ru
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Канал የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 14 463 подписчиков, занимая 6 026 место в категории Религия и духовность и 2 324 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 14 463 подписчиков.

Согласно последним данным от 29 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 526, а за последние 24 часа — 12, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 38.31%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 10.22% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 5 538 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 477 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 33.

📝 Описание и контентная политика

Описание канала не предоставлено.

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 30 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

14 463
Подписчики
+1224 часа
+1357 дней
+52630 день
Архив постов
የሰ/ ት/ ቤቶችን ሥርዓተ ትምህርትና የመዝሙር አገልግሎት ዙርያ ምክክር ተደረገ። (መስከረም 20/1/2016 የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ክፍለ ከተማ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በክፍለ ከተማው ስር ለሚገኙ አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በሥርዓተ ትምህርቱና በመዝሙር አገልግሎት ዙርያ ወጥነት ባለው መልኩ በ2016ዓ.ም ለመፈጸም ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር መርሐ ግብር ተደረገ። በክፍለ ከተማው የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከ40 በላይ አጥቢያዎች ያሉ ሲሆን መርሐ ግብሩ የተከናወነው በደብረ ጽጌ ቅዱስ ኡራኤል ቤ/ን አዳራሽ ነው። በጉባኤው ላይ በእንግድነት የተገኙት የአዲስ አበባ ሰ/ት/ቤቶች ሰብሳቢ ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ በመክፈቻ ንገጕራቸው እንደተናገሩት " የሥርዓተ ትምርቱ ን የመተግበር ጉዳይ እስከ ዛሬ የምርጫ ጉዳይ ቢሆንም ከዚህ በኋላ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ትምህርቱን ለትውልዱ ይበጃል ብላ ያዘጋጀችው እንደመሆኑ የቤተክርስቲያንን ትዕዛዝ መቀበልና ማስፈጸም ይገባልና በግዴታ አጥቢያዎች መፈጸም ያለባቸው እና የሚፈጽሙት ነው ብለዋል።" በመቀጠልም ስርዓተ ትምህርቱን የተመለከተ እንዲሁ የዝማሬ አገልግሎት ወጥነትን የተመለከተ በመምህር በላይነህ መኮንን እና ዲያቆን ኢንጅነር ዮናስ አረጋ ገለጻ ተደርጎ ከሰንበት ትምህርት ቤት የተውጣጡት ታዳሚዎች ምክክር ከተደረገ በኋላ ለሚነሱ ጥያቄዎች የክፍለ ከተማው አንድነት አመራሮች እና የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የሥርዓተ ትምህርት አስተባባሪ መምህር ሚኪያስ ግዛቸው እና በአዲስ አበባ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት የትምህርት ክፍል ሀላፊ መምህር ዮሐንስ ምላሽ በመስጠት በክፍለ ከተማው ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ሰብሳቢ መምህር መስፍን የ2016ዓ.ም የሥራ አቅጣጫ ተሰጥቶ የእለቱ መርሐ ግብር ፍፃሜ ሆኗል። የዝግጅት ክፍላችን እንዲህ አይነቱ የምክክር መድረኮች በሌሎችም የአዲስ አበባ ክፍለ ከተሞችና ሀገረ ስብከቶች ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባ መሆኑን ይገልፃል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ ብዙኃን ማርያም ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 33 ቅዱሳት በዓላት መካከል አንዱ መስከረም 21 የሚከበረው ብዙኃን ማርያም በሚባል የሚታወቀው በዓል ነው። ብዙኃን ማርያም ማለት በቁሙ ድንግል ማርያም የብዙ ቅዱሳን የጸጋ እናት ማለት ነው። ታዲያ ይህ ክብረ በዓል የሚከበርበት ምስጢሩ ምንድነው ቢሉ በእመቤታችንና በአማላክ ልጇ የሚያምኑ ሦስት መቶ አስራ ስምንት ቅዱሳን ሊቃውንት በሃገረ ኒቂያ በዘመነ ቆስጠንጢኖስ የሊቢያው ሰው አርዮስን ለማውገዝ ሃይማኖትን ለማቅናት የተሰበሰቡበትን በማሰብ ነው። የሊቢያው ሰው አርዮስ ጌትነት የባህርይ ገንዘቡ የሆነ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ክዶ ለማሳት ሲፋጠን በፈቃደ እግዚአብሔር በጻድቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ጥሪ ከተሰበሰቡት ብዙ ሰው መካከል የአበውን ደቀ መዛሙርት ሳንቆጥር ሃይማኖታቸው የቀና ምግባራቸው የጸና ሦስት መቶ አሥራ ስምንቱ አበው ሊቃውንት ተገኙ። አርዮስ የወልደ እግዚአብሔርን አምላክነት በመካድ ወልድ ፍጡር ነው በማለት ያስተማረውን ትምህርት ለማረም እርሱንም ወደ ቀናች ሃይማኖት ለመመለስ እንዲሁም የእግዚአብሔር ወልድ አምላክነት እምቅድመ ዓለም ከባህርይ አባቱ ከአብ ከባህርይ ህይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በቅድምና በመተካከል የነበረ መሆኑን በሥልጣን በኃይል በአገዛዝ አንድ መሆኑን ለመግለጥ በዚች እለት ከተለያዩ ሃገራት ተሰብስበዋል ። እነዚህ ቅዱሳን አበው ሃይማኖታቸው የቀና በተለያየ ተጋድሎ ከፊሎቹ በሰማእትነት ያለፉ እግዚአብሔር በምግባር ያስደሰቱ እና ፍጻሜያቸው ያማረ በመሆናቸው እና በእመቤታችን የአምላክ እናትነት የሚተማመኑ በመሆናቸው የተሰበሰቡባትን እለት በእናታቸው በቅድስት ድንግል ማርያም እመ ብዙኃን በማለት እናከብረዋለን። ብዙኃን ማርያም መባሉ በእመቤታችንና በልጇ በሚታመኑ ቅዱሳን የጸጋ እናት መሆኗን ለማጠየቅ መሆኑ በማሰብ ለሁላችን እናት ሆና በተሰጠችን በእናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት በማመን እና በመተማመን የክህደት መንገድ ከሆነው የዲያቢሎስ አስራር ርቀን በዓሏን በክብር አክብረ እንድንከብር አምላከ ቅዱሳን ለሁላችን ይፍቀድልን። የወላዲተ አምላክ እናትነት አማላጅነት በረከት አይለየን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት] ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunio

ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ። ጸሎተኛው ፣ ደጉ ፣ ርህሩሁና ታጋሹ አረጋዊው አባት ብፁዕ አቡነ ሰላማ ዛሬ መስከረም ፲፰ቀን ፳፻ ፲ወ፮ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።ብፁዕ አባታችን
ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ። ጸሎተኛው ፣ ደጉ ፣ ርህሩሁና ታጋሹ አረጋዊው አባት ብፁዕ አቡነ ሰላማ ዛሬ መስከረም ፲፰ቀን ፳፻ ፲ወ፮ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።ብፁዕ አባታችን ባደረባቸው ህመም ምክንያት በአዲስ አበባ ሃሌሉያ ሆስፒታል በህክምና ላይ እንዳሉ ነው ከዚህ ዓለም ድካም ያረፉት።የብፁዕነታቸውን ሽኝት መርሐ ግብር በተመለከተ በቋሚ ሲኖዶስ እንደተወሰነ ዝርዝሩን  የምናሳውቅ ይሆናል።   የብፁዕነታቸው በረከት ይደርብን አሜን!!!

ከስር ባለው ማስፈንጠሪያ ( ሊንክ) የመጽሐፍ ኅትመት ፍላጎት ማሳወቂያ ቅጹን ይሙሉ! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የሰንበት-ት-ቤቶች-መማሪያ-መ
ከስር ባለው ማስፈንጠሪያ ( ሊንክ) የመጽሐፍ ኅትመት ፍላጎት ማሳወቂያ ቅጹን ይሙሉ! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የሰንበት-ት-ቤቶች-መማሪያ-መጻሕፍት-የኅት/ የመጻሕፍት ኅትመት ፍላጎት ማሳወቂያ 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ገጻችንን ይቀላቀሉን! ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU

በአሁኑ ሰዓት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ መሪነት የሰሜን፣ የደቡብ፣ የምዕራብ፣ የምሥራቅና የአቃቂ ክፍላተ ከተማ ስንበት ት/ቤቶች አንድነት አስተባባሪ
+2
በአሁኑ ሰዓት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ መሪነት የሰሜን፣ የደቡብ፣ የምዕራብ፣ የምሥራቅና የአቃቂ ክፍላተ ከተማ ስንበት ት/ቤቶች አንድነት አስተባባሪዎች የተዘጋጁ የሰንበት ት/ቤት አባላት መዝሙር ይዘምራሉ፣ መንፈሳዊ ትዕይንት በማሳዬት ላይ ይገኛሉ

ከሩስያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቴዎሎጂ ኮሌጅ የመጡ መዘምራን የ2016 ዓ.ም የመስቀል ጥናትን ተመለከቱ 15/01/2016 ዓ. ም ፤ ከሩሲያ ኦርቶዶክስ ሞስኮ ቴዎሎጂ ኮሌጅ የመጡት የመዘምራን ልዑካ
+6
ከሩስያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቴዎሎጂ ኮሌጅ የመጡ መዘምራን የ2016 ዓ.ም የመስቀል ጥናትን ተመለከቱ 15/01/2016 ዓ. ም ፤ ከሩሲያ ኦርቶዶክስ ሞስኮ ቴዎሎጂ ኮሌጅ የመጡት የመዘምራን ልዑካን ቡድን በምስራቅ ዞን በታዕካ ነገሥት ቅድስት በዓታ ለማርያም የጥናት ቦታቸውን ያደረጉትን ከ1200 በላይ ሰንበት ተማሪዎች ጥናታቸው ላይ በመገኘት የጥናቱን ሁኔታ ተመልክተዋል። መዘምራኑም በራሳቸው ቋንቋ መስቀሉን የሚያወሳና የሚያከብር ልዩ ሕብረ ዝማሬ አቅርበዋል። በተያያዘም ልዑካን ቡድኑ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ተገኝተው ከብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የበላይ ኃላፊ እና የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አመራር ጋር የሰንበት ትምህርት ቤቶችን አገልግሎት በሚመለከት ውይይት አድርገዋል። [የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት] ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

የዘንድሮ የመስቀል በዓል አዘጋጅ ሰንበት ት/ቤት የማሕደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ተክለ ሳዌሮስ ሰ/ት/ቤት ዝግጅት ምን እንደሚመስል በማደራጃ መምሪያውና በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ኃላፊዎች
+1
የዘንድሮ የመስቀል በዓል አዘጋጅ ሰንበት ት/ቤት የማሕደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ተክለ ሳዌሮስ ሰ/ት/ቤት ዝግጅት ምን እንደሚመስል በማደራጃ መምሪያውና በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ኃላፊዎች ጉብኝት ተደረገ። መስከረም 13 2016 ዓ.ም ፤ የ2016 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል ተረኛ አዘጋጅ የሆነው የማሕደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ተክለ ሳዌሮስ ሰ/ት/ቤት እያደረጉ የሚገኘውን ዝግጅት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ አባ ተ/ያሬድ ጎርጎርዮስ ፣ምክትል ኃላፊው መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሳሴ ፣የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ምክትል ሰብሳቢ ዲ.ን ስንታየሁ ምስጋናው እና ዋና ጸሐፊው ቀሲስ አርአያ ተሾመና ሌሎችም የአንድነቱ አመራር አባላት በመሆን ጉብኝት አድርገዋል። ከሰንበት ት/ቤቱ አመራር ጋር ውይይት ተደርጓል። በሌላም በኩል በምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለመስቀል በዓል ዝግጅታቸውን እያደረጉ የሚገኙትንም የማኅበረ ቅዱሳን ዓባላት እንዲሁ በማጥኛ ቦታቸው በመገኘት ዝግጅታቸውን መመልከት ችለዋል። የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት] ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

በመስቀል መዝሙር ጥናት በሰሜን ዞን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ
+4
በመስቀል መዝሙር ጥናት በሰሜን ዞን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ተገኝተው ለሰንበት ትምህርት ቤት ዓባላት ቡራኬ ሰጥተዋል መስከረም 12 ቀን 2016 ዓ.ም ፤ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የመስቀል በዓልን በደማቅ ሁኔታ ለማክበር በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስር በአምስት ዞኖች የመስቀል መዝሙር ጥናት እየተካሄደ ሲሆን የጥናት ቦታውን በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ያደረገው የሰሜን ዞን በማጥኛው ስፍራ የተገኙት ቡፁዕ አብነ ጴጥሮስ "የአንዲት ቤተክርስቲያን ምሳሌ ፣ ለጠፋው ትውልድ ጥሩ ምልክት ናችሁ " በማለት አባታዊ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ብፁዕ አቡነ አብርሃምም "መታዘዝ አንዱ መስዋዕት ነው፤ ታዛዦች ሁኑ በአካሄዳቹ ሁሉ ክርስቶስን ምሰሉ ቤተ ክርስትያንንም ስበኩ" በማለት አባታዊ መልዕክት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬአቸውን ሰጥተዋል። በሰሜን ዞን 22 ደብራት እንዲሁም ከ890 በላይ ሰንበት ተማሪዎች እንደሚሳተፉ ይታወቃል። [የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት] ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

የመስቀል ደመራ በዓል መዝሙር ጥናት እና መዝሙራዊ ትዕይንት ቅድመ ዝግጅት የመዝጊያ መርሐ ግብር ተካሔደ መስከረም12 ቀን 2016 ፤ (ሰ/ት/ቤቶች አንድነት አዲስ አበባ) በ2016 ዓ.ም የሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓልን የተሳካና ያማረ ሆኖ እንዲከበር የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከነሐሴ 24 ጀምሮ መዝሙር ጥናት እና የመዝሙራዊ ትዕይንት ሥልጠና ዝግጅት እያደረገ እንደሆነ የሚታወቅ ሲሆን ትናንት መስከረም 11 ቀን 2016 ዓ.ም የመዝጊያ መርሐ ግብሩን በ ደቡብ ዞን በደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አካሂዶል። በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስር በሚገኙ ከ270 በላይ አጥቢያዎች በ 5 የጥናት ዞኖች በመክፈል ጥናቱ የሚደረግ ሲሆን በደቡብ ዞን በደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ ቆሞስ አባ ተክለ ያሬድ ጎርጎርዮስ በተገኙበት የመክፈቻ መርሐ ግብር መደረጉ ይታወሳል። በትናንትናው እለት ደግሞ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል እና የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የበላይ ጠባቂ ብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ ፤ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ መዝሙር ክፍል ኃላፊ የሆኑት መጋቢ ሐዲስ ሐረገ ወይን ፤ የሀገረ አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ቀሲስ ጥላሁን ደሲሳ በተገኙበት መርሐ ግብሩ ተካሂዶል። በመዝጊያ መርሐ ግብሩም የደቡብ ዞን ጥናት ተሳታፊ የሆኑት ከ51 ደብራትና ገዳማት የተውጣጡ ከ 1500 በላይ ወጣት የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እንዲሁም አስተባባሪዎች ተገኝተው መርሐ ግብሩን የተካፈሉ ሲሆን የሀገረ አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ቀሲስ ጥላሁን ደሲሳ "እንዲሁ እናንተ ደግሞ የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ፦ የማንጠቅም ባሪያዎች ነን፥ ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል በሉ።" የሚለውን ኃይለ ቃል አንስተው ቃለ እግዚአብሔር አስተምረዋል። በመርሐ ግብሩ ላይ ዶ/ር ያየህ ነጋሽ የ21ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያን ተግዳሮቶች በሚል ለተሳታፊው ሥልጠና የሰጡ ሲሆን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ መዝሙር ክፍል ኃላፊ የሆኑት መጋቢ ሐዲስ ሐረገ ወይንም ወረቡን አስከልሰዋል። በመጨረሻም ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል እና የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የበላይ ጠባቂ ብፁዕ አቡነ ቀለሚንጦስ "እርሱም የአካሉ ማለት የቤተ ክርስቲያን ራስ ነው። እርሱም በሁሉ ፊተኛ ይኾን ዘንድ፥ መጀመሪያ ከሙታንም በኵር ነው።" ቆላ 1÷18 ተመርኩዘው "ቤተ ክርስቲያን አንዲት ናት እኛም ውበታችን አንድነታችን ነው እርሱን በትዕግስት፣ በማስተዋልና ራስን በመግዛት እንጠብቀው" በማለት አባታዊ መልእክትና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል፡፡ (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

"የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፤ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም።" ኢያ 1:8 የሰንበት ትምህርት
"የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፤ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም።" ኢያ 1:8 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አተገባበር ዙርያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክርና ገለጻ ተደረገ። መስከረም 11 2016 ዓ.ም ፤ በሲዳማ ሀገረ ስብከት በታላቁ ደብር በሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስ
+6
የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አተገባበር ዙርያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክርና ገለጻ ተደረገ። መስከረም 11 2016 ዓ.ም ፤ በሲዳማ ሀገረ ስብከት በታላቁ ደብር በሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ፀሐይ ቆሞስ አባ ኪዳነ ማርያም አንዱአለም እና መምህራነ ወንጌል በተገኙበት ለደብሩ ሰበካ ጉባኤ አባላት የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አተገባበር ዙርያ ገለጻ ቀርቦ ውይይት ተደረገ። ገለጻውን ያከናወኑት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በ2015 ዓ.ም አዘጋጅቶት በነበረው የክረምት ሥልጠና ደብሩን ወክለው የተሳተፉት ዲ/ን ሳሙኤል እና መ/ር ረድኤት ሲሆኑ ከገለጻው በኋላ ምክክር ተደርጎበታል። የገዳሙ ዋና አስተዳዳሪ እና መላ የሰበካ ጉባኤ አባላትም በቀረበው ሪፓርትና ገለጻ በሰንበት ትምህርት ቤቶች የሥርዓተ ትምህርት እንቅስቃሴ እጅግ መደሰታቸውን ገልፀው ቀጣይ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ወደ ትግበራ ለመግባት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል። በመቀጠልም ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ በማለት የሥራ ክፍፍል አድርገዋል። ዘገባውን መራሔ ሚዲያ (መራሔ ድኅነት ሰ/ት/ቤት መገናኛ ብዙኃን) አጋርቶናል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

"ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" ኤፌ 4፡28 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ
"ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" ኤፌ 4፡28 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu