ru
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Канал የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 14 477 подписчиков, занимая 6 026 место в категории Религия и духовность и 2 324 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 14 477 подписчиков.

Согласно последним данным от 29 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 526, а за последние 24 часа — 12, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 38.31%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 10.22% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 5 538 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 477 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 33.

📝 Описание и контентная политика

Описание канала не предоставлено.

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 30 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

14 477
Подписчики
+1224 часа
+1357 дней
+52630 день
Архив постов
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “አሁንም በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። ከእኔ በኋላ
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “አሁንም በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። ከእኔ በኋላ ለመንጋዪቱ የማይራሩ ነጣቂዎች ተኵላዎች እንደሚመጡ እኔ አውቃለሁ። ደቀ መዛሙርትንም ወደ እነርሱ ይመልሱ ዘንድ ጠማማ ትምህርትን የሚያስተምሩ ሰዎች ከእናንተ መካከል ይነሣሉ። ስለዚህም ትጉ፤ እኔ ሁላችሁንም ሳስተምር ሦስት ዓመት ሙሉ ሌትም፣ ቀንም እንባዬ እንዳልተገታ አስቡ። አሁንም ለእግዚአብሔርና ሊያነጻችሁ በቅዱሳንም ሁሉ መካከል ርስትን ሊሰጣችሁ ለሚችለው ለጸጋው ቃል አደራ ሰጥቻችኋለሁ” (ሐዋ. ፳÷ ፳፰-፴፪)¹ በማለት ያስተማረው ትምህርት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ኤጲስ ቆጶሳትን ስትመርጥ በጣም እንድትጠነቀቅ የሚያሳስብ ቃል ነው። .... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/እርሱን-የምሾመው-ለመንበሩ-ክብር-እንዲሰ/ እርሱን የምሾመው ለመንበሩ ክብር እንዲሰጠው ነው ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

ኤጲስ ቆጶስ ለመሾም የሚያገለግለው መስፈርት ኤጲስ ቆጶሳት የአህጉረ ስብከታቸውን ክርስቲያኖች በአባትነት የሚጠብቁ፣ በመምከር ችግራቸውን የሚያቃልሉ፣ በማንኛውም ነገር አርአያ የሚሆኑ ናቸው። በዓመት
ኤጲስ ቆጶስ ለመሾም የሚያገለግለው መስፈርት ኤጲስ ቆጶሳት የአህጉረ ስብከታቸውን ክርስቲያኖች በአባትነት የሚጠብቁ፣ በመምከር ችግራቸውን የሚያቃልሉ፣ በማንኛውም ነገር አርአያ የሚሆኑ ናቸው። በዓመት ሁለት ጊዜ በሚደረገው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በመሳተፍ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሚጠቅሙ ውሳኔዎች እንዲተላለፉም የድርሻውን ይወጣሉ። ይህም የአገልግሎቱን ከባድነት ሲያመለክት ለከባድ አገልግሎት የሚታጨው አባትም ኃላፊነቱን በመደንብ መወጣት የሚችል መሆኑን ይገባዋል። .... ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ኤጲስ-ቆጶስ-ለመሾም-የሚያገለግለው-መስፈ/ ኤጲስ ቆጶስ ለመሾም የሚያገለግለው መስፈርት ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን አምነው ከተከተሉት መካከል ጥቂቶችን መረጦ ሐዋርያትን ሾመ፡፡ እስከ ዛሬ ድረስ በእረኛውና በመንጋው መካከል ላለው መስተጋብር መሠረት
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን አምነው ከተከተሉት መካከል ጥቂቶችን መረጦ ሐዋርያትን ሾመ፡፡ እስከ ዛሬ ድረስ በእረኛውና በመንጋው መካከል ላለው መስተጋብር መሠረት አስቀመጠ፡፡ የዛሬዎቹ አበው ጳጳሳት እና ካህናት የዚህ ሐዋርያዊ ውርስ ተቀባዮች ናቸው፡፡ በሐዋርያነት የተሾሙት ለተጠሩበት ሐዋርያዊ አገልግሎት ስኬት የሚያስፈልጋቸውን ሥነ ምግባርና ዕውቀት ከጌታ በነቢብም በገቢርም ተምረዋል፡፡ ዛሬም ድረስ ለተጠሩበት አገልግሎት የሚመጥን ሥነ ምግባር እና ትምህርት (ዕውቀት) የሢመተ ጵጵስና ሁለት ምሰሶዎች ናቸው፡፡ https://eotc-gssu.org/a/በበጎነት-ላይ-ዕውቀትን-ጨምሩ-፪ኛ/ ‹‹በበጎነት ላይ ዕውቀትን ጨምሩ›› (፪ኛ ጴጥ. ፩፥፭-፯) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ምእመናንን ማእከል ያደረገ ነው። ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያትን የሰጣቸው ዋናው ትእዛዝ “አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም
የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ምእመናንን ማእከል ያደረገ ነው። ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያትን የሰጣቸው ዋናው ትእዛዝ “አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸውና ያዘዝኋችሁን ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርቴ አድርጓቸው” (ማቴ. 28፡19-20) የሚል ነው። ስለሆነም ሐዋርያትና በሐዋርያት እግር የተተኩት ሐዋርያውያን አበው፣ ዐቃብያነ እምነት፣ ሊቃውንት በአጠቃላይ በየዘመኑ የተነሡ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ዋና ግብራቸው ይህን ታላቁን ተልእኮ መፈጸም ነበር። ጌታችን ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ለሐዋርያት ለሦስተኛ ጊዜ በተገለጠላቸው ወቅት ስምዖን ጴጥሮስን ሦስት ጊዜ ትወደኛለህን? ብሎ እየጠየቀ የሰጠው ትእዛዝም በተመሳሳይ “ግልገሎቼን አሰማራ፣ ጠቦቶቼን ጠብቅ፣ በጎቼን አሰማራ” (ዮሐ. 21፡15-17) የሚል ነው። ... https://eotc-gssu.org/a/ሢመተ-ኤጲስ-ቆጶሳትና-የምእመናን-ሱታፌ/ ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳትና የምእመናን ሱታፌ ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

ኤጲስ ቆጶስነት ምቾትን አብዝቶ ለሚሻው፣ አድልኦንና ወገንተኝነት ለሚስማማው ለሥጋ ጠባይ የሚመች ሓላፊነት አይደለም፡፡ ሰዋዊ ባሕርይን ገርተው የነፍስ ባሕርይን ገንዘብ ወደሚያደርጉበት ማዕርግ የሚሰግ
ኤጲስ ቆጶስነት ምቾትን አብዝቶ ለሚሻው፣ አድልኦንና ወገንተኝነት ለሚስማማው ለሥጋ ጠባይ የሚመች ሓላፊነት አይደለም፡፡ ሰዋዊ ባሕርይን ገርተው የነፍስ ባሕርይን ገንዘብ ወደሚያደርጉበት ማዕርግ የሚሰግሩበት ራስን በመካድ መሠረት ላይ የቆመ የእግዚአብሔር ጥሪ ነው፡፡ ክህነት ትሑት ሰብናን የሚሻ የአገልግሎት ሥልጣን ነው፡፡ አንዱን ከሌላው አስበልጠው ለመጥቀም፣ ያልተደሰቱበትን ደግሞ ከሌላው በታች አድርገው ለመጉዳትለቂም መወጫነትዐስበው የሚሹትበትረ ሥልጣን አይደለም፡፡ የቂም በትረ ወይም የድሎት መወጣጫ እርካብ ላድርግህ ቢሉት ባለቤቱ እውነተኛው ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ (ዕብ. ፯፥፳፰) መክሊቱን የጠየቀ ዕለት መሸሸጊያ ጥግ ይጠፋል፡፡ እናም ኤጲስ ቆጶሳት አገልግሎታቸውን የሚፈጽሙት እውነተኛ ዳኝነት የባሕርይው በሆነ በእግዚአብሔር ፊት መሆኑን ለአፍታ መዘንጋት እንደሌለባቸው ቤተ ክርስቲያን አበክራ ታስገነዝባለች፡፡ ... https://eotc-gssu.org/a/እንኳን-ደስ-አለዎ-ወይስ-እግዚአብሔር-ያስ/ እንኳን ደስ አለዎ ወይስ እግዚአብሔር ያስችልዎ?

https://eotc-gssu.org/a/አክሊል-የሆነችው-ሢመት-መርጣ-የምታርፍባ/ አክሊል የሆነችው ሢመት መርጣ የምታርፍባቸው አባቶች:: ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@e
https://eotc-gssu.org/a/አክሊል-የሆነችው-ሢመት-መርጣ-የምታርፍባ/ አክሊል የሆነችው ሢመት መርጣ የምታርፍባቸው አባቶች:: ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

https://eotc-gssu.org/a/አክሊል-የሆነችው-ሢመት-መርጣ-የምታርፍባ/ አክሊል የሆነችው ሢመት መርጣ የምታርፍባቸው አባቶች:: ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

እንኳን ለመልአኩ ለቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሠላም አደረሳችሁ! ባሕራንኒ ይቤ ዘነገደ ባሕር ርኢክዎ ለሚካኤል ወስዕንኩ ጠይቆቶ ዮም ሰማያዊ በምድር አስተርአየ የመልአኩ ፈጣን ተራዳኢነት ከ
እንኳን ለመልአኩ ለቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሠላም አደረሳችሁ! ባሕራንኒ ይቤ ዘነገደ ባሕር ርኢክዎ ለሚካኤል ወስዕንኩ ጠይቆቶ ዮም ሰማያዊ በምድር አስተርአየ የመልአኩ ፈጣን ተራዳኢነት ከሁላችንም ጋር ይሁን! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

በኢ/ኦ/ተ/ቤ የሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ የዓለም አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ፲፪ኛው ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ከግንቦት 26-27 ቀን 2015 ዓ.ም ተከናውኖ በቀረቡ ሪፖርቶች፣ ጥናታዊ ሰነዶች፣ ከሁሉም አካባቢዎች ከቀረቡ የውይይት ግብዓቶች በመነሳት ባለ 11 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል 1.  በ12ኛው ጠቅላላ ጉባኤ የቀረበውን ሪፖርትና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተቀብለን አጽድቀናል ለትግበራው በጋራ እንሰራለን፡፡ 2.  ከጠቅላይ ቤተክህነት ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ሀገር አቀፍ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እስከ አጥቢያ ሰ/ት/ቤት የቀረበውን የአደረጃጀት መዋቅር በጥልቀት ገምግመናል፡፡በጉባኤው የተሰጡ ማስተካከያዎችን በማካተት ወደ ስራ እንዲገባ ወስነናል፡፡ 3.  የሥርዓተ ትምህርት መጻሕፍትን ለማሳተም የበጀት እጥረት እንዳለ ተገንዝበናል፡፡ይህንን ከቅዱስ ሲኖዶስ እስከ ሀገረ ስብከት ያሉ የቤተክርስቲያን መሪዎች በመገንዘብ ለሕትመቱ ተዘዋዋሪ በጀት/Revolving budget/ እንዲፈቀድና የተዘጋጁ መጻሕፍት ወደ ሕትመት እንዲገቡ በየደረጃው ለሚመለከታቸው አካላት ጥያቄ እንዲቀርብና ክትትል እንዲደረግ በአጽንዖት እንጠይቃለን፡፡ 4.  ሀገሪቱ ላይ በሚከሰቱ የተለያዩ አለመግባባቶች ምክንያት ያለ እዳዋ እዳ የተሸከመችው ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን በአቢያተ ክርስቲያኗ ላይ የሚደርሰው መቃጠልና መዘረፍ በምእመናን እንዲሁም በሰንበት ት/ቤት ወጣቶቻችን ላይ የሚደርስ የህይወት መጥፋት፣ የአካል መጉደልና መሳደድ እንዲቆም የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ እንጠይቃለን፡፡ 5.  ሀገሪቱ ላይ በሚከሰቱ ጦርነቶችና የተለያዩ አለመግባባቶች ምክንያት ያለ እዳዋ እዳ የተሸከመችው ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን በአቢያተ ክርስቲያኗ ላይ የሚደርሰው መቃጠልና መዘረፍ በምእመናን እንዲሁም በሰንበት ት/ቤት ወጣቶቻችን ላይ የሚደርስ የሕይወት መጥፋት፣ የአካል መጉደልና መሳደድ፣ እንዲሁም በተለያዬ ምክንያት የቤተ ክርስቲያንን መ/ራንና አገልጋዮችን ማሰር እንዲቆም የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ እንጠይቃለን፡፡ 6.  የቤተክርስቲያናችን አንድነት ተጠብቆ ምዕመናን ከመደናገር ወጥተው ሥርዓተ አምልኮ በነጻነት መፈጸም ይችሉ ዘንድ ይቅርታና ሰላምን ሲያስተምሩ የኖሩ የትግራይ አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳትና የአስተዳደር አካላት ለቤተክርስቲያ አንድነትና ለምዕመናን ሲሉ ወደ ውይይትና ይቅርታ እንዲመለሱና ቅዱስ ሲኖዶስ ያቀረበውን የሰላም ጥሪ እንዲቀበሉ በልጅነት መንፈስ እየጠየቅን ቅዱስ ሲኖዶስና በአንጻራዊ ሰላም ውስጥ ያለው የቤተ ክርስቲያን መዋቅር በትግራይ በተፈጠረው ጦርነት ለተፈጠረው ችግር ተገቢውን ድጋፍ ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ እንጠይቃለን፡፡ 7.  በቃለ አዋዲ የተደነገገው የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ አደረጃጀት ከአጥቢያ ቤተክርስቲያን በቀር እየተተገበረ አለመሆኑ በቤተክርስቲያን አስተዳደራዊ ሂደት ላይ ክፍተት እንደፈጠረ በጉባኤው በጥልቀት ተነስቷል፡፡ስለሆነም ከወረዳ ቤተክህነት እስከ ጠቅላይ ቤተክህነት ድረስ በቃለ አዋዲው መሰረት የካህናት፣የምዕመናን እና የሰንበት ት/ቤት አባላት ተሳትፎ እንዲከበር በታላቅ አጽንዖት እንጠይቃለን፡፡ 8.  ሥርዓተ አምልኮ ለመፈጸም፣ልጆች ወልዶ ለማሳደግና ተተኪ ትውልድ ለማፍራት ሀገር ያስፈልጋል፡፡በሀገር ውስጥም ሰላም ከሌለ ምንም ማከናወን አይቻልምና በመላው ሀገሪቱ በተቃርኖ የሚገኙ አካላት በሚያርጉት ጦርነትና የእርስ በእርስ ግጭት ምክንያት ንጹሀን ዜጎች ሕጻናት፣ሴቶችና ካህናት ላይ የሚደርስ እንግልትና ጉዳት እየከፋ መምጣቱን በመገንዘብ ልዩነታቸውን በውይይትና በድርድር ብቻ እንዲፈቱ እንጠይቃለን፡፡ 9.  ከሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ ችግሮች በፍጹም ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን የሚመጥኑ ሆነው አላገኘናቸውም፡፡በመሆኑም ሲመቱ ሕገ ቤተክርስቲያንን፣ፍትሐነገሥትንና ቃለ አዋዲን ባከበረና ባከበረ መልኩ ብቻ እንዲደረግ በልጅነት መንፈስ እንጠይቃለን፡፡ 10.  በቤተክርስቲያናችን የሚስተዋሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት በተለያዩ የቤተ ክርስቲያን አካላት ተጠንተው የሚቀርቡ የመፍትሔ ሀሳቦችን ቅዱስ ሲኖዶስ በምክረ ሃሳብነት እንዲቀበላቸውና በማዳበር እንዲተገበሩ አቅጣጫ እንዲሰጥ ከጠቅላይ ቤተክህነት ጀምሮ ያሉ የቤተ ክርስቲያን መዋቅር አካላት የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ያለምንም መሸራረፍ ተግባራዊ እንዲያደርግ በአጽንዖት እናሳስባለን፡፡ 11.  በቤተክርስቲያናችን ውስጥ የሚስተዋሉ የአስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ በሚያስችሉ ሥራዎች ላይ ሁሉ በመሳተፍና እንደ ቤተክርስቲያን ተተኪ ልጅነታችን የበኩላችንን ኃላፊነት በባለቤትነት መንፈስ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት እስከ አጥቢያ ባለዉ መዋቅር ትኩረት ሰጥተን የምንሠራ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ ግንቦት 27 ቀን 2015 ዓ.ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

"እንግዲህ በመንፈስ ቅዱስ እንነሳ፤ በጸጋውም እንደግ" መጽሐፈ ቅዳሴ በእንተ ቅድሳት የ12ኛው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላላ ጉባኤ ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለጸ! በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ
+1
"እንግዲህ በመንፈስ ቅዱስ እንነሳ፤ በጸጋውም እንደግ" መጽሐፈ ቅዳሴ በእንተ ቅድሳት   የ12ኛው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላላ ጉባኤ ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለጸ! በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ፣ 12ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ግንቦት ከ 26– 27 ቀን 2015  ዓ.ም. ድረስ ይካሄዳል፡፡ በመሆኑም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አዘጋጅ ዐቢይ ኮሚቴው ማምሻውን ዝግጅቱን ማጠናቀቁ ገልጸሏል። ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg                      ✍️ Facebook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የአጭር ጊዜ የሥራ ላይ ልምምድ ማስታወቂያ ፩_ ለሥርዓተ ትምህርት ዝግጅት ( በመምህርነት፣ በአሰልጣኝነት፣ በጹሑፍ ዝግጅት፣ በአርትኦት) ተፈላጊ ልምድ/ችሎታ ▶️ በሰ/ት
በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የአጭር ጊዜ የሥራ ላይ ልምምድ ማስታወቂያ ፩_ ለሥርዓተ ትምህርት ዝግጅት ( በመምህርነት፣ በአሰልጣኝነት፣ በጹሑፍ ዝግጅት፣ በአርትኦት) ተፈላጊ ልምድ/ችሎታ ▶️ በሰ/ት/ቤት እና ግቢ ጉባኤያት ሥራ አስጻሚነት ወይም ክፍል ተጠሪነት ያገለገለ/ለች ▶️ በሰ/ት/ቤት ትምህርት እና ሕጻናት ክፍል ▶️ በሰ/ት/ቤት በማስተማር መምህርነት ልምድ ያለው ▶️ በሰ/ት/ቤት አሰልጣኝነት ልምድ ያለው.  ▶️በመምህርነትና በአሰልጣኝነት ስልጠና የወሰደ ▶️በማንኛውም የትምህርት ዘርፍ የተመረቀ/ች ▶️ከምፒወተር ዕውቀት ያለው/ያላት ፪.  ለሚዲያ (ጋዜጠኝነት፣ ቪዲዮ ኤዲቲንግ፣ ግራፊክስ ዲዛይን፣ ስዕል፣ ሥነጹሑፍ፣…  ተፈላጊ ልምድ/ችሎታ ▶️በሰ/ት/ቤት እና ግቢ ጉባኤያት ሥራ አስጻሚነት ወይም ክፍል ተጠሪነት ያገለገለ/ለች ▶️በሰ/ት/ቤት ሥነ ጹሑፍና ስነ ጥበባት፣ መዝሙር፣ ሚዲያ ክፍሎች ያገለገለ/ለች ▶️በዘርፉ ስልጠና የወሰደ እና  ፍላጎት ያለው/ያላት ▶️በዘርፉ ሙያ ወይም ተመሳሳይ የተመረቀ/ች ▶️ከምፒዩተር ዕውቀት ያለው/ያላት 🍀የሚያገኟቸው ዕድሎች፡- ✳️  በረከት እና የአገልግሎት ልምድ፣ ✳️ በተመረጡ ሙያዊ ዘርፎች ስልጠና  እና ሰርተፊኬት በነጻ፣ ✳️ የሥራ ልምድ ደብዳቤ፣ ✳️በቆይታቸው የኪስ ገንዘብ፣ የሚፈለግ የሰው ኃይል ብዛት = 10 ተሳታፊዎች ከኮሌጅ ወይም ከዩኒቨርሲቲ ተመርቀው ሥራ በመፈለግ ላይ የሚገኙ አባላትን ይመለከታል፡፡ ለመመዝገብ ቀጥሎ በቀረበው ሊንክ እስከ ሰኔ 28/2015 ዓ.ም ድረስ  ሞልተው ይላኩ፡፡ 📮https://eotc-gssu.org/a/የአጭር-ጊዜ-የሥራ-ላይ-ልምምድ-መመዝገቢያ/

በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የአጭር ጊዜ የሥራ ላይ ልምምድ ማስታወቂያ ፩_ ለሥርዓተ ትምህርት ዝግጅት ( በመምህርነት፣ በአሰልጣኝነት፣ በጹሑፍ ዝግጅት፣ በአርትኦት) ተፈላጊ ልምድ/ችሎታ ▶️ በሰ/ት/ቤት እና ግቢ ጉባኤያት ሥራ አስጻሚነት ወይም ክፍል ተጠሪነት ያገለገለ/ለች ▶️ በሰ/ት/ቤት ትምህርት እና ሕጻናት ክፍል ▶️ በሰ/ት/ቤት በማስተማር መምህርነት ልምድ ያለው ▶️ በሰ/ት/ቤት አሰልጣኝነት ልምድ ያለው. ▶️በመምህርነትና በአሰልጣኝነት ስልጠና የወሰደ ▶️በማንኛውም የትምህርት ዘርፍ የተመረቀ/ች ▶️ከምፒወተር ዕውቀት ያለው/ያላት ፪.  ለሚዲያ (ጋዜጠኝነት፣ ቪዲዮ ኤዲቲንግ፣ ግራፊክስ ዲዛይን፣ ስዕል፣ ሥነጹሑፍ፣…  ተፈላጊ ልምድ/ችሎታ ▶️በሰ/ት/ቤት እና ግቢ ጉባኤያት ሥራ አስጻሚነት ወይም ክፍል ተጠሪነት ያገለገለ/ለች ▶️በሰ/ት/ቤት ሥነ ጹሑፍና ስነ ጥበባት፣ መዝሙር፣ ሚዲያ ክፍሎች ያገለገለ/ለች ▶️በዘርፉ ስልጠና የወሰደ እና  ፍላጎት ያለው/ያላት ▶️በዘርፉ ሙያ ወይም ተመሳሳይ የተመረቀ/ች ▶️ከምፒዩተር ዕውቀት ያለው/ያላት 🍀የሚያገኟቸው ዕድሎች፡- ✳️  በረከት እና የአገልግሎት ልምድ፣ ✳️ በተመረጡ ሙያዊ ዘርፎች ስልጠና  እና ሰርተፊኬት በነጻ፣ ✳️ የሥራ ልምድ ደብዳቤ፣ ✳️በቆይታቸው የኪስ ገንዘብ፣ የሚፈለግ የሰው ኃይል ብዛት = 10 ተሳታፊዎች ከኮሌጅ ወይም ከዩኒቨርሲቲ ተመርቀው ሥራ በመፈለግ ላይ የሚገኙ አባላትን ይመለከታል፡፡ ለመመዝገብ ቀጥሎ በቀረበው ሊንክ እስከ ሰኔ 28/2015 ዓ.ም ድረስ  ሞልተው ይላኩ፡፡ 📮https://eotc-gssu.org/a/የአጭር-ጊዜ-የሥራ-ላይ-ልምምድ-መመዝገቢያ/

እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ፡፡ ግንቦት 26 እና 27 በጠቅላይ ቤተ ክህነት
እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ፡፡ ግንቦት 26 እና 27 በጠቅላይ ቤተ ክህነት

በየዓመቱ ከግንቦት 21-25 የምናከብረው የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓል  እመቤታችን  በግብጽ ሀገር ደብረ ምጥማቅ በምትባል ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ የወርቅ ወንበር ላይ ተቀምጣ ለአምስት ተከታታይ ቀናት  የታየችበት ነው። ይህም በዓል ከ33ቱ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ሲሆን ከግንቦት ፳፩-፳፭ ያለማቋረጥ ከመላእክት፣ ከሊቃነ መላእክት፣ ከነቢያት፣ ከሐዋርያት፣ ከጻድቃን፣ ከሰማዕታት፣ ከደናግል እና ከመነኮሳት ጋራ ሁና ትገለጽላቸው ነበር፤ አማኒውም ኢአማኒውም ያያት ነበር፤ ያመኑት ክርስትያኖች እምነታቸው ሲጸናላቸው፤ ያላመኑት ደግሞ እያመኑ ከእግዚአብሔር ወልድ ከልጇ ሀብተ ውልድና ስመ ክርስትና ይቀበሉ ነበር፡፡በዚህ ቀን ግብጽ ደብረ ምጥማቅ በተባለ ቦታ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን እመቤታችን ጻድቃን ሰማዕታትን፤ ቅዱሳን መላእክትን አስከትላ ትገለጽላቸው ነበር። አህዛብም ክርስቲያንም በግልጽ ይመለከቷት ነበር። በጒልላቱ ላይ ስትገለጽ በውስጥ በአፍአ በነፍስ በሥጋ ንጽሕት የሆነችው የቅድስት ድንግል ማርያም የፊቷ ውበትና ብርሃን እጅግ ድንቅ ነበርና ካህናቱም ሕዝቡም ሁሉ ልክ እንደ ኤልሳቤጥ “የጌታችን እናት ለእኛ ትገለጪ ዘንድ እኛ ምንድን ነን” እያሉ ይጮኹ ነበር፤ እርሷም ትባርካቸው ነበር፡፡ ከየሀገሩ ያሉ ሰዎች ይሰበሰባሉ፤ ድንኳን ተክለው ሰቀላ ሠርተው አጎበር ጥለው ይከትማሉ ፤ ድንግልም ከግንቦት 21 ቀን ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ሳታቋርጥ ትገለጽላቸው ነበር፤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ምድረ ግብጽና ኢትዮጵያ በተሰደደች ጊዜ በአሁኑ ጊዜ ደብረ ምጥማቅ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ ዐርፈው ነበር:: ጌታችንም ቦታውን ባርኮ የእርሷ መገለጫ እንዲሆን ቃል ኪዳን ገብቶላት ስለ ነበር ጊዜው በደረሰ ሰዓት ደብረ ምጥማቅ ተገድሞ የበርካታ መነኮሳት በዓት ሆነ:: በደብረ ምጥማቅም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ብርሃን ተጎናጽፋና በሠራዊት መላእክት ታጅባ ተገልጣለች፤ በዚያን ጊዜም ሱራፌል ማዕጠንታቸውን ይዘው ሰገዱላት፤ እንዲህ እያሉም አመሰገኗት፤ ‹‹አብ በሰማይ አይቶ እንዳንቺ ያለ አላገኘም፤ ባንቺም ሰው ሆነ፡፡›› (መጽሐፈ ስንክሳር ግንቦት ፳፩ ገጽ. ፫፻፲፰) ሰማዕታትም እንደየክብራቸው ማዕርግ ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ሊሰግዱ ረቂቃን በሆኑ ፈረሶቻቸው ተቀምጠው ወደ እርሷ ቀረቡ፤ በመጀመሪያ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሁሉም ቀድሞ ከሰገደላት በኋላ ቅዱስ መርቆሬዎስ በጸሊም ፈረሱ ተቀምጦ ወደ እርሷ በመምጣት ሰገደላት፡፡ ሌሎቹም በተመሳሳይ መልኩ ሰገዱላት፡፡ ከዚህም በኋላ  ጻድቃን በአንድነት ቀርበው ለክብሯ ሰገዱላት፤ ቀጥሎም በንጉሥ ሄሮድስ በግፍ የተገደሉት ሕፃናት ለእርሷ ሰገዱ፤ በደስታና በፍቅርም ተጫወቱ፡፡ በዚያ የተሰበሰቡትም ክርስቲያኖችና አህዛብ አረማውያን ይህን በአዩ ጊዜ ደስታ ሞልቶባቸው በተለየ ዓለም ያሉ ይመስላቸው ነበር፡፡ (መጽሐፈ ስንክሳር ግንቦት ፳፩ ገጽ. ፫፻፲፰) አባ ጽጌ ድንግልም በደብረ ምጥማቅ በታላቅ ክብር ለምእመናን የታየችው የአምላክ እናት የድንግል ማርያምን መገለጥ በማኅሌተ ጽጌ ድርሰቱ እንዲህ በማለት ገልጾታል፤ ‹‹አመ ትበርቂ በደብረ ምጥማቅ ኀምሰ ዕለታተ፣ ትእምርተ ገጽኪ ይርአይ እስከ ይትነሣእ ዘሞተ፣ሚ መጠነ ማርያም ታሥተፌሥሒ ትፍሥሕተ፣ ኅድጊሰ ጽጌ ፍቅርኪ በጊዜ ንቃሁ መዓልተ፣ ብፁዕ ዘርእየኪ በሕልሙ ሌሊተ፤ የፊትሽን መልክ ያይ ዘንድ የሞተ ሰው እስኪነሣ ድረስ በደብረ ምጥማቅ ለአምስት ቀናት ያህል በተገለጽሽ ጊዜ ማርያም ምን ያህል ደስ ታሰኚ ኖሯል! በቀን የታየው የፍቅርሽ አበባ ይቅርና ሌሊት በሕልሙ ያየሽ ምስጉን ነው፡፡›› (ማኅሌተ ጽጌ) በዚያ የተሰበሰበው ሕዝብ ልዩ ልዩ ጥያቄ ይጠይቃታል፤ ገሚሱ አዳም አባታችንን አሳይን ይሏታል ገሚሱ ነብዩ ዳዊትን ገሚሱ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሳይን ይሏታል አንዳንዱም ከዚህ ቀደም የሞተ ዘመዱን እንድታሳየው ይጠይቃታል ፤እርሷም ለሁሉም ፍቃዳቸውን ትፈጽምላቸው ነበር፤ አዳምን ስትጠራው ከሔዋን ጋር ዳዊትን ስትጠራው ከበገናው ጋር ቅዱስ ጊዮርጊስን ስትጠራው ከጸአዳ ፈረሱ ጋር ነው። ወይ ግሩም ታዲያ ይህ በዚያ ደጉ ዘመን ነበር፤ አሁን ግን ኃጢያታችን ሲበዛ በረድኤት ወይም ለበቁ ካልሆነ በገሃድስ ተገልጻ አትታይም። አንዳንዶች ደግሞ መሀረባቸውን ወደ ላይ በሚወረውሩላት ጊዜ እርሷ የወደደቻቸው እንደ ሆነ በእጅዋ ተቀብላ መልሳ ትጥልላቸዋለች፤ ሁሉም ለበረከት ይካፈሉታል፡፡ እነርሱም ወደ ቤታቸውም ለመሄድ በሚፈልጉ ሰዓት ተሰናብተውና ተባርከውም ይሄዳሉ፡፡ (መጽሐፈ ስንክሳር ግንቦት ፳፩ ገጽ. ፫፻፲፱)