የኔ' ማስታወሻ ..🧚
Открыть в Telegram
በዚህ ቻናል የማይዳሰስ ጉዳይ የለም የተለያዩ አስገራሚ ታሪኮችን፣ ግጥሞችን፣ መጣጥፎችን፣ ወጎችን እንዲሁም በጥበባዊ እይታ የተቃኙ ሁሉ አይነት ጉዳዮችን እናይበታለን ሼር በማድረግ ቤተሰብ እናብዛ... እወዳችኋለሁ❤️ for any comment :- 👉 @Hamy_Hamy Subscribe 👇👇👇 https://www.youtube.com/@Yenemastawosha
Больше1 841
Подписчики
Нет данных24 часа
+147 дней
+2730 день
Архив постов
1 840
....20ዎቹ ወይም 30ዎቹ እድሜ ውስጥ ነህ?
ጠዋት ከእንቅልፍህ ስትነሳ “ህይወቴ ዘግይታለች” የሚል ስሜት ይሰማሀል?
ዙሪያህን ስትመለከት ሁሉም ሰው የህይወቱን መንገድ ያገኘ ይመስልሃል…
አንዱ ቢዝነስ ከፍቷል…
አንዱ ተጋብቷል…
ሌላው አለምን ይዞራል…
ሁሉም ደስተኛ፣ ውጤታማ፣ የተሳካላቸው ይመስሉሀል…
አንተ ግን እዛው ቆመህ ራስህን “ገና ጊዜ አለኝ…” እደርስባቸዋለህ ብለህ ለማሳመን ትሞክራለህ።
ግን ውስጥህ አይቀበልህም… ውስጥህ አልፎብሀል የሚል ጩሀት ያስተጋባል .....
ወንድሜ… ችግሩ ከአንተ አይደለህም።
ችግሩ ራስህን ከሌሎች ጋር ማወዳደርህ ነው።
Social media ላይ የምታየው ሙሉ ህይወት አይደለም…
ሰዎች የሚያሳዩህ ድሎቻቸውን....ስኬታቸውን ብቻ ነው…
እንባቸውን፣ ውድቀታቸውን፣ ጭንቀታቸውን አያሳዩህም።
በ 23 አመቱ ድርጅት የከፈተውን ወጣት ታያለህ…
ከ6 ወር በኋላ መክሰሩን ግን አታይም።
በ25 አመቷ አለምን ስትዞር ታያታለህ…
በእዳ እንደምትኖር ግን አታውቅም።
በ27 አመታቸው በደማቅ ሰርግ የተጋቡትን ጥንዶች ታያለህ…
እርስ በእርስ ቀስ ብለው ያለ ጭቅጭቅ መነጋገር እንደማይችሉ ግን አታይም።
ወዳጄ…
አንተ ዘግይተህ አይደለህም።
ህይወት ውድድር አይደለችም።
20ዎቹና 30ዎች “ሁሉን ነገር መጨረሻ” ሳይሆን
ሁሉን ነገር የመጀመሪያ ፣
የመሞከሪያ ፣ የመውደቅ፣ የመነሳት ዘመን ናቸው።
20ዎቹን አልፈህ ....
በ30ዎቹ መጨረሻ ስራህን ልታገኝ ትችላለህ…
በ40ዎቹ ደሞ ራስህን ልታገኝ ራሰህን ልታውቅ ትችላለህ…
በ50ዎቹ ፍቅር ውስጥ ልታገባ ትችላለህ…
ምንም “ትክክለኛ የህይወት ሰዓት” የሚባል የለም።
ላንዱ ቀድሞ የተሳካለት ላንዱ በእስተርጅናው ሊሳካለት ይችላል።
ማምሻም እድሜ ነው....የማታ እንጀራ ይስጠኝ የሚባለው
ፀሎት የሚፀለየው ለዚህ ነው።
ስለዚህ…
ዛሬ ከሌሎች ህይወት ይልቅ የራስህን ጉዞ አክብር።
ቀስ ብለህ ብትሄድም እየተራመድክ ነው።
ውድቀትህ መጨረሻህ አይደለም…
የዛሬ ውድቀትህ ለነገ ስኬትህ ምክንያት ነው።
አንተ የማትረባ ሰው አይደለህም…
አንተ በሂደት ላይ ያለህ ጠንካራ ብርቱ ሰው ነህ!!
ፈጣሪ ሀሳብህን በሙሉ ያሳካልህ፣አግኝቶ ከማጣት
ይሰውርህ..
ሰላም አዳር🙏
@poethaymi
1 840
#ጠያቂ - መርዝ ምንድነው?
#ሩሚ- ማንኛውም ከሚያስፈልገን መጠን በላይ የሆነ ነገር ሁሉ መርዝ ነው። ስልጣን ፣ ሀብት፣ ድህነት፣ ንዴት፣ ስግብግብነት፣ ስንፍና፣ ጥላቻ ፣ ራስ ወዳድነት፣ ፍቅር፣ ጉጉት፣ ወይንም ሌላ ማንኛውንም ነገር ሊሆን ይችላል።
.
#ጠያቂ - ፍርሃት ምንድነው?
#ሩሚ- እርግጠኛ አለመሆንን አለመቀበል ነው። እርግጠኛ አለመሆናችንን ብንቀበል ፣ ፍርሃትገድል ይሆናል።
.
#ጠያቂ - ቅናት ምንድነው?
#ሩሚ- የሌሎችን በጎ ነገር አለመቀበል ነው። የሌሎችን በጎነት ብንቀበል ፣ መነሳሳት ይፈጥርልናል።
.
#ጠያቂ - ንዴት ምንድነው?
#ሩሚ - ከቁጥጥራችን ውጪ የሆኑ ነገሮችን አለመቀበል ነው። ያንን ብንቀበል ትእግሥት ይሆነናል።
.
#ጠያቂ - ጥላቻ ምንድነው?
#ሩሚ - ጥላቻ አንድን ሰው እንዳለ በሰውነቱ መቀበል አለመቻል ነው። አንድን ሰው ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ መቀበል ብንችል ግን፣ ያ ጥላቻ ፍቅር ይሆናል።
"አንድን ነገር በጥሞና እና በጥልቅ ከተረዳህ፣ በዛ ውስጥ ሁሉንም ነገር ትረዳለህ"
@poethaymi
1 840
በራስ መተማመን በአንድ ጀምበር አይገነባም፤ ልክ እንደ ጡንቻ በልምምድ የሚያድግ ክህሎት ነው!
✔️ታላቁ የሥነ-ልቦና ጠቢብ ዴል ካርኔጌ "በራስ መተማመን" በተሰኘው ድንቅ መጽሐፉ ፍርሃትን አሸንፈን የስኬት ማማ ላይ የምንወጣባቸውን 3 ወርቃማ ምስጢሮች እንዲህ ያስቀምጣል፡
✅ ፍርሃትን ፊት ለፊት መጋፈጥ፦ ፍርሃት የሚጠፋው በመሸሽ ሳይሆን ውስጥ ገብተው ሲለማመዱት ነው።
✅ በቂ ዝግጅት፦ የምታደርገውን ነገር በሚገባ ስታውቀው፣ ልብህ ሙሉ ይሆናል፤ ፍርሃትህ ይበናል!
✅ ራስህን ሁን፦ ሌላውን ለመምሰል አትጣር፤ ያንተ ትልቁ ውበትና ጥንካሬ "ራስህን መሆን" ላይ ነው።
✔️"ማንም ሰው ተደብቆ እንዲኖር አልተፈጠረም። ተለማመድ፣ ተዘጋጅ፣ ፍርሃትህን ሰብረህ ውጣ!"
#በራስመተማመን #ዴል ካርኔጌ
@poethaymi
1 840
በዚህ ዓለም ላይ ያለህ ዋጋ የሚለካው በምትሰጠው አገልግሎትና በምታመጣው ውጤት እንጂ በአንተ ሰብዕና ወይም በልብህ ንፅህና አይደለም። ሰዎች ጓደኛዬ ወይም ወዳጄ የሚሉህ የአንተ መኖር ለኑሯቸው ምቾት እስከሰጠ ወይም የሆነ ፍላጎታቸውን እስካሟላህ ድረስ ብቻ ነው። ልክ እንደ ባትሪ፣ ኃይልህ ሲያልቅና ጥቅም መስጠት ስታቆም ያለምንም ርህራሄ ተጥለህ በሌላ ትተካለህ። ማንም ሰው "ስለ ወደድኩህ አጠገብህ እቆያለሁ" ቢልህ አትመን፤ እውነቱ ግን "ካንተ የምፈልገው ነገር እስካለ ድረስ አጠገብህ ነኝ" የሚል ነው። የሰው ልጅ በተፈጥሮው ራስ ወዳድ ነው፤ የራሱን ጥቅም ለማስከበር ሲል አንተን እንደ መሰላል ተጠቅሞብህ ሊሄድ ይችላል። ይህን መራራ እውነታ ተረድተህ ካልኖርክ፣ በሰዎች ጥቅመኝነት ዘወትር እየተሰበርክ ትኖራለህ። ዓለም የምታከብረው ጠቃሚ እቃን እንጂ መልካም ሰውን አይደለም።
📕 ርዕስ፦ የሰው ልጅ የተፈጥሮ ህጎች
✍️ ደራሲ፦ ሮበርት ግሪን
@Bemnet_Library
@poethaymi
1 840
⭐
ሰዎች አንዳንዴ ህመማቸውን መጥተው ሲነግሯችሁ በተቻለ መጠን ትሁት መሆን እና ከእነርሱ በላይ አንገት መስበር ያስፈልጋል🤗❤️🙌🏼 ⭐ችግራቸውን ስትሰሙ እና ስታማክሯቸው ቤተመቅደስ እንደሚገባ ሰው ጫማ አውልቃችሁ የመግባት ያህል ትሁት ሁኑ!! ትሁት ሁኑ ሰው ችግሩን እና ጉዳቱን ለመናገር አመናችሁ ማለት በዙሪያው የገነባውን አጥር እና ግድግዳ አፍርሶ ነው ወደ ህይወቱ ያስገባችሁ ማለት ነው:: ጋሻ በሌለው ሰው ላይ ደግሞ ጦር አይሰበቅም !! ✍@poethaymi
1 840
ቸኩለንም አይተነዋል ፤ ዘግይተንም አይተነዋል ነገር ግን .. እግዚአብሔር ሲፈቅድ ብቻ ነው ሁሉም ነገር የሚሆነው🙏♥️@poethaymi
1 840
😂 50 አመት በትዳር የመቆየት ሚስጥር!😂
👉ጋዜጠኛ🧔:- "እንዴት ለ 50 አመታት በትዳር ውስጥ በሰላም ዘለቃችሁ?"
👉ሚስት👵:- "ገና እንደተጋባን ከቤተሰቦቼ ቤት በበቅሎ ጭነው ይዘውኝ ሲመጡ በቅሎይቱ ታስቸግራለች ባለቤቴም "ተይ ብያለሁ አንድ😳" አስጠነቀቁ ትንሽ ከሄድን በኋላ እንደገና ደንብራ አስቸገረች ባለቤቴም መልሰው "ተይ ብያለሁ ሁለት😳!" ከትንሽ መንገድ በኋላ ሶስተኛ አስቸገረች ሽጉጣቸውን አውጥተው እንቺ ቅመሽ አሏትና እቤት በእግራችን ገባን።"
"በማግስቱ ገና ሳይነጋ ተነስተው "ተነሽ ውሀ አቀብይኝ" አሉኝ "አረ እኔ መንገዱ አድክሞኛል ትንሽ ልተኛ" ብላቸው ተቆጥተው "ተይ ብያለሁ አንድ!😳" አሉኝ።
ይኸው ከዛች ቀን በኋላ አንድም ቀን ሳንጋጭ ሃምሳ አመት ሞላን እልሀለው።"
😂😂😂😂
@poethaymi
1 840
ሳቅ ሲበዛ የሐዘንን ያህል እንምባ ያስፈስሳል፤መቀመጥ ሲበዛ የመስራትን ያህል ያደክማል፤ደግነት ሲበዛም እንዲሁ የክፋትን ያህል ይጎዳል እንጂ አይጠቅምም። . . . ሁሉን ነገር በመጠን ከያዙት ግን እንኳንስ መልካሙ ክፋውም ይጠቅማል ።#ከበደ_ሚካኤል @poethaymi
1 840
ስለስሜታችሁ ሳይሆን ስለተግባራችሁ!
ስለሚሰማችሁ ስሜት በፍጹም ተጠያቂነት ውስጥ ገብታችሁ እንደማታውቁ አትርሱት፡፡ ተጠያቂነት ውስጥ ራሳችሁን የምታገኙት ወደ እንቅስቃሴ በተለወጠው ተግባራችሁ ምክንያት ነው፡፡ ይህ መርህ በአዎንታዊ ስሜቶችና ተግባሮችም ሆነ በአሉታዊዎ ስሜቶችና ተግባሮች አንጻር እውን ነው፡፡ ለምሳሌ፣ በአንድ ሰው ላይ በውስጣችሁ ምንም አይነት ጤና-ቢስ ስሜት ቢኖራችሁም፣ በንግግር፣ በሁኔታም ሆነ በተግባር እስካልገለጣችት ድረስ በሃላፊነት አትጠየቁም፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ ለአንድ ሰው በውስጣችሁ ምንም አይነት ጤናማ ስሜት ቢኖራችሁም ያንን ስሜት በንግግር፣ በሁኔታም ሆነ በተግባር እስካልገለጣችሁት ድረስ ምንም መልካም ውጤት አይኖውም፡፡ 🚢🚢🚢 ውጤታቸው ጥሩ የማይሆኑትን፣ አሉታዊና ለግንኙነት ቀውስ ምክንያት ሊሆኑ የሚችሉትን ስሜቶች በትክክለኛው መንገድ የምታስተናግዱበትንና የምታስተነፍሱበትን ሁኔታ ማመቻቸት ሃላፊነቱ የእናንተ ነው፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ ውጤታቸው መልካም፣ አዎንታዊና ላሏችሁ ግንኙነቶች ጠቃሚ መዋጮ የሚያደርጉ ስሜቶቻችሁን ለትክክለኛው ሰው፣ በትክክለኛው ጊዜና በትክክለኛው መንገድ የመግለጽ ልምምድን ስታዳብሩ ውጤቱን ማግኘታችሁ አይቀርም፡፡Dr. Eyob mamo @poethaymi
1 840
በእየለቱ በኑሮህ ጠንቃቃ ሁን። ያለፀፀት ነገን ለመኖር ዛሬን በቁምነገር አሳልፍ። ውሳኔዎችህ ትክክለኛ መሆናቸውን መርምር ልክ እንደገና በህይወት የመኖር ዕድል ቢኖርህ ወይም እንደገና የመወለድ ዕድል ቢኖርህ ደግመህ የምትኖረውን እና ለማከናወን የምትመርጠውን አይነት ህይወት ለመኖር ሞክር።ዝጎራ📖 @poethaymi
1 840
ወደጫፉ ኑ!ምንም ተጨማሪ ማብራሪያ ሳያስፈልገኝ ስላነበብኳቸው ብቻ ከሚያነሳሱኝ አባባሎች አንዱ፣ ታዋቂ የ20ኛ ክፍለ-ዘመን ደራሲ የነበረው ፈረንሳዊው Guillauame Apollinaire የተናገረው ይገኝበታል፡- “ወደጫፉ ኑ አላቸው፡፡ እነሱም፣ እንፈራለንና አንመጣም አሉ፡፡ እንደገና፣ ወደጫፉ ኑ አላቸው፡፡ በቀስታ መጡለት፡፡ ከዚያም በድንገት ገፋቸው … መብረር ጀመሩ!” ለረጅም ጊዜ በከረሙበት ስፍራ ተደላድለው መኖር የለመዱ ሰዎች ወደተሻለ ስኬታማነት ለመዝለቅ ከፈለጉ ያንን “ምቹውን ቀጠና” በመልቀቅ ወደ “አስጊው ቀጠና” እና ጫፍ መንቀሳቀስ እንዳባቸው የሚገልጽ አባባል ነው፡፡ ያለንበት ሁኔታ መለወጥ እንዳለበት እያወቅነው ለውጥን ለማምጣት መፍራት ሁሉም ሰው የሚጋራው ስሜት ነው፡፡ ስለሆነም፣ አንዳንድ ጊዜ ምንም መሻሻል ከሌለበት የተሰላቸ ሁኔታችን ለመውጣት የሚያነሳሳን ሰው ወይም ሁኔታ ያስፈልገናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን ገፍቶ የሚያስገባን ሰው ወይም ሁኔታ የግድ ነው፡፡ በሰዎችም ሆነ በሁኔታዎች ምክንያት ወደማትፈልጉት ጫፍ ደርሳችሁ ራሳችሁን ካገኛችሁት፣ ሁኔታው ወደ አዲስ ከፍታ የመብረር አማራጭ የሌለው ድፍረት የምታገኙበት እድል ነውና በርቱ፡፡ ከአንድ ቦታ ሳይንቀሳቀሱ መኖሩን ያን ያህል ለምዳችሁት ከነበረ ወደ አዲስ ነገር መብረሩንም ትለምዱታላችሁ!
ዶክተር እዮብ ማሞ@poethaymi
1 840
#ከምርጥ_መጽሐፍቶች
“ማንም ሰው በመስጠት ደሀ አይሆንም፡፡”
"ያም ሆነ ይህ ሰዎች ከስር መሰረታቸው መልካሞች ናቸው፡፡ "
#ከአና_ፍራንክ መጽሐፍ የተወሰደ
“አንዳንድ ሰዎች የሰዎችን ከባድ ችግር መቅረፍ ቢችሉም በእነሱ ጥቂት ችግር ይወድቃሉ፡፡”
"በህይወትህ ትልቁ ጠላትህ ውስጥህ ያለው መጥፎ ሀሳብ ነው ስለዚህ መጀመሪያ እሱን ታግለህ አሸንፍ ከዛ ሌላው ቀላል ነው!"
''ለሰዉ የከበደዉ የወደቀን ማንሳት እንጅ የቆመን በርታ ማለት አይደለም፡፡''
#ከውብ መጽሐፍ የተወሰደ
“ሞት ሆይ ....ና እስቲ እቀፈኝ ፤ ድብን አድርገህ እቀፈኝ ወደ ሰማየ ሰማያት እንምጠቅ።”
#ከየጭን_ቁስል መጽሐፍ የተወሰደ
“ቀን ጎድሎብህ ሁሉንም ብታጣ፣ሁሉም ቢከዳህ፣ ሁሉን ነገር እንደ ነበረ መመለስ የሚያስችልህ አንድ ነገር ብቻ አለ፣ በራስ ልቦና ዉስጥ የምትፈጥረዉ የአይበገሬነት እልህ።”
#ከያልታበሱ_እንባዎች" መጽሐፍ የተወሰደ
@poethaymi
1 840
ልቤ መሻር በጀመረ ጊዜ……ያለመኖራቸውን እውነቱን ተቀብዬ መኖር በጀመርኩ ጊዜ……በመሄዳቸው የፈጠሩብኝን ክፍተት ለመልመድ እየዳኹ ባለ ጊዜ……ከረፈደ በኋላ ሰው ቢመጣ የመቀበል አቅም በሌለኝ ጊዜ… መጣ……ጠየቀኝ……በተሽመደመደው ልቤ ተመርቼ መለስኩለት
"ምን አጣሽ?"
እራሴን
"ለምን?"
እነሱን ስመስል
እንዲወዱኝ ሳስመስል
"ምን አተረፍሽ?"
ፍራቻ
"ከየት መጣ?"
የቀረኝ መልካምነት ጭራሽ እንዳይጠፋ
ፈራሁ በከፉብኝ ልክ እንዳልከፋ
"ምን አድርገው ሰበሩሽ?"
ፈቅጄላቸው……ኑ ብዬ ድክመቴን አሳይቼያቸው።
"ህይወት ምን አስተማረችሽ?"
አንዳንዴ…
የሰውን ልጅ ባህሪ ሳይሆን ሰው መቀየር እንደሚሻል፡፡
"ምን ወሰንሽ?"
መሄድን
ብቻ መልመድን
"እሺ እኔስ...?"
አንተ ምን?
"እወድሻለሁ፡፡"
አመሰግናለሁ፡፡
"በኔ ሊክስሽ ቢሆንስ?"
በደከመኝ ሰዓት መጣህ……
"አንድ እድል ስጪኝ"
እድል ጨረስኹ…
የቀረኝን ለራሴ ሰጠሁኹ
በተቀመጠበት ትቼው ሄዱኩኝ………ቃል አጣች እንጂ ልቤ ስትወራጭ እሰማታለሁ.……ፊቷን አዙራ በጀርባዬ እያየችሁ
"ሞክር ተስፋ አትቁረጥ……ብቻዋን ምትችል ይመስል እያስመሰለች ነው" ብትለው ደስ ባላት ነበር………ድሮም መሰበር ልማዷ ነው አይቻል እንጂ ከሰውነት ለመጉደል በሌለች ነበር እስካሁን።
ሰው እንዴት ህመሙ ካለበት ይከርማል?
ልቤ ግን ምን ሆና ነው?
ተይ ብላት የማትሰማው……
እኔ የምለው "መተው" ግን እንዴት ነበር?
እንጃ……
@poethaymi
1 840
#ፓፒዮ_ማን_ይሆን❓
(ፓፒዮ መጽሐፍን አንብባችሁታል❓ ካላነበባችሁት እንድታነቡት የሚከተለውን ላካፍላችሁ....)
ፓፒዮ አንድ ያለኃጢያቱ በግድያ ወንጀል ተከሶ ገና በሃያ አምስት ዓመቱ የእድሜ ልክ እስራት የተፈረደበት ወጣት ሲሆን ነጻ እስከ ወጣበት እስከ ''1945 ዓ.ም'' ድረስ ለ13 ተከታታይ ዓመታት ከእስር ቤት ለማምለጥ የሚያደርገውን እጅግ ፈታኝና የማይታመኑ የሚመስሉ ጀብዱዎችን በባሕርና በየብስ ሲፈፅም እንደነበረ የሚተርክ በራሱ የተጻፈ ልብወለዳዊ የሕይወት ታሪክ (autobiographical novel) ነው።
የታሪኩም ሆነ የመጽሐፉ ባለቤት ሔንሪ ሻሪየ (በቅጽል ስሙ ፓፒዮ) የተባለ ፈረንሳዊ ነው።
ፓፒዮ አልሸነፍ ባይነት ፣ ቅንነት ፣ በእምነት መጽናት ፣መስዋትዕነት ፣ ብሩህ ህልም፣ ተስፋ አለመቁረጥ፣ነፃነትን በአንድ ላይ ያጣመረ ተወዳጅ መፅሀፍ ነው።
.
ፓፒዮ በፈረንሳይኛ (Papillon) ቢራቢሮ ማለት ሲሆን፣ሻሪየ ደረቱ ላይ የቢራቢሮ ንቅሳት ስለነበረው የቅጽል ስሙንም ከዚያ እንዳገኘ ይነገራል።
መጽሐፉ በ1969 ዓ.ም እንደ አውሮፓ አቆጣጠር ለንባብ ሲበቃ እጅግ ተወዳጅና ተነባቢ በመሆኑ የበርካታ አንባቢዎችን ቀልብ ስቦ እንደነበር ተጽፏል።
ሻሪየ በሕይወት በነበረበት ዘመን በተደረገለት ቃለ መጠይቅ መፃፉ ሰባ አምስት ፐርሰንቱ(75%) ትክክለኛና በራሱ
የደረሰ እውነተኛ ታሪክ መሆኑን ተናግሯል።
..........................
👉 ፓፒዮ
ዘመን አይሽሬውን መጽሐፍ ጋበዝኳችሁ🙏🙏
//__
@poethaymi
1 840
ሁለት ሰዎች ከእኛ ሱቁ ፊት ለፊት ተቀምጠው ያለማቋረጥ እየሳቁ ነበር።
አንድ የሰፈራችን የመንግስት ባለስልጣን በአጠገባቸው ሲያልፍ ስለሚያውቃቸው በሳቃቸው ተገርሞ ለምን እንደሚስቁ ጠየቃቸው።
እነርሱም፦“ጌታዬ ለዚህች ሀገር ችግር መፍትሔ አለን።” አሉት
ባለስልጣኑ በጉጉትና በግርምት ጠየቃቸው፦“መፍትሔው ምን ይሆን?”
መለሱለት፦“ሕዝቡን በጠቅላላ ሰብስበን እንቀብራቸዋለን። ከሕዝቡ ጋር አንድ አህያ አብረን እንቀብራለን”
ባለስልጣኑ፦“አህያውን ለምንድነው ከእነሱ ጋር አብረን የምንቀብረው?”
ሁለቱም ሰዎች ከቅድሙ ይብስ ጮክ ብለው እየሳቁ አንደኛው ለሌኛው እንዲህ አለው፦“አየህ አልነገርኩህም ነበር ማንም ስለሕዝቡ አይጠይቅም” 😂
@poethaymi
1 840
( ያ ሰው ... )
=================
አውቀዋለሁ እኮ ....
ሁሉን ቻል ባረኩ ፈርቼ እንዳይመስለው
መች ተረሳኝና ልቤን ስንቴ ከአመድ እንዳንደባለለው
ወደአምና ቁጭቴ .....
ጎትቶ አይጨምረኝ ተው በለው ይሄን ሰው
በደል አመርቅዞት የመረረ ቁስሌን ይቅር አይቀስቅሰው
(እያልኩ ጠላቴን ጌታ ፊት ስከሰው ..)
ከዘርፋፋ ልብሱ ገለጠና አካሉን
ዘመን ያላጠፋው አሳየኝ ችንካሩን
የደም ላብ ያወዛው አስነካኝ ግንባሩን
ትኩስ ደም ያዘለ ዳሰስኩኝ ሰምበሩን ...
አለቀስኩ በብርቱ ...
ህማሙ መከራው ሆዴን አላወሰው
ዳግም ዘምበል አለ ዝንጉ ልቦናዬን ሊመክር ሊወቅሰው
" ልጄ ...
በደል አትቋጥሪ ይቅር አትክሰሽው
አልታወሰሽ እንጂ ያኔም ' ውደጅ ' ያልኩሽ
ነበር ይሄንን ሰው !!! "
ጠላቶቻችሁን ውደዱ ፤ የሚረግሟችሁን መርቁ ...
Kiyorna
@poethaymi
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
