ru
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Открыть в Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Больше
2 639
Подписчики
+124 часа
+167 дней
+5630 день
Архив постов
ከዕረፍታቸው በኋላ የተደረጉ በርካታ ታላላቅ ተአምራት አሉ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ አንዱ እርሳቸው ካረፉ ከትንሽ ቀናት በኋላ በመቃብራቸው ላይ ዘይት ፈለቀ፡፡ ከዚያም በእንጨት በተሰራ መቅጃ እየተቀዳ ወደ ትልቅ መጠራቀምያ ገብቶ ለቤተ መቅደስ መብራት በ12 ተቅዋም ተደርጎ ከዓመት እስከ ዓመት ይበራ ጀመር፡፡ ከተጠራቀመ ዘይቱም ለታመሙ ይቀቡትና  ከተለያዩ ሕመሞች ይድናሉ፡ ያዕ 5:14፡፡ ዳግመኛም ኤርትራ በሚገኙት በሌሎቹ በአባታችን ደብር ውስጥ ከብዙ ጊዜ በኋላ በደብረ ሣህል ደብራቸውና በደብረ ጽጌ ፈለቀ፡፡ ቅብዓ ኑጉም ለታመሙ ፈውስ እየሰጠ ለቤተ መቅደስም መብራት ሆነ፡፡ ዳግመኛም ከተደረጉት ተአምራት ውስጥ አንዱ እንደ ቤተክርስቲያን ሕግጋት ጻድቁ ካረፉ በኋላ ለጸሎትና ለኑዛዜ ሰዎች ተሰብስቦው እህል እና ውሃ ተዘጋጅቶ በነበረበት ሰዓት "በዚ ቀን ሁሉ ሰው ተገኝቶ ያለሥጋ ዋልን›› ሲሉ ሦስት የተለያዩ ሚዳቆዎች በአቡነ ዮናስ ጸሎት ድንገት መጥተው በሰዎቹ መሐል ተገኙ፡፡ ሰዎቹም ሚዳቆዎቹን አረደው በሉ፡፡ ጻድቁ በስማቸው የተገደሙ ገዳማት (ደብረ ድኁኃንበ- ቆሓይን፣ ደብረ ጽጌ ትምዛእ፣ ደብረ ጽዮን ዓዲ ወሰኽ፣ ደብረ ጸሪቅ ትግራይ፣ እና ደብረ ሣህል ዓረዛ) ይባላሉ፡፡ አቡነ ዮናስ ያረፉት መጋቢት 17 ቀን ሲሆን ይህ ወቅት ታላቁ ዐቢይ ጾም የሚውልበት ስለሆነ በዓለ ዕረፍታቸውን ጥር 21 ቀን እንዲያከብሩ ለልጆቻቸው አስቀድመው ነግረዋቸዋል፡፡ በመሆኑም በዚሁ ዕለት ጥር 21 ቀን በሁሉም ገዳማቸው ውስጥ በታላቅ ክብረ በዓል ታስበው ውለዋል፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር መጋቢት_17 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት ዐሥራ ሰባት በዚች ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚወደው በአራተኛውም ቀን ከመቃብር ያስነሣው የከበረ #ጻድቅ_አልዓዛር አረፈ፣ አናጕንስጢስ #ቅዱሰ_ቴዎቅሪጦስ በሰማዕትነት አረፈ፣ ኢትዮጵያዊው #ጻድቅ_አቡነ_ዮናስ የበዓለ ዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አልዓዛር_ሐዋርያ መጋቢት ዐሥራ ሰባት በዚች ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚወደው በአራተኛውም ቀን ከመቃብር ያስነሣው የከበረ ጻድቅ አልዓዛር አረፈ። ይህም ጻድቅ ሰው ከእስራኤል ልጆች ውስጥ ነው ማርያና ማርታ የተባሉ ሁለት እኅቶች አሉት። ማርያም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሸቱ የቀባችው ናት። እነርሱም ለጌታ ደቀመዛሙርቶቹ ናቸው ስለ ምግባራቸውም ጌታችን ይወዳቸዋል ሁሉም ያላገቡ ድናግል ናቸው። በሰው ወገን ሁሉ ላይ የተቆረጠና የተወሰነው ሰዎችም ሊጠጡት ያላቸው የሞት ጻዋን የሚጠጣበትና እጁን ለሞት የሚሰጥበት ለዚህ ጻድቅ ጊዜው ሲደርስ እርሱም እጁን በመስጠት አረፈ። የክብር ባለቤት ጌታችን ግን የሚሠራውን ያውቃልና መጀመርያ ከሞት አላዳነውም ጠርቶ እስከሚአሥነሣው ድረስ ሙቶ በመቃብር አራት ቀን እንዲኖር በዚህ በአራት ቀንም የጻድቃንን ማደሪያዎችንና የኃጥአንን የሥቃይ ቦታዎች እንዲያይ ተወው እንጂ አላዳነውም ያን ጊዜም ታላቅ ምልክት ትሆናለች። ከአራት ቀኖችም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መጥቶ አልዓዛር አልዓዛር ና ውጣ ብሎ ከመቃብር ውስጥ ጠራው ያን ጊዜ አጆቹና እግሮቹ እንደታሠሩ ሙታኖችንም እንደሚጠቀልሏቸው በሰበን ፊቱ ተጠቅልሎ ወጣ። እጆቹና እግሮቹ እንደ ተጠቀለሉና እንደ ታሠሩ ከመቃብር የመውጣቱ ምክንያት ሰዎች ሁሉ መሞቱን እንዲረዱ ሌሎችም ይህ በመካከላቸው በስምምነት የሆነ ነው ብለው እንዳያሰቡ። ስለዚህም እንደ ገነዙት ሁኖ እንዲወጣ ጌታችን አዘዘው ይችም ምልክት እንድትሆን። ከሀዲዎችም በመቃብር ውስጥ ሕያው እንደ ነበር ቢያስቡም እጆቹና እግሮቹ ፊቱም እንደ ተጠቀለሉ እንዴት ይወጣ ነበር እኛ የክርስቲያን ወገኖች ግን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአራት ቀኖች በኋላ አልዓዛርን ያስነሣው እርሱ እንደሆነ እናምናለን። እንታመናለንም እርሱ በሥራው ሁሉ ላይ ችሎታ አለውና። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ቴዎቅሪጦስ_አናጉንስጢስ በዚችም ዕለት አናጕንስጢስ ቴዎቅሪጦስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም ቅዱስ የሮሜ አገር ሰው ነው። ዐላውያንም ለጣዖት እንዲሠዉ ክርስቲያኖችን ይዘው በአስገደዷቸው ጊዜ እርሱንም ከእነርሱ ጋር ያዙት ወደ ንጉሥም አቀረቡት ያንጊዜ የዐሥራ አምስት ዓመት ልጅ ነበር። ንጉሡም በማመጣብህ ሥቃይ ትፈተናለህን ወይስ ለአማልክት ትሠዋለህ አለው። ቴዎቅሪጦስም እኔስ ለክብር ባለቤት ለጌታዬ ለፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ እሠዋለሁ አለው።ንጉሡም ቴዎቅሪጦስ ሆይ በክፉ አሟሟት እንዳትሞት ለአማልክት መሥዋዕት አቅርብ አለው። እርሱም ንጉሥ ሆይ መሥዋዕቴን እንድታይ ና አለው ንጉሡም ወደ ጣዒቱ ቤት እንዲወስዱትና በዚያ እንዲሠዋ አዘዘና እርሱም በበር ቆመ። ቅዱሱም በጸለየ ጊዜ ንውጸውጽታ ሁኖ አጽቀላጽዮስ የሚሉት አምላካቸው ወድቆ ተሰበረ ። ንጉሡም እንደ ዘበተበት አይቶ አፍንጫውን ቆረጠው አሥረው በወህኒ ቤት እንዲአስገቡት አዘዘ። በማግሥቱም አውጥተው በብረት ምጣዶች ውስጥ ጨመሩት ደግመው ጥልቅ ግድጓድ ቆፈሩ በውስጡም እንጨት ረብርበው ሥጋው ከመለያያው እስቲቦጫጨቅና ቅልጥሙም ከአጥንቶቹ እስቲፈስ ድረስ ወረወሩት ። በዚህም ሊአጠቁት አለቻሉም የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ከእርሱ ጋር አለና። ከዚህ በኋላ አማልክቶቻቸው የሚበቀሉት መስሏቸው ከአማልክቶቻቸው ቤት አስገብተው በዚያ ዘጉበት ። ቴዎቅሪጦስ ግን ከጣዖታቱ ላይ ያለውን ወርቅ ቀጥቅጦ በሥውር ይዞ እየወጣ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች መጸወተው። ተመልሶ ሲገባም ደጃፉ እንደ ቀድሞው ራሱ ይዘጋል። በስምንተኛውም ቀን ንጉሡ መጣ ከደጃፍም ሁኖ አየ አማልክቶቹም ተጥለው ተሰባብረው የከበረ ቴዎቅሪጦስም ሲዘብትባቸው አገኛቸው። ዕውነተኛ ቴዎቅሪጦስንም የሆድ ዕቃው እስቲታይ እንዲሰነጣጥቁት አዘዘ። ደግመው ወደ ጨዋታ ቦታ እንዲአስገቡትና በላዩ አንበሶችን እንዲአስገቡአቸው አዘዘ። አንበሶችም ቁስሎቹን ላሱለት። ዳግመኛም ሕዋሳቱ እስቲነጣጠል ከሚአጣብቅ ቦታ እንዲአስገቡት መላ አካላቱም ታጥፎ እስቲቆለመም እንዲአሠቃዩት አዘዘ። በዚህም ተሸብሮ አላሸነፉትም ንጉሡም ብርታቱን አይቶ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ። የከበረ ኤጲስቆጶስ ኤሞሬዎስና ህዝብ ሁሉ በጸሎት እየተራዱት ቅዱስ ቴዎቅሪጦስን ተከተሉት በቅዱሳን ሰላምታም ተሳልመውት ተሰናበቱት ባለወግ ወታደርም ሰይፉን አንስቶ አንገቱን ቆረጠው ምስክርነቱንም ፈጸመ፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ጻድቁ_አቡነ_ዮናስ በዚኽች ዕለት አቡነ ዮናስ የበዓለ ዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው፡፡ አቡነ ዮናስ አባታቸው ንዋየ እግዚእ እናታቸው ኂሩተ ማርያም ይባላሉ፡፡ በኅዳር 17 ቀን 1357 ዓ.ም በሀገረ ቡር (ሀገረ መስቀል) ሚባል ተወለዱ፡፡ አቡነ ዮናስ በሕፃንነታቸው በጎች እየጠበቁ ሳለ መንፈስ ቅዱስ አደረባቸው፣ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም መዝሙረ ዳዊት ኣስተማራቸው፡፡ እርሳቸውም ይህን ዓለም ንቀው ከመነኮሱ በኋላ 150 መዝሙረ ዳዊት በአንድ ጊዜ እየጸለዩ 3 ሺህ ስግደት ይሰግዱ ነበር፡፡ ቀንና ሌሊት ሲጸልዩም "ጠላቂት" በሚባል ሐይቅ ውስጥ እየገቡ እስከ አንገታቸው ድረው በሐይቁ ውስጥ ገብተው ይጸልዩ ነበር፡፡ ከተሰጧቸውም ጸጋዎች ውስጥ አንዱ 10 ጣቶቻቸው ወደ ሐይቁ ሲገቡ ይበሩ ነበር፡፡ አቡነ ዮናስ በየቀኑ ከ5 ፍሬ "ዳዕሮ" ወይም "ዓየ" በቀር ሌላ ምግብ አይመገቡም ነበር፡፡ ከዚኽም በኋላ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ኀብስተ ኣኩቴትን ጽዋ በረከት ከሰማይ አውርዶላቸዋል፡፡ ጻድቁ እግዚአብሔር ባዘዛቸው መሠረት ወደተለያዩ ቦታዎች እየዞሩ የተለያዩ ተኣምራት በማድረግ ሕሙማንን በመፈወስ ሙታን በማስነሣት ብዙዎችን ከክህደት ወደ እምነት ከኃጢአት ወደ ጽድቅ ከጣኦት ኣምልኮ ወደ እግዚአብሔር ኣምልኮ መልሰዋል፡፡ ጌታችን በአምላካዊ ቅዱስ ቃሉ ‹‹ከመቃብርህ ጸበል የተቀባ የጠጣ ከኃጥያቱ ይነጻል›› የሚል ቃልኪዳን አስቀድሞ የሰጣቸው ሲሆን በዚህ ድንቅ ቃልኪዳን መሠረት ዛሬም ድረስ ከመካነ መቃብራቸው ላይ ፈዋሽ የሆነ ቅብዓ ቅዱስ ይፈልቃል፡፡ ይህንንም በ2011 ዓ.ም ለአንድ ወር በአክሱምና ኤርትራ የዞር ጉዞ ባደረግንበት ወቅት ወደዚህ ታላቅ ገዳም ሔደን የጻድቁን ገዳም ተሳልመን ቅብዓ ቅዱሱን በዐይናችን አይተን በአባቶች ተቀብተን በረከታቸውን አግኝተናል፡፡ ቅብዓ ቅዱሱ በተለይም ጆሮውንና ዐይኑን ለሚያመው ሰው መድኃኒት ነው፡፡  አቡነ ዮናስ ይይዙት በነበረው መቋሚያ በውኃ እየታጠበ ውኃው በጣም ለታመሙ ሰዎች እየተሰጠ በቶሎ ከበሽታቸው ይድኑበታል፣ የማይድኑም ከሆነ ቶሎ በሞት ያርፋሉ፡፡ የሚታጠቡበት ሁሉ ለድኅነት ከሆናቸው በአጭር ጊዜ ይድናሉ ወይም ለዕረፍት ከሆናቸው ወደ እግዚአብሔር ዕረፍት ያሰናብታቸዋል፡፡ አቡ ዮናስ በቁርባን ጊዜ ወደ ኢየሩሳሌም በሠረገላ መንፈስ ደርሰው ያስቀድሱ እንደነበር ገድላቸው ይናገራል፡፡

🔴#ስንክሳር መጋቢት_16 #አባ_ሚካኤል_ሊቀ_ዻዻሳት አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት ዓሥራ ስድስት በዚች ቀን በእስክንድርያ ከተሾሙ አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ ሰባተኛ የሆነ የእስክብድርያ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት አባ ሚካኤል አረፈ። ይህም አባት በአስቄጥስ በአባ መቃርስ ገዳም መንኲሶ በገደል ተጸምዶ ኖረ ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎድሮስ በአረፈ ጊዜ በላዩ የትንቢት መንፈስ ያደረበት አንድ ጻድቅ ሰው እስከ ሚአስረዳቸው ድረስ ኤጲስቆጶሳት ስብሰባ አድርገው ለዚች ሹመት ስለሚሻል ሲመክሩና ሲመረምሩ ብዙ ቀኖች ኖሩ። ከዚህም በኋላ ያ ሰው እኔ በአባ መቃርስ ገዳም በነበርኩ ጊዜ ስጸልይ የሊቀ ጵጵስና ሹመት ለሚካኤል ይገባዋል ለዚች ሹመት የሚሻል እሱ ነውና የሚል ቃልን ከሰማይ ሰማሁ አላቸው፡፡ ሁሉም ስለ ትሩፋቱ ተናገሩ ስለ እርሱም ተስማምተው ከገዳሙ ወደ እስክንድርያ ሊያመጡት ከመስር ገዥ ዘንድ ደብዳቤ አጽፈው ያዙ። ሊያመጡትም ሲሔዱ ስለ ገዳሙ አገልግሎት ከሽማግሎች መነኰሳት ራር ወደ ጋዛ ከተማ ሲመጣ በመንገድ አገኙት ይዘውም አሠሩት። ወስደውም በመስከረም ወር በዐሥራ ሰባት ሊቀ ጵጵስና ሾሙት ያቺም ዕለት በጌታ ደም የከበረ መስቀል በዓሉ የሚከበርባት ናት። ይህም የሆነው ከዲዮቅልጥያኖስ ዘመን በኋላ የሐሚድ ልጅ እልሲድ በሚገዛበት ዘመን ነው። በሹመቱ ወራትም መርዋን አልጋዲን ነገሠ። የእስክንድርያም አገር ሰዎች ከጥቂት ካፊያ በቀር ብዙ ዝናብ ሳይዘንብላቸው ብዙ ዓመታት ኖሩ። በዚያች እርሱ በተሾ መባት ቀን በሁለተኛውም በሦስተኛውም ብዙ ዝናብ ዘንቦላቸው እጅግ ደስ አላቸው። በዚህም አባት ዘመን በክርስቲያን ወገኖች ላይ ታላቅ መከራ ደረሰ ከምእመናንም ብዙዎች ሸሹ የክብር ባለቤት ክርስቶስንም የካዱት ሰዎች ቁጥራቸው ሃያ አራት ሺህ ሆነ። ለዚህ ነገር ምክንያት የሆነውን ከእርሱ እግዚአብሔር እስከአጠፋው ድረስ ይህ አባት ስለዚህ በታላቅ ኀዘን ውስጥ ነበር። ዳግመኛም በዚህ አባት ዘመን ለመለካውያን ቆዝሞስ ሊቀ ጵጵስና ተሹሞ ሳለ የክብር ባለቤት ስለሆነ ስለ ክርስቶስ ተዋሕዶ ከዚህ አባት ከአባ ሚካኤል ጋራ ተከራክሮ ይህ አባት አባ ሚካኤል እንዳስረዳው አመነ። እንዲህም ብሎ በእጁ ጻፈ የክብር ባለቤት ክርስቶስ ከተዋሕዶ በኋላ ሊቀ ጳጳሳት ቄርሎስ እንደተናገረ የመለኮቱና የትስብእቱ አንድ ባሕርይ በመሆን ጸንቶ ይኖራል ሲል ኤጲስቆጶሳቱም እንዲሁ ከተዋሕዶ በኋላ ስለ ክርስቶስ የተለያዩ ሁለት ባሕርያት ሁለት ገጻት አሉት ይሉ ዘንድ የሚገባ አይደለም ሲሉ ጻፉ። ሐዋርያትም በሰበሰቧት በከበረች በአንዲት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአንድነት ጸንተው ሊኖሩ ተስማሙ። ከዚህም በኋላ ከእስክንድርያ ሰዎች መለካዊ የሆነ ስሙ አንስጣስዮስ የሚባል ሰው በላያችው ጥፋትን አመጣ እርሱ ኤጲስቆጶስነት እንዲሾሙት ሽቶ አልሾሙትምና ስለዚህ ወደ እስላሞች ንጉሥ ሒዶ በአባ ሚካኤል ነገር ሠራበት ከዐመፀኞች ነገሥታትም ብዙ መከራ ደረሰበት። ጽኑዕ የሆነ ሥቃይም አሠቃዩት ብዙ ግርፋትም ገረፈው ለረጂም ጊዜ በእግር ብረት አሠሩት። አንገቱንም በሰይፍ ሊቆርጡ ወደ መኰንኑ አቅርበውት ነበር ስለ መንጋዎቹም ጥበቃ እግዚአብሔር አዳነው። ዳግመኛም በመርዋን አልጋዲ ዘመነ መንግሥት የሙሴ ልጅ በሆነ በንጉሥ አገልጋይ አደባባይ በታላቅ ሥቃይ አሠቃዩት። መኰንኑም ገንዘብ እንዲሰጠው ሽቶ ሊቀ ጳጳሳቱን አባ ሚካኤልን አሠረው ሰዎችም መጥተው ዋስ ሁነው አወጡት። ምጽዋትም ጠይቆ ለመኰንኑ ብዙ ገንዘብ አምጥቶ እንዲሰጠው ወደ ላይኛው ግብጽ ወሰዱት። ይህ አባትም ወደ ላይኛው ግብጽ በሔደ ጊዜ በዚያ ብዙ ተአምራትን አድርጎ የክብር ባለቤት ክርስቶስን የካዱትን ምእመናን ብዙዎቹን ወደቀናች ሃይማኖት መልሶ አስገባቸው። የኢትዮጵያ ንጉሥም ይህን አባት የእስላሞች መኳንንት እንዳሠቃዩት በሰማ ጊዜ ፍጹም ኀዘንንም አዘነ። መንፈሳዊ ቅናትንም ቀንቶ ወደ ግብጽ አገር ዘምቶ ከላይኛው ግብጽ ደረሰ፡፡ ከርሱ ጋርም መቶ ሺህ ፈረሰኞች አርበኞች መቶ ሺህ በበቅሎ የተቀመጡ አሁንም በግመል የተቀመጡ መቶ ሺህ አርበኞች ወታደሮች ነበሩ ብዙ አገሮችንም አጠፉ ብዙዎችንም ማረካቸው። የግብጽ ንጉሥም ይህ ሁሉ የሆነው ስለ ሊቀ ጳጳሳቱ ስለ አባ ሚካኤል እንደሆነ ዐውቆ ከእሥራቱ ፈጥኖ ፈታው ታላቅ ክብርንም አከበረው እንዲሁም የክርስቲያንን ወገኖች ሁሉ እጅግ አከበራቸው። ከዚህም በኋላ ለኢትዮጵያ ንጉሥ ደብዳቤ ጽፎ ይልክ ዘንድ ወደ አገሩም እንዲመለስ ያዝዘው ዘንድ የግብጽ ንጉሥ ይህን አባት አባ ሚካኤልን ለመነው። ይህም አባት ወደ ኢትዮጵያ ንጉሥ እርሱንና መኳንንቱን መሳፍንቱንና ሠራዊቱን እየባረከና እየመረቀ ደብዳቤ ጽፎ ላከ ።እንዲህም አለው እነሆ በአንተ ምክንያት ከእሥራትና ከዽቃይ ሁሉ እግዚአብሔር አድኖናልና አሁን ወደ አገርህ በሰላም በፍቅር ተመለስ ስለ እኔና ስለ ክርስቲያን ወገኖች ሁሉ ስለ ደከምክ መልካም ዋጋህን እግዚአብሔር በመንግሥተ ሰማያት ይስጥህ። የኢትዮጵያ ንጉሥም የዚህን አባት የሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤልን ደብዳቤ በአነበበ ጊዜ ፈጥኖ ተነሥቶ ወደ አገሩ በሰላም በፍቅር አንድነት ተመለሰ። አባ ቆዝሞስና ወገኖቹም ከሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤል ጋራ በተስማሙ ጊዜ አባ ቆዝሞስ በውዴታው ለምስር ኤጲስቆጶስ ሁኖ ተሹሞ ከዚህ አባት ከአባ ሚካኤል ስልጣን በታች ሆነ። ይህም አባት መልካም ተጋድሎውን በፈጸመ ጊዜ ወደ ወደደው እግዚአብሔር ሔደ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የቅዱሱም አማልጅነቱ በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ይሁን አሜን ።https://t.me/finotebirhan12

5. የተከበራችሁ በትግራይ ክልል የምትገኙ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እናት ቤተ ክርስቲያን በአባቶቻችሁ ሐዋርያዊ ተልዕኮ ጸንታ እስከአሁን መቆየቷን ለእናንተ መንገር ለቀባሪው ማርዳት ነው፡፡ በመሆኑም በአገራችን በተከሰተው ፖለቲካዊ ችግር ዘመናትን በጽናት የተሻገረችውን እናት ቤተ ክርስቲያን መዋቅራዊ አንድነቷ መፍረስ ሲኖዶሳዊ ልዕልናዋ መጣስ የሌለበት መሆኑን በጽናት እንደምታምኑ እምነታችን የጸና ነው፡፡ ስለሆነም በሚያልፍ ችግር የማያልፍ ታሪክ ጥለን ማለፍ ስለሌለብን እንደቀደሙ አባቶቻችሁ አበው ሊቃውንት ለቤተ ክርስቲያናችን ተቋማዊ አንድነት አስፈላጊውን ዋጋ ሁሉ በመክፈል በጽናት ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ በቀደሙ አባቶቻችን ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ 6. የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ ጊዜያዊ የሽግግር መንግስቱም በክልሉ ተፈጥሮ የቆየው ችግር በሰላማዊ መንገድ በውይይት በመፈታቱ እናት ቤተ ክርስቲያን የተሰማትን ደስታ እየገለጸች አስቀድሞ ችግሩ ከመከሰቱ በፊት አለመግባባቶች በውይይት እንዲፈቱ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርካችን የተመራው የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለቀረበው የሰላም ጥሪ እናት ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛውን ሚና እንደተጫወተች እናስታውሳለን፡፡ በመሆኑም በተከሰተው ችግር የተፈጠሩ ጉድለቶች ካለ ጉድለቶችን ለማረምና ችግሮቹን ለመፍታት ቤተ ክርስቲያናችን ያላትን የጸና አቋም እየገለጽን በክልሉ የተከሰተውን ተቋማዊ አንድነትን የሚጥስና ቀኖና የጣሰ አደረጃጀት እንዲቆም የበኩሉን ሚና በመጫወት ለቤተ ክርስቲያናችን ተቋማዊ አንድነት ኃላፊነቱን እንዲወጣ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ በመጨረሻም መላው በትግራይ ክልል የምትገኙ ምእመናንና ምእመናት በአሁኑ ወቅት በቤተ ክርስቲያናችን ላይ የተከሰተው ፈተና እንዲወገድና አንድነቷ ጸንቶ እንዲኖር በጸሎትና በምሕላ ጸንታችሁ ስታግዙ እንደቆያችሁት ሁሉ አሁንም በክልሉ የተከሰተውን ቀኖናዊ ጥሰትና ሕገወጥ አደረጃጀት ቆሞ እናት ቤተ ክርስቲያን በአንድነቷ ጸንታ እንድትኖር እንደአሁን ቀደሙ በጸሎትና በምሕላ ጸንታችሁ የበኩላችሁን ሚና እንድትወጡ እየጠየቅን የኢፌዴሪ መንግስትም እንደአሁን ቀደሙ በሲኖዶሳዊ አንድነት ላይና በቤተ ክርስቲያናችን መዋቅራዊ አደረጃጀት ላይ የተጋረጠው ችግር ልዩ ትኩረት በመስተጠና የበኩሉን ሚና በመጫወት የቤተ ክርስቲያናችንን ሲኖዶሳዊ አንድንትና ነባር መዋቅራዊ አደረጃጀት ጸንቶ እንዲኖር አገራዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ መጋቢት 15 ቀን 2015 ዓ.ም. አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ምንጭ :-Eotc

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለረጅም ዘመናት በአገራችን ኢትዮጵያ አገራዊ አንድነት ጸንቶና ልዩነቶች ተወግደው እንዲኖሩ አርአያና ምሳሌ የሆነ ተቋማዊ አደረጃጀት ፈጥራና በአንድ መዋቅራዊ አስተዳደር ጸንታ መኖሯ የሚታወቅ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በአገራችን እየተከሰቱ ባሉ አለመግባባቶች መነሻነት ከአገራችንም አልፎ ጸንቶ በቆየው የቤተ ክርስቲያናችን ተቋማዊ መዋቅር ላይ እየተከሰቱ ካሉ ተግዳሮቶች መካከል አንዱ በፌዴራል መንግስትና በትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት መካከል በተፈጠረው የእርስ በእርስ ጦርነት ነው፡፡ በዚሁ ምክንያት በቤተ ክርስቲያኒቱ የበላይ መዋቅርና በትግራይ ክልል አህጉረ ስብከት መካከል አስተዳደራዊና መዋቅራዊ ግንኙነት መቋረጡን ተከትሎና በጦርነቱ ምክንያት ሁሉም የባንክ ተቋማት ሥራቸውን በማቆማቸው በየጊዜው እንደሌሎች አህጉረ ስብከት ለትግራይ አህጉረ ስብከት ይላክ የነበረው በጀት መላክ አልተቻለም፡፡ ይህም በጦርነቱ ከደረሰው ጉዳት በላይ በመዋቅሮቻችን ሥር ተመድበው ይሰሩ የነበሩ የቤተ ክርስቲያናችን አባቶችና አገልጋይ ሠራተኞች ላይ የበጀት እጥረት አጋጥሞ ቆይቷል፡፡ ምንም እንኳን በባንክ መዘጋት ለአገልጋይ ሠራተኞች በጀት መላክ ባይቻልም የደመወዝ መክፈያ የባንክ ሂሣባቸው በአዲስ አበባ ከፍተው ሲገለገሉ የቆዩት አባቶች ማለትም፡ - ብፁዕ አቡነ ኢሳይያስ የመቐለ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣ - ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የማዕከላዊ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስና - ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የሽሬ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ በጦርነቱ ወቅትም ሆነ ከጦርነቱ በኋላ እስከአሁን ድረስ ያለምንም መቆራረጥ ወርኃዊ ደመወዛቸው ወደ ባንክ ሂሣባቸው ሲገባ የቆየና እየገባ ይገኛል፡፡ - የብፁዕ አቡነ መርሐክርስቶስ የአዲግራት ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የባንክ ሂሣብ ግን በዚያው በሚኖሩበት አካባቢ የተከፈተ በመሆኑና በአካባቢው የባንክ አገልግሎት በመቆሙ በጀቱን ማድረስ ያልተቻለ ነው፡፡ በዚህም የዋናው መ/ቤት በእጅጉ ያዘነና በአገሪቱ የተከሰተው ጦርነት ሰላማዊ እልባት አግኝቶ መንግስታዊ መዋቅራዊ ግንኙነቱ እንደተጀመረ የተከሰቱ ችግሮችንና የደረሰውን የጉዳት መጠንና ማዕከል ያደረገ ውይይት በማድረግ ተገቢና ችግር ፈቺ በጀት ለመመደብ ይቻል ዘንድ ለሁሉም የትግራይ አህጉረ ስብከት ሊቃነጳጳሳት በቁጥር 197/897/2015 በ1/6/2015 ዓ.ም. በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ፊርማ በተጻፈ ደብዳቤ ቤተ ክርስቲያናችን ጥሪ አስተላልፋለች፡፡ ቢሆንም ለቤተ ክርስቲያኒቱ ችግር ፈቺ ጥሪ አዎንታዊ ምላሽ መስጠት ሲገባ በክልሉ የተከሰተውን ችግር ቤተ ክርስቲያናችን እንዳላዘነችና የጉዳቱ ቀጥተኛ ተጠቂ መሆኗን ከግምት ውስጥ ያላስገባ ምላሽ አዘል መግለጫ እንደደረሰን ጉዳዩን በጽሞናና በትዕግስት በማየት በጥናት ላይ የተመሰረተ ችግሩን ሊፈታ የሚችል የአቀራራቢ ሽማግሌ ልዑካንን ለመመደብ በዝግጅት ላይ እያለን መጋቢት 13 ቀን 2015ዓ.ም. የቤተ ክርስቲያናችንን ጸንቶ የቆየ ተቋማዊ አንድነትና ነባር መዋቅራዊ አደረጃጀትን በሚንድ መልኩ “መንበረ ሰላማ የትግራይ ጠቅላይ ቤተ ክህነት” ጽ/ቤት የሚል አዲስ ሕገወጥ ክልላዊ መዋቅር በመፍጠርና ያለምንም በቂ ማስረጃ ዋናው መ/ቤት በጀት እንደከለከለ፣ የሠራተኞችን ደመወዝ እንዳገደ በአጠቃላይ በክልሉ በሚገኙ አህጉረ ስብከት ላይ አቅዶ ችግር እንደፈጠረ የሚያስመስልና ሕገ-ቤተ ክርስቲያኑን የጣሰ መግለጫ ከመሰጠቱም በላይ በሕገ-ቤተ ክርስቲያኑ ላይ በግልጽ እንደተደነገገው በሁሉም አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳት ሊመደቡ የሚችሉት በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔና በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ፊርማ መሆኑ እየታወቀ ሆን ተብሎ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በሥራ ላይ እያሉና ሲኖዶሳዊ አንድነቱ ጸንቶ ባለበት ሀኔታ ላይ ከቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ውጭና ያለቅዱስ ፓትርያርኩ ፊርማ የቤተ ክርስቲያኒቱ ቀኖናዊና አስተዳደራዊ አሠራርን በጣሰ ሁኔታ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ሊቃነ ጳጳሳት ተመድበው በሚሠሩባቸው የውጭ ዓለማት አህጉረ ስብከት ላይ ሊቃነ ጳጳሳት ከቀኖና ውጭ ራሳቸውን በራሳቸው በመመደብ መግለጫ መስጠታቸውን በመገናኛ ብዙኃን በመስማታችን በእጅጉ አዝነናል፡፡ በመሆኑም የእምነትና የታሪክ መሠረት በሆነው በታላቁ የትግራይ አህጉረ ስብከት እንዲህ ዓይነት መዋቅርን የሚንድና ቤተ ክርስቲያናችንን ለአደጋ የሚያጋልጥ በዓለም መላውን የእምነቱን ተከታዮች የሚያሳዝን አድራጐት ለታሪካዊ ለትግራይ ሕዝብና ሊቃውንት የማይመጥን አድራጎት ከመሆኑም በላይ ለቤተ ክርስቲያናችን መዋቅራዊ አንድነትና መስፋፋት ተጋድሎ የፈጸሙ የቀደሙ ቅዱሳን አባቶቻችንን ያሳዘነ መሆኑን ለተከበረው የትግራይ ሊቃውንትና ሕዝብ የተሰወረ እንዳልሆነ በጽኑ እናምናለን፡፡ በመሆኑም ከላይ በዝርዝር ለመግለጽ እንደሞከርነው ፡- 1. በትግራይ ክልል የሚገኙ አህጉረ ስብከት በጀት እንዳይላክ በቅዱስ ሲኖዶስ የተወሰነ አንድም ውሳኔ የሌለና በተፈጠረው የእርስ በእርስ ጦርነት ምክንያት የባንክ አገልግሎት በመቆሙ የተከሰተ የግንኙነት መቋረጥ መሆኑ ታውቆ በጀቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከቆመበት ጊዜ ጀምሮ ከአህጉረ ስብከት ጋር በመነጋገር ለመላክ ዝግጁ መሆናችንን እናሳውቃለን፡፡ 2. በክልሉ የተከሰተውን ጦርነት ተከትሎ የደረሰውን ጉዳትና ችግር ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የተሰማትን ሐዘንና በችግሩም ወቅት ለአህጉረ ስብከቱ በበጀት ተደራሽ ባለመሆናችን ያስከተለው ችግር ያሳዘነን መሆኑን በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ፊርማ በተጻፈ ደብዳቤ ገልጸን እያለንና የተከሰተው ጦርነት እንዲቆም በጸሎትና በምሕላ ስንማጸን መቆየታችን ወደጐን ተትቶና ተዘንግቶ ቤተ ክርስቲያናችን የጦርነቱ ደጋፊ በሚያስመስል መልኩ የተሰጠው መግለጫ ተቀባይነት የሌለውና ቤተ ክርስቲያናችንንም የማይገልጽ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡   3. እናት ቤተ ክርስቲያን በኦሮምያ ክልላዊ መንግሥት በምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በዳጩ ሆሮ ባለወልድ ቤተ ክርስቲያን የተፈጸመውን ሕገወጥ ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት ፈተና ለመፍታትና የቤተ ክርስቲያናችንን ሲኖዶሳዊ አንድነትን ለማጽናት በከፍተኛ ኃላፊነት እየሠራች ባለበት ሁኔታ ለዚህ የቤተ ክርስቲያናችን ተልዕኮና ተቅማዊ አንድነት መጽናት በጸሎትም በሐሳብም ልንታገዝ ሲገባ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ አበው የእምነትና የታሪክ መሠረት በሆነው የትግራይ ሊቃውንት እንዲህ ዓይነት ድርጊት መከሰቱ ለአገሩም ሆነ ለሕዝቡ የሚመጥን አድራጐት ባለመሆኑ በአስቸኳይ እንዲቆም እናሳስባለን፡፡ 4. በክልሉ ያለው አጠቃላይ መዋቅራዊ ችግሮችን በሚመለከትና አጠቃላይ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ የተከሰቱትን ችግሮች ተወያይቶ ለመወሰን መጋቢት 21 ቀን 2015ዓ.ም. በሕገ ቤተ ክርስቲያኑ አንቀጽ 19 ንዑስ ቁጥር 3 የሕግ ድንጋጌ መሠረት የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልዓተ ጉባኤ የተጠራ ስለሆነ በክልሉ በቅዱስ ሲኖዶስ ተመድባችሁ በመሥራት ላይ የምትገኙ ሊቃነጳጳሳት በጥሪው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ላይ እንድትገኙና ክልላዊ ችግሩን ለመፍታት በሚደረገው ውይይት ላይ በመሳተፍ የበኩላችሁን ሚና እንድትወጡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከአደራ ጭምር ጥሪዋን ታስተላልፋለች፡፡

🔴#ስንክሳር መጋቢት_15 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት ዐሥራ አምስት በዚች ቀን የከበረች ተጋዳይ መነኰሳዪት #ቅድስት_ሣራ አረፈች፣ #ቅዱስ_ሰለፍኮስ በሰማዕትነት አረፈ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #መነኰሳዪት_ቅድስት_ሣራ መጋቢት ዐሥራ አምስት በዚች ቀን የከበረች ተጋዳይ መነኰሳዪት ሣራ አረፈች። ይቺም ቅድስት ከላይኛው ግብጽ ናት ወላጆቿም የክብር ባለቤት ክርስቶስን የሚያመልኩ ክርስቲያን ናቸው። እጅግም ባለጸጎች ነበሩ ነገር ግን ከእርስዋ በቀር ልጆች የሏቸውም በመልካም አስተዳደግም አሳደጓት ለክርስቲያን የሚገባ ትምህርትን ሁሉ አስተማሩዋት ደግሞም ጽሕፈትን አስተማሩዋት ሁልጊዜም የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍት ታነባለች ይልቁንም የመነኰሳትን ዜና ታነብ ነበር። መጻሕፍትንም አዘውትራ ስለምታነብ የምንኲስና ልብስ ለመልበስ ፈለገች በላይኛው ግብጽ ከሚገኙ ገዳማትም ወደ አንዱ ገዳም ሒዳ ገባች ብዙ ዘመናትም ደናግልን እያገለገለች ኖረች። ከዚህም በኋላ የምንኲስና ልብስን ለበሰች ሰይጣንን ድል እስከ አደረገችው ድረስ ሰይጣን የሚያመጣውን ሥጋዊ ፍትወት እየታገለች ዐሥራ ሦስት ዓመት ኖረች። ንጽሕናን ከመውደዷ ጽናት በተሸነፈ ጊዜ በትዕቢት ሊጥላት ወዶ በቤት መዛነቢያ ልትጸልይ ቁማ ሳለች ተገልጦ ሣራ ሆይ ሰይጣንን ድል አድርገሽዋልና ደስ ይበልሽ አላት እርሷም መልሳ እኔ ደካማ ሴት ነኝ ከክብር ባለቤት ከጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ድል አድርጌ ላበረው አልችልም አለችው። ይህችም ቅድስት አብረዋት ላሉ ደናግል ጥቅም ያላቸውን ብዙ ትምህርቶችን ታስተምራቸው ነበር እንዲህም ትላቸዋለች ከቀን ብዛት ጠላት እንዳያስተኝ እኔ እንደምሞት አስቀድሜ ሳላስብ እግሬን ከአንዱ መወጣጫ ደረጃ ወደ ሁለተኛም አውጥቼ አላኖራትም። ዳግመኛም ለሰው ርኅራኄ ማድረግ በተሻለው ነበር ይህንንም በሚያደርግ ጊዜ የኋላ ኋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ ውስጥ ይኖራል በዜና አረጋውያን መነኰሳት መጽሐፍ ውስጥ የተጻፈ ሌሎች ብዙ ቃሎችንም ተናግራለች። ታላቅ ተጋድሎም እየተጋደለች በዓቷም በባሕር ዳርቻ ሁኖ ሰባት ዓመት ኖረች አንዲት ቀን እንኳ ከሰው አንዱም አላያትም እርሷ ግን ሁሉን ታይ ነበር። ሸምግላ እስከ ሰማንያ ዓመት በደረሰች ጊዜ ከዚህ ዓለም የሕይወት ማሠሪያ ተፈትታ የዘላለም ተድላ ደስታ ወደሚገኝበት ሔደች። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ሰለፍኮስ በዚችም ቀን ዳግመኛ የቅድስት አስጠራጦኒቃ እጮኛዋ ቅዱስ ሰለፍኮስ በሰማዕትነት አረፈ። የዚህን ቅዱስ ዜና ክርስቲያን እንደሆነ ከሀዲ ንጉሥ በሰማ ጊዜ ያመጡት ዘንድ አዘዘ ወደርሱም ሲቀርብ የአስጠራጦኒቃ እጮኛዋ ሰለፍኮስ የተባልክ አንተ ነህን አለው አዎን ነኝ አለ። ዳግመኛም ማንን ታመልካለህ አለው እርሱም እኔ የክብር ባለቤት የሆነ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን አመልከዋለሁ ብሎ መለሰ። ንጉሡም መርዝ ያላቸው እባቦች ወዳሉበት እንዲጨምሩት አዘዘ እግዚአብሔርም አዳነው። ከዚህም በኋላ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡት አዝዞ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12

ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ቆርጠው ለውሾች እንዲጥሉት አዘዘ ውሾች ግን ፈጽሞ አልቀረቡትም ሌሊትም ሲሆን ምእመናን መጥተው ሥጋውን ወሰዱ በአዳዲሶች ልብሶችና በጣፋጭ ሽቶዎች ገነዙት በሣጥንም አድርገው ቀበሩት።ከሥጋውም ብዙዎች አስደናቂዎች ተአምራቶች ተደረጉ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱሳን_አጋንዮስ_አውንድርዮስና_ብንድዮስ በዚህችም ቀን ደግም የከበሩ አጋንዮስ አውንድርዮስና ብንድዮስ በሰማዕትነት አረፉ። እሊህም ቅዱሳን ከአባቶቻቸው ጀምሮ ክርስቲያኖች ናቸው አምላካዊ ትምህርትንም ሁሉየተማሩ ናቸው። በእግዚአብሔርም ሕግ ጸንተው ሲኖሩ የኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አርሞስ መርጦ ኤጲስቆጶሳት አድርጎ ሾማቸው ግን በታወቁ ቦታዎች ላይ አይደለም በብዙዎች አገሮች ውስጥ እንዲሰብኩ ላካቸው እንጂ። በሀገሮችም ያሉ ከሀዲያን ያዙአቸው ያለርኀራኄም አብዝተው ገረፉአቸው በደንጊያም ወገሩአቸው ነፍሳቸውንም በጌታችን እጅ ሰጡ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር መጋቢት_14 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት ዐሥራ አራት በዚህችም ቀን #ቅዱስ_ቶማስ ሐዋርያ በአንዲት ሴት ላይ ተአምራትን አደረገ፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #የቅዱስ_ቄርሎስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ፣ ከአረጋውያን ፍጹማን መነኰሳት ውስጥ አንዱ #ቅዱስ_አባ_ባጥል አረፈ፣ #ቅዱስ_አባት_አባ_ሲኖዳ በሰማዕትነት አረፈ፣ የከበሩ #ቅዱሳን_አጋንዮስ_አውንድርዮስና_ብንድዮስ በሰማዕትነት አረፉ፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ቶማስ_ሐዋርያ መጋቢት ዐሥራ አራት በዚህችም ቀን ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ ሰባት ዓመት ያህል የጋኔን ግንኙነት በአስቸገራት በአንዲት ሴት ላይ ተአምራትን አደረገ። ሐዋርያ ቶማስንም የችው ጊዜ የክርስቶስ ሐዋርያው ሆይ እጅግ ከሚያሠቃየኝ ጠላት አድነኝ ብላ ወደርሱ ጮኸች። እርሱም በምን ምክንያት አገኘሽ አላት እርሷም ከመታጠቢያ ከውሽባ ቤት ስወጣ እንደ ሰው ድው ድው እያደረገ በመታወክ መጣ ድምጡም ሰላላና ቀጪን ነው በሴትና በወንድ ሥራ ሁሉ ነይ እርስበርሳችን አንድ እንሁን አለኝ በተኛሁም ጊዜ በሌሊት መጥቶ ከእኔ ጋራ አንድ ሆነ ብሸሽም አይተወኝም መጥቶ ያሠቃየኛል እንጂ እኔም ከጸሎትህ የተነሣ አጋንንት እንደሚንቀጠቀጡ አውቃለሁና ጸልይልኝ አድነኝም አለችው። ሐዋርያ ቶማስም ሰምቶ ጸለየ ጋኔኑንም ከእርሷ እንዲወጣ አዘዘው ያንጊዜም በእሳትና በጢስ አምሳል ከሴቲቱ ላይ ወጥቶ ተበተነ ከዚህ በኃላ በክርስቶስ መስቀል በላይዋ አማተበ ሥጋውንና ደሙንም አቀበላት ወደ ዘመዶቿም አሰናበታት። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #የቅዱስ_ቄርሎስ በዚህች ቀን በእስክንድርያ ለተሾሙ አባቶች ሰባ አምስተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የቅዱስ ቄርሎስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ። እርሱም በምግባሩ ፍጹም ዐዋቂ ሆነ ሀገሩም ፍዩም ይባላል በእርሷም ቅስና ተሹሞባት ነበር። ከዚያም ለቆ ወደ አባ ፊቅጦር ገዳም ደረሰ እርሱም ከምስር ከተማ ውጭ የኢትዮጵያውያን ዐዘቅት የዐባይ ግድብ በአለበት ነው። በዚያም ታላቅ ገድልን እየተጋደለ ብዙ ዘመናትን ኖረ። ብዙ መጻሕፍትንም ተምሮ ትርጓሜያቸውንና ምሥጢራቸውን ጠንቅቆ ዐወቀ። አሸናፊ ወደሚባለውም ንጉሥ አደባባይ ቀርቦ የእስላሞች ታላላቅ ሊቃውንቶቻቸውና ከምሁራኖቻቸው ውስጥ መምህሮቻቸው ተከራከሩት። ጠቃሚ የሆነ ዕውቀት የተመላበትን መልስ አገኙ የሚጠይቁትንም ሁሉ በመልካም አመላለስ ነገራቸው። ከዚህ በኃላ የዕውቀቱና የቅድስናው ዜና በተሰማ ጊዜ ያለ ፈቃዱ ይዘው በእስክንድርያ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት መንጋውንም ጠበቀ በጸሎትና በቅዳሴ ያገለግሉ ዘንድ ለካህናት ሥርዓትንና መመሪያን ሠራ። ይህም አባት በሊቀ ጵጵስናው ሰባት ዓመታት ከዘጠኝ ወር ከዐሥር ቀኖች ኖረ። ከቀኑም በሦስት ሰዓት አረፈ በምስክርነት አደባባይም ተቀበረ፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_አባ_ባጥል በዚህችም ዕለት ከአረጋውያን ፍጹማን መነኰሳት ውስጥ አንዱ አባ ባጥል አረፈ። ይህም ቅዱስ ሰው አባ ዮሐኒ የተባለ አበምኔት በመነኰሳት ላይ ነገረ ሠሪን እንደ ሚቀበል በሰማ ጊዜ በዓቱን ትቶ ወደ እስክንድርያ መጥቶ የሴት አዳሪዎችንና የአመንዝራዎችን ሁሉ ስማቸውን ጻፈ። ከኪራይ ሠራተኞችም ጋራ ሲሠራ ይውላል። ደመወዙን በተቀበለ ጊዜ የሽንብራ ቂጣ ግዝቶ ይበላል የቀረውንም ገንዘብ ይዞ ወደ አንዲቱ ሒዶ ይሰጣታል በዚች ቀን ከአንቺ ጋራ አድራለሁና ራስሽን ለእኔ አዘጋጂ ይላታል። ከኃጢአትም ሊጠብቃት ከእርስዋ ዘንድ ያድራል ሌሊቱን ሁሉ ተነሥቶ ሲጸልይና ሲሰግድ እግዚአብሔርንም ሲለምን ያድራል ሲነጋም ሥራውን ለማንም እንዳትገልጥ አምሏት ወደ ተግባሩ ይሔዳል። በየዕለቱም ወደ አመንዝራዎቹ እየሔደ እንዲህ ያደርግ ነበር አንዲቱም ሴት ምሥጢሩን ገለጠች ጋኔንም ይዞ አሳበዳት። ሰዎችም ስለዚህ ክፉ ሽማግሌ ክፉ ሥራ የለበትም ብላ ዋሽታለችና እግዚአብሔር መልካም አደረገባት ተባባሉ። እርሷም እንዳናመነዝር ገንዘብ በመስጠት ከኃጢአት ይጠብቀናል እንጂ ነውር የለበትም ብላ ነበርና። የቀሩት አመንዝራዎች በእርሷ ላይ የሆነውን በአዩ ጊዜ ደነገጡ እንደርሷም እንዳያብዱ እውነቷን ነው ማለትን ፈሩ። እርሱም ይችስ በእገሌ ዕለት ትጠብቀኛለች ይል ጀመረ ሰዎችም ሁሉ ያሙት ጀመር እርሱም እንደ ሰው ሁሉ ሥጋ የለኝምን ወይስ እግዚአብሔር መነኰሳትን ተቆጥቶ በፍትወት ተቃጥለው እንዲሞቱ ትቷቸዋልን አላቸው። እነርሱም ልብስህን ለውጠህ ሚስት አግባ ይህ ይሻልሃልና አሉት። እርሱም አዎን ብወድ በሚስቴ እጠነቀቃለሁ በዚህም በክፉ አኗኗር እኖራለሁ እናንተ ግን ከእኔ ዘንድ ሒዱ ምን ትሻላችሁ በእኔ ላይ እግዚአብሔር ፈራጆች አድርጓችኃልን ይልቁንስ እናንተ እንዳይፈረድባችሁ ለራሳችሁ አስቡ ፈራጅ አንድ ነውና ዕለቲቱም አንዲት ናትና አላቸው ይህም ቅዱስ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነትን አገኘ በሰው ዘንድ ግን የተናቀ ሁኖ ኖረ። ከእርሱ ጥቅም የአገኙ አመንዝራዎችም ዝሙታቸውን ተው። ከእርሳቸውም ሕራዊ ጋብቻ ተጋብቶ የኖረ አለ ወደ ገዳምም ገብቶ መንኵሶ በጾም በጸሎት ተወስኖ የኖረ አለ። በአንዲት ዕለትም ከአንዲት አመንዝራ ቤት ሲወጣ ያቺን ሴት አስቀድሞ የለመዳት አንድ ሰው አገኘውና ይህ ሽማግሌ እስከ መቼ ድረስ በዚህ በክፉ ሥራ ይኖራል ብሎ ፊቱን በጥፊመታው። ከዚህም በኃላ በአንዲት ቀን በበዓቱ ውስጥ ሰግዶ ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ውስጥ ሰጥቶ በቤቱም መድረክ የዚች አገር ሰዎች ጊዜው ሳይደርስ በማንም ላይ አትፍረዱ እንዳይፈረድባችሁ የሚልም ጽሑፍ ተጽፎ ተገኘ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_አባት_አባ_ሲኖዳ በዚህችም ቀን ደግሞ ቅዱስ አባት አባ ሲኖዳ በሰማዕትነት አረፈ። እርሱም በግብጽ አገር ከብሕንሳ ከተማ ነው ወደ መክስምያኖስም ክርስቲያናዊ ሲኖዳ አማልክትን የማያመልክ ነው ብለው ነገር ሠሩበት። እርሱም አስቀርቦ ስለ ሃይማኖቱ ጠየቀው በንጉሡም ፊት በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ እርሱም ዕውነተኛ አምላክ እንደ ሆነም መሰከረ፡፡ መክስምያኖስም ይህን የከበረ አባ ሲኖዳን በምድር ላይ ዘርግተው በበትሮች እንዲደበድቡት አዘዘ። ዐጥንቶቹ እስቲሠነጠቁ ደሙም በምድር ላይ እንደ ውኃ እስቲፈስ እንዲሁ አደረጉበት። ከዚህም በኃላ እግሩን ይዘው ጎትተው ወስደው ሽታው በሚከረፋ በጨለማ ወህኒ ቤት ጣሉት የእግዚአብሔርም መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ተገለጠለት። ቊስሎቹንም አድኖ ጤነኛ አደረገው አበረታውም በርታ አትፍራ ስለ መከራህም የክብር አክሊል ተዘጋጅቶልሃልና ደግሞም በጽኑዕ ሥቃይ ትሠቃይ ዘንድ አለህ እግዚአብሔር እንዳዘዘኝ እኔም ከአንተ ጋራ እኖራለሁ አለው ከዚያም ከእርሱ ተሠወረ። በነጋ ጊዜም የነገሥታትን ትእዛዝ የሚተላለፍ ያንን ዐመፀኛ ሒዳችሁ እዩት ሙቶም ከሆነ ለውሾች ጣሉት ብሎ መክስምያኖስ ወታደሮቹን አዘዘ። ወደርሱም በደረሱ ጊዜ ቁሞ ሲጸልይ አግኝተውት ያለምንም ጥፋት ጤነኛ እንደሆነና በሥጋውም ውስጥ የሕማም ምልክት እንደሌለ እርሱም ከቶ ምንም ሥቃይ እንዳላገኘው እንደ ጤነኛና ደስ እንዳለው ሰው ተግቶ እንደሚጸልይ ስለርሱ ለንጉሡ ነገሩት። ንጉሡም ወደርሱ አስመጣው ከሕይወቱም የተነሣ አደነቀ ልብሶቹንም አስወልቆ ያለጉዳት ጤነኛ እንደሆነ ሥጋውን አየ ደንግጦም ይህ ያየሁት ሥራይ ታላቅ ነው አለ። ከዚያም ዘቅዝቀው ሰቅለው ከበታቹ እሳትን እንዲአነዱ አዘዘ ይህንንም አደረጉበት ደግሞ በመንኰራኩር አሠቃዩት በአለንጋዎችም አብዝተው ገረፉት ደበደቡትም።

ዳግመኛም ጌታችን አባ መቃርስን መሥዋዕቱን ተሸክሞ በመሠዊያ ላይ ይቀድስ ዘንድ አዘዘው አባ መቃርስም ጌታችንን የሐዋርያት አለቃ አባታችን ጴጥሮስን እንዲቀድስ እዘዘው ይኽቺ ዕለት በከበረ ስምህ በዚች ደሴት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ መሥዋዕት የተሠዋባት ናትና አለው። ጌታም ላንተ ይገባል አንተ በዚች ደሴት ዘርተሃልና እኔም አሳደግሁ በደቀ መዝ ሙሬ በጳውሎስ አድሬ የተናገርኩትን አላስተዋልክምን የዘራና የደከመ እርሱ አስቀድሞ ፍሬውን ይብላ ያልሁትን አለው። አባት መቃርስም የቅዳሴውን ሥርዓት ከጌታ ተባርኮ በጀመረ ጊዜ ከእስክንድርያዊ መቃርዮስ ጋራ ይራዱት ዘንድ ጴጥሮስ በቀኙ ማርቆስ በግራው ሁሉም ሐዋርያት በዙሪያው ቆሙ።ጳውሎስና ዮሐንስም የየራሳቸውን መልእክት አነበቡ ሉቃስም የሐዋርያትን ሥራ አነበበ ዳዊትም መዝሙሩን ዘመረ ለስም አጠራሩ ምስጋና ገንዘቡ የሆነ ጌታችንም ወንጌሉን አነበበ።በነጭ ርግብ አምሳልም መንፈስ ቅዱስ በኅብስቱና በውይኑ ላይ ወርዶ የጌታችን ክርስቶስን ሥጋና ደም ወደመሆን ለወጣቸው። አባት መቃርስም ወደ ጽዋው ጣቱን በአስገባ ጊዜ ጣቱ በደም ታለለ።የመላእክት ሠራዊት ሁሉ በመሠዊያው ላይ ክንፋቸውን ዘርግተው ይራዱት ነበር ሚካኤልና ገብርኤልም መጡ የመላእክት አንድነት ሁሉም በእርሱ በአባት መቃርስ አምሳል ሁነው እየተራዱት ለሕዝቡ የከበረ ሥጋውንና ደሙን አቀበለ። ከቁርባን ሥርዓት ፍጻሜ በኃላ ጌታችን ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመቃርስ አምሳል ሁኖ ወንጌል በሚነበብበት አትሮንስ ላይ ተቀመጠ ፊቱም እንደ ፀሐይ ይበራ ነበር ለሕዝቡም ቡራኬ ሰጥቶ ወደ መሠዊያው ተመለሰ ሐዋርያትም ከርሱጋራ። ዳግመኛም ከሰባት ቀኖች በኃላ አባታችን መቃርስ ስለ ቤተ ክርስቲያን የሹመት ማዕርግ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ የክብር ባለቤት እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስም ተገልጦ በእኔ ዘንድ ለዚህ ታላቅ ክብር የምትገባ አንተ ነህና አለው። ሽማግሌውም ሰምቶ አለቀሰ በእግዚአብሔርም ፊት ሰገደ አቤቱ በሲሐት ገዳም ወዳሉ መነኰሳት ልጆችህ ጊዜው ሲደርስ እመልስሃለሁ ከዚህ ከሥጋህ ሳትለይ ያልከኝን አስብ።ይህ ካልሆነ መቃራ የምንኲስናውን ሥራ ትቶ ፓትርያርክ ሆነ ይላሉ አለ። ጌታችንም የመረጥኩህ መቃርስ ሆይ እኔ የልብህን ፍላጎት ሁሉ እፍጽምልሃለሁ ግን ፓትርያርክ ትሾም ዘንድ ከልጆችህ የመረጥከውን አንድ አቅርብ አለው። ቅዱስ መቃርስም አቤቱ አንተ ልብ ያሰበውን የምታውቅ ነህ እኔ ግን ወደዚህ አንጥረኛ ሽማግሌ ሰው ተመለከትኩ። እርሱ በቀናች ሃይማኖት የጸና ከሴቶችም ጋር ግንኙነት የማያውቅ ነው አለው ጌታችንም አንተ እንዳልክ ደግ ነው አለ። ቅዱስ መቃርስም ያንን አንጠረኛ ጠርቶ ወደ ታቦተ ሕጉ አቀረበው ያን ጊዜም ወንጌላዊው ማርቆስ መጣ እጁንም በአንጠረኛው ራስ ላይ ጭኖ ዲቁና ሾመው። ደግሞ ቅስና ሾመው ከዚያም የሊቀ ጵጵስና ሹመት እስከ ሚፈጽም በየመዐርጉ ሾመው ስሙንም ዮሐንስ አለው የሰማይ ሠራዊትም ሁሉም የወንጌላዊ ማርቆስ አዲስ ተክል የሆነ ለመቃርስ ልጅ ለዮሐንስ ሊቀ ጵጵስና ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል እያሉ ሦስት ጊዜ ጮኹ በዚያ ያሉ ሕዝብም እሊህን ቃሎች ይሰሙ ነበር። ጌታችንም የሊቀ ጳጳሳት የዮሐንስን ዓይነ ልቡናውን ገልጦለት በሚቻለው መጠን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አየው።ብዙ ቃላትንም ተናገረ ደግሞ ረቂቃን በሆኑ በሰማይ ሠራዊት ቤተ መቅደሱ ተመልቶ አየ የከበሩ ነቢያትና ሐዋርያትም በዚያ አሉ። ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታላቁ አባ መቃራንና የእስክንድርያውን አባ መቃራን ጠራቸው እንዲህም አላቸው በምድር ሳሉ መታሰቢያችሁን የሚያደርጉ ሰዎች የተመሰገኑ ናቸው የዘላለም ሕይወትን ይወርሳሉና በራሴ እምላለሁ ስለ ስሜ የተቀበላችሁትን መከራ በትጋት የሚአስበውና የሚጽፈው የሚሰማው ሁሉ ያመሰግነኝ ዘንድ በቤተ ክርስቲያን የሚያነበው እኔ በጎ ነገርን ሁሉ እሰጠዋለሁ። ከበጎ ነገርም ምንም አላሳጣውም ከመከራውም ሁሉ አድነዋለሁ ኃጢአቱንም ሁሉ አስተሠርይለታለሁ። ከዚህ ዓለምም በሚለይለት ጊዜ ነፍሱን ወደ ዘላለም ተድላ ደስታ ይወስዱ ዘንድ እናንተ ወደም ታስቡትም መንግሥቴ ሊአስገቡት የምሕረት መላእክትን እልካለሁ። በገዳም ወይም በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ወይም በአገር ውስጥ ይህ ዜናችሁ በሚነበብበት እኔ አድራለሁ በረከቴንና ሰላሜንም እስከ ዓለም ፍጻሜ በውስጥዋ አደርጋለሁ። ለዚህ ለስደታችሁ ዜና ተቃራኒ የሚሆን ባልተወለደ በተሻለው ነበር። በእውነት እነግራችኋላሁ በሰው ፊት እንደአመናችሁብኝ በሰማያት በአለው አባቴ ፊትና በከበሩ መላእክቶቼ ፊት አምንባችኋለሁ። አሁን ግን ወደ ሀገራችሁ የምትመለሱበት ጊዜ ደረሰ ይህንንም ብሎ ሰላምታ ሰጥቷቸው ወደ ሰማይ በክብር ዐረገ። ከዚህ በኋላ ሕዝቡን ሁሉ ንጉሡንም ሰበሰቧቸው ወደ አገራቸውም እንደሚመለሱ ነገሩአቸው የክርስቶስንም ሕጉን ሁሉ እንዲጠብቁ ለሊቀ ጳጳሳቱ ዮሐንስም እንዲታዘዙ አዘዙአቸው።ከቀናች ሃይማኖት ወደ ቀኝም ቢሆን ወደ ግራም ፈቀቅ እንዳይሉ በብዙ አማፀኑአቸው አስጠነቀቋቸውም። ሕዝቡም ሰምተው ደነገጡ መሪር ልቅሶንም አለቀሱ ቅዱሳን አባቶቻችንም ከእሳቸው ጋራ በአንድነት አለቀሱ ከእዚህም በኋላ እየአንዳንዳቸውን ባረኳቸውና ተሰናበቷቸው። ያን ጊዜም ከኪሩቤል ወገን የሆነ መልአክ መጣ አውጥቶም በክንፎቹ ተሸከማቸው ወደ እስክንድርያም አድርሶ በሊቀ ጳጳሳቱ ደጅ እሑድ ጥዋት አወረዳቸው።ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ጢሞቴዎስም ሰምቶ እጅግ ደስ አለው።ሁለተኛም በአያቸው ጊዜ አለቀሰ ሰገደላቸውም እነርሱም ሰገዱለት እርስ በርሳቸውም እጅ ተነሣሥተው ሰላምታ ተለዋወጡ። ጤንነታቸውንም ተነጋገሩ ደግሞም ልዩ የነበሩ የአሕዛብን ወደ እግዚአብሔር ስለመመለሳቸውና ስለ ተደረጉት ድንቆች ተአምራት ነገሩአቸው።ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ጢሞቴዎስና ይህን የሰሙ ሁሉም ሕዝብ አደነቁ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት አባቶቻቸንም በዚያ ስምንት ቀን ተቀመጡ። ከዚህም በኋላ ያ መልአክ ተገልጦ በክንፎቹ ደግሞ ተሸከማቸው ወደ ደብረ ሲሐትም አደረሳቸው አንዱ ኪሩብም ከአየር ሁኖ የአባት መቃርስ ልጆች ሆይ አባታችሁ የመንፈስ ቅዱስን ፍሬዎች ተሸክሞ ከስደት ተመልሶ መጥቷልና ወጥታችሁ ተቀበሉ እያለ ጮኸ፡፡ ይህንንም በሰሙ ጊዜ ከታላላቆች እስከ ታናናሾች ወጡ ቁጥራቸውም አምሳ ሺህ መነኰሳት ሆኑ። ከውስጣቸውም በዚያን ጊዜ አባ ዮሐንስ ሐፂርና አባ ብሶይ አሉ የደረሰባቸውንም ሥቃይ በነገራቸው ጊዜ እጆቹንና እግሮቹን እየሳሙ መሪር ዕንባ አለቀሱ። ደግሞ ፊቱን ስለአዩ ደስ አላቸው እርሱም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ባረካቸው። የክርስቶስ ወገን የሆናችሁ በዓለሙ ሁሉ የምትገኙ ምእመናን ሆይ በዘመናት ሁሉ በዓል እያደረጋችኋት በዚች ዕለት ደስ ሊላችሁ ይገባል።ይህም ለአምላካችን ክርስቶስ ስለ ስሙ ደማቸውን እንዳፈሰሱ እንደ ጴጥሮስና እንደ ጳውሎስ መታሰቢያ ለእሊህ ታጋዮች አባቶች ለመከራቸው መታሰቢያ እንዲሆን። እሊህም ታላቁ አባ መቃርስና ባልንጀራው የእስክንድርያው አባ መቃርስ ናቸው በዚች በመጋቢት ወር በዐሥራ ሦስተኛ ቀን ሉክዮስ ከእስክንድርያ አስቀድመን ወደ አወሳናት ደሴት አጋዛቸው ደግሞ በዚሁ ቀን ተመልሰው ወደ እስክንድርያ ደረሱ፡፡https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር መጋቢት_13 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት ዐሥራ ሦስት በዚህችም ቀን የታላቁ አባት #የቅዱስ_መቃርስ እና #የቅዱስ_መቃርዮስ_ዘእስክንድርያ የስደታቸውን መታሰቢያ ነው፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_ዲዮናስዮስ አረፈ፣ የከበሩ #ቅዱሳን_አርባ_ሐራ ሰማይ በሰማዕትነት አረፉ፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ታላቁ_ቅዱስ_መቃርስ እና #ቅዱስ_መቃርዮስ_እስክንድርያዊ መጋቢት ዐሥራ ሦስት በዚህችም ቀን ኦርቶዶክሳውያን ሰዎች የታላቁ አባት የመቃርስን የእስክንድርያው የመቃርዮስን የስደታቸውን መታሰቢያ ያከብራሉ። ይህም በሮም መንግሥት ከወንድሙ ከዋልጥስ በኋላ በነገሠ ጊዜ በኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ላይ ስደትንና መከራን አመጣ።የረከሰ የማኒንና የከሀዲው አርዮስን እምነት ስለሚከተል ነው ለእስክንድርያም ሉክዮስን ሊቀ ጳጳሳት አድርጎ ሹሞ ሐዋርያዊ አትናቴዎስን አሳደደው። ይህም ከሀዲ ሉክዮስ ታላቁን አባት አባ መቃሪን እስክንድርያዊውን አባት መቃርዮስን ፈልጎ በንጉሥ ትእዛዝ ወደርሱ ከገዳማቸው አስመጣቸው። ወደርሱም በደረሱ ጊዜ ለያይቶ በለሰለሰ አንደበት በመሸንገል ወደረከሰ የአርዮስ ሃይማኖት ይገቡ ዘንድ አግባባቸው። እነርሱ ግን ወደ ነገሩ አልተመለሱም ሳይፈሩትም መለሱለት በቅንነትና በትዕግሥትም መከሩት ገሠጹት እንጂ የአርዮስንም ሃይማኖት ብላሽነት የባህሉንም አስከፊነት ከቅዱሳት መጻሕፍት ለይተው አስረዱት። በዚያን ጊዜም ተቆጣ ከቊስጥንጥንያ መካከል ወደምትርቅ ደሴት አጋዛቸው ከእስክንድርያም መርከብን የሚጠብቋቸውንም ወታደሮችን በእነርሱ ላይ በሚያደርጉት ሥራ ሁሉ አጫንቀው በብረት አሥረው ይወስዱአቸው ዘንድ አዘጋጁ። ወደዚች ደሴት በደረሱ ጊዜ በደሴቱ ንጉሥ ፊት አቆሙአቸው ንጉሡም ሰይጣንን የሚያመልክ የከፋ ሰው ነበር የደሴቱም ሰዎች አምላክ ነው ብለው እስቲ አምልኩትና እስቲሰግዱለት ድረስ በሥራዩ አስቷቸው ነበር። እሊህ አባቶቻችንም ከስሕተቱ እንዲመለስ አስተማሩት ለመኑትም አልሰማቸውም ከብዙ ሥቃይ ጋር በወህኒ ቤት ዘጋባቸው እንጂ በጽኑዕ ሥቃይም አሠቃያቸው ጌታችንም ተገልጦ የሚያጸናቸውና የሚያስታግሣቸው ሆነላቸው። የክብር ባለቤት ጌታችንም ጽድቃቸውንና ትሩፋታቸውን ሊገልጥ በወደደ ጊዜ የንጉሡን ልጅ ሰይጣን ያዛት። አባትና እናቷም በታላቅ ኀዘን ላይ እስቲሆኑ አብዝቶ አሠቃያት በከተማ ውስጥም ሰይጣናት ተገልጠው መቃርስና ባልንጀራው ሆይ እኛ ከእናንተ እናንተ ከኛ ምን አላችሁ ከአገራችሁ ያሰደዳችሁን እያሉ ተገልጠው ይጮኹ ጀመር።በንጉሡ ልጅ ያደረውም ሰይጣን ንጉሥ ሆይ መቃርስና ባልንጀራው ካልመጡ ከልጅህ ላይ አልወጣም ብሎ ጮኸ ንጉሡና አብረውት ያሉ አደነቁ ወደ ንጉሡም ቅዱሳንን አመጡአቸው። እሊህ ቅዱሳን መቃርስና ባልንጀራው ወደ ንጉሥ በደረሱ ጊዜ በንጉሡ ልጅ ያደረ ሰይጣን እንዳያሠቃዩት ለመነ። ንጉሡና አብረውት ያሉትም ስለ ሥራቸው ቅዱሳንን መረመሩአቸው፡፡ እነርሱም የሆነውን ሁሉ ነገሩአቸው ስለ ንጉሡም ልጅ ያድኑዋት ዘንድ ለመኑዋቸው። እነርሱም ንጉሡን ገሠጹት እንዲህም አሉት አንተ ሰው ስትሆን ለምን ራስህን አምላክ ታደርጋለህ ዓለምን የፈጠረ አምላክ ከሆንክ ራስህንና ልጅህን ማዳን ይገባህ ነበር። ያን ጊዜም ወደ ክብር ባለቤት ጌታችን ጸልየው ጋኔኑም በወጣ ጊዜ ስለ ክፉ ሥራቸው ንጉሡንና የዚያችን ደሴት ሰዎች ዘለፋቸው። ንጉሡና በዚያ የተሰበሰቡት ይህን አይተው በእሊህ ቅዱሳን አምላክ እናምናለን ከእሊህ ቅዱሳን አምላክ ከእግዚአብሔር በቀር በሰማይና በምድር ሌላ አምላክ እንደሌለ ተረድተናልና እያሉ ጮኹ። የከበሩ አባቶቻችንም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማመንን አሰተማሩአቸው እነርሱም በሽተኞቻቸውን ሁሉ ሰበሰቡ አባቶቻችንም በዘይት ላይ ጸልየው በመስቀል ምልክት አማትበው ቀብተው በሽተኞችን ሁሉ አጋንንት ያደሩባቸውንም ሁሉንም አዳኑአቸው እንዲሁም እያደረጉ እያስተማሩዋቸውም ብዙ ቀን ኖሩ። ከዚህም በኋላ የሀገሩን ምኵራብ አስፈርሰው ቦታውን አጸዱ አነፁ ቦታውም እጅግ ስፋት ያለው መልካም ስለሆነ ቤተ ክርስቲያን አሳነፁ ንጉሡም ስፍር ቁጥር የሌለው ወርቅና ብር የሐር ልብሶችንም ለእግዚአብሔር መቅደስ ለሚአሻውም ሁሉ አመጣ። የከበሩ አባቶቻችንም ጥበብ ያላቸው አንጣሪዎችን ሚዛኑ ለየአንዳንዱ ዘጠኝ ልጥር የሚሆን አሥራ ሁለት ጻህሎችን ሠርተው የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስንና የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ሥዕል የሁለቱንም የመላእክት አለቆች የሚካኤልንና የገብርኤልን ሥዕል በውስጡ እንዲሥሉ ደግሞ አሥራ ሁለት መንበሮችን ለመሠዊያ የሚፈለገውንም ሁሉ አሥራ ሁለት ጽዋዎችና አሥራ ሁለት ዕርፈ መስቀልም እያንዳንዱ ሦስት ሦስት ልጥር የሆኑ ሃያ አራት መስቀሎችን እንዲሠሩ ሦስቱንም የመቅደስ ግድግዳ እንዲሥሉ አዘዙ። የቤተ ክርስቲያኒቱ የሕንፃዋ ሥራ ተፈጸመ። የተረፈውንም ገንዘብ ለድኆችና ለችግረኞች በተኑ። ጌታችን የተጠመቀባት ጥር ዐሥራ አንድ ቀን በሆነች ጊዜ ወደ ባሕር አጠገብ እንዲወርዱና እንዲሰበሰቡ የአገሩን ሰዎች አዘዙዋቸው። ከእስክንድርያም በተሰደዱ ጊዜ እግረ መንገዳቸውን የያዙትን የከበረ ሜሮንን አመጡ። ይህም ከሐዋርያዊ አትናቴዎስ ጊዜ ጀምሮ የተጠበቀ ሉክዮስም ያላገኘው ጌታችንም በዘመናት ሁሉ የጠበቀው ጥፋት ያላገኘው ነው።ይህ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ሆኖአልና። በዚያንም ጊዜ አባት መቃሪ በከበረ ሜሮን በጥልቁ ባሕር ላይ ባረከ ባሕሩም ከእሳት ኃይል የተነሣ በድስት እንደሚያፈሉት ውኃ የሚፈላ ሆነ ዘይቱና ሜሮኑም በውኃው ላይ ተንሳፈው እንደሚያበሩ ከዋክብት ሆኑ ከእርሳቸውም እንደ ፀሐይ የሆነ ታላቅ ብርሃን ታየ። ንጉሡና የተሰበሰቡት ሕዝብ አይተው ፈሩ። የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠ። አጥማቂው ዮሐንስና ቅዱሳን መላእክትም ውኃው በመከብርበትና በሚለወጥበት ጊዜ ተገለጡ። ሕዝቡም ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠመቁ ያንጊዜ ከሽቱ ሁሉ መዓዛው የሚጣፍጥ ሽታ ሸተተ። በዚያን ጊዜም የከበሩ አባቶቻችን ይህን አይተው በምድር ላይ ወድቀው ሰገዱ በስግደታቸው እዚያው ዘገዩ። አባት መቃርስም ሰግዶ ሳለ ጌታችንን እንዲህ ሲል ለመነው። ጌታዬ እለምንሃለሁ ቸርነትህ ትድረሰኝ የዚች ታቦትና ንዋየ ቅድሳቷ ቡራኬ በአምላካዊት እጅህ እንዲሆን አለው።ጌታም እሺ በጎ ብሎ ሜሮኑን ከአባ መቃሪ እጅ ተቀብሎ ታቦቱንና ንዋየ ቅዱሳቱን አከበረ። ከዚያም በኋላ አባት መቃርስን ሦስቱን ደርብ ትባርክ ዘንድ እኔ አዝሃለሁ እኔም ካንተ ጋራ አለሁ ይህንንም ንጹሕና ክቡር የሆነ አገልግሎት ባልንጀራህ አብሮህ ያገልግል። በመጀመሪያም የመካከለኛውን ደርብ በሥጋ በወለደችኝ በድንግል ማርያም ስም ለይተህ አክብር ደግሞ በቀኝ በኩል ያለውን በከበረ መስቀል ስም ለይተህ አክብር በግራ በኩል ያለውን ደርብ በስምህ ለይተህ አክብር በከሀዲ ሉክዮስ እጅ ስለ ስሜ በዚች ደሴት ውስጥ ደምህን አፍሰሃልና አለው። እሊህም የተባረኩ አባቶች ጌታችን እንደ አዘዘ ሊሠሩ በጀመሩ ጊዜ ንጉሥ ዳዊት በመዝሙር ሊያመሰግን ጀመረ መላእክትም በመልካም ቃላት በቋንቋቸው ያመሰግኑ ጀመር ሕዝቡም አድንቀው እግዚአብሔርን አመሰገኑ።

የብፁዕ አቡነ ባስልዮስ እና የብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ሥርዓተ ቀብር እሑድ መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈፀማል። የብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ክቡር አስ
+1
የብፁዕ አቡነ ባስልዮስ እና የብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ሥርዓተ ቀብር እሑድ መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈፀማል። የብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ክቡር አስክሬን ከሰሜን አሜሪካ ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ሀገር ቤት ገብቶ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም እንደሚያርፍና የብፁዕ አቡነ አረጋዊ ዶ/ር ክቡር አስከሬንም በዚሁ ዕለት ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም እንደሚገባ ተገልጿል፡፡ በማግስቱም ማለትም እሑድ መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ከቅዳሴ በኋላ የሁለቱም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ክቡር አስክሬን በቅዱስ ፓትርያርኩ እና በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እንዲሁም በሊቃውንትና በምዕመናን ታጅበው ወደመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ያመራሉ፡፡ በካቴድራሉም አውደ ምሕረት የሁለቱም አባቶች የሕይወት ታሪክ ከተነበበና በሊቃውንት መንፈሳዊ አገልግሎት ከቀረበ በኋላ ሥርዓተ ቀብራቸው እንደሚፈጸም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዶ/ር ስለሥርዓተ ቀብሩ መርሐ ግብር መጋቢት 13 ቀን 2015 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል፡፡ የሁለቱም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ይድረሰን    © EOTC TV

#አሳዛኝ_ዜና #ብፁዕ_አቡነ_አረጋዊ_ዶክተር_አረፉ ሐምሌ 9 ቀን 2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃ
+2
#አሳዛኝ_ዜና  #ብፁዕ_አቡነ_አረጋዊ_ዶክተር_አረፉ ሐምሌ 9 ቀን 2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አንብሮተ ዕድ የሾሙት ጳጳሳት 14 ኤጲስ ቆጶሳት  መካከል አንዱ የሆኑት በቀድሞ ስማቸው  አባ ኃይለማርያም መለሰ ዶ/ር በጵጵስና ስማቸው ብፁዕ አቡነ አረጋዊ ዶ/ር የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት እና የውጪ ግንኙነት መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋና የጅቡቲ  አህጉረ  ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። ብፁዕነታቸው ለረጅም ጊዜ ከሀገር ውጪና በሀገር ውስጥ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሊሻላቸው ሳይችል ቀርቶ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ  ተለይተዋል። በረከታቸው ይደርብን።

አባ ዮልያኖስም በአረፈ ጊዜ በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ሾሙት በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር ከእርሱ በቀር ሚስት ኑራው የተሾመ የለም። ሰይጣንም በሰዎች ልቡና አደረ። በእርሱ ላይም በመናገር የሚአሙት ሆኑ። ስለዚህም ነገር ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ለቅዱስ ድሜጥሮስ ተገልጦ እንዲህ አለው ከሕዝቡ የሚአሙህ አሉና ከልባቸው ጥርጥርን ልታርቅ ይገባሃል። ከሚስትህም ጋር ያለውን የገድልህን ምሥጢር ልትገልጥላቸው ይገባሃል አንተ ራስህን አድነህ በአንተ ምክንያት ሌሎች ይጠፉ ዘንድ አይገባህም ቸር ጠባቂ ከሆንክስ ወገኖችህን ለማዳን ታገል። ማግስት በሆነ ጊዜም ይህም መጋቢት ዐሥራ ሁለት ቀን ነው የቍርባንን ቅዳሴ ቀደሰ፡፡ ሕዝቡንም እንዲጠብቁ እንጂ ከቤተ ክርስቲያን እንዳይወጡ አዘዛቸው። ደግሞ እሳትን እንዲአነዱ አዘዛቸው ወደ ሴቶች መቆሚያም ልኮ ሚስቱን አስመጣት ከሥራው የተነሣ ሕዝቡ ያደንቁ ነበር ምን ሊሠራ እንደፈለገ ሕዝቡ አላወቁምና ። ከዚህም በኋላ ቅዱስ ድሜጥሮስ ተነሥቶ ተንቀሳቀሰ ከእሳቱ መካከል ገብቶ በመቆም እሳቱ እየነደደ በውስጡ ጸለየ ከእሳቱም ፍም በእጁ ዘግኖ በልብሰ ተክህኖው ላይ አኖረ በእሳቱ ውስጥም ቁሞ ለረጅም ጊዜ ጸለየ በልብሰ ተክህኖው ውስጥ ያለ እሳትም አይቀጣጠልም። ከዚህም በኋላ ሚስቱን ጠርቶ ያንን እሳት በመጐናጸፊያዋ ውስጥ ጨመረ ረጅም ጸሎትም ጸለየ እሳቱም ከልብሶቻቸው ምንም ምን አላቃጠለም። ሕዝቡም አድንቀው እግዚአብሔርን አመሰገኑ። ሕዝቡም ይህን ሥራ በምን ምክንያት እንደሠራ ያስረዳቸው ዘንድ የከበረ ድሜጥሮስን ለመኑት። እርሱም ከሚስቱ ጋራ ያለውን ገድሉን ገለጠላቸው ያለውዴታው እርሷም ጋብቻን ሳትሻ እንዳጋቡት እንዲህም አለ እነሆ በአንድነት እኛ ሠላሳ ስምንት ዓመት ስንኖር በጋብቻ ሥርዓት ከተገናኘንበት ጊዜ ጀምሮ በአንድ አልጋ አንድ ልብስ ለብሰን እንተኛለን። ግን ወንዶች ሴቶችን በግብር እንደሚአውቋቸው ሴት እንደሆነች አላውቃትም። በዚህ ሁሉ ዘመን በየሌሊቱ የእግዚአብሔር መልአክ ከሰማይ እየወረደ በክንፎቹ ይሸፍነናል። ይህንንም በዚህ ሁሉ ዘመን ከሰው ወገን ለማንም ከቶ አልገለጥኩም። ልገልጠውም ከቶ አልሻምና ግን እናንተ ከበደል ትድኑ ዘንድ እርሱ እግዚአብሔር አዘዘኝ እንጂ አላቸው። ከአዩትና ከሰሙት የተነሣ ሕዝቡ እጅግ አደነቁ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት እርሱን ስለማማታቸውም የበደሉትን በደል ይቅር ይላቸው ዘንድ እያለቀሱ ቅዱስ ድሜጥሮስን ለመኑት። እርሱም ስሕተታቸውን ይቅር ብሎ በጎ ሥራን ከሚጠላ ከሰይጣን እንጂ ከእናንተ አይደለምና አትዘኑ አላቸው። ከዚህም በኋላ ባረካቸው ወደ ቤታቸውም ይገቡ ዘንድ በሰላም በፍቅር አሰናበታቸው ከሊቀ ጳጳሳቱ ከቅዱስ ድሜጥሮስ ከአዩት ተአምራት የተነሣ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ወደ ቤታቸው ገቡ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አቡነ_ተስፋ_ጽዮን ዳግመኛም በዚህች እለት አቡነ ተስፋ ጽዮን እረፍታቸው ነው፡፡ ጻድቁ ሀገራቸው ሸዋ ሲሆን የንጉሡ የዐፄ ዳዊት ልጅና የዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ወንድም ናቸው፡፡ ስንክሳሩ ‹‹መናኔ መንግሥት ወብእስት›› በማለት ይጠራቸዋል፡፡ አቡነ ተስፋ ጽዮን በመጀመሪያ ‹‹በዓለም ነግሦ መኖርን አልፈልግም›› በማለት የዓለምን ጣዕም ንቀው በመተው ገዳም ገብተዋል፡፡ በታላቅ ተጋድሎ እየኖሩ አጠቃላይ የመርሐ ቤቴ ገዳማትን ሲመሩና ሲያስተዳድሩ ነበር፡፡ ጻድቁ በመስቀላቸው በመባረክ በሐምሌ ወር የዠማን ወንዝ አቆመው የተሻገሩ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ብዙ ሙታንን በማስነሣትና ታላላቅ ተአምራትን በማድረግ ነው ወንጌልን ሲሰብኩ የነበረው፡፡ አበታችን ከመላእክት ጋር በማዕድ አብረው ይቀመጡ የነበሩ ናቸው፡፡ በተለያየ ሀገር የሚኖሩ ቢሆኑም ከወለቃው አቡነ ዘአማኑኤል ጋር በመንፈስ ቅዱስ መሪነት እየተገናኙ ስለ ገዳማት ይወያዩ ነበር፡፡ አቡነ ተስፋ ጽዮን በትግራይ ትልቅ ገዳም ያላቸው ሲሆን በደብረ በግዕና በዜና ማርቆስ ገዳም ደግሞ ቅዱስ ገድላቸው ይገኛል፡፡ ጻድቁ ከብዙ ተጋድሎ በኋላ ጌታችን ተገልጦላቸው ታላቅ ቃልኪዳን ሰጥቷቸው በዛሬዋ ዕለት መጋቢት 12 በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር መጋቢት_12 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጋቢት ዐሥራ ሁለት በዚች ዕለት እግዚአብሔር #ቅዱስ_ሚካኤልን  ወደ ጠንቋዩ በለዓም ላከው፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_ድሜጥሮስ ድንግልናው የተገለጠበት ነው፣ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ #አቡነ_ተስፋ_ጽዮን እረፍታቸው ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ሚካኤል መጋቢት ዐሥራ ሁለት በዚች ዕለት እግዚአብሔር ቅዱስ ሚካኤልን ወደ ጠንቋዩ በለዓም ላከው። "የእስራኤልም ልጆች ተጓዙ፥ በኢያሪኮ ፊት ለፊት በዮርዳኖስ ማዶ ባለው በሞዓብ ሜዳ ሰፈሩ። የሴፎር ልጅ ባላቅ እስራኤል በአሞራውያን ላይ ያደረገውን ሁሉ አየ። ብዙም ነበረና ሞዓብ ከሕዝቡ እጅግ ፈራ፤ ከእስራኤልም ልጆች የተነሣ ሞዓብ ደነገጠ። ሞዓብም የምድያምን ሽማግሌዎች። በሬ የለመለመውን ሣር እንደሚጨርስ ይህ ጭፍራ በዙሪያችን ያለውን ሁሉ ይጨርሳል አላቸው። በዚያን ጊዜም የሴፎር ልጅ ባላቅ የሞዓብ ንጉሥ ነበረ። በወንዙ አጠገብ ባለችው በሕዝቡ ልጆች ምድር በፋቱራ ወደ ተቀመጠው ወደ ቢዖር ልጅ ወደ በለዓም። እነሆ፥ ከግብፅ የወጣ ሕዝብ አለ፤ እነሆም፥ የምድሩን ሁሉ ፊት ሸፈነ በአቅራቢያችንም ተቀምጦአል፤ አሁንም ይህ ሕዝብ ከእኔ ይበልጣልና ልወጋቸውና ከምድሪቱ ላሳድዳቸው እችል እንደ ሆነ፥ እባክህ፥ ና ርገምልኝ፤ አንተ የመረቅኸው ምሩቅ የረገምኸውም ርጉም እንደ ሆነ አውቃለሁና ብሎ ይጠሩት ዘንድ መልእክተኞቹን ላከ። የሞዓብ ሽማግሌዎችና የምድያም ሽማግሌዎችም የምዋርቱን ዋጋ በእጃቸው ይዘው ሄዱ፤ ወደ በለዓምም መጡ፥ የባላቅንም ቃል ነገሩት። እርሱም። ዛሬ ሌሊት በዚህ እደሩ፥ እግዚአብሔርም እንደሚነግረኝ እመልስላችኋለሁ አላቸው፤ የሞዓብም አለቆች በበለዓም ዘንድ ተቀመጡ። እግዚአብሔርም ወደ በለዓም መጥቶ። እነዚህ በአንተ ዘንድ ያሉ ሰዎች እነማን ናቸው? አለው። በለዓምም እግዚአብሔርን። የሞዓብ ንጉሥ የሴፎር ልጅ ባላቅ። እነሆ፥ ከግብፅ የወጣ ሕዝብ የምድርን ፊት ሸፈነ፥ አሁንም ና እርሱንም ርገምልኝ፤ ምናልባት እወጋው አሳድደውም ዘንድ እችል እንደ ሆነ ብሎ ወደ እኔ ልኮአል አለው። እግዚአብሔርም በለዓምን። ከእነርሱ ጋር አትሂድ፤ የተባረከ ነውና ሕዝቡን አትረግምም አለው። በለዓምም ሲነጋ ተነሥቶ የባላቅን አለቆች። ከእናንተ ጋር እሄድ ዘንድ እግዚአብሔር አልፈቀደምና ወደ ምድራችሁ ሂዱ አላቸው። የሞዓብ አለቆች ተነሡ፥ ወደ ባላቅም መጥተው። በለዓም ከእኛ ጋር ይመጣ ዘንድ አልፈቀደም አሉት። ባላቅም ደግሞ ከፊተኞች የበዙና የከበሩ ሌሎችን አለቆች ሰደደ። ወደ በለዓምም መጥተው። የሴፎር ልጅ ባላቅ። ክብርህን እጅግ ታላቅ አደርገዋለሁና፥ የተናገርኸውንም ሁሉ አደርግልሃለሁና እባክህ፥ ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ ምንም አይከልክልህ፤ እባክህ፥ ና፥ ይህን ሕዝብ ርገምልኝ አለ ብለው ነገሩት። በለዓምም መልሶ የባላቅን ባሪያዎች። ባላቅ በቤቱ የሞላውን ወርቅና ብር ቢሰጠኝ፥ በትንሹ ወይም በትልቁ ቢሆን የአምላኬን የእግዚአብሔርን ቃል እተላለፍ ዘንድ አይቻለኝም፤ አሁንም እግዚአብሔር ደግሞ የሚነግረኝን አውቅ ዘንድ፥ እባካችሁ፥ ዛሬ ሌሊት ደግሞ በዚህ እደሩ አላቸው። እግዚአብሔርም ወደ በለዓም በሌሊት መጥቶ። ሰዎቹ ይጠሩህ ዘንድ መጥተው እንደ ሆነ፥ ተነሣ ከእነርሱም ጋር ሂድ፤ ነገር ግን የምነግርህን ቃል ብቻ ታደርጋለህ አለው። በለዓምም ሲነጋ ተነሣ፥ አህያይቱንም ጭኖ ከሞዓብ አለቆች ጋር ሄደ። እርሱም ስለ ሄደ እግዚአብሔር ተቈጣ፤ የእግዚአብሔርም መልአክ ሊቋቋመው በመንገድ ላይ ቆመ። እርሱም በአህያይቱ ላይ፥ ሁለቱም ሎሌዎቹ ከእርሱ ጋር ነበሩ። አህያይቱም የእግዚአብሔርን መልአክ በመንገድ ላይ ቆሞ የተመዘዘም ሰይፍ በእጁ ይዞ አየች፤ ከመንገዱም ፈቀቅ ብላ ወደ እርሻው ውስጥ ገባች፤ በለዓምም ወደ መንገድ ይመልሳት ዘንድ አህያይቱን መታት። የእግዚአብሔርም መልአክ ከወይኑ ቦታዎች መካከል በወዲያና በወዲህ ወገን ግንብ በነበረበት በጠባብ መንገድ ላይ ቆመ። አህያይቱም የእግዚአብሔርን መልአክ አየች፥ ከበለዓምም በታች ተኛች፤ በለዓምም እጅግ ተቈጣ፥ አህያይቱንም በበትሩ ደበደባት። እግዚአብሔርም የአህያይቱን አፍ ከፈተ፥ በለዓምንም። ሦስት ጊዜ የመታኸኝ ምን አድርጌብህ ነው? አለችው። በለዓምም አህያይቱን። ስላላገጥሽብኝ ነው፤ በእጄስ ሰይፍ ቢኖር አሁን በገደልሁሽ ነበር አላት። አህያይቱም በለዓምን። ከብዙ ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ የምትቀመጥብኝ አህያህ አይደለሁምን? በውኑ እንዲህ አደርግ ዘንድ ልማዴ ነበረን? አለችው። እርሱም። እንዲህ አላደረግሽብኝም አላት። እግዚአብሔርም የበለዓምን ዓይኖች ከፈተ፤ የእግዚአብሔርን መልአክ በመንገድ ላይ ቆሞ የተመዘዘም ሰይፍ በእጁ ይዞ አየ፤ ሰገደም፥ በግምባሩም ወደቀ። የእግዚአብሔርም መልአክ። አህያህን ሦስት ጊዜ ለምን መታህ? እነሆ፥ መንገድህ በፊቴ ጠማማ ነውና እቋቋምህ ዘንድ ወጥቼአለሁ፤ አህያይቱም አይታኝ ከፊቴ ሦስት ጊዜ ፈቀቅ አለች፤ ከፊቴስ ፈቀቅ ባላለች በእውነት አሁን አንተን በገደልሁህ፥ እርስዋንም ባዳንኋት ነበር አለው። በለዓምም የእግዚአብሔርን መልአክ። በድያለሁ፤ አንተ በመንገድ ላይ በፊቴ እንደቆምህብኝ አላወቅሁም፤ እንግዲህም አሁን አትወድድ እንደ ሆነ እመለሳለሁ አለው። የእግዚአብሔርም መልአክ በለዓምን። ከሰዎቹ ጋር ሂድ፥ ነገር ግን የምናገርህን ቃል ብቻ ትናገራለህ አለው። በለዓምም ከባላቅ አለቆች ጋር ሄደ። ባላቅም በለዓም እንደ መጣ በሰማ ጊዜ በአርኖን ዳር ዳርቻ በመጨረሻ ወዳለችው ወደ ሞዓብ ከተማ ሊገናኘው ወጣ። ባላቅም በለዓምን። በውኑ አንተን ለመጥራት አልላክሁብህምን? ለምንስ ወደ እኔ አልመጣህም? በውኑ አንተን ለማክበር እኔ አልችልምን? አለው። በለዓምም ባላቅን። እነሆ፥ ወደ አንተ መጥቼአለሁ፤ በውኑ አሁን አንዳችን ነገር እናገር ዘንድ እችላለሁን? እግዚአብሔር በአፌ የሚያደርገውን ቃል እርሱን እናገራለሁ አለው። በለዓምም ከባላቅ ጋር ሄደ፥ ወደ ቂርያት ሐጾትም መጡ። ባላቅም በሬዎችንና በጎችን አርዶ ወደ በለዓም ከእርሱም ጋር ወዳሉት አለቆች ላከ። በነጋውም ባላቅ በለዓምን ይዞ ወደ በኣል ኮረብታ መስገጃ አወጣው፤ በዚያም ሆኖ የሕዝቡን ዳርቻ አየ። ..... በለዓምም መርገሙን ወደ በረከት መለሰው። (ሙሉ ታሪኩን ለማንበብ ኦሪት ዘኁልቁ  ምዕራፍ ፳፪፣ ፳፫፣ ፳፬ እስከ ፍጻሜ) ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ድሜጥሮስ_ሊቀ_ዻዻሳት በዚህችም ዕለት የከበረና የተመሰገነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ዐሥራ ሁለተኛ ተሿሚ የሆነ የድሜጥሮስ ድንግልናው የተገለጠበት ሆነ። የመገለጡ ምክንያትም እንዲህ ነው ከእርሱ በፊት ሊቀ ጳጳሳት ለነበረው ለቅዱስ ዮልያኖስ መንፈቀ ሌሊት በሆነ ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገልጦለት አንተ ወደ ክብር ባለቤት ወደ ክርስቶስ ትሔዳለህ የወይን ዘለላ ይዞ ነገ ወደ አንተ የሚገባ ሰው ከአንተ በኋላ ሊቀ ጳጳስ ሊሆን የሚገባው እርሱ ነው አለው። ማግስት በሆነ ጊዜም የከበረና የተመሰገነ ድሜጥሮስ የወይን ዘለላ ይዞ ወደ ከበረ ዮልያኖስ ዘንድ ገባ ቅዱስ ዮልያኖስም ያዘው ከእኔ በኋላ ሊቀ ጳጳሳታችሁ እነሆ ብሎ ለሕዝብ አስረከባቸው ስለእርሱም የእግዚአብሔር መልአክ እንደተገለጠለት ነገራቸው።