Haala Ilaalcha Ortodoksii(ኦርቶዶክሳዊ ማዕቀፈ እሳቤ)
Открыть в Telegram
Waa'ee Mana Kiristaanaa Fi Biyya Keenyaa Haala Ilaalcha Ortodoksiin Hubachuu የቤተክርስቲያናችንና ሀገራዊ ሁኔታዎችን በኦርቶዶክሳዊ ማዕቀፈ እሳቤ መረዳት
БольшеСтрана не указанаКатегория не указана
273
Подписчики
Нет данных24 часа
-37 дней
-1330 день
Архив постов
+1
"እኞች "ፍጅቱ ተባባሪዎች ናቸው
👉 እልቂት እንዳይፈጸም አስቀድመው አይሠሩም
👉 ከተፈጸመ በኋላም ፈጥነው መግለጫ አያወጡም
👉 መግለጫ አወጡ ብንል እንኳ "እናዝናለን" እያሉ ከመሳለቅ በቀር የገዳዩን ስም አይጠቅሱም፣መንግሥትን አይኮንኑም፣እንደውም ይባስ ብለው እልቂታችንን ለመሸፋፈን እስከ ቦታው ድረስ ሰው ልከው "ኦርቶዶክሳውያን አልሞቱም"ያስብላሉ
👉 "እየተወያየን ነው፣ እየተነጋገርን ነው፣ኮሚቴ አቋቁመናል...እያሉ ሕዝቡን ያዘናጉትና ያስፈጁታል( ሌላውን እንተወውና ስለ አርሲ የወጡ መግለጫዎችን መለስ ብለን እንቃኝ)
👉 የተጨፈጨፉትን ሄደው አይቀብሩም፣ያለጧሪ ቀበሪ ፣ያለ አሳዳግቢ ብቻቸውን የቀሩትን ሄደው አይጠይቁም አያጽናኑም(ለህንጻ ምርቃት ሲሆን ግን ተጠራርተው እዚያው አርሲ አሰላ ከተማ ድረስ ሄዱ ።ፍጅቱ የሚፈጸሙባቸው አከባቢዎች እምብዛም ከዚህ አይርቁም )
👉የተሰደዱትን መልሰው አያቋቁሙም የገንዘብ ድጋፍም አያደርጉም
👉ማንንም ሰው ስለ እልቂቱ እንዳይተነስ ያስፈራራሉ(አቡን ሳዊሮስ )
👉 ኦርቶዶክሳውያን በመከራና በሰቆቃ ውስጥ ሆነው እነርሱ መናፈሻ ይጎበኛሉ
👉ስለ ኦርቶዶክሳውያ ፍጅት የሚጮኹትን ያሳድዳሉ ለሥርዐቱ አሳልፈው ይሰጣሉ
👉"ሞት ብርቅ አይደለም አታከብዱ" እያሉ ሕዝቡን ያሳቅቃሉ
👉እንደዚህ ዘመን ለቤተ ክርስቲያን ተመችቷት አያውቅም ይላሉ
👉ከመንግሥት ጋር መጣላት አንፈልግም ይላሉ
👉በኦርቶዶክሳውያንን ላይ የሚፈጸመውን መፍጅት ለመሸፋፈን በሚነዛው ፕሮፓጋንዳ ሁሉ ተባባሪ ናቸው።
👉በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚፈጸመውን ሁለንተናዊ ጭፍጨፋ ለመታደግ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ አያደርጉም
ይኽን ማስተባበል ይቻል ይኾን?
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
የአሰኮ ኦርቶዶክሳውያንን ያስጨፈጨፉ ባለሥልጣናት
ሌሎች ስማቸው ያልተጠቀሱም ኡሉ
የፍትሕ ፀሕይ ስትወጣ በዘር ማጥፋት የሚፈለጉ ናቸው። ዛሬ ጊዜው የእነርሱ ስለሆነ ጠያቂም ከሳሽም የላቸውም።
https://t.me/Eyo21e
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
+2
በአርሲ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚፈጸመው የዘር ማጥፋት በመንግሥት መዋቅር የሚደገፍ ነው። ከፌዴራል እስከ ቀበሌው ድረስ ድረ ያለው ያለው መዋቅር ተሳታፊ ነው ።ፌዴራሉ ከላይ ሁኖ ይመራል።ከክልል እስከ ቀበሌ ድረስ ያሉ ባለሥልጣናት ፍጅቱን ያስፈጽማሉ ።
ለታሪክ ይቀመጥ
https://t.me/Eyo21e
በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ትናንት በተቀሰቀሰ መጠነ ሰፊ ጥቃት የ37 ምዕመናን ሕይወት ማለፉና ከ200 በላይ መኖሪያ ቤቶች መቃጠላቸውን ታወቀ
(መሠረት ሚድያ)- በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን በአሰኮ ወረዳ ከትናንት ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ተነጣጥሮ በተሰነዘረ መጠነ ሰፊ እና አሰቃቂ ጥቃት እስካሁን የ37 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ለመሠረት ሚዲያ ከአካባቢው የደረሰው መረጃ አመላከተ።
በጥቃቱ በአሰኮ ወረዳ በሚገኙት በጠለታ ገብርኤል እና በኩፍቴና መድኃኔዓለም አካባቢዎች ከፍተኛ ውድመትና ዘረፋ መድረሱ የታወቀ ሲሆን ሁለት ታሪካዊ አብያተ ክርስቲያናትን ጨምሮ 234 መኖሪያ ቤቶች ሙሉ በሙሉ በቃጠሎ መውደማቸውን ከአካባቢው በቀጥታ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
ይህ ጥቃት ዛሬ ግንቦት 24 ቀን ቀጥሎ የዋለ ሲሆን በወረዳው ስር በሚገኙ በርካታ ቀበሌዎች ውስጥ በአሁኑ ሰዓት 'እጅግ የከፋ' የተባለ ጥቃት እየተካሄደ መሆኑ ታውቋል።
ለመሠረት ሚዲያ በደረሰው ወቅታዊ መረጃ መሠረት በዛሬው ዕለት በዘዲቡ፣ በእሬቻ ሚካኤል፣ በሱንቴ ማርያም፣ በቦግዶ አቦ፣ በሌንጫ ኦዳ፣ በጂሶ እና በኳስ ድሬ ቀበሌዎች ውስጥ ጥቃቱ እየተፈፀመ ይገኛል።
የአካባቢው ነዋሪዎች ጥቃቱን በራሳቸው ኃይል መቋቋም የማይችሉበት ደረጃ ላይ ስላሉ እንዲሁም ንብረታቸውና መኖሪያ ቤታቸው የተቃጠለባቸውና ለሕይወታቸው የሰጉ በርካታ ቁጥር ያላቸው ነዋሪዎች በአሁኑ ሰዓት ወደ ጫካዎች በመሰደድ ላይ እንደሚገኙ ታውቋል።
"ነዋሪዎቹ ቀደም ሲል ባላቸው አቅም ራሳቸውን ለመከላከል ጥረት ያደርጉ የነበረ ቢሆንም የመንግሥት ካድሬዎች አካባቢውን በማረጋጋትና ዋስትና በመስጠት ስም ነዋሪውን እንዲዘናጋ በማድረጋቸው ምክንያት ሕዝቡ ለከፍተኛ ጥቃት ተጋልጧል" በማለት አንድ የአካባቢው ምንጭ በስልክ ተናግረዋል።
በዚህ ዙርያ ዛሬ ማምሻውን የወጡ ተጨማሪ ዘገባዎች ደግሞ የዚህን ጥቃት መነሻና አጠቃላይ የጀርባ ታሪክ በተመለከተ ተጨማሪ ማብራሪያዎችን ይሰጣሉ።
በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ያለው አጠቃላይ ትኩረት ወደ አገራዊ ምርጫው ማድላቱንና በዚሁ ሳቢያ በአካባቢው የተፈጠረውን የጸጥታ ክፍተት የታጠቁ ኃይሎች እንደ ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በጥቃቱ ላይ መሰማራታቸው ተገልጿል።
ይህ በምሥራቅ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ በሚገኙ አካባቢዎች በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ያነጣጠረው መጠነ-ሰፊ ጥቃት በአገራዊ ምርጫው ዋዜማና በዕለቱ የታቀደ ይመስል የተፈጸመ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ።
በወረዳው ሥር በሚገኘው ጠላታ ጨፋ ቀበሌ በተፈጸመው ጥቃት የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች መኖሪያ ቤቶች በተለየ ሁኔታ እየተለዩ መቃጠላቸውና ከብቶቻቸውን ጨምሮ በርካታ ንብረቶቻቸው በታጣቂዎች እየተዘረፉ መሆኑ ተረጋግጧል።
በዚህም የተነሳ ነዋሪዎቹ አካባቢያቸውን ሙሉ በሙሉ ለቀው ሱንቴ ወደሚባል ስፍራ ለመሰደድ ተገድደዋል።
በተመሳሳይ ሁኔታ በዚሁ ወረዳ በሚገኘው ካራ ኩፍቴና ቀበሌ የነዋሪዎች ቤቶች በተጠናከረ ሁኔታ እየተቃጠሉ በመሆኑ ሕዝቡ የመድኃኔዓለምን ታቦት በክብር ይዞ ሕይወቱን ለማዳንና ቅዱሳን ንዋያተ ቅድሳቱን ከቃጠሎ ለመታደግ ወደ ሱንቴ አካባቢ መሸሹ ታውቋል።
ይህ ጥቃት በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ብቻ ሳይሆን በታሪካዊ የሃይማኖት ተቋማት ላይም ያነጣጠረ እንደነበረ የተረጋገጠ ሲሆን ከ101 ዓመታት በላይ የአካባቢው ማኅበረሰብ ታሪካዊ መለያ ሆኖ የቆየው የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በቃጠሎ ወድሟል ተብሏል።
ከዚህም በተጨማሪ የካራ ኩፍቴና መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ንብረት የሆኑ ልዩ ልዩ የአገልግሎት መስጫ ክፍሎች፣ የእንግዳ ማረፊያዎችና ልዩ ልዩ ሕንፃዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ በእሳት እንዲጋዩና እንዲወድሙ መደረጋቸው ተሰምቷል።
ይህ በተደጋጋሚ ጊዜያት መሰል አሰቃቂ ጥቃቶች እንደሚፈጸሙበት የሚነገረው የምሥራቅ አርሲ አካባቢ አሁንም በአገራዊ ምርጫው ዋዜማና በዕለቱ መጠነ-ሰፊ የጥቃት ሰለባ መሆኑ የአካባቢውን ማኅበረሰብ እጅግ አሳዝኗል።
ነዋሪዎቹ በአሁኑ ሰዓት በጫካዎች ውስጥ ተጠልለው የሚገኙ ሲሆን ለሕይወታቸውና ለቀሪው ንብረታቸው ምንም ዓይነት የጸጥታ ከለላ እንደሌላቸው በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።
"ድምፅ ሁኑን እባካችሁ" በማለት ለመሠረት ሚዲያ ድምፃቸውንና ምሬታቸውን ያስተላለፉት የአካባቢው ተወላጆች መንግሥትና የሚመለከታቸው የፌደራልና የክልል የጸጥታ አካላት በአስቸኳይ ጣልቃ በመግባት ይሄንን እየተካሄደ ያለውን ደም አፋሳሽ ጥቃትና መፈናቀል እንዲያስቆሙ፣ ለተፈናቀለውና በጫካ ውስጥ ለሚገኘው አቅመ-ቢስ ሕዝብም አስቸኳይ የሰላምና የሰብአዊ ድጋፍ እንዲቀርብ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
መሠረት ሚዲያ በአካባቢው ያለውን ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታና ተጨማሪ መረጃዎችን በቅርበት እየተከታተለ ለሕዝብ የሚያደርስ መሆኑን ይገልፃል።
| መሠረት ሚድያ |
Gurra Kan qabu haa dhaga’u
Nuti hordoftoonni amantaa Ortodoksii akka uummataatti lafa kana irratti jiraachuu kan dandeenyu:
1. Gadi fageenya dhukkubbii keenyaa hubannee waliin dhukkubsachuu fi waliin qabsaawuu yoo eegalledha,
2. Dhibee gandummaa, naannummaa fi sanyummaa irraa bilisa taanee tokkummaan dhaabbachuu yoo dandeenyedha,
3. Hanga gubbaa Sinnoodositt caasaa mana kiristiyaanaa kan dhuunfatan, garaa isaanii yoo guutee fi qomni isaanii gabbatee baqanni mana kiristaanaa fi duguuggaan Ortodoksitootaa kan isaan hin gaddisiisne, akkasumas caasicha meeshaa balleessitootaa kan taasisan hattoonni, basaastoonni fi warri amantaa hin qabne caasichaa keessaa haxaa’amanii yoo ba’an qofadha.
👉 Inni tokko gubachaa inni biraan yoo qoose dhumiinsi keenya hin dhaabbatu
👉 Qulqulluu of fakkeessuun dhumaatiin keenya hin dhaabbatu
👉 Bakka haqni hin jireetti haqa jechaa iyyuun dhumaatiin keenya hin dhaabbatu
👉 Gandummaa fi sanyummaan addaan ba’uun/qoqqoodamuun duguuggaan keenya hin dhaabbatu
👉 Dubbii shiraafi qumaaraa hamtootaatiin dhumaatiin keenya hin dhaabbatu
👉 Tikseewwan basaastotaafi amantaa hin qabne duukaa deemuun dhumaatiin keenya hin dhaabbatu
👉 Barsiisota fi faarfattoota sammuu hadoochan duukaa deemuun dhumaatiin keenya hin dhaabbatu
👉 Caasaa meeshaa balleessitootaa ta’e eeguun dhumaatiin keenya hin dhaabbatu
Yoo hadhaa’es dhugaansaa kanadha
Hamma ammaattii odeeffannoo naqaqqabeen, kaleessa (23/09/2018 A.L.H) Zoonii Arsii Bahaa keessatti aanaalee sadii qofa keessatti hordoftoonni amantaa Ortodoksii 14 ajjeefamaniiru. Aanaa Honqoloo Waabeetti 2, Shirkaatti 2, akkasumas Aanaa Asakootti Ortodoksoonni 10 ajjeefamaniiru. Duguuggaan sanyii kun hundi caasaa mootummaatiin kan raawwatamudha.
እስካሁን በደረሰኝ መረጃ መሠረት በትናንትነው ዕለት(23/09/2018ዓ.ም) በምሥራቅ አርሲ ዞን በሦስት ወረዳዎች ብቻ 14 ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል።በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 2፣በሽርካ 2 እና በአሰኮ ወረዳ 10 ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል። ይኽ ሁሉ እልቂት በመንግሥት መዋቅር የሚፈጸም ነው።
እስካሁን በደረሰኝ መረጃ መሠረት በትናንትነው ዕለት(23/09/2018ዓ.ም) በምሥራቅ አርሲ ዞን በሦስት ወረዳዎች ብቻ 14 ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል።በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 2፣በሽርካ 2 እና በአሰኮ ወረዳ 10 ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል። ይኽ ሁሉ እልቂት በመንግሥት መዋቅር የሚፈጸም ነው።
ሀገራዊ ምርጫውን ተገን በማድረግ በምሥራቅ አርሲ በኦርቶዶክሳውያን ላይ ዘግናኝ ጥቃት ተፈጸመ፤10 ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል አብያተ ክርስቲያናትና የነዋሪዎች ንብረቶች ተቃጥለዋል
የሁሉም ትኩረት በሀገራዊ ምርጫ ላይ ማረፉን እንደ ምቹ ሁኔታ በመጠቀም፣ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ በሚገኙ አካባቢዎች በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ያነጣጠረ መጠነ-ሰፊ ጥቃት መፈጸሙ ተገለጠ። ከትላንት ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በተቀሰቀሰው በዚህ ጥቃት የሰው ሕይወት ማለፉን፣ ታሪካዊ አብያተ ክርስቲያናት መቃጠላቸውንና ከፍተኛ የንብረት ዘረፋና ውድመት መድረሱን የአካባቢው መረጃዎች አመልክተዋል።
የሰው ኃይል ጉዳት እና መፈናቀል በወረዳው ሥር በሚገኘው ጠላታ ጨፋ ቀበሌ በተፈጸመው ጥቃት እስካሁን የ10 ሰዎች ሕይወት በግፍ ማለፉ ተረጋግጧል።
በጥቃቱ ወቅት የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች መኖሪያ ቤቶች ተለይተው እየተቃጠሉና ከብቶቻቸውን ጨምሮ በርካታ ንብረቶቻቸው እየተዘረፉ መሆኑ ተመልክቷል።
በዚህም ምክንያት ነዋሪዎቹ አካባቢያቸውን ለቀው ሱንቴ ወደሚባል ስፍራ ለመሰደድ ተገደዋል።
በተመሳሳይ ሁኔታ በዛው ወረዳ በሚገኘው ካራ ኩፍቴና ቀበሌ የነዋሪዎች ቤቶች እየተቃጠሉ በመሆኑ፣ ሕዝቡ የመድኃኔዓለምን ታቦት ይዞ ሕይወቱን ለማዳን ወደ ሱንቴ አካባቢ መሸሹ ታውቋል።
በአብያተ ክርስቲያናት ላይ የደረሰ ውድመት
ጥቃቱ በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ብቻ ሳይሆን በታሪካዊ የሃይማኖት ተቋማት ላይም ያነጣጠረ ነበረ። በዚህም መሠረት ከ101 ዓመታት በላይ ያስቆጠረው የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በቃጠሎ ወድሟል።
የካራ ኩፍቴና መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ንብረት የሆኑ ልዩ ልዩ የአገልግሎት መስጫ ቤቶችም ተቃጥለዋል።
የጥቃቱ ወቅታዊ ሁኔታ የአካባቢው ምንጮች እንደሚጠቁሙት፣ ጥቃቱ የተፈጸመው በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ያለው አጠቃላይ ትኩረት ወደ አገራዊ ምርጫው ባዘነበለበት ማግስት፣ የተፈጠረውን የጸጥታ ክፍተት እንደ ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ነው።
ይህ በተደጋጋሚ ጥቃት እንደሚፈጸምበት የሚነገረው የአርሲ አካባቢ ኦርቶዶክሳውያን፣ አሁንም በምርጫው ዋዜማና ዕለት የጥቃት ሰለባ ሆኗል።
ድምፀ ተዋሕዶ
አሳዛኝ ዜና
በምሥራቅ አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ ሚታና ዋጂ ቀበሌ ሁለት ወንድማማች ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል። ትናንት ማለትም 23/09/2018 ዓ.ም ምሽት ቤታቸው ገብተው ሁለቱንም አፍነው ወሰደዋቸው 10ከ.ሚ በላይ እንዲጓዙ ካደረጉ በኋላ ጋዶ ማርያም ቤተ ክርስቲያን በቅርብ ርቀት ላይ አንዱን በአሰቃቂ ሁኔታ ያረዱት ሲሆን አንደኛውን ደግሞ ረሽነው ጥለው ሄደዋል።ሥርዐተ ቀብራቸው ዛሬ በጋዶ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።ጥቃቱን የፈጸሙት በመንሥት መዋቅር የሚመሩት አክራሪ ወሀቢያዎቹ ናቸው።
https://t.me/Eyo21e
ጆሮ ያለው ይስማ
እኛ ኦርቶዶክሳውያን እንደ ሕዝብ በዚህች ምድር ላይ መኖር የምንችለው፦
፩ የሕመማችንን ጥልቀት ተረድተን እኩል መታመም ስንጀምርና እኩል መታገል ስንጀር
፪ ከጎጠኝነት፣ከመንደርተኝነት እና ከዘረኝነት ደዌ ተላቀን በኅብረት መቆም ስንችል
፫ ከአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ጀምሮ እስከ ሲኖዶስ ቤተ ክህነቱን የተቆጣጠሩ ሆዳቸው ከሞላ ደረታቸው ከቀላ የቤተ ክርስቲያን ስደት የኦርቶዶክሳውያን እልቂት የማይገዳቸው መዋቅሩን የአጥፊዎች መጠቀሚያ ያደረጉ አረመኔዎች፣ምንደኞችና ኢአማንያን ተጠራርገው ሲወጡ ነው።
👉 አንዱ እያረረ ሌላው እየቀለደ እልቂታችን አይቆምም
👉 ጻዲቅ ጻዲቅ በመጣወት እልቂታችን አይቆምም
👉ፍትሕ በሌለበት ፍትሕ እያሉ በመጮህ እልቂታችን አይቆምም
👉 በጎጥና በዘር በመለያየት እልቂታችን አይቆምም
👉 በተንኮለኞች ቁማራዊ ንግግር እልቂታችን አይቆምም
👉 ምንደኛ ና ኢአማንያን እረኞችን በመከተል እልቂታችን አይቆምም
👉አድርባይና አደንዛዥ መምህራንንና ዘማርያንን በመከተል እልቂታችን አይቆምም
👉የአጥፊዎች መጠቀሚያ የሆነን መዋቅር በመጠበቅ እልቂታችን አይቆምም
ቢመርም እውነታው ይኽ ነው!!!
https://t.me/Eyo21e
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
የኦርቶዶክሳውያን ደም ለምርጫው ግብር
አርሲ አሁንም በኦርቶዶክሳውያን ደም መጨቅየቷን ቀጥላለች።በምሥራቅ አርሲ ዞን ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ በሥልጣና ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ ሁለት ታላላቅ ኦርቶዶክሳውያን አባወራዎች በአሰቃቃ ሁኔታ ተገድለው ደማቸው ለምርጫው ግብር ሆኖ ቀርቧል።ይኽ በእንዲህ እንዳለ ጭፍጨፋው ከሚፈጸሙባቸው ወረዳዎች ከሽርካ፣ከጉና፣ከአሰኮ፣ከመርቲ "ሊገድሉን እየፈለጉን ነው" የሚሉ መረጃዎች በተደጋጋሚ እየደረሱኝ ነው።
የእኔ መልእክት፦
ነጻነት በብላሽ አይገኝምና ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ኅልውናውን ለማስከበር መነሳት አለበት።ከዚህ ውጭ መውጫ መንገድ የለም ።
Qoosuun Dawweessuu
Naxalaa uffachuu qofaan rakkoo Mana Kiristanaa ni hiikama jedhanii yaaduun mana Kiristaanarratti qoosuu dha.
Onneen laafanii kanneen biroo laaffisan ofii isaaniitiyyuu rakkoodha malee furmaata rakkichaa miti.
"Jireenyi keessan nu hin yaaddessu, maallaqa keessan qofa barbaanna" jechuun Wangeelli dhalootaaf itti fufuu dandeessii? Gonkumaa itti hin fuftu.
"Isin mootummaa waaqayyootti namoota fulduratti waan cuftaniif, isiniif wayyoo! Ofii keessanii hin galtan, kanneen galanillee akka hin galle ni dhowwitu" (Maatewos 23:13) jechuun jechi dubbatame sun akka nu hin dhaqqabne ni sodaachiisa.
በማፌዝ ማፋዘዝዝ
ነጠላ በመላበስ ብቻ የቤተ ክርስቲያን ችግሩን ለመፍታት ማሰብ በቤተ ክርስቲያን ማፌዝ ነው።
በየዓውደ ምህረቱ በተሰለበ ልቡና በመለገብ ብቻ ችግሩን እፈታለሁ ማለት በምእመናን ሞት መሳለቅ ነው።
ተሰልበው የሚሰልቡ ስልብ ልቦች ራሳቸው ችግር ናቸው እንጂ ችግር ፈቺ አይደሉም።
ሕይወታችሁ አያገባንም ገንዘባችሁን ግን እንፈልገዋለን በማለት ወንጌል ለትውልድ ትቀጥላለች? በፍጹም አትቀጥልም።
"መንግሥተ ሰማያትን በሰው ፊት ስለምትዘጉ ወዮላችሁ እናንተ አትገቡም የሚገቡትንም እንዳይገቡ ትከለክላላችሁ።"ማቴ.፳፫፥፲፫ ያለው ቃል እንዳይደርስብን ያስፈራል።
Repost from ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት
✔️በቋንቋ የሚመሰገን መንፈስ ቅዱስ እንጂ በቋንቋ የሚከፋፈል መንፈስ ቅዱስ የለም።
✔️የሰናኦር ሰዎች በ፴፻ (በሦስት ሺህ) ዐመተ ዓለም ከእግዚአብሔር ርቀው ሰናኦር በሚባል ሜዳ ሰፍረው ከሞት የሚድኑበትን ረጅም ህንጻ ገነቡ እግዚአብሔርም አምላክ በአምላክነቱ ንጉሥ በመንግሥቱ ጎልማሳ በሚስቱ የመጡበት እንደሆነ አይወድምና ቋንቋቸውን ከሰባ አንድ ከፋፈለባቸው መግባባት ተስኗቸው እርስ በእርሳቸው የሚገዳደሉና የሚጫረሱ ሆነዋል ። እስከዚያ ዘመን ድረስ ግን ሁሉም በአንድ ቋንቋ ይናገሩ ነበር።፤ስለዚህም፡ስሟ፡ባቢሎን፡ተባለ፥እግዚአብሔር፡በዚያ፡የምድርን፡ቋንቋ፡ዅሉ፡ደባልቋልና፤ከዚ ያም፡እግዚአብሔር፡በምድር፡ዅሉ፡ላይ፡እነርሱን፡በትኗቸዋል።
ዘፍ ፲፩÷፱
✔️ክርስቶስ ሰው ሆኖ በዚህ ምድር ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ተመላልሶ ወንጌልን አሰተምሮ ወደሰማይ ካረገ በኋላ ባረገ በአስረኛው በተነሳ በአምሳኛው ቀን ለሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ልኮ በዓለሙ ያለውን ቋንቋ ሁሉ ገልጾላቸዋል ።
በዅሉም፡መንፈስ፡ቅዱስ፡ሞላባቸው፥መንፈስም፡ይናገሩ፡ዘንድ፡እንደ፡ሰጣቸው፡በሌላ፡ልሳኖች፡ይናገሩ ዠመር
ሐዋ ፪÷፬
✔️ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ ልዩ ልዩ ቋንቋን የገለጠ ሊመለክበት ዓለምም አንድ ሊሆንበት እንንጂ ዓለም ሊከፋፈልበት አይደለም።
ከዚህም፡በዃላ፡በዓለም፡አይደለኹም፥እነርሱም፡በዓለም፡ናቸው፥እኔም፡ወዳንተ፡እመጣለኹ ቅዱስ፡አባት ሆይ እነዚህን፡የሰጠኸኝን፡እንደ፡እኛ፡አንድ፡እንዲኾኑ፡በስምኽ፡ጠብቃቸው ዮሐ ፲፯÷፲፩
✔️ቋንቋ ምክንያት ሆኖ ከእግዚአብሔር የሚያርቅ ከሆነ እርሱ ሰይጣን እንጂ ቋንቋ ሊባል አይችልም።
✔️ቋንቋ ከሃይማኖት በላይ ሆኖ ሰውን ከቤተክርስቲያን የሚያርቅ እግዚአብሔርን የሚያስክድ ከሆነ? እርሱ ጣዖት እንጂ ቋንቋ አይደለም።
✔️ቋንቋ ከክርስትና በላይ ሆኖ ቋንቋየን ያላከበረ ሃይማኖት ይቅርብኝ የሚያሰኝ ከሆነ እርሱ ትውልድን ከእግዚአብሔር ጉያ እየነጠቀ የሚበላ ተኵላ እንጂ ቋንቋ አይደለም።
✔️ቋንቋ እግዚአብሔርን የምናመልክበት እንጂ እግዚአብሔርን የምንክድበት ከሆነ ምክንያት ሆኖ አዳምና ሔዋንን ያሳተ ዲያብሎስ እንጂ ቋንቋ አይደለም።
✔️ቋንቋ የነባቢነት መገለጫ እንጂ የማንነት መገለጫ አይደለም ማንነትም አይደለም።
✔️ቋንቋ በዓቅማችን እግዚአብሔርን አመስግነን መንግሥተ ሰማያትን የምንወርስበት እንጂ ከመንግሥተ ሰማያት የምንወጣበት መሆን የለበትም።
✔️ጥንቱን ሰው ሲፈጠር መግባቢያ ቋንቋ ተሰጠው እንጂ ለቋንቋ የተፈጠረ ሰው የለም ለመንግሥተ ሰማያት እንጂ ለቋንቋ የተፈጠረ ሰው የለምና።
✔️ለሐዋርያት ሰባ አንድ ቋንቋን የገለጠ ሰውን ሁሉ በሚሰማው ቋንቋ ወንጌልን እንዲያስተምሩበት እንጂ ማንነቴ መገለጫዬ ወዘተ እያለ ዓለም ከወንጌል እንዲርቅበት አይደለም ።
✔️ቋንቋ ተናጋሪ ትውልድ እንጂ ቋንቋ የሆነ ትውልድም የለም።
ለምሳሌ፦
አምሐርኛ ተናጋሪ ሰው እንጂ አማራ የሚባል ሰው የለም።
ኦሮሞኛ ተናጋሪ ሰው እንጂ ኦሮሞ የሚባል ሰው የለም።
ትግርኛ ተናጋሪ ሰው እንጂ ትግሬ የሚባል ሰው የለም።
አገውኛ ተናጋሪ እንጂ አገው የሚባል ሰው የለም።
ዓረብኛ ተናጋሪ ሰው እንጂ ዓረብ የሚባል ሰው የለም።
እንግሊዝኛ ተናጋሪ ሰው እንጂ እንግሊዝ የሚባል ሰው የለም።
ፈረንሳይኛ ተናጋሪ ሰው እንጂ ፈረንሳይ የሚባል ሰው የለም።
✔️በመጨረሻም እግዚአብሔር ለፍርድ ሲመጣ ሰውን በመላ በሁለት ከፍሎ ጻድቃንና ኃጥአን (በጎችና ፍየሎች) ብሎ ይከፍለዋል እንጂ በቋንቋውም በብሔሩም በሀገሩም በሰፈሩም በዘር ሐረጉም አይጠራውም ።
✔️ለሰው ልጅ በሙሉ ከእግዚአብሔር ጋራ የሚግባባበት ቋንዉ ግብሩ እንጂ ዘይቤ ቋንቋ አይደለምና።
አሕዛብም፡ዅሉ፡በፊቱ፡ይሰበሰባሉ፤እረኛም፡በጎቹን፡ከፍየሎች፡እንደሚለይ፡ርስ፡በርሳቸው፡ይለያቸዋል፥
በጎችን፡በቀኙ፡ፍየሎችንም፡በግራው፡ያቆማቸዋል
ማቴ ፳፭÷፴፪~፴፫
✔️ስለዚህ በግብር እንጂ በዘር
በበጎነት እንጂ በቋንቋ
በአንድነት እንጂ በልዩነት የምትወረስ መንግሥተ ሰማያት የለችም።
