የመድኃኔዓለም ወገኖች ሆይ! የጌታችን ሞቱ በፈቃዱ መሆኑንና የትዕግሥቱን ብዛት አይተን እናደንቅ ዘንድ ከመጻሕፍት ጠቅሰን እንነግራችኋለን፡፡ አይሁድ ጌታችን አብርሃም ሳይወለድ በፊት እርሱ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በአንድነት በሦስትነት የሚመሰገን አምላክ መሆኑን ቢነግራቸው ሊወግሩት ድንጋይ አነሡ፡፡ እሱ ግን ጊዜው ገና ነበርና ተሰውሮአቸው በመካከላቸው አልፎ ሲሄድ በፍጹም አላዩትም ነበር፡፡ በቅዱስ ወንጌል ላይ እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ፡- ‹‹አባታችሁ አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሐሤት አደረገ፥ አየም ደስም አለው። አይሁድም:- ገና ሃምሳ ዓመት ያልሆነህ አብርሃምን አይተሃልን? አሉት። ኢየሱስም:- እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ አብርሃም ሳይወለድ እኔ አለሁ አላቸው። ስለዚህ ሊወግሩት ድንጋይ አነሡ፤ ኢየሱስ ግን ተሰወራቸው ከመቅደስም ወጥቶ በመካከላቸው አልፎ ሄደ ››
ዳግመኛም በዮሐንስ ወንጌል ላይ እንደተጻፈው አይሁድ መድኃኔዓለምን ሊይዙት የጦር መሣሪያቸውን ሰብስበው ወደ ጌቴሴማኒ በመጡ ጊዜ ‹‹ማንን ትፈለጋላችሁ?›› ቢላቸው ‹‹የናዝሬቱን ኢየሱስን እንፈልጋለን›› ሲሉት ‹‹እኔ ነኝ›› ቢላቸው ከአንደበቱ የወጣውን መለኮታዊ ቃል ብቻ መቋቋም አቅቷቸው መሬት ላይ ወድቀው ተዘርረዋል፡፡ (ዮሐ.18 ) እናም የጌታችን ሞቱ በፍጹም ፈቃዱ ባይሆን ኖሮ በጌቴሴማኒ ሊይዙት የመጡት ክፉዎች አይሁድን እንደመጀመሪያው ሁሉ በተሠወራቸው ነበር አሊያም ከአንደበቱ በሚወጣው አምላካዊ ቃሉ ብቻ ባጠፋቸው ነበር፡፡ በመጨረሻ ግን ጌታችን ወደዚህች ምድር የመጣበትን ዓላማ ይፈጽም ዘንድ እንዲገድሉት በፈቃዱ ራሱን አሳልፎ ቢሰጣቸው ያን ሁሉ እጅግ አሠቃቂ መከራ አደረሱበትና ለመስቀል ሞት አበቁት፡፡
ወዮ ለዚህ ለመድኃኒዓለም ፍጹም ትዕግስት አንክሮ ይገባል! ዓለምን በመዳፉ የያዘ አምላክ በአይሁድ እጅ እንደሌባ ተያዘ፡፡ ሠራዊተ መላእክት ለምሥጋና በፊቱ የሚቆሙለት መድኃኔዓለም እርሱ ሊፈረድበት በፍርድ አደባባይ ቆመ፡፡ በእስራት ያሉትን የሚፈታ እርሱ በብረት ችንካር ተቸነከረ፡፡ ሰማይን በከዋክብት ምድርም በአበባ ያስጌጠ እርሱ ግን የእሾህ አክሊል በራሱ ላይ ደፋ፡፡ ዓለሙን ሁሉ በቸርነቱ የሚመግብ እርሱ ተጠማሁ አለ፡፡ ወዮ የመድኃኔዓለም የማዳኑ ምሥጢር ምንኛ ድንቅ ነው!!! ለዚህ ባሕርይው አንክሮ ይገባል፡፡
በመድኃኔዓለም ክርስቶስ ሞት በአንድነት እናለቅስ ዘንድ ሁላችሁም ኑ መድኃኒታችን ሞቷልና ፍጥረታት ሁሉ አልቅሱ መከራን የተቀበለ ጌታችን ሞቷልና። የጌታችን ወዳጆቹ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ገንዘው በሐዲስ መቃብር ቀበሩት በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ተነስቷል።
ዳግመኛም መድኃኔዓለም ክርስቶስ ከዕርገቱ በኋላ ለቅዱሳን ሐዋርያት የሞቱን መታሰቢያ እንዲያደርጉ ነግሯቸዋልና፡፡ ሕማሙንና ሞቱንም እንዲዘክሩ አዟቸዋልና አሁንም ያንን ሁሉ የመድኃኔዓለምን ሞቱን ያላሰበና የሞቱን መታሰቢያ በዓል ያላከበረና እርሱንም የማይወደው ቢኖር ዕድል ፈንታው ጽዋ ተርታው ከአይሁድ ጋር ነው፡፡ የአምላካችንን የመድኃኔዓለምን ሞቱን በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ተባብረን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ከእርሱ ለመተባበር ያብቃን። አሜን
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
ሶስተኛ ዙር የተልዕኮ ትምህርት ምዝገባ
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ት/ቤት ለሦስተኛ ጊዜ የተልዕኮ ትምህርት ለማስተማር ምዝገባ ጀመረ።
ትምህርቱ በቤተክርስቲያናችን ሊቃውንት መምሕራን የሚሰጥ በመሆኑ ተመዝግባችሁ የነፍስዎ ምግብ የሆነውን ቃለ እግዚአብሔር ይመገቡ ትምህርቱ የሚሰጠው በወር አንድ ጊዜ እሑድ ጠዋት ከ3:30- 6:30 በመሆኑ አይሆንልኝም አይመቸኝም እንዳይሉ ምክንያቱም ቢያንስ በወር አንድ ጊዜ ነፍስዎን ለመመገብ መስነፍ የለብዎትም በአካል በወር አንዴ በመገኘት በመማሪያ መጻሕፍት በመታገዝ ያለብዎትን የጊዜ እጥረት ታሳቢ በማድረግ መሠረታዊ የቤተክርስቲያን ትምህርት እንዲማሩ ለእርስዎ እንዲበረቱ ከፈጣሪያችን ከቅዱስ እግዚአብሔር ጋር እንዲቀራረቡ የተላከልዎት መልእክት ነው።
ለመመዝገብ ይህንን ሊንክ ተጭነው በሚመጣልዎት የቴሌግራም ቻናል ላይ
https://t.me/+CqpDqmvBwLc3OWNk በዚህ ሊንክ ገብተው
ስም
ስልክ
አድራሻ በመስጠት መመዝገብ ይችላሉ።
የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
🎙የመናገሻ ገነት ጽጌ ሰንበት ትምህርት ቤት በልማት ምክንያት ቤታቸው ለፈረሰባቸው አባላቱ፣ ተማሪዎች፣ ወላጆችና የአካባቢው ወጣቶች የምክክር እና የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል።
ቀን:- እሑድ መጋቢት 22
ሰዓት:- ከ7:30 ጀምሮ
ቦታ:- በመናገሻ ገነተ ጽጌ ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ
መጻጉዕ
"...ልትድን ትወዳለህን?..." (የዮሐንስ ወንጌል 5: 6)
ይህንን ጥያቄ ያቀረበው የዓለም መድኃኒት፣ የነፍስ የሥጋ ፈጣሪ፣ የሁላችን አምላክ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን፤ ጥያቄው የቀረበለት ደግሞ ለ38 ዓመታት በደዌ ዳኛ በአልጋ ቁራኛ ተይዞ በጸበል ቦታ ለሚገኝ አንድ መጻጉዕ ሰው ነበር። "እንዴት እንዲህ ባለ ስቃይ ውስጥ ላለ ሰው ይሄ ጥያቄ ይጠየቃል?" ብለን እናስብ ይሆናል፤ ነገር ግን እግዚአብሔር የሰጠንን ሙሉ ነጻ ፈቃድ ተጠቅመን በጎውን የሕይወት መንገድ ራሳችን እንድንመርጥ ክፉውን የሞት ጎዳና ደግሞ በራሳችን ፈቃድ እንድንተው የእኛን ነጻ ፈቃድ ይጠይቀናል። ልትድን ትወዳለህን? ይለናል።
መጻጉዕ የመለሰው መልስ ግን ከጥያቄው የራቀ፤ ከጥያቄው ይልቅ ስለ ከባቢው ሁኔታ ማብራሪያ የሰጠ ነበር "ድውዩም፦ ጌታ ሆይ፥ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል ብሎ መለሰለት " (የዮሐንስ ወንጌል 5: 7)
ብዙዎቻችን የዚህ የመጻጉዕ ጠባይ ይታይብናል። እግዚአብሔር የሚጠይቀንን ቀላል ጥያቄ ትተን ያልተጠየቅነውን እንመልሳለን፣ በእግዚአብሔር ፍጹም ከማመን ይልቅ በዙሪያችን ከዓለም የቃረምናቸውን እውቀቶች(ፍልስፍናዎች) ምክንያት በማድረግ ለመዳናችን እንቅፋትና ሰበብ እንፈልጋለን። ይህ በሽተኛ(መጻጉዕ) በሥጋ ደዌ የተያዘ ብቻ አልነበረም። ለ38ዓመት ከተኛበት የደዌ አልጋ ላይ ያነሳውን ፈጣሪውን "ሰንበትን እንድሽር አድርጎኛል" ብሎ በጥፊ የመታ የነፍስ በሽተኛ ጭምር ነበር።
ከሥጋ ደዌ የነፍስ ደዌ እጅጉን ይከፉል። ይህም ክህደት፣ ጥርጥር፣ ትዕቢት፣ ፍቅረ ነዋይ፣ ዝሙት፣ ሐሰት.. የመሳሰሉት ናቸው። የሥጋ ደዌ ቢበዛ በሞት እንገላገለዋለን፤ የነፍሥ ደዌ ግን ፍጻሜ የሌለው ስቃይ የሚያመጣብን ረቂቅ ደዌ ነው። የሚያመጣብንም እስከዘለዓለም አብሮን የሚኖር የገሀነም እሳት ሥቃይ ስለሆነ ከሥጋ ደዌ ይልቅ የነፍስ ደዌን ልንፈራ ይገባል።
እኛስ ልንድን እንወዳለንን? ስለዚህ ከነፍስ ደዌ የሚያድነንን በጎ ተግባር እንፈጽም፦በደላችንን አምነን ፍጹም ንስሐ እንግባ፣ ከዲያብሎስ ግዛት እንውጣ እርሱም ዓለማዊነት ነው፣ ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርን እንያዝ፣ በሃይማኖት በምግባር በተስፋ ከማይመስሉን ጋር በማይመች አካሄድ አንጠመድ፣ በጸሎት እንትጋ፣ ከልማዳዊ ክርስትና ወጥተን የእውነት ክርስትያናዊ ሕይወት እንኑር፣ ከበጎ ነገር ጋር እንተባበር ከክፉ ደግሞ እንሽሽ
...
የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ከነፍስና ከሥጋ ደዌ ያድነን አሜን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
ውድ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት እና ወዳጆቻችን በሙሉ የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ በማድረግ እንዲሁም የምንለቃቸውን ትምህርቶችና መዝሙሮች በማየት አገልግሎታችንን ይደግፉ። የዩቲዩብ ቻናል ሊንካችን
https://youtube.com/watch?v=nv7fniVz9cs&si=TUlq9K4FPICFNnUS
ውድ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት እና ወዳጆቻችን በሙሉ የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ በማድረግ እንዲሁም የምንለቃቸውን ትምህርቶችና መዝሙሮች በማየት አገልግሎታችንን ይደግፉ። የዩቲዩብ ቻናል ሊንካችን
https://youtube.com/watch?v=nv7fniVz9cs&si=TUlq9K4FPICFNnUS
ድንቅ የንስሃ ዝማሬ II በአምሳሉ ፈጥሮናል እናመስግነው II ዘማሪ ዲ/ን ዘላለም ታከለ
https://youtube.com/watch?v=nv7fniVz9cs&si=TUlq9K4FPICFNnUS
የቅዳሜ መደበኛ ትምህርት
ምስጢረ ሥጋዌ
በመ/ር ዲያቆን ሞገስ አብርሃም
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቅዳሜ መደበኛ ትምህርት
በዚህ ሳምንት
ምሥጢረ ሥጋዌ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የብርሃን መሰላል
ዘማሪ ተስፋዬ ኢዶ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
መጋቢት 22/2016 ዓ.ም በሰንበት ት/ት ቤታችን በጎ አድራጎት ክፍል በተዘጋጀው በዚህ የበረከት ጉዞ እና የበረከት ስራ ላይ ይሳተፉ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የሰንበት ትምህርት ቤታችን በጎ አድራጎት ክፍል የነዳያን ምገባ አከናወነ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዕለቱ መዝሙር (ከጾመ ድጓ)፦ ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት፤ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ፤
መልእክታት፦(ቆላ.፪፥፲፮ እስከ ፍጻሜ) (ያዕ.፪፥፲፬ እስከ ፍጻሜ)
ወንጌል፦ (ዮሐ.፪፥፲፪-እስከ ፍጻሜ)
(የሐዋ.፲፥፩-፰)
ምስባክ፦ “እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ፡፡ ትዕይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ፡፡ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ፡፡” ትርጉም “የቤትህ ቅንዓት በልቶኛልና፥ የሚሰድቡህም ስድብ በለዬ ወድቆአልና፡፡ ሰውነቴን በጾም አደከምኋት፡፡ (መዝ.፷፰፥፱)
በምሕረቱ ይታደገን፤ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ አሜን!!!
ምንጭ :-ማኅበረ ቅዱሳን
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
