7 367
مشترکین
+424 ساعت
+907 روز
+34030 روز
آرشیو پست ها
7 374
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
እነዚህን ቪድዮዎች አድምጣችሁ ጽሑፉንም ካነበባችሁ በኋላ ምን እንደተረዳችሁ አስተያየቶቻችሁን ታስቀምጣላችሁ
👇👇
7 374
ሥርዐቱ የኦርቶዶክሳውያን እልቂት ለማስቀጥል ለሽፋንና ለማደንዘዣነት የሚጠቀምባቸው፦
👉የሰብአዊ አ መብት ኮሚሽን
👉 ኢሰመኮ
👉 ኢሰመጉ
👉ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን
👉የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ
👉 የሃይማኖት አባቶችን ሽማግሎችንና አባ ገዳዎችን
የቀረውን እናንተ ጨምሩበት
7 374
የእምነትና የጽናት ጥሪ!!
👉ለኦርቶዶክሳዊው እና ለሀገር ወዳዱ የፀጥታ አካላት አባል፦
👉ክቡር የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባልና የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጅ ሆይ!!
👉አንተ የቅዱስ ጊዮርጊስና የቅዱስ መርቆሬዎስ የፅናት ማኅተም በልብህ የታተመብህ፣ በታሪክ አጽናኝነቷና በነጻነት ጠባቂነቷ በምትታወቀው የቅድስት ተዋሕዶ እምነት እቅፍ ውስጥ የበቀልክ ጀግና ነህ።
👉መሣሪያህን ይዘህ የሀገርን ድንበር ስትጠብቅ፣ ከውስጥህ ያለው የእምነትህ መሠረትና የነፍስህ ዋስትና ግን ይቺው በደም የጸናችው ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖትህ ናት።
👉ዛሬ ግን አንተ በተጠንቀቅ በቆምክበት፣ መስዋዕትነት በምትከፍልበትና በምትታዘዝበት መዋቅር ውስጥ ሆነህ፣ ከጀርባህ የእምነትህን ሥርዓት የሚሸረሽሩ፣ ታሪኳንና ክብሯን የሚያደበዝዙ፣ የቅዱሳኑን ቅርስና ትውፊት የሚንዱ ድርጊቶች ሲፈጸሙ በዝምታ ልትመለከት አይገባም!!
"እግዚአብሔርን ከመታዘዝ ይልቅ ለሰው ልንታዘዝ ይገባል?" (የሐዋርያት ሥራ 5:29)
👉የምድራዊ ሥልጣንና የዕዝ ሰንሰለት ክብር እንዳለው ሁሉ፣ ከሁሉ በላይ የሚገዝፈው ግን የሰማያዊው አምላክ ሕግና የሃይማኖትህ ህልውና ነው።
👉ሃይማኖትህ ስትደፈር፣ ሥርዓቷ ሲጣስና ተቋማዊ ክብሯ አደጋ ላይ ሲወድቅ እያየህ «እኔ ወታደር ነኝና ዝም እላለሁ» ማለት የነፍስ ምርኮኛ መሆን ነው።
👉ንቃ!! ተነስ!!
👉ዝም አትበል፦ በዝምታህ ውስጥ የእምነትህ መሸርሸር ፈቃድ እንዳገኘ አይቆጠር።
👉እምቢ በል፦ የቅድስት ቤተክርስቲያንን ክብርና ሉዓላዊነት ከሚጋፉ፣ ሥርዓቷን ከሚያናጉና ተጽዕኖ ከሚያሳድሩ ድርጊቶች ጎን አትቆም።
👉እምነትህን ታደጋት፦ አንተ የእናት ቤተክርስቲያን ልጅ ነህ፤ ዛሬ እሷን ካልታደግሃት ነገ የምትመለስበት መቅደስ፣ የምትባረክበት ጸበል፣ ነፍስህን የሚያማትብባት ካህን ታጣለህ።
👉መቸም ከጎንህ የነበረው ጓደኛህ ተለይቶህ አፈር እንደሆነ ታውቃለህ? ያን አስበው!!አንተን የጠበቀህ አምላክ ለእምነትህ ታሪክ እንድትሠራ ነው።
👉ምድራዊ ግዴታህ የሀገርን ደህንነት መጠበቅ እንደሆነ ሁሉ፣ መንፈሳዊ ግዴታህ ደግሞ የነፍስህን ማደሪያ እምነትህን ከጥፋት መከላከል ነው።
👉ክንድህ ለሀገር ጋሻ ሲሆን፣ ልብህና ፅናትህ ደግሞ ለሃይማኖትህ ግንብ ይሁኑ!
👉የቀደሙት አባቶችህ በጦር ሜዳም ጭምር ታቦት አስቀድመው፣ አምላከ ቅዱሳንን ተማጽነው እምነታቸውንም ሀገራቸውንም አጽንተው አሳልፈውልሃል። አንተም ዛሬ ታሪክህን ጠብቅ፣ እምነትህን አትክዳ፣ እምነትህን ከሚሸረሽር ሥርዓት ራስህን አግልል!!!
👉ከዛሬ ጀምሮ ለእምነትህና ለሕሊናህ እምቢ በል! ወላጅ እናትህ ስለአንተ ሕይወት የምትማጸንባትን ቅድስት ተዋሕዶን ታደጋት!!!
👉አንተ የምታገለግለው ሥርዓት ፀረ ሀገር፣ፀረ ሕዝብ፣ፀረ ሃይማኖት ነውና እሄን የምታገለግል ከሆነ ግን ባትፈጠር ይሻልህ ነበር።
7 374
Repost from እምየ ተዋሕዶ ሚዲያ - Emye Tewahedo Media
በኦርቶዶክሳዊት ግድያ እና እስር የቀጠለ ሲሆን
በጎንደር ወንድማችን ዘመነ ሐብቱ
የጠዳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን እና የሲነርጂ ፎር ሶሻል ቼንጅ የቦርድ ሰብሳቢ ወንድማችን ለምን ስለ አርሲ ድምፅ ሆንክ ተብሎ ከትላንት ግንቦት 29/2018 ዓ/ም ጀምሮ በጎንደር ከተማ 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ በህግ ጥላ ስር ይገኛ ከዋጣ ቀጥሉበት
ሰላም አደራችሁ ውድ ኦርቶዶክሳዊያን
7 374
የይህንን መርዶ ሰምታችኋል!
🗡በአርሲ በባሌ በሐረረ አንድም ኦርቶዶክሳዊ እንዳይኖር እየተሰራ መሆኑን
ከዛም የዋሀቢያ እስልምና ዋና የስልጠና እና የእስትራቴጂክ ቦታ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑ።
🗡በዚህ ሁሉ ኦርቶዶክስን የማጥፋት ዘመቻ ዛሬ ያለው የምጥ መጀመሪያ መሆኑን እና ቁጥሩን የመቀነስ ስራ እየተሰራ መሆኑና ከዛም ጨርሶ ማ*ጥፋት እቅድ እንዳለ።
🗡ዛሬ ኦርቶዶክሳዊያን በሚበዙበት ቦታ ስልታዊ እና ምሥጢራዊ በሆነ መልኩ አማንያንን ማጽዳት፣ ማሸማቀቅ እና የስነ ልቦና ጫና እየደረሰባቸው መሆኑን
7 374
ከግድያ ተርፈው ቤታቸው ሙሉ ሙሉ ወድሞ የተሰደዱ ኦርቶዶክሳውያን በተጠሉበት ቦታ ላይ የምግብ ዕርዳታ ከማቅረብ ይልቅ ኦርቶዶክሳውያን ብቻ አልተገደሉም የሚል የውሸት ፕሮፓጋንዳ ለመሥራት የመንግሥት ሚዲያዎች ወደ አሰኮ ወረዳ አቅንተዋል ።
7 374
7 374
ሌላውን ዝባዝንኬ ንግግሩን ትተን በዋናነት ሊነግረን የፈለገውን መልእክት ከመረመርነው......... "ሺህ መግለጫ ስታወጣ ውለህ ብታድር የመግለጫ ብዛት ከመገደልና ከመሳደድ አያድንህም" ብሎሃል። አራት ነጥብ።
7 374
ሰላም ወንድሜ?እንዴት ነህ? አርሲ ዞን ከመርቲ ወረዳ ነው የምጽፍልህ።ዛሬ የሆነውን ልንገርህ። ከአቦምሳ ከተማ ለአክራሪ እስላም ታጣቂዎች ሬሽን በገፍ ተጭኖ ስሄድ አይተናል ነገር ግን አንድም የጠየቃቸው የመንግሥት አካል የለም።ይህ ምን ያክል እየተናበቡ እንደሚገድሉን የሚገልጽልን ነው።
