TheDeepThingsOfGod
Открыть в Telegram
1 810
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 день
Архив постов
1 810
የኢየሱስ ክርስቶስ ሞት የእኛ ፋሲካ ነዉ።
“...ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአልና፤”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 5፥7
እስራኤላውያን ከበጎች ወይም ከፍየሎች ነውር የሌለበት የአንድ አመት ተባት አርደው ፋሲካን አደረጉ። በዚህም የማለፍ መስዋዕት ሚስጥር ከባርነት አርነት፣ ከሞት ማለፍ እና የለ እርሾ የመሆንን ሃይል አግኝተዋል።
ልክ እንደዚሁ በአዲስ ኪዳን ፋሲካችን ክርስቶስ በመታረዱ ምክንያት እኛም የምናምን ከዓለም(ከግብጽ) ሃይል፣ ከሞትና ከኃጢአት ሃይል አልፈናል። እዚህ ላይ ማስተዋል ያለብን ግብጽ ምድራዊ ቦታ (geographic location) ብቻ ሰይሆን የመንፈሳዊ ባርነት( slavery and bondage) ተምሳሌት መሆኗን ነዉ(ራዕይ 11:8)። ስለዚህ ከዓለም በላይ መሆን ማለት የዚህ ዓለም ገዥ ከሆነው ሰይጣንና ከባርነት በላይ መሆን ማለት ነዉ። በዚህ በክፉ በተያዘ ዓለም ላይ ስንኖር ባሮች አድርጎ ልገዛን ከሚሹ ከመንፈሳዊ ሃይላት ጋር የማይቋረጥ ውጊያ የለን ቢሆንም ነገር ግን በፋሲካ እውነት የምንመላለስ ከሆነ መለኮታዊ ድልና ጥበቃ የተረጋገጠ ነዉ። “ከክፉ እንድትጠብቃቸው እንጂ ከዓለም እንድታወጣቸው አልለምንም።”
— ዮሐንስ 17፥15
ቃሉን የሚሰሙና እግዚአብሔር ያዘጋጀውን የማለፍ መስዋዕት የሚያምን ሁሉ ከሞት ወደ ሕይወት አልፏል።
“እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት #ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።”
— ዮሐንስ 5፥24
ፋሲካችን ክርስቶስ በመታረዱ አሮጌውን እርሾ የማስወገድና አድሱን ሊጥ የመሆንን ሃይል አግኝተናል። ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ በክርስቶስ ኢየሱስ መታረድ ምክንያት ከኃጢአት የመንጻት ሃይል እንዳለን ያስረዳል:-“እንግዲህ ያለ እርሾ እንዳላችሁ አዲሱን ሊጥ ትሆኑ ዘንድ አሮጌውን እርሾ አስወግዱ። ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአልና፤”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 5፥7
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ዮሐንስ 19
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁸ ከዚህ በኋላ ኢየሱስ አሁን ሁሉ እንደተፈጸመ አውቆ የመጽሐፉ ቃል ይፈጸም ዘንድ፦ ተጠማሁ አለ።
²⁹ በዚያም ሆምጣጤ የሞላበት ዕቃ ተቀምጦ ነበር፤ እነርሱም ሆምጣጤውን በሰፍነግ ሞልተው በሁሶፕም አድርገው ወደ አፉ አቀረቡለት።
³⁰ ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ፦ ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።
1 810
“...ቤቶቻችንን ያዳነ የእግዚአብሔር የማለፉ መሥዋዕት ይህች ናት..”
— ዘጸአት 12፥27
የማለፍ መስዋዕት ሚስጥር።
(The mystery of the killing of Passover.)
የፋሲካ እርድ ወይም የማለፍ መስዋዕት በእስራኤላውያን ታሪክ ውስጥ እጅግ በጣም ትልቅ ትርጉም የነበረው ነው። በአድስ ኪዳን ላለን ለእኛ ደግሞ የብሉዩ የማለፍ መስዋዕት እጅግ የሚያስደንቅ ጥላ ነው።
እስራኤላውያን ለአራት ትውልድ በግብፅ ባሮች ሆነው ከቆዩ በኃላ እግዚአብሔር ነቢዩን ሙሴን በመላክ ሕዝቡን ጎበኘው። እግዚአብሔር በሙሴ በኩል ባደረገው ተዓምራት ምልክትና ድንቅ ነገር ሁሉ ሃይሉን ለግብፅ የገለጠ ቢሆንም እስራኤላውያን የማለፍ መስዋዕት እስካደረጉበት ማግስት ድረስ ፈርኦን የእግዚአብሔርን ሕዝብ ለመልቀቅ አልፈቀደም ነበር።
እስራኤላውያን የማለፍ መስዋዕትን(ፋሲካን) ካደረጉ በኋላ እግዚአብሔር በግብጽ ያለን በኩር ከእንስሳ ጀምሮ እስከ ሰው ድረስ፤ በቤተመንግስት ካለው ከንጉሡ በኩር ጀምሮ ወፍጮ ቤት እስካለችው በኩር ድረስ በመግደል በግብጻዊያንና በአማልክቶቻቸው ሁሉ ላይ ፈረደ። ከእስራኤል በኩር ግን አንድም አልወደቀም፤ የፋሲካው ደም በጉበን እና በመቃናቸው ስለነበር እግዚአብሔር ደሙን በየ ጊዜ በበራቸው አለፈ አጥፊውም ለጥፋት ቤታቸው ይገባ ዘንድ አልፈቀደም።
በማለፍ መስዋዕት እስራኤላውያን በዋናነት ሦስት ነገሮች ተደርጎላቸዋል።
1-በማለፍ መስዋዕት ሚስጥር አራት መቶ አመት በሮች ሆነው ከተጋዙበት ግብፅ መውጣትና ወደ ተስፋይቱ ምድር ጉዞ መጀመር። (ነጻነት) /Deliverance from Egypt/
#ዘጸአት11:1-10
2-በማለፍ መስዋዕት ሚስጥር በኩሮቻቸው ከሞት አልፈዋል። / Passover from Death./
#ዘጸአት 12:12-13
3-በማለፍ መስዋዕት ሚስጥር የለ እርሾ የመሆንን ሃይል አግኝተዋል። /Power to purge out the old leaven./
#ዘጸአት 13:6-7
...ይቀጥላል....
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
📖የእግዚአብሔር ቃል📖።
.... ክፍል አንድ....
....የእግዚአብሔር ቃል የሚለው ሃረግ በጥቅሉ ለሁለት ነገር ይውላል። የመጀመሪያው ኢየሱስ ክርስቶስ ነዉ። ሁለተኛው ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ ነዉ። ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር አካላዊ ቃል( personal word) ነዉ። መጽሐፍ ቅዱስ ደግሞ የተጻፈ(written) የእግዚአብሔር ቃል ነዉ።
ሁለቱም አካላዊው የእግዚአብሔር ቃል እና የተጻፈ የእግዚአብሔር ቃል ሙሉ በሙሉ የተስማሙ እና የሚደጋጋፉ ናቸዉ። አካላዊው ቃል የተጻፈውን ቃል ፈጽሞታል። ስለዚህ ከአካላዊው የእግዚአብሔር ቃል ጋር በትክክል ለመግባባት ከተጻፈው የእግዚአብሔር ቃል ጋር በትክክል መግባባት ያስፈልጋል። የተጻፈውን ቃል ከምንወደው በላይም አካላዊውን ቃል ልንወድ አንችልም: ኢየሱስን እወደዋለሁ ግን መጽሐፍ ቅዱስን አልወድም ከልን ኢየሱስንም አንወደውም ማለት ነዉ። ለኢየሱስ ክርስቶስ ጊዜ አለኝ የምንል ከሆነ እና ለመጽሐፍ ቅዱስ ጊዜ ከሌላን ለኢየሱስም ጊዜ የለንም ማለት ነዉ። ምክንያቱም ኢየሱስ ክርስቶስ እራሱ እንደዚህ በማለት ተናግሯል: “ኢየሱስም መለሰ አለውም፦ የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤...”
— ዮሐንስ 14፥23
ስለዚህ በግልጽ እንደምናየው ኢየሱስን የምንወደው ከሆነ ቃሉን እንጠብቃለን። ቃሉን ከምንወደው በላይ ኢየሱስን ልንወደው አንችልም። ቃሉን በወደድን ቁጥር ለኢየሱስ ያለን ፍቅር ይጨምራል።
ለኢየሱስ ያላችሁ ፍቅር እንዲጨምር ትፈልጋላችሁ? ቃሉን ጠብቁ! ቃሉን የበለጠ ውደዱ😍😍😍።
ጉርሻ😁 👉“አቤቱ፥ ሕግህን እንደ ምን እጅግ ወደድሁ! ቀኑን ሁሉ እርሱ ትዝታዬ ነው።”
— መዝሙር 119፥97
“በትእዛዝህ ደስ ይለኛል፤ ቃልህንም አልረሳም።”
— መዝሙር 119፥16
❤️❤❤ ቃሉን ከምንወደው በላይ ኢየሱስን ልንወደው አንችልም❤❤❤
👇👇👇Join the chariot👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
📖የእግዚአብሔር ቃል📖
... ክፍል አራት...
ከመጋቢዎቻችን፤ ከነቢያቶቻችን ወይም ከአስተማሪዎቻችን በላይ የምንመለከተው እና የምንከተለው የሐይማኖታችን ሐዋሪያ እና ሊቀ-ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ በመሆኑ: በዛሬው ጽሑፌ እርሱ ቅዱሳት መጽሐፍትን እንዴት እንደሚመለከት እናያለን። እኛም ልክ እንደ እርሱ ልንመለከታቸው ይገባናል...
ጌታችን ኢየሱስ የቅዱሳት መጽሐፍትን ስልጣን እና ሃይል የገለጸበትን ሁለት የንባብ ክፍል እንመለከታለን: የመጀመሪያው :- “መጽሐፉ ሊሻር አይቻልምና እነዚያን የእግዚአብሔር ቃል የመጣላቸውን አማልክት ካላቸው፥”
— ዮሐንስ 10፥35
ከላይ የምናነበው የጌታችንን ንግግር ነዉ: አይሁድ ለጠየቁት ጥያቄ መልስ ስሰጣቸው "መጽሐፍ ሊሻር አይችልም" /the scriptures can't be broken/ በማለት ስለ ቅዱሳት መጽሐፍት ስልጣን ገልጧል። ከላይ ባለው የጌታ ቃል ውስጥ "መጽሐፍ" ተብሎ በአማርኛው ቅጅ የተተረጎመው ቃል በግሪክ γραφή ---("graphe") የሚል ድምጽ ያለው ቃል ነዉ: ይህም የተጻፈውን የእግዚአብሔር ቃል ለመግለጽ ጥቅም ላይ የዋለ ነዉ።
ሁለተኛው የንባብ ክፍል ---“እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይና ምድር እስኪያልፍ ድረስ፥ ከሕግ አንዲት የውጣ ወይም አንዲት ነጥብ ከቶ አታልፍም፥ ሁሉ እስኪፈጸም ድረስ።”
— ማቴዎስ 5፥18
ከላይ ያነበብነው ቃል ሌላው ኢየሱስ የቅዱሳትን መጽሐፍት ስልጣን የገለጸበት ነዉ። በዚህ ንባብ ውስጥ ሁለት ነገሮች ተጠቅሰዋል: የውጣ እና ነጥብ። በግሪኩ ጽሑፍ የውጣ "iota" ፤ ነጥብ ደግሞ "keraia" ናቸው። የመጀመሪያው ቃል "የውጣ" በዕብራይስጥ ፊደላት ውስጥ የትንሿ ፊደል ስም ነዉ፤ ሁለተኛው ቃል "ነጥብ" የተባለው ደግሞ በዕብራይስጥ ጽሑፎች ውስጥ በፊደል ራስ ላይ የሚደረግ ትንሽ ቀንድ የሚመስል ነጥብ ነዉ።
አስተውሉ እነዚህ ሁለቱ በቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ በጣም ትንንሾቹ ነገሮች ናቸው። ጌታ ግን ከእነዚህ ከትንንሾቹ አንድቱ እንኳ እንደማትሻር በመናገር የቅዱሳት መጽሐፍትን ስልጣን ገልጧል።
(.........መጽሐፍ ሊሻር አይችልምና......)
-victor
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
📖📖የእግዚአብሔር ቃል📖📖
... ክፍል አምስት...
ኢየሱስ ቃሉን አድራጊ ነበር።
(Jesus was a doer of the word.)
ቅዱሳት መጽሐፍትን መጥቀስ ሁሉም የሚችለው ተግባር ነዉ: አማኙም የማያምነውም ከቅዱሳት መጽሐፍት ጠቅሶ ንግግሩን ወይም ድርጊቱን ትክክለኛ (Justify) የማድረግ ዝንባሌ ሁላችንም የምናስተውለው ነዉ። ነገር ግን ስንት ሰው ነዉ የቃሉ አድራጊ የሆነው? ኢየሱስ ጥቅስ የሚጠቅስ ሰው ብቻ አልነበረም: የእግዚአብሔር ቃል አድራጊ ለመሆን በሕይወቱ ሁሉ ፍጹም ትጋት ነበረው ደግሞ ያለነቀፋ ቃሉን ፈጽሞታል:...“እኔ ሕግንና ነቢያትን ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ #ልፈጽም_እንጂ_ለመሻር_አልመጣሁም።”
— ማቴዎስ 5፥17
ጌታችን ኢየሱስ የእግዚአብሔርን ፈቃድ በማድረግ ስራውንም በመፈጸም ይጠግብ ነበር።
“ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ የእኔስ መብል የላከኝን ፈቃድ አደርግ ዘንድ ሥራውንም እፈጽም ዘንድ ነው።”
— ዮሐንስ 4፥34
ይህንንም በመጨረሻ እንደዚህ በማለት መፈጸሙን ተናግሯል: “እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤”
— ዮሐንስ 17፥4
(...በመጨረሻ እኛም ይህንን ማለት እንድንችል ፀጋው ይረዳናል! ብቻ በፀጋው እንትጋ......አሜን!-
ኢየሱስ የቃሉ አድራጊ ነበር። እኛም ልክ እንደ እርሱ የቃሉ አድራጊዎች እንድንሆን መንፈስ ቅዱስ ተናግሮናል....“ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ።”
— ያዕቆብ 1፥22
........የቃሉ አድራጊዎች መሆን ይጠበቅብናል......
👇👇👇👇JOIN👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ይህንን አንብቡና በድጋሚ #ጸልዩ! February 14 የለጠፍኩት ነዉ።
እያንዳንዱን ነጥብ በጥንቃቄ ለተመለከተው ግልጽ ነዉ።
1 810
May God revel himself to you!
Have you ever wondered that God is everywhere(Omnipresent), but many are neither seeing him nor feeling him. Why? The answer is simple yet profound, God is mysterious. He is a mystery beyond human reasoning, you can only know him when He reveals himself to you by his sovereign act.
I PRAY FOR YOU IN THE NAME OF JESUS CHRIST, MAY GOD REVEAL HIMSELF TO YOU.
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
📖የእግዚአብሔር ቃል📖
... ክፍል ስድስት...
❤የእግዚአብሔር ቃል ውጤቶች❤
1-የእግዚአብሔር ቃል የእምነት ምንጭ ነዉ።
“እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።”
— ሮሜ 10፥17
እምነታችሁ ከፍ እንድል ትፈልጋላችሁ? ወደ እግዚአብሔርን ቃል ሂዱ: አንብቡት አሰላስሉት እመኑ ለራሳችሁ ተናገሩት።
2-የእግዚአብሔር ቃል አድስ ልደት ያስገኛል።
“ለፍጥረቱ የበኵራት ዓይነት እንድንሆን በእውነት ቃል አስቦ ወለደን።”
— ያዕቆብ 1፥18
አንድ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል ስያገኘው አድስ ሕይወት ይጀምራል።
3-መንፈሳዊ መብል ነዉ።
“ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥2-3
“ጠንካራ ምግብ ግን መልካሙንና ክፉውን ለመለየት በስራቸው የለመደ ልቡና ላላቸው ለፍጹማን ሰዎች ነው።”
— ዕብራውያን 5፥14
(....በመንፈሳዊ ህይወት ማደግ የሚፈልግ ሰው ምን ማድረግ አለበት? ከቃሉ ጋር መቆየት። የእግዚአብሔር በተለያየ የብስለት ደረጃ ላይ ላሉ ሁሉ ተስማሚ የሆነ አቅርቦት አለው: ከወተት እስከ ጠንካራ ምግብ።)
4-በኃጢአት ላይ ድል ያስገኛል።
መዝሙር 119
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁹ ጕልማሳ መንገዱን በምን ያነጻል? ቃልህን በመጠበቅ ነው።
¹¹ አንተን እንዳልበድል፥ ቃልህን በልቤ ሰወርሁ።
የእግዚአብሔርን ቃል ጠብቆ በልቡ የሚይዝ ጎልማሳ እግዚአብሔርን አይበድልም መንገድም ንጹሕ ይሆናል።
5-የእግዚአብሔር ቃል የማንጻት ውጤት አለው።
ኤፌሶን 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁵-²⁶... በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤
²⁷ እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።
(የእግዚአብሔር ቃል በውሃ ተመስሏል ይህም የማንጻት ሃይል እንዳለው የሚያሳይ ነዉ።)
6-መንፈሳዊ መስታወት ነዉ።
ያዕቆብ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²³ ቃሉን የሚሰማ የማያደርገውም ቢኖር የተፈጥሮ ፊቱን በመስተዋት የሚያይን ሰው ይመስላል፤
²⁴ ራሱን አይቶ ይሄዳልና፥ ወዲያውም እንደ ምን እንደ ሆነ ይረሳል።
(...ውጫዊውን ፊታችንን ለመመልከት ሁላችንም መስታወት እንጠቀማለን: የእግዚአብሔር ቃል ግን የልብን ሰው የሚያሳይ መስታወት ነዉ: ምን እንደምትመስሉ ማወቅ ከፈለጋችሁ ወደ እግዚአብሔር ቃል ጠጋ ማለት ነዉ...)
#የእግዚአብሔርን ቃል አንድ ኃጢአተኛ ስመለከተው የመጀመሪያ የወደቀ እና መነሳት፤ መንጻት፤ መዳንና ሕይወት መግኘት የሚያስፈልገው ኃጢአተኛ እንደሆነ በግልጽ ያሳየዋል በመቀጠልም እግዚአብሔር ያቀረበውን መድኃኒት ያሳየዋል: በዚህ ጊዜ ኃጢአተኛው እግዚአብሔር ያቀረበውን የመፍትሔ መንገድ በእምነት ከተቀበለ ወድያው በክርስቶስ ያገኘውን አድሱን ማንነቱን ያሳየዋል! ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን።)
7-የእግዚአብሔር ቃል አእምሮን ያበራል።
“የቃልህ ፍቺ ያበራል፥ ሕፃናትንም አስተዋዮች ያደርጋል።”
— መዝሙር 119፥130
አስተዋይ መሆን የሚወድ ቃሉን ይስማ!
8-ሕይወት እና አካላዊ ፈውስ ያስገኛል።
“ቃሉን ላከ ፈወሳቸውም፥ ከጥፋታቸውም አዳናቸው።”
— መዝሙር 107፥20
“ለሚያገኙአት ሕይወት፥ ለሥጋቸውም ሁሉ ፈውስ ነውና።”
— ምሳሌ 4፥22
አካላዊ ፈውስ የሚፈልግ የትኛውም ሰው በዚህ ረገድ የእግዚአብሔርን ቃል ማግኘት ከዛም አምኖ መቀበል ነዉ: በፍጹም ጤንነት መመላለስ ይችላል።አሜን።
...የእግዚአብሔር ቃል ይሰራል...
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ያለምንም ነገር መኖር እችላለሁ ደግሞም አይገርመኝም ኖሬ አይቼዋለሁ ግን የለአንተ መንፈስ ቅዱስ እንዴት እኖራለሁ!?
#TakeNotYourHolySpiritFromMe.
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ከክርስቶስ ጋር ያላችሁን አንድነት ወደላቀ የክብር ደረጃ የሚያሸጋግር የመንፈስ ቅዱስ ጉብኝት ዛሬ ምሽት ይሁንላችሁ።
በጌታ ኢየሱስ ስም የሚባክን ዘመን የላችሁም! አሜን።
“ግን እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል።”
— ዮሐንስ 16፥13
1 810
ተመልከቱ በክርስቶስ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ላይ ሰይጣን የከፈተውን ጦርነት! የ YouTube ድርጅት ነቢይ TB Joshua ተመሳሳይ ጾታዊ ግኑኙነት ያላቸውን ሰዎች ከአጋንንት እስራት በጌታ ሃይል ነጻ የወጣባቸው የተለያዩ ቀረጻዎችን ከተመለከተ በኃላ ከ 1.6 ሚልዮን በላይ ተከታይ የነበረውን Emmanuel Tv የ YouTube ቻናል ዘግቷል! ሌላው ደግሞ Facebook ነቢዩ የግብረሰዶም መንፈስ ካለባት ሴት አጋንንት ስያስወጣ የሚያሳይ ምስልን አጥፍቷል።
ይህ ሰይጣንና ዓለም በቤተክርስቲያን ላይ የከፈቱት ጦርነት በዚህ ብቻ የሚያበቃ አይደለም! እቅዳቸው ከጥቂት አመታት በኃላ ሰይጣንን የሚያንቋሽሽ ነዉ ብለው የሚያስቡትን ንግግርና ስብከት ሁሉ ከ Social media ያጠፋሉ! ስለ ሰይጣን ስለ ዓለም እውነትን የሚናገሩ ሰዎች social media ላይ ከ ተወሰኑ ሰዎች በላይ መድረስ እንዳይችሉ ገደቦች (restrictions) ይደረግባቸዋል። በተለይ ሰይጣንን የእግዚአብሔርና የእግዚአብሔር ሕዝብ ጠላት እንደሆነ የሚናገር የትኛውም አይነት ጽሑፍ፤ ምስል ወይም ቪድዮ ይታገዳል። ግብረሰዶማዊነትና ሌሎች መሰል ልምምዶች ኃጢአት እንደሆነ መናገር ከ የትኛው አይነት የማህበራዊ ድረገጽ የሚያሳግድ ከዛም ከፍ ስል በሕግ የሚያስቀጣ ወንጀል ይሆናል።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ሪቫይቫል ያስፈልገናል! ሌላ አማራጭ የለንም።
ሪቫይቫል(Revival) የሚለውን ቃል መስማት አሁን የተለመደ ነዉ። አብዛኛውን ጊዜ ደግሞ ትክክለኛ ትርጉሙን ባልጠበቀ መልኩ መነገሩ ቃሉን አሰልቺ ያደረገው ይመስላል! ከዛም በላይ አልፎ አልፎ ቤተክርስቲያን ውስጥ የሪቫይቫል ቁራጭ የሆኑ ነገሮችን "ይሄ ነው ሪቫይቫል! " የሚል የግል አመለካከት በመስጠት የእውነተኛ ሪቫይቫልን ዋጋ ያሳጠነውም መሆኑ ግልጽ ነዉ። ቢሆንም በዚህ ወቅት ከየትኛውም ጊዜ በላይ እውነተኛ ሪቫይቫል ያስፈልገናል! ሌላ አማራጭ የለንም።
ሪቫይቫል ምንድነው?
ከታሪክ ሁለት የእውነተኛ ሪቫይቫል ምሳሌዎች በአጭሩ እንመልከት።
በ1904 ዌልስ በምትባል አገር የሪቫይቫል ተምሳሌት መሆን የሚችል እውነተኛ ሪቫይቫል ነበር። ይህ ሪቫይቫል ሃገሩን ሙሉ በሙሉ ነበር የደረሰው፤ ሁሉንም ሰው በሁሉም ቦታም መንካት የቻለ ነበር። በጊዜው ዌልስ የድንጋይ ከሰል የሚወጣባት ሃገር ነበረች: አብዛኞቹ ሰዎችም በዚህ የድንጋይ ከሰል የማውጣት ስራ ላይ የተሰማሩ ነበሩ እናም እጅግ በጣም ተሳዳቢ አንደበት ያላቸው ኃጢአተኞች ሰዎች ነበሩ። ነገር ግን የሪቫይቫሉ ንፋስ ምድርቱና ሰራተኞቹን ከመታቸው በኃላ የከሰል አውጪዎቹ ስራ ሙሉ በሙሉ ተመሰቃቀለ! ምክንያቱም የሚያወጡትን ከሰል ከቦታ ቦታ ለማንቀሳቀስ ይጠቀሙ የነበረው አህዮችን ነበር: አህዮቹ ደግሞ ቀድሞ መንቀሳቀስ የለመዱት በስድብ ነበር: እና ከሰል አውጪዎቹ ከሪቫይቫሉ የተነሳ መሰዳብ አቁመው ስለነበር አህዮቹ መታዘዝ አቆሙ😂። ይህ የዌልስ ሪቫይቫል በጥቂቱ ሪቫይቫል በሃገር ላይ ምን የህል መንፈሳዊ ተጽዕኖ ልኖረው እንደምችል የሚያሳይ ነዉ-እውነተኛ ሪቫይቫል። በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ በዌልስ የሚኖሩ ሰዎች ሙሉ በሙሉ በመንፈስ ቅዱስ ተጽዕኖ ውስጥ ወድቀው እንደነበር ይታወቃል።
ሌላው በምድር አሜሪካ በአንዳንድ ከተማዎች ቻርልስ ፊኒ የሪቫይቫል ኮንፍራንሶች በሚያዘጋጅበት ወቅት ይሆን የነበረው ነገር ድንቅ ምሳሌ ነዉ።
ፊኒ ኮንፍራንሶች በሚያዘጋጅበት ወቅት የእግዚአብሔር ሃይል በከተማው ውስጥ ከሰው የማቆጣጠር ችሎታ በላይ ይሆን ስለነበር የፊኒ ኮንፍራንስ ከተማው ውስጥ መኖሩን እንኳን የማያውቁ ከሌሎች ከተሞች የመጡ እንግዳ ሰዎች በሃይል መንገዶች ላይ እየወደቁ ራዕይ ይመለከቱና በጉልበታቸው በየመንገዱ ጥግ እየተንበረከኩ በለቅሶ ከእግዚአብሔር ምህረትን ይጠይቁ ነበር። ይህ ነዉ ሪቫይቫል። የተወሰኑ ሰዎችን ብቻ አይደለም የሚድኑት! እግዚአብሔር የጠራቸው ሁሉ በሪቫይቫል ወቅት በየትኛውም ቦታና ጊዜ በሪቫይቫል ተጽእኖ ስር ይወድቃሉ።
እናም በዚህም ወቅት እንደዚህ አይነት የእግዚአብሔር እንቅስቃሴ ያስፈልገናል!
በእውነተኛ ንስሐ ወደ እግዚአብሔር ሕይወት እንመለስ!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ሰይጣንና ዓለም የክርስቶስን ቤተክርስቲያን ለማጥፋት የሚያዘጋጁትን ውጥን ሳስብ ሁልጊዜ ይሄ ቃል ትዝ ይለኛል!
“በአንቺ ላይ የተሠራ መሣሪያ ሁሉ አይከናወንም፤ በፍርድም በሚነሣብሽ ምላስ ሁሉ ትፈርጂበታለሽ። የእግዚአብሔር ባሪያዎች ርስት ይህ ነው፥ ጽድቃቸውም ከእኔ ዘንድ ነው፥ ይላል እግዚአብሔር።”
— ኢሳይያስ 54፥17
እንዴት ያለ መልካም ዜና ነዉ! ጠላት በብዙ ተጠቦ ከሚያዘጋጃቸው መሳሪያዎች የእግዚአብሔር ባሮች ላይ የሚሰራ አንድም መሳሪያ የለም! ስለዚህ በአንዳች አትጨነቁ። ጠላት መሳሪያዎቹን መጠቀሙን አያቆምም ቢሆንም አለመሳካቱም ይቀጥላል።
ሌላው ማስተዋል ያለበን ነገር "እግዚአብሔር በፍርድ በሚነሣብሽ ምላስ ላይ ይፈርዳል" አይደለም የሚለው። ነገር ግን "በፍርድ በሚነሣብሽ ምላስ ሁሉ ትፈርጂበታለሽ" ነው የሚለው። የእግዚአብሔር ባሮች ከወደድን በፍርድ በሚነሣብን ምላስ ሁሉ ላይ መፍረድ መብታችን ነዉ።
በእኛ ላይ የተናገሩት ንግርት እራሳቸው ላይ ይጠበቅባቸዋል ያጠመዱብን ወጥመድ ዞሮ ይይዛቸዋል! በአንዳች መጨነቅ የማይገባን ስለዚህ ነዉ።
የእግዚአብሔር ባሮች ርስት ይህ ነዉ! ጽድቃቸው ከእግዚአብሔር ዘንድ ነዉ።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
በቤተክርስቲያን(በቅዱሳን) ብልጽግና አምናለሁ!
ቤተክርስቲያን የራሷ ትምህርት ቤቶች ዩንቨርስቲዎች ከተማዎች የአውሮፕላን ማረፍያዎች ሊኖሯት ያስፈልጋል ብዬ አስባለሁ!.....
ቤተክርስቲያን እራሷን የቻለች ብሔር(Nation) ናት!
1 810
በአዉሮፓ ህጻናት ትምህርት ቤት ከመጀመራቸው በፊት የግዴታ መከተብ አለባቸው የተባለውን የክትባት ፕሮግራም የአውሮፓ የሰብዓዊ መብቶች ፍርድ ቤት ደግፎታል። ይህ ማለት የትኛውም ህጻን ይህንን ክትባት ሰይቀበል በትምህርት ቤቶች መሳተፍ አይችልም ማለት ነዉ። ይህ በአውሮፓ የጀመረው እዛ የሚያበቃ አይደለም! እንደዚህ አይነት አሰራሮች በዓለም ሁሉ በአጭር ጊዜ መተግበራቸው እሙን ነዉ።
what's the significance of this?
የዚህ አሰራር ትርጉም ምንድነው ወዴትስ እያመራ ነዉ?
ክትባት መከተብ #ምርጫ ሰይሆን #ግዴታ መሆኑ ነዉ። የክፉው መሳሪያዎች የሆኑ የዓለም መሪዎች የትኛውንም አይነት ክትባት ወይም ሌላም ነገር በፈለጉ ጊዜ ለማህበራዊ ጤንነት፤ ለጋራ ደህንነት ወዘተ እያሉ ወደ ሰው ሰውነት ለማስገባት ያስችላቸዋል።
እነዚህን አሰራሮች የማይቀበል ደግሞ ከትምህርት ቤቶች፤ ከመገበባያ ቦታዎች ይታገዳሉ፤ ወደ ሌላ የዓለም ክፍል መጓዝ ቢፈልጉም የመጓጓዣ መንገድ(Access) አያገኙም።
ክትባቶች እንኳ ብቻቸውን ያን ያህል የከፉ አይደሉም ጥቅምም ይኖራቸው ይሆናል: ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ ክትባቶች በ Digital መንገድ የሚመጡ ይሆናል። በ Digital መንገድ ማለት Microchips ማለት ነዉ። ይሄ Conspiracy theory ብቻ ከመሰለን ተሳስተናል!
You believe it or not we are at the end of this age, and we are about to experience the rapture of the Church!
ወዳጆቼ ንቁና ጸልዩ!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
“ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን ዓለምም በሞላው በክፉው እንደ ተያዘ እናውቃለን።”
— 1ኛ ዮሐንስ 5፥19
“We know that we are of God, and the whole world is under the power of the evil one.”
— 1Jn 5፥19 (AMP)
ይህንን ታውቃላችሁ?
1 810
Geert Vanden Bossche, በጣም የታወቀ የ ክትባት ስፔሻሊስት ነዉ። ባለፈው ሳምንት አንድ ቃለምልልስ ላይ በ COVID 19 ክትባት ምክንያት ምን አልባት አለምአቀፋዊ የሆነ Immunity catastrophe ልንፈጥር እንችላለን በማለት ስጋቱን ተናግሯል።
ክትባቶች ሁሉ አደገኛ ላይሆኑ ይችላሉ ነገር ግን ክትባቶች ጥቅማቸውንም ጉዳታቸውንም ለማወቅ የዓመታት ጊዜ ይጠይቃል።
1 810
This is the plan ~እቅዱ ይሄ ነዉ።
ይሄንን እቅዳቸውን እንዴት የሚያሳኩት ይመስላችኋል? pandemic(virus) and vaccination!
Africa Africa...
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
