ru
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Открыть в Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Больше
2 635
Подписчики
Нет данных24 часа
+157 дней
+5530 день
Архив постов
ኅዳር_21 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ኅዳር ሃያ አንድ በዚህች ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ጽዮን ማርያም የበዓልዋ መታሰቢያ ነው ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅድስት_ጽዮን_ድንግል_ማርያም ኅዳር ሃያ አንድ በዚች ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የበዓልዋ መታሰቢያ ነው። "ጽዮን" ማለት "ጸወን - አምባ - መጠጊያ" ማለት ነው። አንድም በምሥጢሩ "ማሕደረ አምላክ" ማለት ነው። ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራና ለኪዳኑ ጽላት ሲያገለግል በትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም ለቤተ ክርስቲያንና ለዘለዓለማዊት ርስት ያገለግላል። እግዚአብሔር ከዘመነ አበው በሁዋላ በጊዜው ለእሥራኤላውያን ክብር፣ ሞገስ፣ አምባ የምትሆናቸውን ታቦተ ጽዮንን በቅዱስ ሙሴ አማካኝነት ሰጥቷቸዋል። (ዘጸ. 31፥18) ከዚያም ለ500 ዓመታት ከእነሱ ጋር በመሆኗ በፈጣሪና በእነሱ መካከል ድልድይ ሆና ኖራለች። ከዚያም ባለቤቱ ሲፈቅድ በዘመነ ሳባ በቀዳማዊ ምኒልክ (እብነ መለክ-እብነ ሐኪም) አማካኝነት ወደ ኢትዮዽያ መጥታለች። እነሆ በሃገራችን የ3ሺ ዓመት ቆይታዋን ልትደፍን የቀራት ጥቂት ዓመታት ብቻ ናቸው። ጌታ እንደ ፈቀደ ቅዱስ መስቀሉንና ታቦተ ጽዮንን ይዘን ይሔው በቸርነቱ እንኖራለን። ያም ሆኖ ታቦተ ጽዮንን መስረቅ የሚፈልጉ ብዙ ቀሳጢዎች እንዳሉ እናውቃለን። ግን አንጨነቅም። ምክንያቱም የመጣችውም የምትጠበቀውም በፈቃደ እግዚአብሔር ነውና እንጸልያለን እንጂ አንጨነቅም። በተለያየ ወሬም ራሳችንን አናማጥንም። ባለቤቱ እንድትሔድ ከፈቀደ ደግሞ ማንም ጉልበተኛ አያስቀራትም። ታቦተ ጽዮን ብዙ ጊዜ "ጽላተ ኪዳን፣ ታቦተ ሕጉ" እየተባለች ትጠራለች። "ጽሌ" ማለት "ሰሌዳ" እንደ ማለት ሲሆን "ጽላት" ደግሞ በብዙ ቁጥር ነው። "ኪዳን" ደግሞ በፈጣሪና በሰው ልጆች መካከል ያለ "ውል - ስምምነት" ነው። "ታቦት" ማለት "ማሕደር-ማደሪያ" እንደ ማለት ነው። ሕጉ የተጻፈባቸውን ሰላድው "ጽላት" ስንላቸው የጽላቱ ማደሪያ ደግሞ "ታቦት" ይባላል። ጽላት (ታቦትን) ያመጣ ፈጣሪ ነው። በሐዲስ ኪዳንም ምሥጢርና ሐተታ ቢኖረውም 2 ቦታ ላይ ስለ ታቦት ተጠቅሶ እናገኛለን። (2ቆሮ.6፥16 ፣ ራዕይ.11፥19) በመጨረሻም ኅዳር ሃያ አንድ ቀን ጽዮን ማርያምን የምናከብርባቸውን ምክንያቶች እንመለከታለን።              በዚህች_ቀን ✞ ታቦተ ጽዮን (ጽላተ ኪዳን) ለሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ መሰጠቷን እናስባለን። ታቦተ ጽዮን በምርኮ በሄደችበት በሀገረ ፍልስጤም ዳጎን የተባለ የአህዛብን ጣኦት አድቅቃ በድል የተመለሰችበትን ዕለት በማሰብ። - በዘመነ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በአሚናዳብ ሠረገላ ሁና ከአቢዳራ ቤት ስትመጣ ቅዱሱ ንጉሥ በታላቅ ሐሴት በፊቷ ዘመረ። አገለገለ። ምድራዊ ክብሩን እስኪረሳ ድረስ ለታቦተ አምላክ የተቀኘላት በማሰብ። - ታቦተ ጽዮን ንጉሥ ሰሎሞን ወደ ሠራላት ቤተመቅደስ በክብር የገባችበትን ዕለት በማሰብ፤ የቀደሙ ነብያት ስለእመቤታችን በተለያየ አምሳል ያዩበት ለምሳሌ፦ ነብዩ ዕዝራ በሃገር መንፈሳዊት፣ ሕዝቅኤል በተዘጋች ቤተመቅደስ፣ ዘካርያስ በተቅዋመ ወርቅ ወዘተ ያዩበትን ዕለት በማሰብ፤ - ቀዳማዊ ምኒሊክ ከዐሥራ ሁለቱ ነገድ እስራኤል የበኩር ልጅ ጋር ሊቀ ካህናቱን  አዛሪያስንና ታቦተ ጽዮንን ይዞ አክሱም የደረሰበትን ዕለት በማሰብ፤ - በዘመነ አፄ ባዜን (በ4 ዓ/ም አካባቢ) አማናዊት ጽዮን ድንግል ማርያም ወደ አክሱም ጽዮን በስደት መጥታ ገብታለች። በዚህ ጊዜም 2ቱ ጽዮኖች ሲገናኙ ታላቅ ብርሃን አክሱምን ውጧታልና ይህንንም በማሰብ፤ - በአብርሃ ወአፅብሃ ዘመነ መንግስት ክርስትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሃይማኖት ሆኖ አዋጅ የታወጀበትን በማሠብ፤ - አብርሃ ወአጽብሃ በወርቅና በዕንቁ ያሠሩት ባለ አሥራ ሁለት ክፍል ቤተ መቅደስ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት ዕለት በመሆኑ፤ - በዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዮዲት ጉዲት አብያተ ክርስቲያንን ስታቃጥል ታቦተ ጽዮንን ይዘው ወደ ዝዋይ ሀይቅ ከተሰደዱ በኋላ ዘመነ ሰላም ሲጀመር አክሱም በነበሩ ካህናት አስታዋሽነት ከዝዋይ ወደ አክሱም የገባችበት ዕለት በመሆኑ፤ በእነዚህ ምክንያቶች በመላው ኢትዮጵያ በተለይም በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ከፍ ባለ መንፈሳዊ በዓል እናከብራለን። ቅዱስ እግዚአብሔር ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤት በረከት ያሳትፈን ሐገራችንን ሰላም ያድርግልን። አሜን ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12

የሰ/ት/ቤታችን ባለትዳር ጉባኤ አባላት በሙሉ በዚህ ልዩ ጉባኤ ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል። የፊታችን እሑድ ኅዳር 23/2016 ዓ.ም ከቀኑ 5:00 - 7:00
የሰ/ት/ቤታችን ባለትዳር ጉባኤ አባላት በሙሉ በዚህ ልዩ ጉባኤ ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል። የፊታችን እሑድ ኅዳር 23/2016 ዓ.ም ከቀኑ 5:00 - 7:00

በደብራችን እየተከናወነ የሚገኘው የምሕላ ጸሎት ከኢኦተቤ ቲቪ የተላለፈ

ቅዱስ ሲኖዶስ ባዘዘው መሰረት የጸሎትና የምሕላ ሥርዓት ጠዋት እና ማታ በሰርክ በየአድባራቱ እየተከናወነ ይገኛል በርቀት ያላችሁ (የምትገኙ) በሚቀርባችሁ በየትኛውም አቢያተ ክርስቲያን በመገኘት ሥርዓ
+1
ቅዱስ ሲኖዶስ ባዘዘው መሰረት የጸሎትና የምሕላ ሥርዓት ጠዋት እና ማታ በሰርክ በየአድባራቱ እየተከናወነ ይገኛል በርቀት ያላችሁ (የምትገኙ)  በሚቀርባችሁ በየትኛውም አቢያተ ክርስቲያን በመገኘት ሥርዓተ ጸሎእና ምሕላውን እንድትሳተፉ እያሳሰብን በደብራችን በሚደረገውም ጸሎትና ምሕላ ላይ በቀሩት ቀናት ልብሰ ስብሐት በመልበስ በጸሎቱ ሥርዐት እንድትገኙ በትህትና እንጠይቃለን። ቅዱስ እግዚአብሔር ጸሎትና ልመናችንን ይቀበልልን ሀገራችንን ይጠብቅልን።  አሜን።  ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12

ቅዱስ ሲኖዶስ ባዘዘው መሰረት የጸሎትና የምሕላ ሥርዓት ጠዋት እና ማታ በሰርክ በየአድባራቱ እየተከናወነ ይገኛል በርቀት ያላችሁ (የምትገኙ) በሚቀርባችሁ በየትኛውም አቢያተ ክርስቲያን በመገኘት ሥርዓ
+1
ቅዱስ ሲኖዶስ ባዘዘው መሰረት የጸሎትና የምሕላ ሥርዓት ጠዋት እና ማታ በሰርክ በየአድባራቱ እየተከናወነ ይገኛል በርቀት ያላችሁ (የምትገኙ) በሚቀርባችሁ በየትኛውም አቢያተ ክርስቲያን በመገኘት ሥርዓተ ጸሎእና ምሕላውን እንድትሳተፉ እያሳሰብን በደብራችን በሚደረገውም ጸሎትና ምሕላ ላይ በቀሩት ቀናት ልብሰ ስብሐት በመልበስ በጸሎቱ ሥርዐት እንድትገኙ በትህትና እንጠይቃለን። ቅዱስ እግዚአብሔር ጸሎትና ልመናችንን ይቀበልልን ሀገራችንን ይጠብቅልን። አሜን።

የተወደዳችሁ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ   በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይ የምትገኙና በስራችሁ (በሙያችሁ) ሥራ ማግኘት የምትፈልጉ የሰ/ት/ቤታችን አባላት እናንተ ባላችሁ ሙያ ስራ ማሰራት የሚፈልጉ የሰ/ት/ቤት አባላት ወይም ሌሎች ሰዎች በቀላሉ እናንተን ማግኘት ይችሉ ዘንድ  ቀላል የሆነ የሰ/ት/ቤቱ ሙያተኞች ብቻ የሚገኙበት የቴሌግራም ግሩኘ ከፍተን እንድትገናኙ ለማድረግ የሰ/ት/ቤታችን አይሲቲ ክፍል እየሰራ በመሆኑ ከዚህ በታች በምናስቀምጥላችሁ ሊንክ በመግባት    -ሙሉ ስማችሁን   - የሙያ ዘርፋችሁን   - የስራ ልምዳችሁን   - ስልክ ቁጥራችሁን  በማስቀመጥ ከሙያተኛ ፈላጊዎች ጋር በቀላሉ ይገናኙ። ሌሎችም ስራ ማሰራት የምትፈልጉ አባላትና ወዳጆቻችንም ሙያተኞችን ሰብስበን የምንከፍተው የቴሌግራም ሊንካችን ውስጥ በመግባት የምትፈልጉትን ሙያተኛ በመውሰድ በቅንነት በማሰራት እርስ በእርስ እንድንደጋገፍ በትህትና እንጠይቃለን።    የሙያተኛ መመዝገቢያ ሊንክ @AfeworkBe12 @Nebiyu_Elias ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12

ለሰ/ት/ቤታችን አባላት በሙሉ ቅዱስ ሲኖዶስ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት ከኅዳር 15 እስከ 21 ቀን 2016 ዓ.ም  የሚካሔደው የምሕላና የጸሎት መርሐ ግብር የተጀመረ ሲሆን የሰ/ት/ቤታችን አባላትም በምሕላው ላይ ልብሰ ስብሃት በመልበስ ሁላችንም እንድንሳተፍ ጥሪያችንን እያስተላለፍን አገልግሎቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ የህጻናት የማዕከላዊያን እና የወጣት መደበኛ አገልግሎት እንደማይኖርም ከወዲሁ ለማሳወቅ እንወዳለን። የሰንበት ት/ቤቱ ጽ/ቤት   ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12

በዛሬው እለት ኅዳር 16/2016ዓ.ም የሰ/ት/ቤታችን ሕጻናት ክፍል ለወላጆቻቸው "ሕጻናትን እንዴት እናብቃ" በሚል ርዕስ መርሐ ግብርና ትምሕርታዊ ውይይት አከናወነ። በመርሐ ግብሩም ቀሲስ ዬሴፍ ይኩ
+2
በዛሬው እለት ኅዳር 16/2016ዓ.ም   የሰ/ት/ቤታችን ሕጻናት ክፍል  ለወላጆቻቸው "ሕጻናትን እንዴት እናብቃ" በሚል ርዕስ መርሐ ግብርና  ትምሕርታዊ ውይይት አከናወነ። በመርሐ ግብሩም ቀሲስ ዬሴፍ ይኩኖአምላክ ትምህርት እና ውይይት ተደርጓል። ቅዱስ እግዚአብሔር  እነዚህ የነገ የሀገር እና የቤተክርስቲያን ተረካቢ የሆኑ ሕጻናትን ይጠብቅልን በምግባር በሃይማኖት ያጽናልን።   ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12

ለሰ/ት/ቤታችን አባላት በሙሉ በቅዱስ ሲኖዶስ ትዕዛዝ መሰረት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከዛሬ ኅዳር 15/2016 ዓ.ም ጀምሮ የምህላ ጸሎት መጀመሯ የታወቀ ነው ስለሆነም በነገው እለት ማለትም እሑድ ኅዳር  16/2016 በደብራችን የሚደረገውን ምህላ  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ ቴሌቪዥን  ጣቢያ የሚሰራጭ በመሆኑ ነገ ጠዋት ከቅዳሴ በኋላ የምንችል አባላት  በመገኝት  ልብሰ ስብሐት ለብሰን እናገለግል ዘንድ በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን።   እግዚአብሔር አገራችን ኢትዮጵያን  ይጠብቅልን  በሃይማኖታችን ያጽናን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12

የሐዘን መግለጫ እህታችን ማስረሻ ፈንታው ትላንት በ14/03/16 የወንድሟን እረፍተ ሥጋ(መርዶ) ስለተረዳች ዛሬ ማታ ቅዳሜ በ15/03/2016 የለቅሶ መርሐግብር ስለሚኖር በመኖሪያ ቤታቸው ተገኝተን የምናጽናና ይሆናል። አድራሻው ጎርደሜ በታችኛው በር ስለሆነ ተገኝተን እንድናጽናና ይሁን።

እንኳን ለጾመ ነቢያት አደረሳችሁ . ጾመ ነቢያት :- ከጌታ ልደት አስቀድሞ የሚጾም ጾም  ሲሆን  ከኅዳር 15 ቀን ጀምሮ  የሚጾም ሲሆን ፋሲካው ፍቺው በልደት በዓል ነው፡፡ ይህም ጾም በዘመነ ብሉይና በዘመነ ሐዲስ ቅዱሳንና ምዕመናን ጾመውታል፡፡ . ጾመ ነቢያት:- ስያሜውን ያገኘው ነቢያት የተናገሩት ትንቢት ስለተፈጸመበት ነው፡፡ በየዘመናቱ የተነሡ ነቢያት እግዚአብሔር ወደፊት ሊያደርግ ያሰበውን በእምነት ዓይን እያዩ ምስጢር ተገልጦላቸው የራቀው ቀርቦ ፣ የረቀቀው ገዝፎ ጎልቶ እየተመለከቱ ትንቢት ተናገሩ ፤ ያዩትም መልካም ነገር እንዲደርስላቸው ጾሙ ጸለዩ፡፡ . ነቢያት ጌታችን ከእመቤታችን ስለ መወለዱ ፥ ወደ ግብፅ ስለ መሰደዱ ፥ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለ መጠመቁ ፥ ብርሃን በሆነው ትምህርተ ወንጌል ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ ፥ ለሰው ልጆች ድኅነት ጸዋትወ መከራ ስለመቀበሉና ስለ መሰቀሉ ፥ ስለ ትንሣኤው ፥ ስለ ዕርገቱና ስለ ዳግም ምጽአቱ ትንቢት ተናግረው አላቆሙም፡፡ ለአዳም የተሠጠው ተስፋ ተገልጦላቸው ለተናገሩት ትንቢት ፍፃሜ እንዲያደርሳቸው ፈጣሪያቸውን ተማፀኑትም እንጂ፡፡ በየዘመናቸው ፦ "አንሥእ ኃይልከ ፣ ፈኑ እዴከ" እያሉ ጮኹ፡፡ በጾምና በጸሎት ተወስነውም እግዚአብሔር ሰው የሚሆንበትን ጊዜ በቀናት ፣ በሳምንታት ፣ በወራትና በዓመታት ቆጠሩ፡፡  ነቢዩ ኤርምያስ ስለ ሥጋዌው ትንቢት በተናገረ በ446 ዓመት ጌታችን ከእመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው ሆኗል፡፡ ነቢያት ተስፋው በዘመናቸው ተፈጽሞ በዓይነ ሥጋ ለማየት ባይችሉም እግዚአብሔር ፦ "አያደርገውን አይናገር የተናገረውን አያስቀር" ብለው አምነው ከወዲሁ ተደሰቱ፡፡ ለዘመነ ሥጋዌ ቅርብ የነበሩ እነ ነቢዩ ኢሳይያስ ጾሙ እንዴት መፈጸም እንዳለበት ተናግረዋልም፡፡  ኢሳ.58÷3   በመሆኑም በጌታ ልደት ትንቢተ ነቢያት ስለተፈጸመበት ይህ ጾም "የነቢያት ጾም" ይባላል፡፡ የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት ስለሆነም "ጾመ ስብከት" ይባላል፡፡ ይህ ጾም ሌሎች የተለያዩ ስያሜዎችም አሉት። .  ጾመ ማርያም ይባላል :- እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሰማይና ምድር የማይወስኑትን አምላክ ጸንሻለሁ  ምን ሰርቼ እወልደዋለሁ ብላ ጾማለችና ጾመ ማርያም ይባላል። .  ጾመ ፊሊጶስ  ይባላል :- የአፍራቅያ ሰዎች ሐዋርያው ፊሊጶስን ገደሉት የሐዋርያው ደቀ መዛሙርቱ ሊቀብሩት በፈለጉ ጊዜ ተሰወረባቸው ሱባኤ ያዙ በሶስተኛው ቀን ተገለጸላቸውና ቀበሩት እርሱን ቀብረው ጾሙን እስከ በዓለ ልደት ጾመውታልና ጾመ ፊሊጶስ ይባላል። ምንጭ:- ፍትሃነገስት አንቀጽ 15 ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12

የፊታችን እሑድ ኅዳር 16/2016 እንድትገኙ ተጋብዛችኋል።
የፊታችን እሑድ ኅዳር 16/2016 እንድትገኙ ተጋብዛችኋል።

ጾመ ነቢያት ከኅዳር 15 እስከ የገና በዓል ዋዜማ ድረስ የሚጾም ከሰባቱ አጽዋማት የሚመደብ ጾም ሲሆን ቅዱሳን ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ይወርዳል ይወለዳል ብለው ትንቢት ተናግረዋል ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድም በጾም በጸሎት ይተጉ ነበረና የነቢያት ጾም ይባላል።   እንኳን ለጾመ ነቢያት በሰላም አደረሳችሁ። ጾም ጸሎታችን ተቀበልልን ደስ የሚያሰኘን ይሁንልን ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12