ru
Feedback
የካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ት/ጽ/ቤት ቻናል Yeka sub city wereda 4 Education office channel

የካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ት/ጽ/ቤት ቻናል Yeka sub city wereda 4 Education office channel

Открыть в Telegram

Government Educational organization

Больше
360
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 дней
Архив постов
🫶ለ6ኛ እና ለ8ኛ ክፍል ተማሪዎች መብቶችና እና ግዴታዎች 👉ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብና ሥርዓት  አከባበር እንዲሁም የመልስ ወረቀት አጠቋቆርና ተዛማጅ ሁኔታዎችን አስመልክቶ በሚሰጡ ገለፃዎች ላይ የመሣተፍ ግዴታ አለበት። 👉ተፈታኙ በገለፃው ላይ ባለመሳተፉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ኃላፊነቱን ይወስዳል። 👉በመጨረሻም የሰራበትን የመልስ ወረቀት ለፈታኙ በመስጠት  የጥያቄ ወረቀቱን ይዞ መውጣት ይችላል። 👉ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ጥያቄዎቹን መስራት ከመጀመሩ በፊት በፈተና የመልስ መስጫ ወረቀት ላይ የግል መለያ መረጃዎችን በሙሉ ግልፅ በሆነ ሁኔታ በቅደም ተከተል ጽፍ ማጥቆር ይኖርበታል (በተለይ የመለያ ቁጥር እና የትምህርት አይነት ኮድ)። 👉ማንኛውም ተፈታኝ የራሱን ችሎታና ዕውቀት ተጠቅሞ መስራት ይጠበቅበታል፡፡ 👉የሚሠራባቸው የጥያቄና የመልስ መስጫ ወረቀቶች ለሌሎች ተፈታኞች ዕይታ የተጋለጡ እንዳይሆኑ ሸፍኖ መስራት ይኖርበታል። 👉ማንኛውም ተፈታኝ ሞባይል፣ ካልኩሌተርና የመሳሰሉ ማንኛውንም ዓይነት  የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው ። 👉እያንዳንዱ ተፈታኝ ይህንን አውቆ በቅድሚያ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ። 👉ይህንን ባለማድረጉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ተፈታኙ  ራሱ ኃላፊነቱን ይወስዳል። 👉ማንኛውም ተፈታኝ በመፈተን ላይ እያለ ፈተናውን እንዳይሠራ የሚያውኩ ሁኔታዎች ቢያጋጥመው በፈታኙ ሲፈቀደለት ችግሩን በመግለጽ አስፈላጊውን እርዳታ ማግኘት ይችላል። ይሁንና በማንኛውም ምክንያት ለባከነ ጊዜ ተጨማሪ ሰዓት አይፈቀድም። 👉ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከሚጀመርበት ጊዜ ተኩል ሰዓት /30 ደቂቃ/ ቀደም ብለው ከመፈታኛው ቦታ በመገኘት መቀመጫቸውን መያዝ አለባቸው። ፈተናው ከተጀመረ ከ15 ደቂቃ በኋላ የሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተናው አዳራሽ መግባት አይፈቀድለትም። 👉ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ፈተናውን ሠርቶ ቢያጠናቅቅም እንዲወጣ አይፈቀድለትም። ይሁን እንጂ ፈተናው ከተጀመረ ከ45 ደቂቃ በኋላ ከፈተና አዳራሹ ለመውጣት   እንዲፈቀድለት ሲጠይቅ የመልስ ወረቀቱን ለፈታኙ አስረክቦ በጸጥታ እንዲወጣ ይፈቀድለታል። 👉ፈተናው ሊጠናቀቅ ከ10 ደቂቃ ያነሰ ጊዜ ሲቀረው የሚጨርስ ተፈታኝ የሁሉም ተፈታኞች የመልስ ወረቀቶች እስኪሰበሰቡና ለፈተናው የተፈቀደው የጊዜ ገደብ አብቅቶ እስኪደወል ድረስ በቦታው ተቀምጦ እንዲቆይ ይደረጋል። 👉ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ ማንኛውም ተፈታኝ ትክክለኛ ያልሆነ የተቀደደ ወይም የተበላሸ የፈተና ጥያቄ ጥራዝ ከገጠመው ወይም የተሰጠው የመልስ ወረቀት የተበላሸ ከሆነ ወይም በራሱ እጅ ቢበላሽበት እጁን አንስቶ በመጠየቅ ሲፈቀድለት ሊያስቀይር ይችላል። 👉ማየት ለተሳነው እና ድጋፍ የሚሹ ተፈታኝ የፈተናውን ጥያቄዎች የሚያነብለትና የሚሰጣቸውን መልሶች የሚያጠቁርለት ፈታኝ በግሉ እንዲመደብለት ይደረጋል። 👉ተፈታኞች ፈተናውን ለመውሰድ የሚችሉት በቅድሚያ ትም/ቤት በተመዘገበበት ጣቢያ እንጂ የፈተና ጣቢያ ቀይረው ሊፈተኑ አይችሉም። ✍✍✍✍✍✍✍✍✍✍ 🙌 ለተፈታኞች የተከለከሉ ነገሮች ❌📵📱የግል ስልክ (Mobile phone)፣ታብሌት፣ ❌💽📟📞🎧የጆሮ ማዳመጫ (earphone) እና ማንኛውም ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች፣ ❌⌚️⏱የእጅ ሰአት፣ ❌🧻🧢🪥ማንኛውም የግል ጽዳት ማስጠበቂያ ሆነ ማስዋቢያ ቁሳቁስ፣ ❌🎒👜ማንኛውም ዕቃ ለመያዣነት የሚያገለግል ቦርሳ/እቃም የያዘ ቦርሳ፣ ❌🔪🪛ማንኛውም ስለት ነክ ነገርና ብረት መልካም የፈተና ዝግጅት!

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1444ኛው የኢድ አል አድሀ(አረፋ)በአል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ🙏መልካም በአል እንመኛለን።
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1444ኛው የኢድ አል አድሀ(አረፋ)በአል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ🙏መልካም በአል እንመኛለን።

17/10/2015ዓ.ም በዛሬው እለት በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ውስጥ የሚገኘው የአዲስ ብርሃን ቅድመ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት 24 ወንዶችና 27 ሴቶች በድምሩ 51 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎችን በድምቀት አስመርቋል።ለተማሪዎቹ፤መምህራኖቻቸው እና ለወላጆች በአጠቃላይ ለትምህርት ማህበረሰቡ እንኳን ደስ ያላችሁ እንላለን።

11/10/2015ዓ.ም በዛሬው እለት በወረዳችን የካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 የሚገኘው የቀበና ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የKG3 ተማሪዎችን በድምቀት አስመርቋል።እንኳን ደስ ያላችሁ።

ቀን 07/10/2015ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ በከተማ ደረጃ የተዘጋጀው የሁለተኛው ሴሚስተር የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የቀንና የማታ ተማሪዎች የሞዴል ፈተና በመሰጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን በወረዳችን የሚገኘው ቀበና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በከተማው ትምህርት ቢሮ እንደ ናሙና ከተመረጡ ትምህርት ቤቶች አንዱ በመሆኑ ፈተናው በከተማ ደረጃ ተወስዶ እርማት የሚደረግበት ይሆናል።

Repost from Yeka Education
የካ ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት በሳይንስና ፈጠራና ወድድር በከተማ ደረጃ የዋንጫ ጎርፍ አግኝቷል💪💪💪💪💪💪💪
+5
የካ ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት በሳይንስና ፈጠራና ወድድር በከተማ ደረጃ የዋንጫ ጎርፍ አግኝቷል💪💪💪💪💪💪💪

በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ትምህርት ጽ/ቤት በቀን 17/09/2015ዓ.ም የሁለተኛው ሴሚስተር የጥያቄና መልስ ውድድር የተደረገ ሲሆን 1ኛ.ቀበና ኪዳነምህረት ት/ቤት 2ኛ.ቀበና አድቬንቲስት ት/ቤት 3ኛ
+7
በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ትምህርት ጽ/ቤት በቀን 17/09/2015ዓ.ም የሁለተኛው ሴሚስተር የጥያቄና መልስ ውድድር የተደረገ ሲሆን 1ኛ.ቀበና ኪዳነምህረት ት/ቤት 2ኛ.ቀበና አድቬንቲስት ት/ቤት 3ኛ.አዲስ ብርሃን ት/ቤት ደረጃ ይዘው ለተማሪዎችና ለት/ቤቶች እውቅናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE የትምህርት ሚኒስቴር የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቅያ ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን ጊዜ ይፋ አድርጓል። ሚኒስቴሩ ፤ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 30/2
+1
#MoE የትምህርት ሚኒስቴር የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቅያ ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን ጊዜ ይፋ አድርጓል። ሚኒስቴሩ ፤ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም ድረስ #በመንግስት_ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል ብሏል። ዩኒቨርሲቲዎችም ያላቸውን ስራ በማጠናቀቅ ከሐምሌ15/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ሚኒስቴሩ አሳስቧል። @tikvahethiopia

Repost from Yeka Education
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ 6ኛ እና 8 ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ቀናት ይፋ አደረገ። 👉የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ 6ኛ እና 8 ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ቀናት ይፋ አደረገ። 👉የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ የ 8ኛ ክፍል  ፈተና ሰኔ 19 እና 20 እንዲሁም የ 6ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 26 እና 27 እንደሚሰጥ ተናግረዋል:: 👉አያይዘውም ቢሮው ከተማ አቀፍ ፈተናዎቹን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመስጠት ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን የተናገሩ ሲሆን ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቹን የበለጠ ማዘጋጀት እንዲችሉ ከከተማና ክፍለ ከተሞች ጋር በጋራ በመሆን የሞዴል ፈተናዎችን እንዲሰጡ አሳስበዋል :: 👉በ 2015 ዓ. ም 75,100 የ8ኛ እንዲሁም 75,078 የ 6ኛ ክፍል ተማሪዎች ከተማ አቀፍ ፈተናውን እንደሚወስዱ ከስራ ክፍሉ ያገኘነው መረጃ ያሳያል ::

Repost from Yeka Education
👉የ2015 ት/ት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች የፈተና ምዝገባ እስከ ሚያዝያ 20/2015 ዓ/ም ድረስ ብቻ እንደሚካሄድ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። 👉አገልግሎ
👉የ2015 ት/ት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች የፈተና ምዝገባ እስከ ሚያዝያ 20/2015 ዓ/ም ድረስ ብቻ እንደሚካሄድ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። 👉አገልግሎቱ ፥ ማንኛውም የስም፣ የፆታ፣ የተፈጥሮ/የማህበራዊ ዘርፍ እና የፎቶ ማስተካከያ ከፈተና በፊት ስለማይደረግ እያንዳንዱ ተፈታኝና እና መዝጋቢ ትክክለኛነቱን የማጣራትና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት ብሏል። 👉ይህ መሆን ያለበትም ምዝገባው በበየነ መረብ በመሆኑ በትምህርት ቤት ደረጃ የተካሄደው የምዝገባ መረጃ በቀጥታ በማንም ሳይነካ ወደ ተቋሙ የመረጃ ቋት የሚገባ በመሆኑ ነው ሲል አስረድቷል። 👉ከሚያዚያ 20/2015 ዓ/ም በኋላ በግለሰብ ወይም በተቋም በኩል የሚመጡ ተመዝጋቢዎችን አላስተናግድም ሲል በጥብቅ ያሳሰበው አገልግሎቱ ፥ ፈተናው የሚሰጠው በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥና የመፈተኛ ጊዜን ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኋላ እንደሚገለፅ አሳውቋል። 👉የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፥ እስካሁን የመፈተኛ ጊዜ አልተገለጸም ያለ ሲሆን ተፈታኞች ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል።

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን 1444ኛው የኢድ አልፈጥር በአል በሰላም አደረሳችሁ።መልካም በአል እንመኛለን🙏
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን 1444ኛው የኢድ አልፈጥር በአል በሰላም አደረሳችሁ።መልካም በአል እንመኛለን🙏

ማስታወቂያ የተባበሩት ኤምሬትስ የሰጠውን ስኮላርሽፕ እየተጠባበቃችሁ ላላችሁ ተማሪዎች ሁሉ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መንግስት በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ጥሩ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል ለመስጠት በፈቀደው መሰረት ቀደም ሲል በተማሪዎች ቃል የተገባላችሁ ተማሪዎችና በዕድሉ ለመጠቀም ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች Application Form link: http://survey.ethernet.edu.et/index.php/518562?lang=en -- በመግባት ከዛሬ 09/08/15 ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 ቀናት ከላይ በተቀመጠው ሊንክ በመግባት፡- 1. የ12ኛ ክፍል የማትሪክ ውጤት ኮፒ (Grade 12 Result) copy 2. ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ኮፒ (Grade 9-12 transcript) copy 3. CV/ Curriculum Vitae copy 4. የልደት የምስክር ወረቀት ኮፒ (Birth Certificate) copy እና ሌሎች በሊንኩ የተጠቀሱ መረጃዎችን እንድትሞሉ እናሳስባለን ። መረጃዎች ተጣርተው ለፈተና የሚቀረቡ ተማሪዎችን ስም ዝርዝር በቀጣይ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የምናሳውቅ መሆናችንን እንገልጻለን። የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ አበባ

Repost from Yeka Education
+6
👉Addis Ababa Education Bureau 👉Models exam collection 👉Year 2012

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለትንሳኤ በአል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ🙏 የየካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ትምህርት ጽ/ቤት
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለትንሳኤ በአል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ🙏 የየካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ትምህርት ጽ/ቤት

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለስቅለት በአል በሰላም አደረሳችሁ እያልን መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን🙏 የካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ትምህርት ጽ/ቤት
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለስቅለት በአል በሰላም አደረሳችሁ እያልን መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን🙏 የካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ትምህርት ጽ/ቤት