ru
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Канал የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 14 479 подписчиков, занимая 6 043 место в категории Религия и духовность и 2 334 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 14 479 подписчиков.

Согласно последним данным от 30 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 530, а за последние 24 часа — 23, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 39.14%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 10.20% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 5 666 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 477 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 33.

📝 Описание и контентная политика

Описание канала не предоставлено.

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 01 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

14 479
Подписчики
+2324 часа
+1447 дней
+53030 день
Архив постов
ቅዱስነታቸው በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የሽኝት መርሐ ግብር ላይ በመገኘት አሸኛኘት ካደረጉ በኋላ በሰላም ወደ መንበረ ፓትርያርክ ተመልሰዋል። """"""""""""""""""""""""""""""""""""""
+1
ቅዱስነታቸው በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የሽኝት መርሐ ግብር ላይ በመገኘት  አሸኛኘት ካደረጉ በኋላ በሰላም  ወደ መንበረ ፓትርያርክ ተመልሰዋል። """"""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""" የካቲት ፳፪ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ******************** አዲስአበባ -ኢትዮጵያ """"""""""""""""""""" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት  የብፁዕ አቡነ ዮሐንስን እረፍት ተከትሎ   ዛሬ ጠዋት መቐለ የገቡ ሲሆን  በብፁዕነታቸው የሽኝት መርሐ ግብር ላይ የተሰማቸውን ሐዘን በመግለጽ  ቃለ ምዕዳንና ቃለ ቡራኬ ከሰጡ በኋላ በአሁኑ ሰዓት አዲስ አበባ  መንበረ ፓትርያርክ  በሰላም ገብተዋል። + + + @የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ቅዱስ ፓትርያርኩ በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ሽኝት ላይ ለመገኘት ወደ መቐለ አቀኑ! የካቲት 22 ቀን 2015 ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳ
+3
ቅዱስ ፓትርያርኩ በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ሽኝት ላይ ለመገኘት ወደ መቐለ አቀኑ! የካቲት 22 ቀን 2015 ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የሽኝት ሥነ ሥርዓት ላይ ለመገኘት ወደ መቐለ አቀኑ። ቅዱስነታቸው ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትንና ሊቃውንትን አስከትለው በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ሽኝት ሥነ ሥርዓት ላይ ለመገኘት ወደ መቐለ ሲጓዙ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የኒውዮርክ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ተገኝተው ሽኝት አድርገውላቸዋል። በኋላም መቐለ አሉላ ኣባነጋ ዓለም አቀፍ  አየር ማረፊያ በሰላም ገብተዋል ። በአየር ማረፍያ ሲደርሱ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የቤተክህነት ሠራተኞች እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች እና ምእመናን አቀባበል ተደርጎላቸዋል ።

ቅድስት 👉 የአብይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት ቅድስት ይባላል :: በወንድ አንቀጽ ቅዱስ ይባላል ቃሉ የግዕዝ ሲሆን ትርጉሙም ንጹሕ ፣ ንዑድ ፣ ልዩ ፣ ጽኑህ ክቡር ማለት ነዉ። 👉 ይህ ቃል ለእግዚአብሔር የባሕሪው መገለጫ ነው :: በባሕሪው ቅዱስ የሆነውን አምላክ የሚያገለግሉ መላእክት፣ደጋግ ሰዎች ፣ አንድምበእግዚአብሔር የተለየ በቅብዕ ሜሮን የከበረ  ፣ ነገር ሁሉ ቅዱስ ይባላል። "በክህነት ያገለግሉኝ ዘንድ የኦሮንን ልጆቹን ቅባቸው ቀድሳቸዉም ." ዘፀ 30፥30 ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ስለ እግዚአብሔር ቅድስና ሲናገር'' የአሕዛብ አማልክት ሁሉ አጋንንት (ቅድስና የሌላቸው ናቸው) እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ሰራ ምስጋናና ውበቱ በፊቱ ቅድስናና ግርማ በመቅደሱ ውስጥ ናቸው :: እሙ ለሳሙኤል ነብያት ሃናም የእግዚአብሔርን ቅድስና ስትገልጥ " እንደ እግዚአብሔር ቅዱስ የለምና እንደ አምላካችንም ፃድቅ የለምና ከአንተ በቀር ቅዱስ የለም" መጽ ሳሙ 2፥2 በእውነት እንደ አባታችን እግዚአብሔር ቅዱስ ማን ነው እውነተኛ የጽድቅ ፈራጅ  ልጆቼ የሚለን እንደ ኃጢአታችን ያለጠፋን ።  ለዚህ ፍቅሩ ምን እንከፍለዋለን ምስጋና ነው እንጂ ሌላ ምን እንላለን ። 👉 ለዚህም ነው በቅዳሴያችን ካህኑ "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ " ህዝብም "በአማን አብ ቅዱስ በአማን ወልድ ቅዱስ በአማን ውእቱ መንፈስ ቅዱስ " እያልን ልባችንን ለአምላካችን ሰጥተን የምናመሰግነው :: 👉 በቤተ ክርስቲያናቸንም በዚች ቅድስት በተባለች ሳምንት ማቴ 6፥16-25 ይነበባል ቃሉም እንዲህ ይላል "ስትጾሙ እንደ ግብዞች አትጠውጉ  ለሰዎች እንደ ጦመኛ ሊታዩ ፊታቸውን ያጠወልጋሉና እዉነት እላችኀለሁ ዋጋቸውን ተቀብለዋል :: እናተ ግን ስትጾም በስውር ላለው አባትህ እንጂ ለሰዎች እንዳትታይ ራስህን ተቀባ ፍትህንም ታጠብ በስውር የሚያይ አባትህ በግልጥ ያስረክብሃል " ይህን የምንረከበውን ጸጋራ በረከት ቅዱስ ያሬድ" ጾም የነፍስን ቁስል ኃጢአትን ታድናለች :: የሥጋ ፍላጎቶችን የኾኑትንም ሁሉ ቸል ታሰኛለች ለወጣቶችም ጥምናን ታስተምራላች እንኾ ሙሴ በደብረ ሲና ጾሟልና። ፆም የቅድስና አንዱ መስፈርት ነው። ሳይጾሙ እቀደስ ሳይማሩ እሾም የለም :: 👉 አምላካችን እግዚአብሔር  ጌታችን  መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለመቀደስ የቅድስናንም  ሕይወት ሊያስተምረን ወደ ምድር መምጣቱን እናስባለን የቅድስናውን ም ሥራ ሁሉ በልባችን እንስላለን :: ፆም፣ ጸሎቱ ፣ ስግደት ፣ ትሩፋቱን፣ ምፅዋት ማቴ 5-7 እንማራለን። ሐዋሪያዊ ቅዱስ ጴጥሮስ "እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ " 1 ጴጥ 1፥15 እንደ ተባልን እናሳብ ። በጥምቀት ለይቶ ቀድሶን በደሙ ኑ ልጆቼ ብሎ ጠርቶናል በስሙ እንትጋ እንበርታ በፆም በጸሎቱ እንቀደስ እንደ አባቶች በስግደቱ 1 ቆሮ 13፥14 "የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔር ፍቅር የመንፈስ ቅዱስ ሕብረት ከሁላችን ጋር ይሁን " ወስብሐት ለእግዚአብሔር

የዕረፍት ጊዜአችን አይደለም፡፡ አኹን በመከራ አልፈን ፍጹማን ወደመኾን የምንመነደግበት ጊዜ ነው፡፡ ምናልባት አኹን ስደት ላይኖርብን ይችላል፡፡ መከራ ላይኖርብን ይችላል፡፡ ነገር ግን ዕለት ዕለት የሚያገኙን ሌሎች መከራዎች አሉብን፡፡ እነዚኽን ጥቂት መከራዎችን ታግሠን ካልተቀበልን በወዲያኛው ዓለም ከዚኽ የባሰ መከራ ይገጥመናል፡፡ ደግሞም እኮ ከሚቻለን መጠን አንፈተንም፤ ከሌላው ሰው በተለየ መልኩ ለእኛ ልዩ ፈተና አልመጣብንም /1ኛ ቆሮ.10፡13/፡፡ ስለዚኽ “ወደ ፈተና አታግባን” እያልን እግዚአብሔርን እንማልደው፡፡ ወደ ፈተናው ብንገባ ደግሞ ታግሠን መከራውን እንቀበል፡፡ እንዲኽ የምናደርግ ከኾነ ከላይ የገለጥነውን ጽኑ ታጋይን እንመስለዋለን፡፡ ከርሱ በላይ ደግሞ ጽኑ የእምነት አርበኞችን እንመስላቸዋለን፡፡

ኪዳነ ምህረት         ኪዳነ ምህረት   “ከመረጥኋቸው ጋር ቃል ኪዳን አደረግሁ”መዝ.89፥3 በማለት እግዚአብሔር በቅዱስ  ዳዊት አድሮ ከመረጣቸው ጻድቃን፣ቅዱሳን፣ሰማዕታት ቃል-ኪዳን እንደሚያደርግ ተናግራል ** የቀደሙት አባቶቻችን የልባቸው ማረፊያ ትሆን ዘንድ ወልድ በተለየ አካሉ ማደሪያው ያደረጋት መቅደሰ ሰሎሞን፣ የአዳም ተስፋው፣ የኖህ መርከቡ፣ የአብርሃም ድንኳን፣ የሙሴ ጽላት ፣የዳዊት በገና፣ የኢሳይስ ድንግል፣ ታቦት  ዘዶር ድንግል ማርያምም የምህረት ቃልኪዳንን የካቲት16 ቀን ተቀብላለች ይህም ቃልኪዳን የተለየ የምሕረት ቃልኪዳን ነው።ከፍጡራን መካከል እንደእርሷ የተለየ ቃል ኪዳንን የተቀበለ የለም፤ ወደፊትም አይኖርም፣እርሷ ከሁሉም ተለይታ የከበረች ምልዕተ ጸጋ ስለሆነች የቅዱሳንን ሁሉ ጸሎት ታሳርጋለች በተሰጣት ጸጋም ለዘለዓለም ስታማልድ ስታስምር ትኖራለች።   ** ኪዳነ ምህረት ማለት የምህረት መሐላ ውል ስምምነት ማለት ነው፡፡ ከ33ቱ በዓላተ እግዝእትነ ድንግል ማርያም አንዱ ነው፡፡ እመቤታችንም ከጌታችን መቃብር እየሄደች በምትለምንበት ጊዜ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና ምን ልታመጣብን ነው በማለት ሊጣሏት ሲመጡ ጌታችንም ከዓይናቸው ሰውሯታል አይሁድም ጠባቂ ቢያቆሙ እመቤታችን ዕለት ዕለት መሄዷን አላቋረጠችም  እመቤታችንም እንዲህ ብላ ስትጸልይ ልጄ ወዳጄ ሆይ ከስጋዬ ስጋ ከነፍሴ ነፍስ ነስተህ ሰው በመሆንህ ዘጠኝ ወር ከ5 ቀን በቻለ ማሕጸኔ ከአንተ ጋር ሀገር ለሀገር ስለ መሰደዴ ልምናዬን ትሰማኝ ዘንድ እለምንሃለሁ አለች በዚህ ጊዜ ንውጽውጽውታ ሆነ መቃብራት ተሰነጣጠቁ  ጌታችንም ከእልፍ አእላፋት መላዕክቱ ጋር መጥቶ ሰላም ለኪ ማርያም ምን እንዳደርግልሽ ትለሚኚኛለሽ አላት፡፡ እርሷም መታሰቢያዬን ያደረገውን ስለ ስሜ ለችግረኛ የሚራራውን በስሜ ቤተ ክርስቲያን ያነጻውን መባዕ የሰጠውን ከሃይማኖት ከፍቅር ጽናት ልጁን በስሜ የጠራውን ሁሉ ማርልኝ ከሞተ ስጋ ከሞተ ነፍስ አድንልኝ አለችው፡፡    ** ጌታችንም ይህን ሁለ እንዳደርግልሽ "መሐልኩ ለኪ በርእስየ ወበ አቡየ ሕያው ወበመንፈስ ቅዱስ" ብሎ ቃል ገብቶላት አርጓል፡፡ ኪዳነምሕረት ስንል የምሕረት ውል ሰምምነት ማለት ሰለሆነ ድንግል ማርያምም  በቀደመ ልመናዋ ለምና የምታስምር እንደሆነች እንረዳልን ።እመቤታችን ዝክሯን ለሚዘክሩ መታሰቢያዋን ለሚደርጉ ታምሯን  ለሚሰሙ፥ ለሚያሰሙ፥ ለሚተረገሙ ፥ውዳሴዋን ለሚያደርሱ ፣ቅዳሴዋን ለሚቀድሱ ቤተ መቅደሷን ለሚሰሩ ፣በአጠቃላይ ሰሟን ለሚጠሩ ፈጥና የምትደርስ አፍጣኒተ ረድሔት ናት ።   ** ከከበሩት ይልቅ የከበረች ናት እና እናከብራታለን ከፍ ከፍ እናደርጋታለን ስሟ ጠርተን አንጠግብም እና  ደጋግመን እናወድሳታለን ከጥፋት ውኃ የዳንባት የመዳናችን አርማችን ምልክታችን የመዳችን ትምክህት  ሰለሆነች እንደ ልጇ ዳዊት እምነ ጽዮን እያልን እንጠራታለን አምባ መጠጊያ መመኪያችን ከክፋ ቀን መከለያችን እናታችን  እመቤታችን ታቦት ዘዶር ድንግልን እንደ ቅዱሳኑ ኪዳነምሕረት እመቤት ለዓለም ሁሉ መድኃኒት እያልን ሰንማጸናት ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ነጻ ታወጣናለች እና እስከመጨረሻው ድረስ በሃይማኖት በምግባር ተወስነን እንድንኖር የእግዚአሔር ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት ከሁላችን ጋር ይሁን።          ወስብሐት ለእግዚአብሔር ከቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ወንድሞች ሆይ! ክፉዎች በዚኽ ዓለም በተድላ በደስታ ሲኖሩ ዐይተን ግራ አንጋባ፡፡ በአንጻሩ ደግሞ በጎ ሰዎች በዚኽ ዓለም በመከራ ሲኖሩ ዐይተን ግራ አንጋባ፡፡ ክፉዎች በተድላና በደስታ የሚኖሩት እግዚአብሔር ክፉ ሥራቸውን ቢወድላቸው ነውን ብለን አንጠራጠር፡፡ በጎውን ሰው ተቸግሮ ብናየው አንጠራጠር፡፡ የበጎ ሰዎች ዋጋ እንዲኹም የክፉዎች ሰዎች ፍርድ በዚኽ ዓለም አይደለምና አንጠራጠር፡፡ ዳግመኛም ክፉ ሰው ሲባል ከነጭራሹ አንዲትም በጎ ነገር የለውም ማለት አይደለም፡፡ በጎ ሰው ሲባልም ከነጭራሹ አንዳችም በደል የሌለበት ማለት አይደለም፡፡ ስለዚኽ ይኽ ክፉ ሰው ስለ ጥቂት ምግባሩ ተድላ ደስታውን በዚኽ ዓለም ያገኛል፤ በወዲያኛው ዓለም ግን ፍርድ ያገኟል፡፡ ይኽ ክፉ በዚኽ ዓለም ከሌሎች ሰዎች ይልቅ ደስታ ማግኘቱ በወዲያኛውም ዓለም እንደዚኽ በደስታ የሚኖር ስለሚመስለው እኔ መልካም ሰው ነኝ፤ እንዲኽ በደስታ የምኖረውም እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ስላለ ነው ብሎ ያስባል፡፡ አንተ ግን ወዳጄ እንዲኽ የምታስብ አትኹን፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዲኽ ይልኻል፡- “በእናንተ ዘንድ የደከሙና የታመሙ ብዙዎች አሉ፤ አያሌዎችምአንቀላፍተዋል” /1ኛ ቆሮ.11፡30/፡፡ በሌላ ስፍራም፡- “ለሰይጣን እንዲሰጥ ፍርዴ ነው” /1ኛ ቆሮ.5፡5/፡፡ ነቢዩ ደግሞ፡- “ከእግዚአብሔር እጅ ስለ ኃጢአትዋ ኹሉ ኹለት ዕጥፍ ተቀበለች” /ኢሳ.40፡2/፡፡ ነቢዩ ዳዊትም፡- “ጠላቶቼ እንደበዙ እይ፤ የግፍም ጥል ጠልተዉኛል፤ ኃጢአቴንም ኹሉ ይቅር በለኝ” /መዝ.25፡19፣18/፡፡ ልዑለ ቃል ኢሳይያስም በሌላ አንቀጽ፡- “አቤቱ ሥራችንን ሠርተኽልናልና ሰላምን ትሰጠናለህ” አለ /ኢሳ.26፡12/፡፡ እነዚኽ ኃይለ ቃላት የሚነግሩን በጎ ሰዎች መከራቸውን የሚቀበሉት በዚኽ ዓለም እንደኾነ ነው፡፡ ክፉ ሰዎች ግን መከራቸውን የሚያገኙት በወዲያኛው ዓለም ነው፡፡ ይኽንንም ከእኔ ሳይኾን ደጉ አብርሃም ለነዌ ሲነግረው ብታደምጥ ይሻልኻል፡- “አንተ በሕይወትህ ሳለህ መልካም እንደተቀበልህ አስብ፡፡ አልዓዛር ግን እንዲኹ ክፉ፡፡ አኹን ግን ርሱ ይጽናናል አንተም ትሣቀያለህ” /ሉቃ.16፡25/፡፡ እንግዲኽ ነዌና አልዓዛር ገና ይኽ ዓለም ሳያልፍ የሚገባቸውን እንዳገኙ ታስተውላለህን? ነዌ ከጥቂት በጎነቱ በዚኽ ዓለም ዋጋውን (ሀብት) አገኘ፡፡ አልዓዛር ደግሞ ስለ ጥቂት ክፋቱ በዚኽ ዓለም ብዙ መከራ ተቀበለ፡፡ ነዌ የጥቂቷን በጎነት ዋጋውን እዚኽ ዓለም ስላገኘ በወዲያኛው ዓለም ይሠቃያል፡፡ አልዓዛርም የጥቂቷን ክፋቱ ዋጋውን በዚኽ ዓለም ስለተቀበለ በወዲያኛው ዓለም ይጽናናል፡፡ ስለዚኽ ክፉዎች በዚኽ ዓለም ተመችተዋቸው ብናይ፣ በጎዎች ግን ባይመቻቸው አንጠራጠር፡፡ እንደ በጎዎቹ መከራ ሲደርስብንም ደስ ሊለን ይገባል፤ ይኽ ኃጢአታችንን የሚያስተሰርይልን ነውና፡፡ ስለዚኽ በዚኽ ዓለም እንዲመቸን ልንጠብቅ አይገባንም፡፡ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱ በዚኽ ዓለም እስካሉ ድረስ መከራ እንዳለባቸው ነግሯቸዋልና፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም፡- “በእውነትም በክርስቶስ ኢየሱስ እግዚአብሔርን እየመሰሉ ሊኖሩ የሚወዱ ኹሉ ይሰደዳሉ” ብሏልና /2ኛ ጢሞ.3፡12/፡፡ አንድ ታጋይ በጦርነት ጊዜ ገላዉን ታጥቦ፣ ወይንን አውርዶ ለመጠጣት፣ ፍሪዳውን አርዶ ለመብላት አይቀመጥም፡፡ እንዲኽ ያለ ሥራ የታጋይ ተግባር አይደለም፤ የሰነፎች ነው እንጂ፡፡ የሀገር የድንበር ጠባቂ ወታደር እግሩን ለጠጠር፣ ግንባሩን ለጦር ሰጥቶ የቀኑን ሐሩር የሌሊቱን ቁር ታግሦ መከራ ይቀበላል እንጂ በጦርነት ጊዜ እንዲኽ በስንፍና አይቀመጥም፡፡ ጊዜው የውጊያ፣ የኀዘን፣ የመድማት ጊዜ ነውና እንዲኽ ያለ የሰነፎችን ሥራ ለመሥራት አያስብም፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ምን እንደሚል እስኪ አድምጡ፡- “ነፋስን እንደሚጎስም ኹሉ እንዲኹ አልጋደልም” /1ኛ ቆሮ.9፡26/፡፡ ስለዚኽ ልጆቼ! በዚኽ ዓለም ተድላ ደስታ ማግኘት የእኛ ባሕርይ አይደለም ብዬ እነግራችኋለኁ፡፡ ይልቁንም የማያልፈውን ክብር እናገኝ ዘንድ በውጊያ ውስጥ እንዳለ ወታደር ኀዘን፣ መከራ ቢገጥመን እስከ መጨረሻዋ ሕቅታ ድረስ መጽናት ይገባናል፡፡ አኹን

በሰመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን                               "ወጣትነትና ጾም" *  * * -- ቅድስት ቤተክርስቲያን ማንኛዉም ክርስቲያን የጾም ና የፀሎት ሕይወት እንዲኖረው ሥርዓትን ደንግጋ በጾም የሚገኘውን ጥቅም እየዘረዘረች ዘወትር ታስተምራለች ። -- የወጣትነት ዕድሜ የጉልበት ፣ የኃይል ፣ የብርታት ፣ ያሰቡትን የመፈፀምያ፣ አሸናፊነትን ለመጎናጸፍ ሩጫ የሚበዛበት ዕድሜ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ "የጉብዝና ጊዜ " ብሎ እንዲጠራው። " የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጕብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ፤ ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ፤ "እንዲል (መጽሐፈ መክብብ 12፥1) ለዛም ነው አበው ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋ መካከል አንዱ በሆነው በእሳት መስለው "የእሳትነት እድሜ" ብለው የሚጠሩት። -- ይህ የጉብዝና ዕድሜ ለዓለምም ለመንፈሳዊ ነገርም ሊውል ይችላል፤ ዓለምን ወድዶ፣ ስሜቱን አዳምጦ ገንዘብ ብቻ እያሳደደ ለስጋዊ ነገር ብቻ የጎበዘ እንዳለ ሁሉ ሥጋዊ ፍላጎቱን ገትቶ ፣ ገንዘቡንና ጊዜውን ሰውቶ፣ በመንፈሳዊ ምግባራት እየተጋ ፣በእምነት ፈጣሪውን አያስደሰተ ፣ አባቶቹን እያከበረ ይህን የእሳትነት ዕድሜውን የሚሻገር ብዙ አለ። *  * ** --- ይህን የእሳትነት ዕድሜ በብልሀትና በጥበብ ከመሻገርያ መንገዶች አንዱ ጾም ነው። እንዳንጾም ፈተና የሚሆንብን ደግሞ ስለ መብል ማሰብ ሆድን መውደድ አንዱ ነው። ቅዱስ ጳውሎስ ሆዳቸውን ስለሚወዱና ስለ መብል ሲሉ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ለሚጥሱ ለሚያቃልሉ ሰዎች " መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው።" ብሎአቸዋል (ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 3፥19) በተጨማሪ /ጾም አይጠቅምም፣ ዋናው ልብ ነው ፣ዓሳ ብንመገብ ችግር የለውም / እያሉ ስለ ወንጌል ሳይሆን ለከርሳቸው ጠበቃ ስለሚቆሙ ሰዎች " እንዲህ ያሉት ለገዛ ሆዳቸው እንጂ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ አይገዙምና፥ በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግርም ተንኮል የሌለባቸውን ሰዎች ልብ ያታልላሉ።"  ይላል። (ወደ ሮሜ ሰዎች 16፥18)      ** --- የወጣትት ዕድሜ የሩጫ የድካም ጊዜ ነውና አንዳንድ ወጣቶች ለምን አትጾምም ተብለው ሲጠየቁ /ሥራ ላይ ስለሆንኩኝ ፣ ስለሚደክመኝ፣ ቦታው ስለማይመች አልጾምም ብለው/  ወዘተ ተራ ምክንያቶችን እያቀረቡ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ጥሶ በጠዋቱ መመገብ ፋሽን በሆነበት በዚህ ዘመን እንደ ቅዱስ ያሬድ ቃል አንደበቱን ከሀሜት ከስድብ ከልክሎ፣ ዐይኑን ከፉ ከማየት ገትቶ፣ ጆሮውን ክፉ ከመስማት ከልክሎ ፣እጁንም ያልተፈቀደለትን ከመዳሰስ አቅቦ፣ እግሩንም ወደ ኃጢአት ስፍራ ከመጓዝ ከልክሎ፣ ሥርዓተ ቤተርክስቲያንን አክብሮ ቢችል አቅሙ እስከፈቀደው ባይችል እስከ 9 የሚጾም፣ ባለው ሰዓት የስርዓተ ቅዳሴ ተካፋይ የሆነ ፣ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋውን የሚበላ ደሙንም የሚጠጣ ወጣት በትክክልም ይህን የእሳትነት ዕድሜ የሚያሻግረውን መንገድ ይዞአል ያሰኛል። ** አንድ የሚጾም ሰው የሥጋ ድካም ግድና አስፈላጊ ነው። ጾም ሥራን አይከለክልም ሥራም ጾምን አይከለክልም ቤተክርስቲያን በጾም ሥራ አትስሩ የሚል አስተምህሮ የላትም። እንደውም ሥጋን ለማድከም አመቺ ነው በገዳም ያሉ አበው በጾማቸው አዘውትረው ይሰራሉ ለባልንጀሮቻቸው ይታዘዛሉ ሥራ ቢጠፋ ቆባቸውን ቀደው ከእንደገና ይሠፋሉ ይህም በሥራ መፍታት ውስጥ የሚከሰተውን የዲያብሎስ ፈተና ለማሸነፍ ነው። በተጨማሪ ላለመጾም ቦታ የአካባቢ ሁኔታ ምክንያት ከቶ አይሆንም ለምሳሌ በአድዋ ድል ጀግኖች አባትና እናቶቻችን በዛ ጦርነት ውስጥ እንኳን ሁነው በመጾማቸው ከፈጣሪ ኃይል እንደሚያገኙ በማመን እየጾሙ ይዋጉ ነበር እንጂ ጮማውን እንቁረጥ ወይኑን እንጎንጭ አላሉም በሀገርና በሃይማኖት ላይ የመጣ ጠላት ያለ ጾምና ጸሎት ሊወጣ አይችልምና። *   **** --- የወጣትነትድሜ የሥጋ ፍትወታት የሚበረቱበት በተለይም ንፅህናችንን እንድናጎድፍ የዝሙት ፆር የሚበረታበት ስለሆነ በማስተዋል ሊያልፉት የሚገባ ጊዜ ነው። ታድያ ለዚህ መድኃኒቱ ጾም ፀሎት ነው። ራሱን ለጾም የሚያተጋ ወጣት እርጋታን ዝምታን ይማራል ገንዘቡም ያደርጋል፤ ለዛ ነው አበው "ጾም ትፌውስ ቁስለ ነፍስ ወታጸምም ኩሉ ፍትወታተ ዘሥጋ ትሜሕሮሙ ለወራዙት ጽሙና"  ትርጓሜ (ጾም የነፍስን ቁስል ትፈውሳለች የሥጋን ፍትወታት /ፆር/ ታስታግሳለች ለወጣቶችም ከልብ የሆነ ዝምታን ታስተምራለች) /የኪዳነ ምሕረት ዚቅ / በማለት የተናገሩት። --- የሰውነት ቅርጹን ለመጠበቅ ያገኘውን እያግበሰበሰ ጾም ሳይል አርብ ሮብ ሳይተው ከሚመገብ ወጣት ይልቅ በሃይማኖት ሁኖ ሥርዓት እየጠበቀ እየጾመ ጥሬ የሚቆረጥም ወጣት እንደ ሦስቱ ሕፃናት ደምግባቱ ያማረ ልምላሜ ሥጋ ልምላሜ ነፍስ ያልተለየው ይሆናል። --- በአጠቃላይ ጾም በወጣትነት ይበልጥ ልንለማመደውና ልንተገብረው የሚገባ መንፈሳዊ ሕይወትን የሚያሳድግ የወጣቶች በሽታ ለተባለው ዝሙት ሁነኛ መድኃኒት ነው።/ዮሐንስ 2 ትርጓሜ/                                                         ጾሙን ከፈጣሪ የምንታረቅበት ያድርግልን። ሚክያስ ግዛቸው

ሸማግሌዎቹን ከፈጣሪያችን ቤት ሰብስባችሁ በአንድነት ሁናችሁ ወደ እግዚአብሔር ጩሁ / ለምኑ/ ብሏል፡፡ ኢዮብ ምዕ.1፥11፣ 2፣12፣15-16 ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም “በጾም፣ በንጽሐና ተወስናችሁ እግዚአብሔርን አገልግሉ” 2ቆሮ.6፥4-6፡፡ ጾም ከሌለ ወይም ተገቢ ካልሆነ ጌታችን በምትጾሙበት ጊዜ እንደ ግብዞች አትሁኑ ስለ ጽድቅ የሚራቡ የሚጠሙ ንዑዳን ክብራን ናቸው ለምን አለ? ማቴ.5፥፣6፣16፡፡ ነቢዩ ዳዊትም ሰውነቴን በጾም አሳመምኳት በቀጠና፣ በሰልት አደከምኳት ለምን አለ? መዝ.34፥68፣ ት.ዳን.9፥3-4፣ ሐዋርያት ሙሸራውን ከነሱ ለይተው የሚወስዱበት ጊዜ ይመጣል ያን ጊዜ ይጾማሉ ያለውን የጌታን ቃል መሠረት በማድረግ ክርስቶስ በሞት ከተለያቸው በኋላ ጾመዋል፡፡ ጾምንም ሠርተዋል የሐዋ. ሥራ 13፥3፡፡ ሠለስቱ ምዕትም ሐዋርያት የጾሙትንና እንዲጾም የወሰኑትን መጾም ይገባል ብለው ቤተ ክርስቲያን የተቀበለቻቸው አጽዋማት እንዲጾሙ መወሰናቸው ይህን የጌታ ቃል መሠረት በማድረግ ስለሆነ፣ የትእዛዝ መሆኑን ተገንዝበን መጾም አለብን፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሠራዔ ሕግ እንደመሆኑ አርባ ቀን አርባ ሌሊት ጾመ እንጂ እርሱ ሳይጾም ጹሙ አላለንም። ማቴ.4፥2 ምንጭ – ጾምና መንፈሳዊ ሕይወት

ሚክያስ ግዛቸዉ: ለሠራሁት ከባድ ኃጢአት ስንት ዓመት ንስሐ ልግባ? ❀❀❀❀❀❀❀ ☞ ይህ የኃጢአት ሸክም የከበደን፣ ወደ እግዚአብሔር መመለስ የምንሻ፣ የእኛ በደል በእድሜ ዘመናችን ልክ ንስሐ ብንገባ መመለስና ሊደመሰስ የማይቻል የመሰለን የአብዛኞቻችን ጥያቄ ነው፡፡ እስኪ የአባ ባውሚንን ምክር እንስማ፦ ❀❀❀❀❀ ☞ " ከመነኮሳት አባቶች አንዱ ወደ አባ ባውሚን ቀረቦ አባቴ ታላቅ ኃጢአትን ሠርቻለሁና ስለሱ ሦስት ዓመት ንስሐ ልገባ አስቤያለሁ (እወዳለሁ) አላቸው፡፡ አባ ባውሚንም ይህን ሰው ልጄ ሆይ ይህስ ብዙ ነው አለው፡፡ ያም መነኩሴ መልሶ አንድ ዓመትሳ ይበዛልን አለ፡፡ ሽማግሌው አባ ባውሚንም መልሶ ይህም ብዙ ነው አለው፡፡ አብረው ያሉ መነኮሳትም አርባ ቀንሳ ይበዛልን? አሉ፡፡ ሽማግሌው መነኩሴም መልሶ ይሄም ብዙ ነው አላቸው፡፡ አባ ባውሚን ንስሐ ልገባ እወዳለሁ ወዳለው መነኩሴ በመመልከት ሰው በፍፁም(በቁርጥ) ልቡ ንስሐ ከገባ (ከተጸጸተ) ወደ ቀድሞው ኃጢአቱ ለመመለስ ካላሰበ (ካልተመለሰ) እግዚአብሔር በሦስት ቀን ንስሐውን ይቀበለዋል አለው፡፡ ❀❀❀❀❀❀❀❀ ✔ እኛም በደላችንን ይቅር እንዲለን በፍፁም ንስሐ እንመለስ ነብዮ ኢዮኤል፦ " አሁንስ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ በፍጹም ልባችሁ፥ በጾምም፥ በልቅሶና በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ። ልባችሁን እንጂ ልብሳችሁን አትቅደዱ፤ አምላካችሁም እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ፥ ቁጣው የዘገየ፥ ምሕረቱም የበዛ፥ ለክፋትም የተጸጸተ ነውና ወደ እርሱ ተመለሱ። " እንዲል፡፡ ት ኢዮኤል ፪፥፲፪-፲፫ ❀❀❀❀❀❀ ✔ የነነዌ ሕዝቦች ፍፁም በንስሐ ወደ እግዚአብሔር በመቅረባቸው በሦስት ቀን ውስጥ ሊመጣባቸው ያለውን መቅሰፍት እንዲመለስ አድርገውታል፡፡ በቀኑ ማድረግ ያለባቸውን ስላከናወኑ፡፡ ✔ ዛሬም ከፊት ለፊታችን በፍፁም ንስሐ ወደ እግዚአብሔር ልንመለስ የምንችልባቸው ሁለት ወራት (አስራ ስምንት ሦስት ቀናት) አሉልን ኃጢአትን በመጥላት፣ በንስሐ፣ በፍፁም መመለስ፣ ለስጋወ ደሙ በመትጋት፣ ወደ ኃጢአት ባለመመለስ በመንፈሳዊ ትሩፈትን በመፈፀም ልንቀበለው ይገባል፡፡ ❀❀❀❀❀❀                    መልካም ጾም፡፡                   ✍️ሚክያስ ግዛቸው ዘወረደ በዐቢይ ጾም ውስጥ ያሉት ሳምንታት ስምንት ስያሜዎች አሏቸው። እነርሱም ዘወረደ፣ቅድስት፣ምኩራብ፣መፃጉዕ፣ደብረዘይት፣ ገብር ኄር፣ኒቆዲሞስ እና ሆሣዕና ናቸው። የዐቢይ ጾም የመጀመርያው ሳምንት ዘወረደ ይባላል።ዘወረደ ማለት ትርጕሙ ‹ከሰማየ ሰማያት የወረደ› ማለት ነው፡፡ ከሰማየ ሰማያት የወረደውን፣ ከድንግል ማርያም የተወለደውን በጥንት ስሙ ወልድ፣ ቃል በኋላ ስሙ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ አማኑኤል የተባለውን ሰው የኾነውን አምላክ ለማመስገን ርደቱን (ከሰማየ ሰማያት መውረዱን) ለመዘከር የሚጾም ጾም ነው፡፡ ጌታችን ጾመ ከማለት አስቀድሞ ከሰማየ ሰማያት መውረዱን ከድንግል ማርያም መወለዱን መናገር አስፈላጊ ነውና የመጀመሪያው ሳምንት ‹ዘወረደ› ተብሏል፡፡ ‹‹አንተ በሰማይ ወአንተ በምድር ወአንተ በባሕር ወአንተ በየብስ» አንተ በሰማይ አለህ፤ በምድር በባሕርም በየብስም አለህ፤›› የተባለውን በሰማይ በምድር ምሉዕ የኾነውን አምላክ ‹ወረደ፤ መጣ› ብሎ መናገር ‹ሰው ኾነ› ማለት ነው፡፡ሰው ኾኖ መገለጡን ለማስረዳት ነው እንጂ መውረድ መውጣት የሚባሉ ቃላት በዅሉ ምሉዕ ለኾነው መለኮት አይስማሙትም፡፡ ቃላቱ ሰውኛ አነጋገርን የሚያመለክቱ ናቸውና፡፡ መተርጕማን አበው ‹‹‹ዘወረደ› ማለት ‹ሰው የኾነ› ማለት ነው›› ብለው ይተረጕማሉ፡፡ አምላካችን ሰው ከኾነ በኋላ ‹መጣ፤ ሔደ፤ ወረደ፤ ዐረገ› የሚሉ ቃላት ይስማሙታል፡፡ ምልዓቱን ሳይለቅ በሰው አካል ተወስኖ ታይቷልና፡፡ ስለዚህ ‹ወረደ› እግዚአብሔር ሰው ኾኖ መገለጡን፤ ‹ዐረገ› ደግሞ የሰውነቱን ሥራ መፈጸሙን ያሳያል፡፡ ዐረገ ስንልም ቀድሞ በሰማይ የለም ለማለት አይደለም፤ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመለኮቱ በዓለሙ ዅሉ ምሉዕ ነውና፡፡ ይህ የመጀመሪያው ሳምንት ጾመ ሕርቃልም ይባላል፡፡ በ714 ዓ.ም.ሕርቃል / ኤራቅሊየስ/ የቤዛንታይን ንጉሥ ነበረ፡፡ይህ ሳምንት በስሙ የተጠራበት ምክንያት በዘመኑ ፋርሶች ኢየሩሳሌምን ወርረው የጌታችን መስቀል ማርከው ወስደው ነበር፡፡ እርሱ ወደፋርስ ዘመቶ መስቀሉን ከእነርሱ ነጥቆ ይዞ ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሷል፡፡ ሕርቃል ከፋርሶች ጋር ከመዋጋቱ በፊት ሐዋርያት በሲኖዶሳቸው ነፍስ የገደለ ሰው እስከ እድሜ ልኩ ይጹም ብለው ሥርዓት ሠርተዋልና ጾሙን ፈርቶ ስለነበር በኢየሩሳሌም የነበሩ ምእመናን አሳቡ ደግፈው “አንተ ጠላታችንን አጥፋልን ፣መስቀሉን አስመልስልን እንጂ የአንድ ሰው እድሜ ቢበዛ ሰባ ሰማንያ ነው ፡፡ጾሙን አምስት አምስት ቀን ተከፋፍለን እኛ ተከፋፍለን እንጾምልሃለን፡፡”ብለው ጾመውለታል፡፡ይህንን መሠረት በማድረግ ያላወቁት አንድ ጊዜ ጾመው ትተውታል፡፡ ያወቁት ግን ቀድሞም ሐዋርያት ጾመውታል ብለው ሥርዓት አድርገው በዓመት በዐቢይ ጾም መጀመሪያ ላይ ጾመ ሕርቃል ያሉ የሚጾሙት ሆነዋል፡፡ስለዚህ ቤተክርስቲያናችን ይህንን መሠረት በማድረግ በጌታችን ከመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጾም የመጀመሪያውን ሳምንት ጾመ ሕርቃል በሚል ስያሜ እንዲጾም አድርጋለች፡፡ /መጋቢት 10 ስንክሳር ይመልከቱ፡፡/ የቤተ ክርስቲያናችን ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ፣ በዘወረደ ጾመ ድጓው ሰንበት ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን፣ ሕይወት ላለው ነገር ሁሉ ጸጥታና ሰላም የሰፈነባት የዕረፍት ቀን ስለመሆኗ “አዘዞ እግዚአብሔር ለሙሴ ወይቤሎ ሰብዕከ ወላህምከ ወኲሉ ቤትከ ያዕርፍ በሰንበት” ዘፀ.20፥10፣23፣12፣ ጾመ ድጓ፣ እግዚአብሔር ሙሴን ሕዝብህ የከብትህ መንጋህ ቤተሰብህ ሀሉ በሰንበት ቀን ከድካማቸው ይረፉ በማለት አዘዘው ይላል፡፡ በዚህም ዘመነ ጾም፣ ወይም ጾመ ሙሴ ይባላል፡፡ በጾመ ድጓው ዘወረደ እየተባለ የሚታወቀው፣ በጾመ አርባው ወቅት በተለይም በመጀመሪያው ሳምንት የሚገኘው ያሬዳዊ ድርሰት በነግህ በሠለስት፣ በቀትርና በሠርክ እንዲሁም ቅዳሜና እሑድ በሌሊት የሚዘመር ነው፡፡ በውስጡም የያዘው ፍሬ አሳብ፣ የጾምን፣ የጸሎትን፣ የምጽዋትንና የፍቅርን ጠቃሚነት አጉልቶ የሚያስተምር ነው፡፡ በዚህ በጾም ወቅት በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት በአብዛኛው ከቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች ውስጥ የሚዘመረው ምዕራፍ የተባለው ነው፡፡ ምዕራፍ የተባለበት ምክንያትም በየመዝሙራቱ መሀል ሃሌታና ድጓ እያስገባ ለመዝሙሩ ማረፊያ ስላበጀለት በዚህ ምክንያት ምዕራፍ የሚል ስያሜ ሊያገኝ ችሏል፡፡ ይህ የዜማ መጽሐፍ በሁለት ታላላቅ ክፍሎች ይከፈላል፡፡ ይኸውም የዘወትር ምዕራፍና የጾም ምዕራፍ በመባል ይታወቃል፡፡የዘውትር ምዕራፍ የሚባለው በዓመቱ ውስጥ ባሉት ቀናት ውስጥ ሳምንታትና በዓላት ሁል ጊዜ በአገልግሎት ላይ የሚውል ሲሆን፣ የጾም ምዕራፍ የሚባለው ደግሞ በጾመ አርባ ብቻ ለአገልግሎት የሚውል ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በዐሥሩ ምህላት አርዕስተ ምህላ በዚሁ ክፍል ይካተታል፡፡ የምዕራፍ ቅንብር ከመዝሙረ ዳዊት፣ ከድጓና ከጾመ ድጓ ጋር የተቀናጀ ነው፡፡ የትምህርት አሰጣጡም እንደ ድጓው ወይም እንደ ዝማሬ መዋሥዕቱ መጽሐፍ ተዘርግቶ ሳይሆን በቃል የሚጠናና የሚወሰን ነው፡፡ ስለሆነም ምዕራፍን ለመማር 150 መዝሙረ ዳዊትን፣ ከነቢያት 15 ምዕራፎችንና 5 መኃልያተ ሰሎሞንን በቃል ሸምድዶ መያዝ ይጠበቅበታል፡፡ ወይም ግድ ነው፡፡ጾምን መጾም የፈቃድ ብቻ ሳይሆን የትእዛዝም ነው፡፡ በዘመነ ብሉይ ነቢዩ ኢዩኤል “ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ” ጾምን ያዙ አጽኑ ምህላንም ዐውጁ

ማኅበረ ቅዱሳንና ሀገር አቀፍ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ያዘጋጁት የ2015 ዓ.ም የከፍተኛ ት/ተቋማት ገቢ ተማሪዎች ሽኝት መርሐ ግብር ተከናወነ። ወደ ከፍተኛ ት/ተቋማት የሚገቡ ተማሪዎች ትም
+4
ማኅበረ ቅዱሳንና ሀገር አቀፍ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ያዘጋጁት  የ2015 ዓ.ም የከፍተኛ ት/ተቋማት ገቢ ተማሪዎች ሽኝት መርሐ ግብር ተከናወነ። ወደ ከፍተኛ ት/ተቋማት የሚገቡ ተማሪዎች ትምህርታቸውን በሚከታተሉባቸው ጊዜያት ኦርቶዶክሳዊነታቸውን በማጠንከር እና በመንፈሳዊነታቸው በመበርታት ተምስጋኝ መሆን እንደሚገባቸው ብፁእ አቡነ ፊሊጶስ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ሊቀ ጳጳስ ገልጸዋል። ብፁእነታቸው ይህን የተናገሩት በ2015 ዓ.ም ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን ለመሸኘት እና አደራ ለመስጠት በተዘጋጀ መርሐ ግብር ላይ በመገኘት ሲሆን መርሐ ግብሩ በማኅበረ ቅዱሳን እና በሀገር አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አማካኝነት የተዘጋጀ ነው። የካቲት 11/2015 ዓ.ም በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ አዳራሽ በተዘጋጀው በዚህ መርሐ ግብር ላይ ነዋሪነታቸው በአዲስ አበባ የሆነ ኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በዕለቱ የተለያዩ መርሐ ግብሮች የቀረቡ ሲሆን ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ሁለት ተማሪዎች የላፕቶፕ ኮምፒዩተር ስጦታ ተበርክቶላቸዋል። እነዚህ ተማሪዎች ወደተመደቡባቸው ተቋማት ሲሄዱ ከትምህርታቸው ጎን ለጎን መንፈሳዊ ሕይወታቸውንም መርሳት እንደሌለባቸው የተገለጸ ሲሆን ማሳያ እንዲሆንም በተለያየ ጊዜ ከግቢ ጉባኤያት የተመረቁ እና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ አባላት ልምዳቸውን እንዲያካፍሉ ተደርጓል።

አሁን ጀምሯል

"ልዪ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቁጠሩት" (ያዕቆብ መልዕክት1፥2-3)   ያዕቆብ  ለተበተኑ አስራ ሁለት ወገኖቹ የፃፈው ድንቅና ተገቢ ምክር ነበር።ቅዱስ ያዕቆብ መፈተንን እንደ መሉ ደስታ እንቀበለው ዘንድ በአፅንኦት ይነገረናል "የዕምነታችሁ መፈተን ትዕግስትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ፤ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቁጠሩት"ብሎ ፅፎልናል። ማንም ሰው በትክክል ለመስራቱ  እና በፅናትና በታማኝነት ለማገልገሉ የልፋቱን ዋጋና ፍሬ የሚያገኝበት መስፈርት ወይም መመዘኛ ፈተና ያስፈልገዋል። በዓለም የትምህርት ሂደት ውስጥም ያለፈተና ከክፍል ወደክፍል መዘዋወር አይኖርም። ፈተና የተማርነውን ማወቃችንን እና  ለቀጣዩ ክፍል መብቃታችንን የሚያረጋግጥ ከአንደኛው ዝቅታ ወደ ሌላኛው ከፍታ የሚያደርሰን መመዘኛ ነው። ፈተና በመንፈሳዊ ህይወትም ጎልቶ ይታያል ይህንንም ሲያፀናልን ጌታችንም በወንጌሉ "በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ"ብሎናል በመንፈሳዊ ህይወት ውስጥ ዕምነታችንን ሳይቀር የሚፈታተን ሀለወተ እግዚአብሔርን ሳይቀር እንድንጠራጠር አርጎ ሰይጣን ዳቢሎስ ይፈትናል ባአገልግሎታችን መሀል እየተገኘ መንገድን ሊያስተን ባላንጣችን የሆነው ዲያቢሎስ ይፈታተናል። ከበጎው መንገድ እንድንወጣ በልዩ ልዩ ፈተና ሰይጣን የሞገተናል።እንደ ዴማስ ዓለምን ወደን ወደኋላ እንድንቀር ዓለምን የአይን አዋጅ አርጎ ያሳየናል። አሊያም እንደ አዳምና እንደ ሄዋን ያልታዘዝነውን እንበላ ዘንድ ሰይጣን ይፈትነናል። እንደ ኢዮብም ያለንን ሁሉ አሳጥቶ እግዚአብሔርን ሰድበን እንድንሞት ዲያቢሎስ ይሸነግለናል። በመንፈሳዊ ህይወት በውስጥም በውጪም መፈተን አይቀርም።ነገርግን መፈተናችን ለበጎ ነው።በፈተና ውስጥ እራስን ማየትና ዋጋን ማግኘት አለና መፈተናችንን እንደ ሙሉ ደስታ በመቁጠር ማለፍ አለብን። ይህንንም ሲያፀናልን"በፈተና የሚፀና ሰው የተባረከ ነው"ብሎ ነገሩን ይዘጋልናል። ዛሬ በፈተና ውስጥ ማለፍ ነገ ለመባረክ መሆኑን ይገልፅልናል። ዮሴፍ በግፍ በውንድሞቹ ቢሸጥም በግዞት በፈተና ቢሰቃይም በአህዛብ መንድር ነግሶ በረከትን አግኝቷል።ፃድቁ አብርሃምም ሀገሩ እና ቤተሰቡን ጥሎ ቢሰደድም እግዚአብሔር አምላክ ዘሩን ባርኮለት በፈተናውስጥ በረከት እንዳለ በእምነት ውሰጥ ደሞ ፈተና እንዳለ አሳይቶናል። ዛሬም ሰይጣን ዲያቢሎስ ፆሩን አብዝቶ በብዙ ፈተናዎች እኛን ሊጥልና የዕምነታችንን ልክ ሊፈታተን በዙሪያችን ያንዣብባልና ፈተና ሲገጥመን የአባታችን ቅዱስ ያዕቆብ መልዕክት ልናስታውስ ይገባል "የዕምነታችሁ መፈተን ትዕግስትን እንዲያደርግ ላችሁ አውቃችሁ፤ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ መሉ ደስታ ቁጠሩት" ፈተናን በማማረር ሳይሆን እንደሙሉ ደስታ ቆጥረን በፈተና ለመባረክ እንኑር ።   "በፈተና የሚፀና ሰው የተባረከ ነው።" ቤተልሔም