TheDeepThingsOfGod
Открыть в Telegram
1 810
Подписчики
Нет данных24 часа
Нет данных7 дней
Нет данных30 день
Архив постов
1 810
“ከጌታ፤ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብፅዕት ናት።”
— ሉቃስ 1፥45
“And blessed is she that believed: for there shall be a performance of those things which were told her from the Lord.”
— Luke 1፥45 (KJV)
እመን/ኝ እግዚአብሔር የተናገረህ/ሽ አንዲት ነጥብ ሳትቀር ትፈጽማለች!
1 810
~Hear this friends and pray with me!
~ስሙ በእምነት አብራችሁኝ ጸልዩ የእግዚአብሔር ሕይወት.... I can't stop praising God!!!
#You_have_ETERNAL_LIFE_now!
This is deep, it calls the deep only!
ጥልቅ ነዉ የሚጠራው ጥልቅን ብቻ ነዉ።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
“...ዓይን ከማየት አይጠግብም፥ ጆሮም ከመስማት አይሞላም።”
— መክብብ 1፥8
ተወዳጆች ከላይ በለው ቃል ውስጥ የሚያስደንቅ እና ዘመናችንን ከብክነት የሚታደግ እውነት ተቀምጧል። ያለንበት ዓለም እጅግ በጣም ብዙ የሚታዩና የሚሰሙ ነገሮች ያሉት ዓለም ነዉ። በ 2019 ብቻ Box office 42.2 ቢልዮን ዶላር home/mobile entertainment 58.8 ቢልዮን ዶላር በድምሩ የፊልም እንዱስትሪ ከ 100 ቢልዮን ዶላር በላይ ትርፍ ማግኘት ችለዋል! ይሄ በጣም ትልቅ ገንዘብ ነዉ። በ2019 79% የአሜሪካና የካናዳ ሕዝብ በአመት ቢያንስ አንድ ጊዜ ወደ ሲኒማ ቤት ሄደዋል። የሙዚቃው እንዱስትሪም እንደዚሁ ከ 1999-2019 21.5 ቢልዮን ዶላር መስራት ችሏል። እነዚህ እንዱስትሪዎች ብቻ አይደሉም፤ የሰው ዓይን ከማየት የማይጠግብ ከመስማት የማይሞላ መሆኑን የተረዱ የተለየ ግለሰቦች ከዚህ ገንዘብ ለመስራት የማያደርጉት የለም የዜና ሚድያዎች እና የማህበራዊ ሚድያዎች የሰሩት ገንዘብ ቀላል የማይባል ነዉ። ተመልካች ግን ገንዘብ እየተሰራበት እንደሆነ ሳያውቅ 1 ሳንቲም ሳያተርፍ የማይጠግብ አይኑ የሚጠግብ እየመሰለው የማይሞላ ጆሮው የሚሞላ እየመሰለው ፊልም ስመለከት ሙዝቃ ስሰማ ቀኑ መሽቶ ይነጋል። በተለይ የእኛ ዘመን ወጣት ደግሞ የማንነት ቀውስ (Identity crisis) ያለበት በመሆኑ በውስጣዊ እና በውጫዊ ተጽእኖዎች የሚንገላታ ነዉ።ታዲያ ፊልም ሲያይ ሙዚቃ ስሰማ ነግቶ ቢመሽ አይገርምም።
የተወደዳችሁ ክርስቲያን ወንድሞቼና እህቶቼ የማይጠግብ አይናችሁን የማይሞላ ጆሮአችሁን በዓለም ያሉትን በማየትና በመስማት ለማጥገብና ለማርካት አትሞክሩ! ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ፤ ቃሉ ላይ፤ መንፈሱ ላይ ትኩረት አድርጉ! አይናችሁ የሚመኘው ኢየሱስን ጆሮአችሁ የሚናፍቀው ድምጹን ይሁን። ጌታችን የምታዩትን እና የምትሰሙትን በጥንቃቄ ምረጡ እንዳለን አትርሱ።
አይናችሁ የሚጠግበው ኢየሱስን ሲያይ ጆሮአችሁ የሚሞላው ድምጹን ስሰማ ነዉ።
“ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል።”
— 1ኛ ዮሐንስ 2፥17
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
#casting_out_physical_demons!
Immediately ouuutttt🔥🔥😂😂💪💪🔥🔥
pastor I salute you! 😎this is authority💪
1 810
አካላዊ አጋንንቶችን ከቤተክርስቲያን እንዴት ማስወጣት ይቻላል??🤣😂
በምድረ አሜሪካ የጌታችንን ትንሳኤ በማስመልከት በተዘጋጀ የጸሎት ፕሮገራም ላይ ተገኝተው በስመ ኮቪድ ፕሮግራሙን ለማስቆም የሞከሩ ፖሊሶችን መጋቢው እንደዚህ አስወጥቷቸዋል!
ሰው የሚበዛባቸው የገበያ ቦታዎች ሰይዘጉ፤ ትልልቅ የማምረቻ ድርጅቶች ሰይዘጉ፤ ቤተክርስቲያንን ከመሰብሰብ ለመከልከል የሚያደርጉት ሙከራ ምን ማለት እንደሆነ አይናችሁን ከፍታችሁ ተመልከቱ! ይሄ በቤተክርስቲያን ላይ የሚደረገው ጦርነት መጀመሪያ ነዉ!
የክርስቶስን ቤተክርስቲያን ግን ማስቆም አይቻልም! ወደኋላ ታሪክን መመልከት ብቻ በቂ ነዉ! ከተራ የክርስቶስ ተቃዋሚ ቀበሮዎች እስከ ትልልቅ ሃገራትና መንግስታት ድረስ ቤተክርስቲያንን ለመግደል ያላደረጉት የለም: ሁልጊዜም የክርስቶስ ቤተክርስቲያን አሸንፋቸዋለች! ጸንታም ቆማለች! ቀበሮዎቹ ግን የሉም።
ወንድሞቼና እህቶቼ አይኖቻችንን ከፍተን እንመልከት እንጸልይ።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
በሁሉም በኩል ፍጹም በሆነ መንገድ ፍጹም የሆነውን የቀራንዮ ስራ ተመልከቱ! አስቡ።
Consider the work of Calvary perfect in every aspect, perfect in every respect!
በበደለኝነት ስሜት እየተኮነንክ/ሽ ነዉ?
ሰይጣን በሞት ፍርሃት እየገዛህ/ሽ ነዉ?
በበሽታ እየተሰቃየህ/ሽ ነዉ?
ጠፊው ዓለም በውሸቱ እያታለለህ/ሽ ነዉ?
በድህነት እየተጨነክ/ቅሽ ነዉ?
በምንም አይነት መልኩ ክፉ በሕይወትህ/ሽ አለ?
ለዚህ ሁሉ ጨለማ እግዚአብሔር መልስ ከሰጠ 2000 ዓመት አለፈ!
ታስታውሳላችሁ: የእስራኤል ልጆች በሖርም ተራራ በእግዚአብሔርና በሙሴ ላይ ባመጹ ጊዜ ከእግዚአብሔር በተላኩ እባቦች ተነደፉ! እናም ብዙዎች ሞቱ: የምህረት አምላክ እግዚአብሔር ግን የሚድኑበትን መንገድ አዘጋጀ።
ሙሴን ከናስ እባብ ሰርቶ በዓላማ ላይ እንድሰቅል ተናገረው። የናሱንም እባቡ የተመለከቱ ሁሉ በበደላቸው ምክንያት እግዚአብሔር ከሰደደባቸው ጥፋት ዳኑ!
ልክ እንደዚሁ ነዉ! የተሰቀለውን ኢየሱስ ክርስቶስን የሚያይ ሁሉ ይድናል። መስቀል ላይ ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለሙን ኃጢአት እና የኃጢአትንም ውጤት ሁሉ ተሸክሟል! በሉዑል እግዚአብሔር ጥንተ ውሳኔና ምክር መሰረት በሆነ ልውውጥ ኃጢአትና የኃጢአት ውጤት ሁሉ መስቀል ላይ በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ሆነ: ይህም የሆነው: ጽድቅና የጽድቅ ውጤት ሁሉ የተሰቀለውን በሚመለከቱ ሁሉ ላይ እንድሆን ነው።
የተሰቀለውን ስትመለከቱ ኃጢአትና የኃጢአት ውጤት ሁሉ በእናንተ ሕይወት ስፍራ አይኖራቸውም! ነገር ግን ጽድቅና የጽድቅ ውጤት ሁሉ የተሰቀለውን ኢየሱስ ክርስቶስን ለሚመለከቱ በፀጋ ተሰጥቷቸዋል! ሃሌሉያ ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን!
ምስጋናና አዋጅ= የዘላለም አምላክ ሆይ ኢየሱስ ክርስቶስ በእኔ ምትክ ስለሰራው ስራ ሁሉ አመሰግናለሁ! ቅዱስ አባት ሆይ መስቀል ላይ ኃጢአቴና የኃጢአቴ ውጤት ሁሉ በኢየሱስ ከእኔ ላይ ተወስዷል! በኢየሱስ ላይ ሆኗል! በእርሱም ፍጹም መታዘዝ ጽድቅና የጽድቅ ውጤት ሁሉ ለእኔ ሆኗል! ኃጢአት በጽድቅ፤ ጭንቀት በሰላም፤ ሀዘን በሐሴት፤ በሽታ በጤንነት፤ ባዶነት በመትረፍረፍ፤ ሞት በአምላክ ሕይወት ተተክቶልኛል! ሃሌሉያ!
👇👇👇👇👇Join 👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
እየሆነ ያለውን ተመልከቱ! በቻይና ላሉ ክርስቲያኖች ጸልዩ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ እምነታቸውን እንድክዱ እየተገደዱ እና ትልቅ ስደት እየደረሰባቸው ነዉ። አሁን ግን ስደቱ አሰቃቂ እየሆነ ነዉ።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
እንደገና ምራኝ! እንደገና!
እንደገና ያዘኝ! እንደገና!
እንደገና አግዘኝ! እንደገና!
እንደገና አቁመኝ! እንደገና!
የለእረኝነት ያለአንተ መሪነት
አልችልም እኔ!
በዚህች ከፉ ዓለም
መውጣትና መግባት አረ ለብቻዬ!
እፈልግሃለሁ በሁሉም ነገሬ
አንተ ነህ ዋናዬ!
ሰላም ይሰማኛል ድምጽህን ስሰማው
መንፈስ ቅዱስ እኔ!
አንተ ካለህ ይበቃኛል!
ሙሉ ሰላም ይሰማኛል!
መገኘትህ ያረካኛል!
ሕልውናህ ያቆመኛል!
መንፈስ ቅዱስ😭
1 810
....
“ልጆች ሆይ፥ መጨረሻው ሰዓት ነው፥ የክርስቶስም ተቃዋሚ ይመጣ ዘንድ እንደ ሰማችሁ አሁን እንኳ ብዙዎች የክርስቶስ ተቃዋሚዎች ተነሥተዋል፤ ስለዚህም መጨረሻው ሰዓት እንደ ሆነ እናውቃለን።”
— 1ኛ ዮሐንስ 2፥18
በዚህ ክፍል የሐዋሪያው ቅዱስ ዮሐንስ መልእክት የክርስቶስ ተቃዋሚዎች መነሳት በመጨረሻው ሰዓት የመኖራችን ምልክት እንደሆነ በግልጽ የሚያስረዳ ነዉ። ቤተክርስቲያን ገና ከመወለዷ ጀምሮ እኛ እስካለንበት ዘመን ድረስ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች ነበሩ አሁንም አሉ: ነገር ግን አሁን ያለው ሁኔታ ከየትኛውም ዘመን የከፋና ወደ መጨረሻው የተቃረብን መሆኑን የሚያስረዳ ነዉ። ተቃውሞው ከግለሰቦች ያለፈ ሆኗል: ዛሬ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች የሆኑ ግዙፍ ተቋማት እጅግ ብዙ ናቸው ለምሳሌ ዓለም አቀፋዊ ተጽእኖ ያላቸው ሆሊውድ እና የሙዚቃ እንዱስትሪዎች በሚለቋቸው ፊልሞች የተባረከውን የጌታችንን የኢየሱስን ስም በሚያኮስስና በሚያንቋሽሽ መልኩ መጠቀም(Mocking The Name of Our blessed Lord) የተለመደ ሆኗል፤ በጣም የሚደንቀው ነገር ደግሞ እንደዚህ አይነቱ የማንቋሸሽ ተግባር እና የተቃዋሚነት ዘመቻ በክርስቶስ ላይ እና በክርስትና ላይ ብቻ የሚደረግ መሆኑ ነዉ: ከክርስቶስ ውጭ አንድም ኃይማኖት አይነካም: ይሄ ለምን ይመስላችኋል? ግልጽ ነው አይደለም!? ክርስቶስ ብቻ እውነት ስለሆነ ነዉ: ሌሎቹ ከንቱ ስለሆኑ ከግምትም የሚገባ አይደሉም: በፊልሞች ውስጥ ከቀረቡም የሚቀርቡት ተከብረው ነዉ: ምክንያቱም የራሱ የሆነ ላይ ለጥፋት የሚነሳ መንግስት የለም!
በሰይጣናዊ ጥላቻ የተሞሉ እነዚህ ተቀዋሚዎች ኢየሱስ ክርስቶስን መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚተርከው አይነት ሰው እንዳለሆነ አድርገው ፊልሞች በመስራት ለተመልካች ለማቅረብም ሲወተረተሩ መየት የተለመደ ሆኗል። አሁን ደግሞ የሚዲያው እንዱስትሪ ብቻ ሳይሆን አምራች ድርጅቶችም የክርስቶስ ተቃዋሚዎች መሆናቸውን የሚገልጽ ስራዎች ለገበያ በማቅረብ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች መሆናቸውን እያመለከቱ ነዉ።
ይህ የሚደንቅ አይደለም መጽሐፍ ቅዱሱና የክርስቶስ መንፈስ እንደመለከተን እንደዚህ አይነቱን ክህደት በሁሉም በክል የሚመጣ ነዉ። ትምህርት ቤቶቻችን እና የትምህርት ስርዓታቸው በክርስቶስ ተቀዋሚዎች ሰይጣናዊ ትምህርትና አመለካከት እየተመረዘ ነዉ። ቤተክርስቲያን በእግዚአብሔር ሃይልና እውነት በመንፈስ ቅዱስ ታጥቃ የክፉውን ሽንገላ ለመቃወም የማትቆም ከሆነ ከሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት በኃላ በሁሉም ዓለም ልጆችን ወደ ትምህርት ቤት መላክ ዋና የማይችልን ሰው ባሕር ውስጥ የመጣልን ያህል አሰቃቂ እንደሆነ አስባለሁ።
ዋናው የክርስቶስ ተቃዋሚ የሆነው የአመጽ ሰውና የኃጢአት ልጅ በግልጥ ለምድር ሁሉ እንዲታይ: የክርስቶስ ተቃዋሚዎች መንገድ የሚጠርጉለት መሆኑ ግልጽ ነዉ ስለዚህ እንዚህ ቡችሎች በፊልም እንዱስትሪና የሙዚቃ እንዱስትሪ ቢቻ ሰይሆን በፖለቲካው ከዛም አልፈው በየሃይማኖቱም በበግ ለምድ የተሸፈኑ ተኩላዎች ሆነው የምናያቸው ነዉ የሚሆነው። የመጨረሻው ሰዓት እጅግ ፈታኝ ነዉ! ጌታ “...ነገር ግን የሰው ልጅ በመጣ ጊዜ በምድር እምነትን ያገኝ ይሆንን?”— ሉቃስ 18፥8 በማለት የተናገረው ቃል እጅግ ብዙዎች ከእውነትኛ እምነት እንደሚለያዩ የሚያሳይ ነዉ።
መፍተሔው ወደ እግዚአብሔር መንፈስና እውነት መመለስ ነዉ። ወደ ቃሉ መመለስ ነዉ፤ ወደ ሃይሉ መመለስ ነዉ: እናም የተራሮች ጫፍ ላይ መቆም ነው። ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ።
#Victor
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ጽዮን ተራራ ነው።
እግዚአብሔር እያንዳንዱ አማኝ የተራራው ጫፍ ላይ እንዲኖር የፈቀደ ቢሆንም: የጽዮን ነዋሪዎች በልባቸው ፈቃድ በተራራው ላይ የቱ ጋር መኖር እንዳለባቸው ይወስናሉ፤ አንዳንዶች እስከአሁን የተራራው እግር ላይ ናቸው: ሌሎች ደግሞ የተራራው ወገብ አከባቢ እየኖሩ ነዉ: እጅግ ጥቂቶች ግን የተራራው እራስ ላይ ይኖራሉ። እግዚአብሔርን የምናውቅበትም ደረጃ የሚወሰነው በወጣንበት ከፍታ ልክ ነው ሌላው ደግሞ ዓለምን የምናይበት ልክም የሚወሰነው በከፍታችን ነዉ። ይሄንን እውነት መረዳት በጣም አስፈላጊ ነዉ! ጽዮን ተራራ ነዉ! በዚህ ተራራ ላይ የወጣንበት ከፍታ ይለያያል: አስተሳሰባችን ንግግራችን ድርጊታችን ሁሉ በተራራው ላይ በወጣንበት ልክ ነዉ የሚሆነው። ይሄንን ሚስጥር የማያውቁ ሰዎች ይሰናከላሉ: በተራራው የታችኛው ክፍል ያሉ እላይ ያሉት በላቸው አስተሳሰብና የሕይወት ሥርዓት ይሰናከላሉ: ሁላችንም አንድ መድረክ ላይ ነው የቆምነው ብለው ስለሚያስቡ ነዉ። ነገር ግን አንድ መድረክ ላይ አይደለንም! አንዳንዶች እታች ሌሎች ደግሞ እላይ ናቸው። መንፈስ ቅዱስ ይሄንን ሚስጢር ካካፈለኝ በኃላ እኔ የተራራው ራስ ላይ ለመኖር ወስኛለሁ! እግዚአብሔርን ከተራራው ራስ ለማወቅ ወስኛለሁ! ዓለምንም ከተራራው ራስ ላይ ላያት ቆርጫለሁ! ሕይወትን ከተራራው ራስ ላይ ለመኖር ወስኛለሁ! እራስ ላይ መውጣት ተሰጥቶኝ በፍጹም እታች አልኖርም!
እናንተም ወስኑ! ለራሳችሁ ተናገሩ! የተራራው ራስ ላይ እወጣለሁ: እኖራለሁ በሉ። የተራራው ራስ ላይ ለመውጣት የሚጠይቀው: ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ? መገለጥ! Revelation! እያንዳንዱ መገለጥ ወደ ሌላ ከፍታ ይወስዳችኋል!
Revelation brings Elevation!
#Victor
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የተወደዳችሁ መጽሐፍ ቅዱሳችሁን ያነበባችሁት ከስንት ሰዓት በፊት ነበር? ከስንት ቀን በፊት ነበር? ምን አልባትም አንዳንዶች ከሳምንት በፊት ይሆናል። ይህ ለኩነኔ አይደለም! ለማንቃት ነዉ: መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ከሰጣቸው ድንቅና ዋጋ የማይተመንላቸው ስጦታዎች አንዱ እንደሆነ አምናለሁ።
ከመጽሐፍ ቅዱሳችሁ ለአንድ ቀን እንኳ ስትርቁ ሁለት ነገር እንድታስቡ እፈልጋለሁ: የመጀመሪያው መጽሐፍ ቅዱስ ወደዚህ ዘመንና እናንተ ጋር እንድደርስ ሕይወታቸውን መስዋዕት አድርገው የከፈሉ ቅዱሳን ሰማዓታት እንዳሉ፤
ሁለተኛው ደግሞ አሁን እንኳ መጽሐፍ ቅዱስን አንድም ቀን ለመመልከት እድል ያላገኙ በሚልዮን የሚቆጠሩ ሰዎች በዓለም እንዳሉ አስቡ።
የመጀመሪያውን ስታስቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ዋጋው ብር ሰይሆን ደም እንደሆነ ይገባችኋል። መጽሐፍ ቅዱስ እናንተ ጋር የደረሰው ሁለት ወይም ሦስት መቶ ብር ስለከፈላችሁበት ሳይሆን ቅዱሳን አባቶችና እናቶች ደም ደም ስላፈሰሱና ሕይወታቸውን ስለከፈሉበት ነዉ።
ሁለተኛውን ስታስቡ ደግሞ: ፈጽሞ ልትከፍሉለት የማትችሉትን ውድ ነገር እግዚአብሔር በፀጋው(በነጻ) እንደሰጣችሁ ትረዳላችሁ።
#Victor
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
እንደገና አድርገው!?
DO IT AGAIN!?
እግዚአብሔር ሆይ በቀደመው ዘመን ያደረግከውን ስምቻለሁ፤ በቀደመው ዘመን ያደረግከው አስፈሪ ነውና ስሰማ ፈራሁ፤ እባክህ እግዚአብሔር ሆይ በቀደመው ዘመን ያደረግከውን እንደገና አድርግ፤ ያንን አስፈሪ ስራህን በእኛም ዘመን ያለው ትውለድ እንዲያውቅ በድጋሚ አድርግ፤ የሚያስጨንቅ ነገር በመጣ ጊዜ በምህረት ተመልከተን።
“እግዚአብሔር ሆይ፤ ዝናህን ሰምቻለሁ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ ሥራህም አስፈራኝ፤ በእኛ ዘመን አድሳቸው፤ በእኛም ጊዜ እንዲታወቁ አድርግ፤ በመዓት ጊዜ ምሕረትን አስብ።”
— ዕንባቆም 3፥2 (አዲሱ መ.ት)
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
በሰዎች ሁሉ ውስጥ ያለ ትልቅ ጉጉት ነዉ። ነገን ማወቅ! ነገ ምን ይዞ እንደሚመጣ ማወቅ የማይፈልግ የለም።
ይህ የሰው ልጅ ጥልቅ ፍላጎት በታሪክ ውስጥ በተደጋጋሚ ታይቷል። ሰዎች ከጥንት ጀምሮ ነገንና ነገ ይዞት የሚመጣውን ለማወቅ የተለያዩ መንገዶችን ተጠቅመዋል: ይህም ትውልድ የሚጠቀማቸው መንገዶች እጅግ ብዙ ናቸው። ይህንን ትውልድ ጨምሮ በተለይም ጥንታዊያን ኮከብ ቆጠራ(astrology) ፤ ጥንቆላ( fortune-telling) እና የተለያዩ አሁን በጽሑፍ የማይገለጹ ሚስጢራዊ መንገዶችን ተጠቅመዋል: አድሱ ትውልድ ደግሞ ከላይ ያሉት እንደተጠበቁ ሳይንሳዊ የሆኑ መንገዶችን በመጠቀም: ነገን የማወቅ ፍላጎቱን ለማርካት በደረቅና በባሕር ይዞራል።
በዚህ ረገድ የተለያዩ የጥናት ዘርፎች ከማሕበራዊ ጥናት/sociology/ እስከ አየር ንብረት ትንበያ /weather prognostication/ ለመቁጠር የሚያዳግት የምርምር ትንተናዎች አቅርበዋል: እነዚህ ሳይንሳዊ ትንተናዎች የራሳቸው አሁንታዊ ሚና ያላቸው ቢሆኑም: የትኛውም አይነት የሰው ሳይንሳዊ ጥናትም ሆነ የወደቀ ሰው የማሰብ አቅም ነገን የትላንትን ያህል እንኳ አጥርቶ መመልከት የማይቻለውና በተለይም የትኛውም የጥናት ዘርፍ መንፈሳዊውን ዓለም ማጥናት ያልቻለ በመሆኑ የቀረቡትም ሆነ የሚቀርቡት ሳይንሳዊ ጥናቶች በፍጹም ልብ የሚጣልባቸው ከለመሆናቸውም በላይ አሳች ናቸው።
#መጽሐፍ_ቅዱስ
መጽሐፍ ቅዱስ ሁልጊዜ ስለወደፊቱ እውነተኛና ፍጹም የሆነ የመረጃ ምንጭ በመሆን ነገን የማወቅ ጥልቅ የሰው ፍላጎትን ከማርካትም በላይ የሰው ልጅ ምን ማድረግ እንዳለበት በግልጽ በማሳየት እና ደረጃ በደረጃ በመምራት ብቸኛው እስትንፋሰ እግዚአብሔር የሆነ ጽሑፍ መሆኑ በየጊዜው በግልጽ የታየ ነዉ። በዓለም ያሉ ግን ይህንን የእግዚአብሔር ቃል የመረጃ ምንጫቸው ማድረግ አይቻላቸውም! ምክንያቱም ብርሃንን ይጠላሉ ከጨለማ ጋር ተዋደዋል።
እኛ ግን የብርሃን ልጆች ብርሃን ነን! ከሰማይ የሚወጣ ድምፅ የሰማን እንኳ ብንሆን መጽሐፍ ቅዱሳችንን በጨለማ ቤት ውስጥ እንዳለ ሻማ ተጠንቅቀን እንመለከተዋለን። ይህ የጸና የትንቢት ቃል ነውና። በዚህ ዓለም ብንሆንም ከዚህ ዓለም እንደሆኑት በጨለማ አይደለንም! ነገ ምን እንደሚያመጣ እናውቃለን: በእያንዳንዱ ደረጃ መንፈስ ቅዱስ ቃሉን ያስታውሰናል ደግሞም ሊመጣ ያለውን ያሳየናል።
ክርስቲያን ከሆንን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማወቅ ውስጣችን ጥልቅ ፍላጎት ይኖራል። ይህንን ፍላጎት የምንፈጽመው በከባድ ግለት በመጽሐፍ ቅዱስ ገጾች ውስጥ በመመላለስ ነዉ። በተለይ እንደዚህ በለ በመጨረሻው ዘመን የእግዚአብሔር ፈቃድ ማወቅ ወጋ የማይተመንለት ብልጽግና ነዉ። ምን እንጠብቃለን? መጽሐፍ ቅዱሳችንን መንፈስ ቅዱስ እንዲያበራልን እየቃተትን የእግዚአብሔርን ቃል እንፈልግ!
#Victor
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
Nike "ሰይጣናዊ ጫማ" አምርቷል።
የጫማው ሶል ዙሪያ እውነተኛ የሰው ደም የያዘ ነዉ። ሌላው ደግሞ 666 ጥንድ ጫማዎች ብቻ እያንዳንዱ ጥንድ ጫማ በ 1,018 dollar ተሸጠዋል።
ሌላው ደግሞ ሉቃስ 10: 18 በዚህ ጫማ ላይ ተጽፏል: "ሰይጣን ከሰማይ እንደ መብረቅ ስወድቅ አየሁ" ይላል።
ወንድሞቼና እህቶቼ : እንደዚህ አይነት ክህደቶች(Apostasy) ለኃጢአት ሰው መንገድ የሚጠርጉና የሰዎችን አእምሮ ለሚመጣው ስርዓት የሚያዘጋጁ ናቸው።
ግልጽ ነዉ: ዘመኑ ተፈጽሟል! ይህንን የምለው እንደዚህ ያለ ጫማ በመመረቱ አይደለም! መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃዎች ሁሉ ይህንን ግልጽ የሚያደርጉ ናቸው! በዚህ ለይ: ጌታችን በራዕይ የሚመጣውን አመልክቶኛል!
የቤተክርስቲያንን ንጥቀት በየትኛውም ጊዜ ለማለማመድ እየጠበቅን: በመንፈስ እንመላለስ! በቅድስና እንኑር! እንደዚህ አይነት ምርቶችን በፍጹም መጠቀም የለብንም።
ኢየሱስ ክርስቶስ በደጅ ነዉ።
Jesus Christ is near.
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
Song~Changing Lives
By~Don Moen & Frank Edward
(May The Lord Our God, King Of The Universe Change Your life & story!!)
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ሐዋሳ አጂፕ ሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን ከወጣቶች ጋር እግዚአብሔር ለሁለት ተከታታይ ዕሮብ ድንቅ መልእክት ተናግሮናል።እዚሁ አገልግሎት ላይ መንፈስ ቅዱስ ከስተማረን እኔም እንኳ እስከአሁን በጣም እየገረመኝ ያለ እውነት ላካፍላችሁ...
👉ኢየሱስ ክርስቶስ ለአማኙ ራሱን የሚገልጥበት መሰረታዊ መንገድ ምንድነው??
አሁን የለንበ ወቅት(season) የበለጠ አስገዳጅ ቢያደርገውም እያንዳንዱ አማኝ በጊዜውም አለጊዜውም (in season and out of season) ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹምና ግልጽ የሆነ መገለጥ ያስፈልገዋል! ከዚህ እውነት በመነሳት ነዉ ኢየሱስ ለአማኙ ራሱን የሚገልጥበትን መንገድ ለማወቅ የወደድኩት፤ እኔ በለኝ ግላዊ ልምምድ ላይ ተመስርቼ ትምህርት መስራትን ስለማልፈልግ: ኢየሱስ ለእኔ ራሱን የገለጠበትን መንገድ ለሰዎች እንደ ትምህርት አላቀርብም። መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? የሚለው ጥያቄ ከሁሉም በላይ ጥቅም ያለው ነዉ።
ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን በራዕይ ወደ እኔ መጥቶ የገለጠልኝ ነገር ይኖራል: ወደ ሰማያት ተወስጄ ያየሁትም ነገር ይኖር ይሆናል! ደግሞ አለ!.. ይሄ ማለት ግን ኢየሱስ ለአማኙ ራሱን የሚገልጥበት መሰራታዊ መንገድ ነዉ ማለት አይደለም! ኢየሱስ ለሁሉም ራሱን እንደዚያ አይገልጥም ይሆናል: ነገር ግን ለሁሉም አማኝ ኢየሱስ ራሱን የሚገልጥበት መሰረታዊ መንገድ አለ!!! ሃሌሉያ: ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን። አሁን የማሳያችሁ ይህንን መሰረታዊና ለሁሉም የሚሰራ መንገድ ነዉ: መጽሐፍ ቅዱስ እንደዚህ ይላል: “ትእዛዜ በእርሱ ዘንድ ያለችው የሚጠብቃትም የሚወደኝ እርሱ ነው፤ የሚወደኝንም አባቴ ይወደዋል እኔም እወደዋለሁ ራሴንም እገልጥለታለሁ።”
— ዮሐንስ 14፥21
ይህንን ቃል እጅግ ብዙ ጊዜ እንዳነበባችሁት እርግጠኛ ነኝ! በጣም አስተዋዮች ስለሆናችሁ በድጋሚ ደጋግማችሁ እንድታነቡት ልጠይቃችሁ!?
ኢየሱስ ራሱን የሚገልጠው ለማን ነዉ? ኢየሱስ ራሱን የሚገልጥበት መሰረታዊ መንገድስ ምንድነው? መልሱን ደጋግማችሁ እንድታነቡት በጠየኳችሁ ቃል ውስጥ ታገኙታላችሁ: በግልጽ ይነበባል! ኢየሱስ ራሱን የሚገልጠው "የእግዚአብሔር ቃል በውስጡ ላለችው ሰው ነዉ።"
ኢየሱስ በምን አይነት መንገድ ነው ራሱን የሚገልጠው? "ፍቅር" በሚባል መንገድ ነዉ። ኢየሱስ ለእኛ ራሱን የሚገልጠው እኛ ለእርሱ በለን ፍቅር አማካኝነት ነዉ። በዚያው ጥቅስ ላይ እንደተገለጸው አማኝ ለኢየሱስ ያለው ፍቅር የሚገለጠው "ቃሉን በማድረግ" ነዉ። የእግዚአብሔር ቃል በእርሱ ዘንድ ያለችው "የሚጠብቃትም የሚወደኝ" እርሱ ነዉ። ደቀመዝሙር ለመምህሩ ያለው ፍቅር የሚፈተነው ለመምህሩ ቃል በለው ክብር እና ጠንቅቆ ለመጠበቅ በለው መሰጠት ነዉ።
ኢየሱስ እንዲገለጥለት የሚፈልግ አማኝ ሁሉ መልሱ ይሄ ነዉ። "ቃሉ በአንተ ዘንድ ይኑር ቃሉንም ጠብቅ!" "ቃሉ በአንቺ ዘንድ ይኑር ቃሉንም ጠብቂ!"
በጥቂት ቃላት:-ቃሉ ከሌለህ እና ቃሉን የማትጠብቅ ከሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ በአካል ፊትህ ላይ ቆሞ እንኳ አታየውም! አይገለጥልህም!
#እውነት_ነጻ_ያወጣል።
#ProphetVictor
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
"O, How I love Jesus, Because He first Love Me."😊
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ኢየሱስን ለዚህኛው ሕይወት ተስፋ ማድረግ ስህተት ነዉ??? ኢየሱስን በምድር ላይ ለሚገኝ ትልቅነት፤ ስኬት፤ መልካም ትዳር የተሳካ ኑሮ... ወዘተ ተስፋ ማድረግ ስህተት ነዉ??? አይደለም! በፍጹም አይደለም! ስህተት የሚሆነው ለዚህኛው ሕይወት #ብቻ ተስፋ ማድረግ ነዉ። ኢየሱስ ለዚህኛውም ሆነ ለሚመጣው ሕይወት ተስፋችን ነዉ። በዚህስ ምድር ቢሆን ከእርሱ የተሻለ ተስፋ ልናደርግበት የምንችለው ምን አለ??? ማንም የለም! ምንም የለም።
ኢየሱስን ለዛሬም ለነገም ተስፋ እናደርገዋለን! አሜን።
