Sinksar tube(ስንክሳር)
Открыть в Telegram
እኔ ቅዱስ ነኛና ቅዱሳን ሁኑ 1ጴጥ 1:15
БольшеСтрана не указанаКатегория не указана
2 500
Подписчики
-1024 часа
+1137 дней
+42130 дней
Архив постов
2 499
💠የንስሐ ◇የሽብሻቦ ◇ወረብ ◇የቅዱሳን እንዲሁም የመላእክት መዝሙር የምትፈልጉ ከሆነ አሁኑኑ JOIN በሉት ይሄ ቻናል ምርጥ ምርጥ መዝሙሮችን በጥራትና በፍጥነት ያሳያል። 𝐉𝐨𝐢𝐧👇👇👇
https://t.me/addlist/sZA2UFcsVPplMjI0
2 499
📖 ስለ ምልጃ በሃያ ክፍል የተጠየቁ ጥያቄዎች እና በጽሑፍ የተመለሱ (የተላለፉ) ትምህርቶች በእነዚህ ሊንኮች ይገኛል👇
📖 አማላጅ ማለት ምን ማለት ነው❓
📖 ማማለድ ምንድን ነው❓
📖 አማላጅ የምንለው ማንን ነው❓
📖 የቅዱሳን አማላጅነት ለምን አስፈለገ❓
📖 የቅዱሳን አማላጅነት በብሉይ ኪዳን እና በአዲስ ኪዳን❓
📖 የቅዱሳን መላእክት አገልግሎቶች ምን ምን ናቸው❓
📖 የቅዱሳን መላእክት አማላጅነት እንዴት ይገለጻል❓
📖 የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት እና ተራዳኢነት ስንል ምን ማለታችን ነው❓
📖 ክርስቶስ አማላጅ ነው? አምላክ ነውና ወደ ማን ይማልዳል❓
ይ🀄️ላ🀄️ሉ 👇
🤗https://t.me/addlist/sZA2UFcsVPplMjI0
2 499
🔴 ኦርቶዶክስ ኖት ❓️
🌹🌹🌹
🌹🌹🌹🌹
🌹🌹🌹🌹🌹
🌹🌹🌹🌹🌹🌹
🌹🌹🌹🌹🌹🌹
🌹🌹🌹🌹🌹🌹
🌹🌹🌹🌹🌹
🌿🌹🌹🌿
🌿🌿
🌿
🌿 🌿🌿
🌿 🌿🌿🌿
🌿 🌿🌿🌿🌿
🌿 🌿🌿🌿🌿
🌿 🌿🌿🌿🌿
🌿 🌿🌿🌿
🌿
🌿
🌿
🌿
🌿
🌿
🔴የአበባውን ምስል አንድ ጊዜ በመጫን ጠቃሚ ነገር ይመልከቱ አንድ ጊዜ ብቻ ይንኩት፡፡❤
2 499
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
እንኳን ለቅድስት ሐና ወርሐዊ የመታሰቢያ በዓል አደረሰን
‘’ለምንጠራው መልክአ ሥጋሽ ሁሉ መፅኛ (መቆምያ) ለሆኑ እግሮችሽ ሰላም እላለሁ ቅድስት ሐና ሆይ ያንቺን መታሰቢያ በጉባኤ ፊት የሚያደርግ እና ካለው ሁለት ልብስ አንዱን የሚሰጥ። ትንሣኤ ሙታን በሆነ ጊዜ ሕይወትን ያገኛል ።"
መልክዐ _ሐና
2 499
በዚኽች ዕለት ሰኔ 11 ቀን በዓመታዊ የዕረፍት በዓሉ ታስቦ የሚውለው የሰማዕቱ የቅዱስ ገላውዲዮስ ቤ/ክ!
በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ የሚቀበረው አስክሬን ከሳምንት በኋላ የት እንደሚሄድ ሳይታወቅ አስክሬኑ ይሰወራል፡፡ ይህ የቅዱስ ገላውዴዎስ ቤተ ክርስቲያን የሚጠበቀው በንብ ነው፡፡ ምግብ በልቶ ወደዚህ ቤተ ክርስቲያን መግባት ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ በድፍረት በልቶ የሚገባም ካለ ጠባቂው የንብ መንጋ መጥቶ ይወረዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ የሚገኘው ደቡብ ጎንደር ዞን ደራ ወረዳ (አፈሯ እናት) ተብሎ በሚጠራውና ከባህርዳር ወደ ጎንደር ከሚወስደው የአስፋልት መንገድ ሐሙሲት ከተማ ላይ አንበሣሜ-አርብ ገበያ ገላውዴዎስ ቀበሌ ኒፋራ ጫካ ሥር ነው፡፡
በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ የካህናት፣ የወንዶችና የሴቶች መካነ መቃብር የተለያየ ሲሆን የሚቀበረው አስክሬን ከሳምንት በኋላ የት እንደሚሄድ ሳይታወቅ አስክሬኑ ይሰወራል፡፡ በመቃብሩም በሳምንቱ ሌላ የሞተ ሰው ይቀበርበታል፡፡ አዲስ የሚቀበረውም አስክሬን ከሣምንት በኋላ ይሰወራል፡፡
ይኽንን ድንቅና ተአምረኛ ቤተ ክርስቲያን ያሠሩት በሰማዕቱ ስም የተጠሩት ደገኛው ዐፄ ገላውዲዮስ ናቸው፡፡ እርሳቸውም ስዕለት ተስሐው በእመቤታችንና በሰማዕቱ ገላውደረዎስ ምልጃ ግራኝ አህመድን ፈጽመው ድል ካደረጉና ቤተ ክርስቲያንን ከ15 ዓመት እጅግ አስከፊ ሥቃይና ሠቆቃ ከታደጉ በኋላ ነው ያሠሩት፡፡ ሌላው በሰማዕቱ በቅዱስ ገላውዲዮስ ስም የተሰየመና የራሱ የሆነ ታሪክ ያለው ታቦት አዲስ ዘመን ጣራ ገዳም ውስጥም ይገኛል፡፡ የሰማዕቱ የቅዱስ ገላውዴዎስ ረድኤት በረከት ይደርብን!፡፡
2 499
2 499
"ሰይጣን የማይነካው ዕቃ"በአንድ ሐገር ድንገት የአንድ" ጠንቋይ ዝና ከዳር ዳር ተሰማ። ሰውዬው የማያሳየው ምትሐት የለም። አንበሳ ላለ አንበሳ፣ ነብር ላለ ነብር፣ የሞተ ዘመዴን ላለ የሞተ ዘመዱን፣ የጠፋብኝን ዕቃ ከቤት ፈልገህ አምጣልኝ ላለ ዕቃውን ያመጣለታል። እንደሚታወቀው አጋንንት ከክብራቸው የተዋረዱ መላእክት ናቸው። መላእክት ደግሞ በፈለጉት ሁኔታ መገለጥ ይችላሉ። ይህ ጠንቋይ የሚሰጣቸውን ገጸ ባሕርይ ተቀብለው አንዴ አንበሳ፣ አንዴ ነብር፣ አንዴ ሰው እየሆኑ የሚተውኑት እንግዲህ አጋንንቱ ነበሩ። የዚህ ጠንቋይ ዝና ወደ ንጉሱ ደረሰ። ንጉሱ ደግሞ ክርስቲያን ቢሆንም ከመጸሐፍ ቅዱስ ይልቅ እንዲህ ያለ ተአምር እዚህ ቦታ ተፈጸመ ሲባል ለማየተት የሚሮጥ ሰው ነበር። ተአምር የሚወድ ሰው ደግሞ ክርስቲያንም ቢሆን ሰይጣን በሚሰራው ምትሐት መታለሉ የማይቀር ነው። ስለዚህ ይህ ንጉስ የተማረውን መጽሐፍ ቅዱስ ዘንግቶ በጠንቋዩ ምትሐት አመነ። ይህንን የሰሙ የንጉሱ ንስሐ አባት ነገሩን ሰምተው ወደ ቤተ መንግሥት ሲሮጡ ደረሱ። ሲደርሱ ንጉሡ ከቁም ነገር አልቆጠራቸውም። እሱ የጠንቋይ ትርዒት ማየት ቀጠለ። "እስቲ አሁን ደግሞ እእእ ነጭ ፈረስ አምጣልኝ" ማለቱን ቀጠለ በነገሩ ያዘኑት "ኧረ ንጉሥ ሆይ ይተዉ፡ ይህ እኮ የሰይጣን ምትሐት ነው " ብለው ሊያስረዱት ሲሉ በቁጣ አስቆማቸው። ተአምር የሚከተል ሰው መቼስ ቢነግሩት አይሰማም። ጭራሽ እንዲያው ለንስሐ አባቱ እንዲህ አላቸው። "የሰይጣን ስራ ነው አትበሉ፤ ቅናት ነው ይኼማ,,,, ይልቅ እርስዎም የሚፈልጉትን ነገር ይጠይቁት ያምጣልዎት!"አላቸው። ጠንቋዩ «የፈለጉትን ላምጣልውት,,,,,ምን ይፈልጋሉ,,,, " የሞተ ዘመድ አለዎት,,,,, ወይስ ከቤትዎ,,,, » አላቸው በኩራት። ካህኑ ውስጣቸው በመንፈሳዊ ቅናት ተቃጠለ። « እንግዲያውስ የፈለኩትን ማምጣት ከቻልህ ወደ ቤተ መቅደስ ሔደህ ልብሰ ተክህኖዬ ውስጥ መስቀል አለ እርሱን ይዘህልኝ ና » አሉት። ይህን ጊዜ ጠንቋዩ ገና ድግምቱን ሲጀምር አጋንንቱ እላዩ ላይ ሰፍረው ጣሉት። በካህኑ ፊት ወደቀ። ሰይጣን ምንም ነገር ማምጣት ይችል ይሆናል። መስቀሉን ግን ማምጣት አይችልም። አባቶቻችን ሰይጣን እንኳን መስቀል ቀርቶ መስቀለኛ መንገድም አይወድም ይላሉ። የጌታችን ቅዱስ መስቀል ሆይ ቅዱስ ዳዊት እንዳለ «ብከ ንወግዖሙ ለኩሎሙ ጸርነ» «በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን! 📝ከዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
2 499
††† እንኳን ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዓመታዊ የተድላና የደስታ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። †††
††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††
††† በዚሕች ቀን ለ40 ዓመታት በመላው ዓለም የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናት የተከፈቱበት ቀን ይታሠባል:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ ልቡና ታስባ : በዓለመ መላእክት ከታየች በኋላ:-
¤አበው ተስፋ ሲያደርጓት
¤ነቢያት ትንቢት ሲናገሩላት
¤ሱባኤ ሲቆጥሩላት
¤ምሳሌም ሲመስሉላት ኑረዋል::
††† ዘመኑ በደረሰ ጊዜ በአምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ :-
¤በመጸነሱ ተጸንሳ
¤በመወለዱ ተወልዳ
¤በጥበብና በሞገስ አብራው አድጋ
¤በጥምቀቱ ተጠምቃ
¤በትምሕርቱ ጸንታ
¤በደሙ ተቀድሳ
¤በትንሣኤው ከብራ
¤በዕርገቱ ሰማያዊነቷን አጽንታ
¤በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስ ወርዶላት በይፋ ለልጆቿ ተሰጥታለች::
††† አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት በመላው ዓለም ዞረው በብዙ ድካም የሠሯት ቤተ ክርስቲያን ለ200 ዓመታት እጅግ የበዙ መከራዋችን አሳልፋለች:: በ265 ዓ/ም የመጣባት መከራ ግን በዓለም ታሪክ እስካሁን አልታየም:: የወቅቱ ኃያላን ነገሥታት (ዲዮቅልጢያኖስና መክስምያኖስ) ዓለምን ለ2 ተካፍለው ክርስቲያኖችን የማጥፋት ዘመቻ ጀመሩ::
በመጀመሪያም በዓለም ያሉ ሁሉም አብያተ ክርስቲያናት እንዲቃጠሉ ካልሆነም እንዲዘጉ : በፈንታቸው ደግሞ አዽሎን: አርዳሚስ የተባሉ ጣዖቶች እንዲተኩ ትዕዛዝ ተሰጠ:: ለ40 ዓመታት ክርስቲያን ስለሆኑ ብቻ ሚሊየኖች ተገደሉ: ታሰሩ: ተሰቃዩ: ተሰደዱ:: መጻሕፍት ተቃጠሉ: አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ወደሙ::
በአባቶቻችንና እናቶቻችን ላይ ልንናገረው ከምንችለው በላይ ጭንቅና መከራ ደረሰ:: ነገር ግን ቅዱሳኑ ያን ሁሉ ችለው ጸኑ:: 47 ሚሊየን የሚያሕሉትን ደግሞ ሰይፍና እሳት በላቸው:: በዛ ዘመን አንድ ቤተ ክርስቲያን ለማግኘት ከአሕጉር አሕጉር መሔድን ይጠይቅ ነበር::
ከዚሕ ሁሉ በኋላ ግን እግዚአብሔር "ግፍ ይበቃል" ሲል በ305 ዓ/ም ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ነገሠ:: መክስምያኖስን በጦርነት ሲማርከው አውሬው ዲዮቅልጢያኖስ ግን አብዶ ሞተ:: ይህ ከተደረገ ከዓመታት በኋላ (በ313 ዓ/ም) ታላቁ ቆስጠንጢኖስ የዓለም መሪዎችን በዚሕች ቀን ጠርቶ አዋጁን በአዋጅ ሻረው:: "ሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ይከፈቱ:: በፈንታው ደግሞ ሁሉም ጣዖት ቤቶች ይዘጉ" አለ::
በሺሕ የሚቆጠሩ አብያተ ክርስቲያናትን በወርቅ አስለበጠ:: በዚሕ ምክንያት ይህች ቀን ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን "ዕለተ ትፍሥሕት (የደስታ ቀን)" ተብላ ትከበራለች::
††† ቸሩ አምላክ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ከመከራ ይሠውርልን:: ከበረከቷም ያድለን:: ትውልዱ ደካሞች ነንና ከማንችለው ፈተናም ይጠብቀን::
††† ሰኔ 10 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
2.ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ
3.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት (ከታላላቆቹ ሶፍያዎች አንዷ ናት)
4.ቅዱሳት ሰማዕታት ደባሞንና ብስጣሞን (የቅድስት ሶፍያ ልጆች)
5.ቅዱስ አውሎጊስ ሰማዕት
6.ቅዱስ ዋርስኖፋ ሰማዕት
††† ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
2.ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
3.አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
4.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ እልፍዮስ)
5.ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
6.ቅዱስ ዕፀ መስቀል
††† "ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሒድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ::
ኢየሩሳሌም ሆይ እግሮቻችን በአደባባይሽ ቆሙ::
ኢየሩሳሌምስ እርስ በርሷ እንደ ተገለጠች ከተማ ተሠርታለች . . .
ስለ ወንድሞቼ ስለ ባልንጀሮቼም በውስጥሽ ሰላም ይሁን አልሁ::
ስለ አምላካችን ስለ እግዚአብሔር ቤት ላንቺ መልካምነትሽን ፈለግሁ::" †††
(መዝ. 121:1-9)
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
2 499
2 499
2 499
🔴 ኦርቶዶክስ ኖት ❓️
🌹🌹🌹
🌹🌹🌹🌹
🌹🌹🌹🌹🌹
🌹🌹🌹🌹🌹🌹
🌹🌹🌹🌹🌹🌹
🌹🌹🌹🌹🌹🌹
🌹🌹🌹🌹🌹
🌿🌹🌹🌿
🌿🌿
🌿
🌿 🌿🌿
🌿 🌿🌿🌿
🌿 🌿🌿🌿🌿
🌿 🌿🌿🌿🌿
🌿 🌿🌿🌿🌿
🌿 🌿🌿🌿
🌿
🌿
🌿
🌿
🌿
🌿
🔴የአበባውን ምስል አንድ ጊዜ በመጫን ጠቃሚ ነገር ይመልከቱ አንድ ጊዜ ብቻ ይንኩት፡፡❤
