ru
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

Открыть в Telegram

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

Больше
1 719
Подписчики
-224 часа
-77 дней
-1830 день
Архив постов
ጊዜ በሰኮንዶች ድምር በደቂቃ መሄድ በሰአታት ማለፍ በቀናቶች መንጎድ በወራት መተካት በአመታቶች መክነፍ በጊዜ ሽቅድድም በወቅታቶች ማለፍ አካልም ይደክማል ደጋፊውን ይሻል በወጣትነቱ የዘራውን ያጭዳል ባሳለፈው ትላንት ጊዜ ፈራጅ ሁኖ ዛሬ ላይ ይቀጣል። እምነት @Enku41

እኔ እና አንቺ አንቺ ማለት ጸሃይ፡ እኔ ጨረቃዋን ባንቺ ብርሃን የምፈካ፡ ባንቺ መጥፋት የምባክን አንቺ ሙሉ አለም፥ እኔ ትንሽ ድንኳን ኢብራሂም አብዱ @Ibrocr7

ቃና : ዘ : ገሊላ_.. በጎደለ : ቀኔ : የሞላውን : ውሀ ሲያቅረኝ : ለመንኩት : እንዲሆን : አምሀ እሱም : ቃሌን : ሰምቶ : ወይን : አደረገልኝ ቀድቼ : ጠጥቼ : ጥማትን : : ሰከርኩኝ _በል: እንግዲህ_ ..... አገባለሁ : ብዬ : የጠራሁት : ሚዜ : ተሞሽሯልና ወይኑን : ውሀ : አርግልኝ : ስትመለስ : ቃና... /***/ ✍ናታን ኤርምያስ @UniqueDY

ጥላሸት በጥብጣ ድርብ መርፌ ይዛ፣ ህመሜን እንድችል በአረቄ አደንዝዛ፤ ድዴን ትወቅራለች ፥ ጉራማይሌ ጥርሴን፣ እንጃ ከዚህ ኋላ ፥ እህልም መቅመሴን። ፈገግታ እየቆጠብኩ ፥ እኖራለሁ እንጂ ፣ እንዲህ ነው 'ሚያደርገኝ ጥለሽኝ ስትሄጂ ። ጥርሴን ተነቅሼ ፥ ለሳቅ ለጨዋታ ፣ እንኳንስ ከንፈሬ ፥ ግንባሬ አይፈታ። አስካለ ልቅና @AskuAn

የትም ቦታ ይጣለኝ አደባባይ መሀል ቁና ሙሉ ቅማል ስቀምል ያውለኝ መሪ ምርኩዝ ይንሳኝ አውላላ ሜዳ ላይ ገደል ገባሁ እያልሁ ስደናበር ልገኝ በጠራራ ጠሀይ ሚፋጅ አስፓልት ላይ እንደ እህል ልሰጣ ዶፍ እየዘነበ መሸሸጊያ ልጣ ታድያ እንዲህ ሲያደርገኝ አትሁኚ ጎኔ አብረሺኝ ከሌለሽ ገሀነም ራሱ ገነቴ ነው ለኔ @Fullof_memory

ኅልቆ - ሸለፈት ------------------- የሚገለማ ~ ስጋ ታቅፌ በምን ብልኃት ~ ልኑር አርፌ ጥሎብኝ ቁልፈት ~ ክፉ ሸለፈት ከላዬ ሰፍፎ ~ ልክ እንደ ገፈት ዛሬ ብቆርጠው ~ ነገ ሊመዘዝ ስንቴ ልቀንጠብ ~ ስንቴስ ልገረዝ? #ዮናታን @yonii_boss

😫ችግር😩 ችግር ይበርታ እና ይቸግር ጠንክሮ ስልጣኔም አይዘግይ÷አያብዛ ቀጠሮ ችግር ፈቺ ትውልድ ነገ እንዲኖረን ችግርን ማግነን ነው ዛሬ የሚያስፈልገን🤔🤪 ✍️ህሊና @Hilina70

A poetry contest for Gitem Sitem's telegram family! With a chance to win a hiking trip to Damocha! Terms and Conditions —————
A poetry contest for Gitem Sitem's telegram family! With a chance to win a hiking trip to Damocha! Terms and Conditions ——————— 1. The contestant must be a member/follower of our channel. 2. The pieces should be submitted by contestants via telegram to @seifetemam until Thursday midnight. 3. Only those who are 18 years old and above are eligible. 4. There is no specific theme or topic for the contest but it should not be longer than 8 lines. 5. Poems with most likes until Mid day Friday will be the winner. Good Luck! #gitemsitem #damocha #ma_trip #hiking

A poetry contest for Gitem Sitem's telegram family! With a chance to win a hiking trip to Damocha! Terms and Conditions ——————— 1. The contestant must be a member/follower of our channel. 2. The pieces should be submitted by contestants via telegram to @seifetemam until Thursday midnight. 3. Only those who are 18 years old and above are eligible. 4. There is no specific theme or topic for the contest but it should not be longer than 8 lines. 5. Poems with most likes until Mid day Friday will be the winner. Good Luck! #gitemsitem #damocha #ma_trip #hiking

ለግጥም ሲጥም የቴሌግራም ቤተሰቦች በልዩነት የተዘጋጀ የአጭር ግጥም ውድድር!!! ወደ ዳሞቻ ተራራ የሚደረግ ጉዞን የሚያሸልም ደንብ እና ሁኔታዎች ——————— 1. ተወዳዳሪዎች የቴሌግራም ቻናላችን ተ
ለግጥም ሲጥም የቴሌግራም ቤተሰቦች በልዩነት የተዘጋጀ የአጭር ግጥም ውድድር!!! ወደ ዳሞቻ ተራራ የሚደረግ ጉዞን የሚያሸልም ደንብ እና ሁኔታዎች ——————— 1. ተወዳዳሪዎች የቴሌግራም ቻናላችን ተከታይ መሆን ይኖርባቸዋል። 2. ተወዳዳሪዎች ግጥማቸውን እራሳቸው በቀጥታ በቴሌግራም ወደ @seifetemam እስከ ሐሙስ ለሊት 6 ሰዓት ብቻ መላክ ይኖርባቸዋል። 3. ተወዳዳሪዎች ከ 18 ዓመት በላይ መሆን አለባቸው። 4. ግጥሙ በማንኛውም ርዕሰ ጉዳይ ላይ መሆን ሲችል ከ8 መስመር ያልበለጠ መሆን አለበት። 5. የተወዳዳሪዎቹ ግጥም በቻናሉ ከተለጠፈበት ሰዓት አንስቶ እስከ አርብ 6 ሰዓት (ከቀኑ) በብዙዎች የተወደደው ግጥም አሸናፊ ይሆናል። መልካም ዕድል! #ግጥምሲጥም #ዳሞቻ #ማትሪፕ #ጉዞ

ፍቅር ይሻለኛል እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች የልቦለድ መጽሐፍ እሁድ ነሃሴ 2 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ጀምሮ አራት ኪሎ ቱሪስት ሆቴል ጀርባ በሚገኘው፤ በኢክላስ ሕንፃ ዋልያ መጽሐፍ ቤት
ፍቅር ይሻለኛል እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች የልቦለድ መጽሐፍ እሁድ ነሃሴ 2 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ጀምሮ አራት ኪሎ ቱሪስት ሆቴል ጀርባ በሚገኘው፤ በኢክላስ ሕንፃ ዋልያ መጽሐፍ ቤት ይመረቃል። በዝግጅቱ ላይ ኤፍሬም ስዩም፣ ኢዘዲን ካሚል፣ ደምሰው መርሻ፣ አዳነ አረጋ፣ ዲበኩሉ ጌታ ፣ ማርቆስ ዘመንበረ ልዑል ፣ ስላባት ማናዬ፣ አሸናፊ መለሰ እና ሌሎች ተጋባዦችም ዝግጅታቸውን ያቀርባሉ እና ሁላችሁም እንድትታደሙ ተጋብዛችኋል።

Come join Poetic Saturdays at GUAC-ON in Hayahulet this coming Saturday, August 7th 2021! Please note that this event is 21 a
Come join Poetic Saturdays at GUAC-ON in Hayahulet this coming Saturday, August 7th 2021! Please note that this event is 21 and over only. As usual, we will start registration at 2: 00 pm. Only perform YOUR ORIGINAL work. The audience is there to listen to your truth! Each performer gets 5 minutes total. You can perform as many times but respect the time limit. All languages welcome. All performance art forms welcome! We are excited our audiences and honored our performing family is growing. So come by and witness the amazing talents brewing in our city. Tell a friend! . . . #poetry #performanceart #openmic #artspace #poeticsaturday #saturday #words #open @gitemsitem @guac_on_addis @arada.et @linkupaddis @artsmailinglist @contemporary_nights @seifetemam @cttotheg @christooz @ye_getaneh_lij

#ትሁት_ካልሆንክ_ጠቢብ_አይደለህም! • እውነት እውነት እልሃለሁ፤ ትሁት ካልሆንክ #ጥበብን_አታውቃትም__ጥበብም_አንተን_አታውቅህም። ... ጠቢብ የብርሐን ተምሳሌት ነው። ብርሐን ተፈጥሮው መብራት ነው። ፀሐይ የምትለየው በብርሐኗ ለሌሎች መትረፍ ነው። በመስጠት። ፅልመትን በመግፈፍ። የጠቢብ ባህርዩ የሌሎችን መልካምነትና ውበት ገላልጦና አጋልጦ ማሳየት ነው። ፀሐይ ፅልመትን ስትገፍ፣ 'ጀብድ ሰራሁ' ብላ አትዘግብም። ጮሃም አትናገርም። ቅንነት ተፈጥሮዋ ነውና። ጠቢብም የልቦና ብርሐን ነውና፤ የሌሎችም ፅልመት በቅንነት ብርሐኑ፣ በፍቅር ፀሐዩ ገልጦ ውበታቸውን ያጎላል እንጂ ስለ ፅልመታቸው እየተረከ ገናናነቱን አይዘግብም። መጀመሪያ ሰው ሆኖ መቅረብ ይቀድማል። ከዚያም ፍቅርና ብርሐናችንን መግለጥ። በፍቅርና በብርሐናችን ሁሉን ማቀፍ መቻል። ለሁሉ ማብራት፤ ሁሉን ማክበር። እኛ ብርሐን ነን አንልም። ሌሎች በብርሐናችን ያውቁናል እንጂ። እኛ ስለሰዎች ፅልመት አናወራም። ሰዎች ስለብርሐናችን ኃይል ይናገራሉ እንጂ። ጠቢብነት በትህትና ይመዘናል። ሌሎችን አክብሮ በመውደድ ኃይል። ሁሉን መቀበል፣ ሁሉን መውደድ በመቻል ኃይል። ጠቢብ ድክመት ነቃሽ አይደለም። ደካማውን አበርቺ፣ የተሰወረውን ጥንካሬ ነቅሶ አውጪ እንጂ። በትችት አይጠመድም። በማሳነስ ገዝፎ ለመታየትም አይሞክርም። ማግዘፍ እንጂ ማኮሰስ የባህርይ ገንዘቡ አይደለም። ጠቡብ ቡድን የለውም። ፀሐይ መንደር መርጣ፣ ያ ክፉ ያኛው ደግ ብላ አዳልታ እንደማታበራ ሁሉ። ለበዳይም ለተበዳይ፣ ለገፊም ለተገፊም በእኩል ብርሐኗን ትለግሳለች። ተፈጥሮዋ መስጠት ብቻ ስለሆነ። #ትህትና። እውነት እውነት እልሃለሁ። ሰዎችን የምትጠላ፣ የምታበላልጥና ስህተታቸውም ነቅሰህ በጎአቸውን የምትጋርድ ከሆንክ፣ ጥበብን አታውቃትም፤ ጥበብም አንተን አታውቅህም። #ትህትና__ትህትና #የግዝፈቶች_አክሊል_የቅንነት_ካባ #ባክህ__ልቤ_ግባ! #ፍቅር_በሌለበት_ጥበብ፣ #ጥበብ_በሌለበትም_ፍቅር_የለም። ጠቢብ መጀመሪያ ሰው ነው። መጀመሪያ የሁሉ ወዳጅ። ሁሉን አክባሪ። ሁሉን አበርቺ። ሁሉን አግዛፊ። ሚዛኑ ለሐሜት የማይታዘዝ። ልቡ ለአድልዎ የማይታጠፍ። የእነእገሌ አደግዳጊ፣ የእነእገሌ ጠላት አይደለም። የጠቢብ ነፍስ ጥላቻን ትጠየፋለች። የጠቢብ ልብ ከፍቅር በቀር አይዘምርም። የጠቢብ ዐይኖች ከፅልመት ውስጥ ብርሐንን፣ ከድክመት ውስጥ ብርታትን፣ ከጥመት ውስጥ ቅንነትን፣ ከፀያፍ ውስጥ ውበትን መንጥረው ያያሉ። ጠቢብ ሁሉን ያለ ጥቅም ይወዳል። ተሥፋን፣ ፍቅርን፣ ክብርን፣ ነፃነትን ይለግሣል። ለማቅናት አያፈርስም፤ የፈረሰውን ያቀናል እንጂ። ለመወደድ አይወድም። ለመቀበል አይሰጥም፤ መውደድ ሰጥቶ መውደድ ይበዛለታል እንጂ። ጠቢብ ውዳሤ ከንቱን ይፀየፋል። በማዕረግ አይታሰርም። በስምና በክብር ኬላ ከሰዎች መነጠል አይፈልግም። የትም፣ እንዴትም፣ ከማንም፣ ከምንም፣ ሁሌም ሰው አክሎ መገኘት ይችልበታል። ጎዝጉዙልኝ፣ አንጥፉልኝም አይልም። በተገኘበት ድባቡ ይነግሣል እንጂ። ፍቅሩ፣ ትህትናውና አክብሮቱ በመገኛው አድባር ያደርጉታል እንጂ። ጠቢብ ዋርካ አይደል? ሁሉን ሰብሳቢ። በግዝፈቱ የሚያስመካ። በቅርንጫፎቹ የሚያስጠልል። ጥላ የሚሆን፣ የሚያሳርፍ፣ ተራማጁንም፣ በራሪውንም፣ ተሳቢውንም፣ አመንዣጊውንም፣ ሁሉን የሚያስጠጋ - ዋርካ ጠቢብ አይደል? ጠቢብም ዋርካ። ነፋስ የማይጥለው ሥሩ ጥልቅ፤ ዝናብ የማይጥለው ግንዱ ጥብቅ። ትሁት ካልሆንክ ጥበብ ትጠየፍሃለች። ፍቅርም፣ ፍትህም ብርሐንም አይበቅሉብህም። #ትህትና_ትህትና #የግዝፈቶች_አክሊል__የቅንነት_ካባ #ባክህ_ልቤ_ግባ! #ሠይፈ__ወርቅ♥

ግጥም ሲጥም ፭ - Gitem Sitem 5 የክፍት መድረክ ክበብ መግቢያው ላይ በመመዝገብ በቻ የፈለጋችሁትን፣ ልባችሁ ያላችሁንና ነፍሳችሁ የወደደችውን የምታቀርቡበት። የመጀመሪያ ጊዜያችሁ ከሆነ በታላ
ግጥም ሲጥም ፭ - Gitem Sitem 5 የክፍት መድረክ ክበብ መግቢያው ላይ በመመዝገብ በቻ የፈለጋችሁትን፣ ልባችሁ ያላችሁንና ነፍሳችሁ የወደደችውን የምታቀርቡበት። የመጀመሪያ ጊዜያችሁ ከሆነ በታላቅ ደስታ እንቀባላችኋለን። የመድረክ ልምድ ያላችሁ ከሆነ ደግሞ በታላቅ ደስታ እንቀበላችኋለን! ተመዝግቡ - አቅርቡ! An Open Mic Circle of Poetry and Fun Sign up and perform whatever is in your heart! If you are a first timer for stage, that's a win for us! If you are well experienced, that's still our win! Share the stage with one of the amazing poets in town. Sign up and perform #gitemsitem #heransyoga #seifetemam #shifta

ነፍስ ቦታ ዐስር የዚህ ትውልድ ዕጹብ ገጣሚያን የተሳተፉበት የ'ነፍስ ቦታ' የመጽሐፍ ማስተዋወቂያ (ቅድመ-ምረቃ) ዝግጅት ሀሙስ፣ ሐምሌ 21 ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ በዋልያ የመጽሐፍት መደብር፣ አራት
ነፍስ ቦታ ዐስር የዚህ ትውልድ ዕጹብ ገጣሚያን የተሳተፉበት የ'ነፍስ ቦታ' የመጽሐፍ ማስተዋወቂያ (ቅድመ-ምረቃ) ዝግጅት ሀሙስ፣ ሐምሌ 21 ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ በዋልያ የመጽሐፍት መደብር፣ አራት ኪሎ ከቱሪስት ሆቴል ጀርባ በሚገኘው ኢኽላስ ህንጻ #July_29_21 https://t.me/Kunet_Sitem #ነፍስ_ቦታ #ግጥም_ሲጥም #ሮማናት #ዋልያ_መጽሐፍት

Yes, that. Those days You know, Where your lungs feels like a solitary confinement with four people in it breathing over your shoulder You know, Where your eyes are sensitive to light, Any light Light coming from your phone, the window, fluorescent tubes, smiles and kind hearts You know, Where you can taste the rust against the weathering gears in your brain Where you hear others calling out your name but you have to blink hard a couple of times To make sure whether you’re falling asleep or if it’s really coming from across your table You know, Where you don’t want to get out of the taxi In fact, you didn’t want to get in, in the first place In fact, you wanted to stay in In your room your bed your mind your dream your skin You know, . . . Don’t you?

ክረምት እና ንባብ 📅 ሐምሌ 15 እስከ ነሐሴ 10 2013 📍 4ኪሎ ቱሪስት ሆቴል ጀርባ ኢክላስ ህንፃ 🙏 Siti አዘጋጁ ዋልያ ኢቨንት ሲሆን የዝግጅቱ መሪ ቃል "ንባብና ክረምት" ነው። የመጻህ
ክረምት እና ንባብ 📅 ሐምሌ 15 እስከ ነሐሴ 10 2013 📍 4ኪሎ ቱሪስት ሆቴል ጀርባ ኢክላስ ህንፃ 🙏 Siti አዘጋጁ ዋልያ ኢቨንት ሲሆን የዝግጅቱ መሪ ቃል "ንባብና ክረምት" ነው። የመጻህፍት አውደርእዩ ከሐምሌ 15 እስከ ነሐሴ 10 በሚቆይበት ጊዜ የተለያዩ መሪ ቃሉን የሚያጎሉ ዝግጅቶች በእያንዳንዱ ምሽቶች ሲካሄዱ ዋና ዋናዎቹም የሚከተሉት ናቸው _ቁጥራቸው ከአስር በላይ የሆኑ ነባርና አዳዲስ ደራስያን መጽሐፎቻቸውን ያስመርቃሉ። እንደ ደራሲ ሐይለመለኮት መዋእል ያሉ አንጋፋ ጀራስያን ልምዶቻቸውን ያካፍላሉ። ዛጎል የመጻሕፍት ባንክ ከአንባብያን የተለገሰውን መጻሕፍት ለተለያዩ ገጠርና ከተማ ለሚገኙ አስር መጻሕፍት ቤቶች ያስረክባል። ግጥሞች ለአባይ በሚል ርእስ ልዩ የስነጽሑፍ ምሽት ይደረጋል። በዚህ ዝግጅት ከነባር ገጣምያን መካከል የባለቅኔ ጸጋዬ ገብረመድሕንና ነሰይፉ መታፈርያ ፍሬው ግጥሞች አሁን ካሉት ደግሞ ዶክተር በድሉ ዋቅጅራና አንዱአለም አባተ (ያጸደ ልጅ) ይሳተፉበታል። ከቀናት መሃከል በአንዱ ወጣቱ ደራሲና የፍልስፍና ሰው መሐመድ ቡርሐን ዲስ @eventsethiopia

#መጨመሪያ
#መጨመሪያ

Follow me on Instagram! Username: gitemsitem https://www.instagram.com/gitemsitem?r=nametag
Follow me on Instagram! Username: gitemsitem https://www.instagram.com/gitemsitem?r=nametag