ru
Feedback
ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ

ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

Открыть в Telegram

ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

Канал ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ  (@computer_android_tricks) является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 11 983 подписчиков, занимая 17 269 место в категории Образование и 2 838 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 11 983 подписчиков.

Согласно последним данным от 04 марта, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -107, а за последние 24 часа — 0, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 0%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает N/A% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 0 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 0 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 0.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 05 марта, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Образование.

11 983
Подписчики
Нет данных24 часа
-337 дней
-10730 день
Архив постов
📌 #በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ በደማቸው እንዳለ ከተረጋገጠው 56 ሰዎች ውስጥ 23ቱ የመጨረሻ የጉዞ በረራቸው ዱባይ ነው። #ዱባይ የምስራቅ አፍሪካ ብቸኛዋ የኮሮና ቫይረስ ማምረቻ እና ማከፋፈያ ማህበር ብያታለው። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#ዶናልድ ትራምፕ ለዶክተር ቴድሮስ ምላሽ ሰጡ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በዶክተር ቴድሮስ አድኃኖም ላይ የከፈቱትን የቃላት ጦርነት ቀጥለውበታል። ዶ/ር ቴድሮስ ትናንት "ጤናን ወደ ፖለቲካ አንጠምዝዘው" ማለ
#ዶናልድ ትራምፕ ለዶክተር ቴድሮስ ምላሽ ሰጡ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በዶክተር ቴድሮስ አድኃኖም ላይ የከፈቱትን የቃላት ጦርነት ቀጥለውበታል። ዶ/ር ቴድሮስ ትናንት "ጤናን ወደ ፖለቲካ አንጠምዝዘው" ማለታቸውን ተከትሎ ትራምፕ ዋይት ሐውስ ውስጥ በሚካሄደው ዕለታዊ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ምላሽ ሰጥተዋል። ዶክተር ቴድሮስ "ፖለቲካውን ትተን ወረርሽኙን ለማቆም ካልሰራን ሬሳ ሳጥን ማብዛት ነው" ስለማለታቸው ምላሽ የሰጡት ትራምፕ…"ምን ማለታቸው ነው ተጨማሪ ሬሳ ሳጥን ሲሉ…መጀመርያ እሱ (ዶ/ር ቴድሮስ) አገለግለዋለሁ ለሚለው ሕዝብ ኃላፊነቱን መወጣት ነበረበት።" "ሁሉም ሥራው ቻይናን መሠረት ያደረገ ነው፤ ድንበር አትዝጉ፣ ከሰው ወደ ሰው አይተላለፍም ሲል ነበረ፤ ድንበር አትዝጋ ቢለኝም እኔ ግን ዘግቻለሁ…(ከዓለም ጤና ድርጅት በተቃራኒው ስለሄድን ነው ሰው ማዳን የቻልነው)" ብለዋል ትራምፕ። ትራምፕ ለዓለም ጤና ድርጅት የሚያዋጡትን 400 ሚሊዮን ዶላር፣ ቻይና ከምትሰጠው 40 ሚሊዮን ዶላር ካወዳደሩ በኋላ ይህንን ፈንድ የመስጠቱን ጉዳይ እንደሚያጤኑት ተናግረዋል። በተመሳሳይ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው ማይክ ፖምፔዎ "ለዓለም ጤና ድርጅት የምንሰጠውን ገንዘብ እናጤነዋለን" ብለዋል ዛሬ፡፡ 🔸 ዜናው የ BBC ነው ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#ኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ህይወቱ ያለፈ አስከሬን ወደ አገር ውስጥ እንዳይገባ ከለከለች። የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን እንዳስታወቀው የኮሮና ቫይረስ መስፋፋትን ተከትሎ በውጭ አገራት በቫይረሱ ምክንያት ህይወቱ ያለፈ አስከሬን ወደ አገር ወስጥ እንዳይገባ ታግዷል።ባለስልጣኑም ወደ በኢትዮጵያ አየር ክልል የመብረር ፈቃድ ላላቸው 14 አየር መንገዶች አስከሬን ወደ ኢትዮጵይ ይዘው እንዳይገቡ ማገዱን ለኢትዮ ኤፍ ኤም በላከው መግለጫ አስታውቋል።እገዳው የኢትዮጵያ አየር መንገድንም እንደሚመለከት ባለስልጣኑ አስታውቋል። Via Ethio FM

#በኢትዮጵያ አንድ (1) ተጨማሪ ሰው በቫይረሱ ተይዟል። አጠቃላይ በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 56 ደርሷል። 📌የታማሚው ሁኔታ ፦ ዛሬ በቫይረሱ መያዙ የተረጋገጠው ግለሰብ የ43 ዓመት ካናዳዊ በትውልድ ደግሞ ኢትዮጵያዊ ሲሆን ከካናዳ ወደ ዱባይ ከዛም ከዱባይ ወደ ኢትዮጵያ የመጣና በልይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ ነው።

📌ኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ1.5 ሚሊየን ተሸገረ። ከዚህ አሃዝ መካከል ከ940 ሺህ በላይ ቁጥር የተመዘገው በአምስት ሃገራት ሲሆን ሃገራቱም አሜሪካ፣ ስፔን፣ ጣሊያን፣ ጀርመንና ፈረንሳይ ና
📌ኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ1.5 ሚሊየን ተሸገረ። ከዚህ አሃዝ መካከል ከ940 ሺህ በላይ ቁጥር የተመዘገው በአምስት ሃገራት ሲሆን ሃገራቱም አሜሪካ፣ ስፔን፣ ጣሊያን፣ ጀርመንና ፈረንሳይ ናቸው። ከፍተኛ የቫይረሱ ስርጭት እየተመዘገበባት የምትገኘው አሜሪካ 435 ሺህ 160 ዜጎቿ በኮቪድ-19 መያዛቸውን ሪፖርት አድርጋለች፡፡ አሜሪካ በ2 ሚሊየን 226 ሺ 116 ዜጎቿ ላይ ባደረገችው ምርመራ ነው እነዚህ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ያረጋገጠችው፡፡ በዚሁ ቫይረስ ሳቢያ 14 ሺህ 797 ዜጎቿን በሞት በመነጠቅም ከጣሊያን በመቀጠል በርካታ ሞት የተመዘገበባት ሃገር ሆናለች፡፡ ጣሊያን በበኩሏ 139 ሺህ 422 ሰዎች በቫይረሱ የተያዙባት ሲሆን 17 ሺህ 669 ዜጎቿን ቀብራለች፡፡ ስፔንም ከአሜሪካ በመቀጠል በርካታ ዜጎቿ በበሽታው የተያዙባት 148 ሺህ 220 ታማሚዎችን መዝግባለች፡፡ እስካሁን 88 ሺህ 565 ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን 331 ሺህ 354 ታማሚዎች ደግሞ ከበሽታው ማገገም ችለዋል። Via #Walta_Tv ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከስፔን በለጠ። አሜሪካ እንደተባለውም የከፋውን ጊዜ እያስተናገደች ነው። በአሁን ሰዓት በአሜሪካ በቫይረሱ የሞቱ ሰዎች 14,797 ደርሰዋል፤
በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከስፔን በለጠ። አሜሪካ እንደተባለውም የከፋውን ጊዜ እያስተናገደች ነው። በአሁን ሰዓት በአሜሪካ በቫይረሱ የሞቱ ሰዎች 14,797 ደርሰዋል፤ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥርም ከ435,000 በልጧል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለአለም የጤና ድርጅት ድጋፍ እንደሚያደርጉ አስታወቁ ፡፡‼️ ትራምፕ ተቋሙን ቢተቹም ማክሮን ግን በአለም የጤና ድርጅት ላይ እምነት እንዳላቸዉ እና ሀገራቸዉ ድ
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለአለም የጤና ድርጅት ድጋፍ እንደሚያደርጉ አስታወቁ ፡፡‼️ ትራምፕ ተቋሙን ቢተቹም ማክሮን ግን በአለም የጤና ድርጅት ላይ እምነት እንዳላቸዉ እና ሀገራቸዉ ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል በመግለጽ ፤ በዚህ ዉስጥ ለተንፀባረቀው የቻይናና አሜሪካ የንግድ ጦርነት ለመመልከት ፍቃደኛ አለመሆናቸዉን ከኢልሲል ቤተ መንግስት የወጣዉ መረጃ አመላክቷል። የፈረንሳይ ሁለት ዶክተሮች የኮሮና መድኃኒት አፍሪካዉያኑ ላይ ይሞከር ማለታቸዉ የፈረንሳይን መንግስት ፖሊሲ የማይወክል አስተያየት እንደሆነም ማክሮን ተናግረዋል፡፡

#የአፍሪካ መሪዎች ዶ/ር ቴድሮስ አድኃኖምን ከትራምፕ እየተከላከሉ ነው ❗️ ✅የተለያዩ የአፍሪካ አገራት መሪዎች ዶ/ር ቴድሮስን #እየደገፉ ነው✅ ⚡️ትራምፕ ማክሰኞ እለት፤ የዓለም ጤና ድርጅትን “በ
#የአፍሪካ መሪዎች ዶ/ር ቴድሮስ አድኃኖምን ከትራምፕ እየተከላከሉ ነው ❗️ ✅የተለያዩ የአፍሪካ አገራት መሪዎች ዶ/ር ቴድሮስን #እየደገፉ ነው✅ ⚡️ትራምፕ ማክሰኞ እለት፤ የዓለም ጤና ድርጅትን “በዋነኛነት በአሜሪካ ቢደጎምም፤ በጣም ለቻይና የወገነ ድርጅት ነው” ሲሉ ተደምጠዋል። ለድርጅቱ ድጋፍ ማድረጌን ላቆም እችላለሁ ሲሉም አስፈራርተዋል። ⚡️የሩዋንዳው ፕሬዘዳንት ፖል ካጋሜ ዶ/ር ቴድሮስን ከደገፉ መሪዎች አንዱ ናቸው። ⚡️የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሞሳ ፋኪ ማሐማት ከዓለም ጤና ድርጅት ኃላፊው ጎን ነኝ ማለታቸውን ተከትሎ፤ ፖል ካጋሜ “እኔም እስማማለሁ፤ ትችቱ ለዶ/ር ቴድሮስ፣ ለዓለም ጤና ድርጅት እና ለቻይና ነው ወይስ በጋራ ነው ጥቃት የተሰነዘረባቸው?” ብለዋል። ⚡️የናሚቢያው ፕሬዘዳንት ሀጌ ጄኒግቦ “የመላው ዓለም ትብብር አስፈላጊ በሆነበት ሰዓት አብሮነትን ያሳዩ እውነተኛ መሪ” ሲሉ ዶ/ር ቴድሮስን ገልጸዋል። ✅ WE STAND WITH DR TEDROS ADHANOM ✅

#DrTedrosAdhanom #WHO #DonaldTrump ትላንት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሀገራቸው ለWHO የምትሰጠውን ከፍተኛ ገንዘብ እንደምታቅብ ተናገረዋል። የዓለም የጤና ድርጅት ኮቪ
#DrTedrosAdhanom #WHO #DonaldTrump ትላንት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሀገራቸው ለWHO የምትሰጠውን ከፍተኛ ገንዘብ እንደምታቅብ ተናገረዋል። የዓለም የጤና ድርጅት ኮቪድ-19 የዓለም አቀፍ ወረርሽኝ መሆኑን በጊዜ አልተናገረም ብለዋል ፕሬዘዳንቱ። ድርጅቱ ይህን ያደርገው በሽታው ለተጀመረባት #ቻይና ሲል ሊሆን ይችላል ሲሉ ግምት አዘል አነጋገር ተናግረዋል። "በጣም ቻይና ተኮር ይመስላሉ ፣ ይህን ማጤን ይኖርብናል' ሲሉ ተደምጠዋል ዶናልድ ትራምፕ። በዓለም አቀፍ ደረጃ ወረርሽኝ ባለበት በዚህ አይነት ሁኔታ ለጤናው ድርጅት /WHO/ የሚዋጣ ገንዘብ መከልከ ተገቢ ነው ወይ? ተብለው ከጋዜጠኛ የተጠየቁት ትራምፕ 'እኔ አንሰጥም አላልኩም፣ እናጤነዋለን ነው ያለኩት' ሲሉ መልሰዋል። ከፍተኛ ዘመቻ እየተካሄደባቸው የሚገኙት የዓለም የጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ዛሬ በሰጡት ዕለታዊ መግለጫቸው ላይ የግድያ ዛቻ እንደደረሰባቸው ፤ እሳቸው ግን ግድ እንዳልሰጣቸው ተናግረዋል። በማን ይህ ሊደረግ እንደቻለ ግን አልተናገሩም። ከሁለት (2) እና ከሦስት (3) ወር በላይ #ዘረኛ ጥቃቶች ተሰንዝረውብኛል ያሉት የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቴድሮስ 'ጥቁር ተብያለሁ። እውነቱን ለመናገር እኔ በጥቁርነቴ እኮራለሁ። የሚባለው ነገርም ግድ አይሰጠኝም' ሲሉም ተደምጠዋል። ምንጭ፦ ቢቢሲ፣ ቪኦኤ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#DrTedrosAdhanom ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የግድያ ዛቻና የዘረኛ ንግግር ጥቃት እየተሰነዘረባቸው መሆኑን ዛሬ በሰጡት መግለጫቸው ተናግረዋል። “I can tell you personal attacks that have been going on > 3 months. Racist comments, black or Negro. I’m proud of being black, proud of being Negro. I don’t care, to be honest ... even death threats. I don’t give a damn." MORE : https://telegra.ph/BBC-04-08 #SamiraSawali ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

እንደ #ካራንቡላ፣ #ፑል፣ #መጠጥ፣ #ጭፈራ፣ እና ሌሎች ብዙ ሰው የሚሰበሰብባቸው የንግድ ድርጅቶች በሽታው በቁጥጥር ስር እስኪውል ድረስ #ተዘግተው #የሚቆዩ ይሆናል ሲል ብሔራዊ የገበያ ማረጋጋት ግብ-ረኃይል ዛሬ ባደረገው ስብሰባ አስታውቋል❗️ © ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

ቻይና የኮሮና ቫይረስ የመጀመሪያዎቹን ሁለት የህመም ደረጃዎች ለማከም የተጠቀመችባቸውን የባህል መድሃኒቶች ለኢትዮጵያ በድጋፍ መልክ ልትሰጥ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለፀ፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና የጤና ሚኒስቴር ከቻይና የባህል ሃኪሞችና ተመራማሪዎች ጋር ቫይረሱን መቆጣጠር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በቪዲዮ ኮንፈረንስ ተወያይተዋል፡፡ ቻይና የባህላዊ መድሃኒቶችን በመጠቀም ስኬታማ በሆነ መልኩ የኮሮና ቫይረስን መቆጣጠር የቻለችባቸው መንገዶችን ለኢትዮጵያ ለማጋራት ፍቃደኛ መሆኗን ገልፃለች፡፡ በተለይ የቫይረሱ ህመም የመጀመሪያዎቹ ሁለት ደረጃዎችን ለማከም የተጠቀመችባቸውን ሁለት የመድሃኒቶች ዓይነቶች ለኢትዮጵያ በድጎማ መልክ ለመስጠት ተስማምታለች፡፡ ረጅም እድሜ ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ የባህል ህክምና ተቋማዊ በሆነ መልኩ ወደ ስራ እንዲገባ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረትም በቴክኖሎጂ፣ በቁሳቁስ እና በሙያም እደግፋለሁ ብላለች፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር ኢንጂ.) የኮሮናን ቫይረስ ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደ ሀገር ከተጀመሩ ስራዎች ጎንለጎን የቻይና ድጋፍ ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ የባህላዊ መድሃኒቶችም ህጋዊ ማዕቀፍ ኖሯቸው ወደ ስራ እንዲገቡ የተጀመረው ጥረት እንዲሳካም የቻይናን ልምድ ኢትዮጵያ ትፈልጋለች ብለዋል፡፡ Via #EthioFM ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በሚል የ5 ወራት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁን የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ አስታወቀ። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ረፋድ ባካሄደው ስብሰባ የኮሮና ቫይረስ ስጋት እየጨመረ በመምጣቱ ለ5 ወራት የሚዘልቅ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁን አስታውቅል። እንደ ፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ መረጃ ከሆነ ይህ አዋጅ የሚከለክላቸው፣የሚፈቅዳቸው እና ሌሎች ዝርዝር አፈጻጸሞች በቀጣይ ለህዝቡ ይፋ ይደረጋሉ።...

#Ethiopia : የአዊ ብሔ/አስተዳደር ጤና መምሪያ ፦ - ከአዊ ብሔራዊ/አስተዳደር ከተላኩት 8ት ናሙናዎች ነው አንዱ የኮሮና ቫይረስ እንዳለበት ዛሬ የተረጋገጠው። ቀሪዎቹ 7ቱ ከቫይረሱ ነፃ ናቸው
#Ethiopia : የአዊ ብሔ/አስተዳደር ጤና መምሪያ ፦ - ከአዊ ብሔራዊ/አስተዳደር ከተላኩት 8ት ናሙናዎች ነው አንዱ የኮሮና ቫይረስ እንዳለበት ዛሬ የተረጋገጠው። ቀሪዎቹ 7ቱ ከቫይረሱ ነፃ ናቸው። - የ36 ዓመቱ ኢትዮጵያዊ ነዋሪነቱ አዲስ ቅዳም ከተማ ሲሆን ከዚህ በፊት ቫይረሱ ከተገኘበት ግለሠብ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ነበረው፤ በእንጅባራ ዮኒቨርስቲም በለይቶ ማቆያ ውስጥ ነበረ፤ አሁን ግለሠቡ ወደ ባህርዳር መኮድ ሆስፒታል ተልኳል። - ዛሬ ቫይረሱ ከተገኘበት ግለሰብ ጋር የቅርብ ግንኙነት/ንክኪ የነበረቸው ተጠርጠሪዎች ወደ ለይቶ ማቆያ እየገቡ ናቸው። ምንጭ:- የአዊ ብሔ/ጤና ጥበቃ መምሪያ አቶ አዲሱ ጌትነት

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 3 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው #Ethiopia : ኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 225 ሰዎች ውስጥ ሶስት ግለሰቦች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው ተረጋገጠ። ቁጥሩም ወደ 55 ከፍ ብሏል።  የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደተናገሩት፤ ቫይረሱ ወደ ኢትዮጵያ ከገባ ጀምሮ እስካሁን ባለው ሂደት ለ2 ሺህ 496 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተከናውኗል። ዛሬ የተገለጸውን ጨምሮ በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር ወደ 55 ከፍ ብሏል ነው። ባለፉት 24 ሰዓታት ቫይረሱ እንዳለባቸው የተረጋገጠው ሶስቱም ግለሰቦች ኢትዮጵያዊያን ሲሆኑ ሁለቱ የውጭ አገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው ናቸው። ሁለቱ ግለሰቦች የ29 ዓመት እድሜ ያላቸውና ከዱባይ መጥተው በለይቶ ማቆያ ውስጥ ክትትል ሲደረግላቸው የነበሩ መሆናቸውንም ሚኒስትሯ ገልጸዋል። አንደኛው ግለሰብ የ36 ዓመት እድሜ ያለውና በአማራ ክልል የአዊ ዞን አዲስ ቅዳምን ከተማ ነዋሪ ነው። ግለሰቡ የውጭ አገር የጉዞ ታሪክ የሌለው ሲሆን፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ እንዳለው ተጠርጥሮ ምርመራ እንደተደረገበት ተገልጿል። ቫይረሱ ከተገኘባቸው መካከል አንድ ሰው ወደ ጽኑ ህሙማን ማቆያ መግባቱንና ይህም በጽኑ ህሙማን መቆያ ውስጥ ያሉ ዜጎች ቁጥር ሁለት እንዳደረሰው ዶክተር ሊያ ተናግረዋል። ቫይረሱ ከተገኘባቸው ጋር የቅርብ ንክኪ ያላቸው ግለሰቦች ባሉበት ክልል በተዘጋጀ የነጻ የስልክ መስመሮች በመደወል ሪፖርት እንዲያደርጉም ሚኒስትሯ ጥሪ አቅርበዋል። ህብረተሰቡ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት የወጡ መመሪያዎችን ተግባራዊ እንዲያደርግም ነው ያሳሰቡት። በኢትዮጵያ ቫይረሱ ከተገኘባቸው ሰዎች መካከል አራቱ ያገገሙ ሲሆን፤ ሁለቱ ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል። ሌላ ሁለት ግለሰቦች ደግሞ ወደ አገራቸው ተሸኝተዋል። Via #ENA ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#Ethiopia : በኢትዮጵያ ተጨማሪ 3 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው

መጋቢት 30፣2012 ሰበር ወሬ የኢትዮጵያ መንግሥት የኮሮና ወረርሽኝ እየተባባሰ በመምጣቱ ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ ማወጁን ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ። #ShegerWerewoch #COVI
+1
መጋቢት 30፣2012 ሰበር ወሬ የኢትዮጵያ መንግሥት የኮሮና ወረርሽኝ እየተባባሰ በመምጣቱ ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ ማወጁን ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ። #ShegerWerewoch #COVID_19 ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#በአሜሪካ በአንድ ቀን ከፍተኛው ሞት ተመዘገበ‼️ ✒️በአሜሪካ በ24 ሰዓት ውስጥ ብቻ በኮሮናቫይረስ ምክንያት 1736 ሰዎች ሞቱ።ወረርሽኙ ከጀመረ ወዲህ በየትኛውም አገር በአንድ ቀን ይህን ያህል ሰው ሞቶ አያውቅም ተብሏል። አሜሪካ ማክሰኞ ዕለት ብቻ በ24 ሰዓት 1ሺህ 736 ሰዎች ሞተውባታል፡፡ይህም እስካሁን በአሜሪካ ምድር የሟቾችን ቁጥር 12ሺህ 722 ያደርሰዋል፡፡በአሜሪካ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ጠቅላላ ቁጥር 400 መቶ ሺ ለመድረስ 2ሺ ሰዎች ብቻ ናቸው የቀሩት፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር 1 ሚሊዮን 400ሺ እያለፈ ይገኛል፡፡ Via #BBC ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#ዉሃን_ከተማ ለመጀመርያ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ክፍት ሆነች የተቀረው ዓለም ቀስ በቀስ በሩን እየከረቸመ ባለበት በአሁኑ ሰዓት ቫይረሱ ተወልዶባታል የምትባለው ዉሃን ከተማ ለመጀመርያ ጊዜ ለእንቅስቃሴ በሯን ሙሉ በሙሉ ከፍታለች፡፡ ጤናማነታቸው የተረጋገጠና ይህንኑ የሚመሰክር አረንጓዴ ኩፖን ምልክትት (በስልክ መተግበሪያ ላይ የሚገኝ) የያዙ ነዋሪዎቿ አሁን ወደየትም አገር መጓዝ ይችላሉ፡፡ የባቡር መንገዶቿ፤ የመኪና አውራ ጎዳናዎቿም ለመጀመርያ ጊዜ በሙሉ ኃይል ክፍት ሆነዋል፡፡ የ11 ሚሊዮን ቻይናዊያን መኖርያ የሆነችው ውሃን ለ11 ሳምንታት ሙሉ በሙሉ ተዘግታ፤ እንቅስቃሴዋ ታግዶ ከርማ ነበር፡፡ በቻይና ወረርሽኙ ከተነሳ ወዲህ 3300 ሰዎች ብቻ የሞቱ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ የሚበዙቱ የዚች ከተማ ነዋሪዎች ነበሩ፡፡ Via #BBC ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#Coronavirus በኬንያ 17 የፓርላማ አባላት የኮሮና ቫይረስ እንዳለባቸው በምርመራ መረጋገጡን ዘ ስታር የተባለ የሀገሪቱ ጋዜጣ አስነብቧል። ባለፈው ሳምንት ከ200 የሚመበልጡ የሀገሪቱ የፓርላማ
#Coronavirus በኬንያ 17 የፓርላማ አባላት የኮሮና ቫይረስ እንዳለባቸው በምርመራ መረጋገጡን ዘ ስታር የተባለ የሀገሪቱ ጋዜጣ አስነብቧል። ባለፈው ሳምንት ከ200 የሚመበልጡ የሀገሪቱ የፓርላማ አባላት የቫይረሱን ምርመራ አድርገው ውጤታቸው ባለፈው ሰኞ እንደተሰጣቸው ጋዜጣው ገልፆ ስማቸውን ግን ማግኘት እንዳልቻለ ፅፏል። Via:- Tesfay Getnet ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━