Puritans pool
رفتن به کانال در Telegram
Now that we have all this sound doctrine,we need to see it applied and worked out in our head and our hearts and in our hands,and we need to see it worked out in our homes, in our Churches,and our communities,and live in accordance with it everywhere.
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
417
مشترکین
+424 ساعت
+67 روز
+1730 روز
آرشیو پست ها
God hath given us divers ordinances to be exercised in, that if we be dull and weary in one, we may go to another, if you be weary in prayer, you may go to reading; if weary in reading, then go to meditating; if weary in meditation, you may go to conference; if you will spend your self only in one duty, there will dulness and deadness upon you; but if you exercise your self according to that variety which God hath given you, your heart will be kept up with an holy freshness unto things above.
William Bridge
Prayer/ጸሎት
Puritans በእርግጥም የጓዳ ሰዎች ነበሩ። ለጸሎት ብቻ በተለየችው በዚያች የግል ጓዳቸው ውስጥ ሆነው፣ በራሳቸው፣ በአገልግሎታቸው፣ በቤተሰባቸው፣ በአብያተ ክርስቲያናቶቻቸውና በሀገራቸው ላይ መለኮታዊ በረከት እንዲወርድ ወደ እግዚአብሔር ድምፃቸውን አውጥተው ይጮኹ ነበር። ጸሎትን በሰማይ እና በአማኙ ነፍስ መካከል የሚደረግ ቅዱስ ሕብረት መሆኑን በመገንዘብ ሃሴት ያደርጉ ነበር። ቅዱሳት መጻሕፍት የተለያዩ የጸሎት ዓይነቶችን ያስተምራሉ ፤ ለአብነት ያኽል፦ የእግዚአብሔርን ክብር praise ማድረግ፣ ኃጢአትን መናዘዝ፣ ፍላጎትን መጠየቅ፣ ስለ እግዚአብሔር ምሕረት ምስጋናን ማቅረብ፣ ስለ ሌሎች ማማለድ፣ እንዲሁም እግዚአብሔር ለጸሎት መልስ ለመስጠት ፈቃደኛና ቻይ መሆኑን በልበ ሙሉነት መመስከር ናቸው...እውነተኛ ጸሎት በእግዚአብሔር ፊት በሚቀርብ ቅንነትና ፍቅር (ናፍቆት) ይገለጣል። በልብ ውስጥ የሌለውን ነገር በአፍ ብቻ ማነብነብ ግብዝነት ነው። Thomas Brooks ሲጽፍ እንዲህ ብሏል፦ “ልባችን በቅንነትና በሙሉነት ካልተገኘበት በቀር፣ በእግዚአብሔር ዘንድ የታወቀ፣ የተወደደ፣ የተቀበለው፣ የተመዘገበ ወይም ዋጋ የተሰጠው ምንም ዓይነት ጸሎት የለም።"...እውነተኛ ጸሎት በእግዚአብሔር የተስፋ ቃላት ላይ የተመሠረተ ነው። Puritans ብዙ ጊዜ በጸሎታቸዉ የእግዚአብሔርን የተስፋ ቃላት በእምነት ወደ እርሱ መልሰው ይጸልዩ ነበር። William Gurnall ሲጽፍ፦ “ጸሎት ማለት እግዚአብሔር የሰጠንን የተስፋ ቃል መልሰን ለእርሱ የምናቀርብበት፣ ወይም የእግዚአብሔርን ቃል ሞግቶ በእምነት አማካኝነት መልሰን ወደ እግዚአብሔር የምንሰነዝርበት መንገድ እንጂ ሌላ አንዳች አይደለም”። እግዚአብሔር በሉዓላዊነቱ ለቤተክርስቲያኑ በሰጣቸው የተስፋ ቃላት እራሱን አስሯል(bound አርጓል)። ውጤታማ የጸሎት ሕይወት እንዲኖረን ከፈለግን፣ በጸሎታችን ጊዜ የእግዚአብሔር የእራሱን የእጅ ጽሕፈት (የተስፋ ቃሉን) እንዲያይ ማድረግ አለብን። በfervent prayer ጌታ አብዝቶ ይባርከን!
Meditation(ተመስጦ፣አንድን ነገር በጥልቀት ማሰብ፣ማዉጠንጠን፣ማሰላሰል)
Puritans መፅሐፍ ቅዱሳዊው meditation ሁለት ነገርን ያማከለ ነው ይላሉ፤እነሱም ሥሉስ አምላክን እና ቅዱስ ቃሉን ማሰብ ነው። ጤናማ የሆነ meditation ሊኖረን የሚችለው ሕያው በሆነው ቃል፣በኢየሱስ ክርስቶስ እና በተፃፈው በእግዚአብሔር ቃል፣በመፅሐፍ ቅዱስ አዕምሮአችንንና ልባችንን ስንሞላ ነው። ምክንያቱም ሰው ክርስቲያን ሆኖ እንኳን meditate እያረኩ ነው በሚል ብዙ ጉድ የሚያስብሉ ነገሮችን ሊያዉጠነጥን ይችላል። ለMysticism ማለትም መፅሐፍ ቅዱሳዊ ይዘት ለሌለው ምናባዊና ቅዠት ለሞላው አስተሳሰብ ተጋላጭ ይሆናል። Puritans meditationን በመፅሐፍ ቅዱስ ጥናት/ስብከትን በመስማት እና በፀሎት መሐከል ያስቀምጡታል። በሌላ ቋንቋ meditation ማለት አማኙ ያነበበውን ወይም የሰማዉን የእግዚአብሔር ቃል በማሰላሰል፣ስለእራሱ እና ስለ እግዚአብሔር የተገነዘበውን በጸሎት ሕይወቱ ተግባራዊ በማድረግ ብዙ በረከት የሚያገኘበት መሣሪያ ነው።
Puritans ስለ ሁለት ዓይነት meditation አስተምረዋል፣እራሳቸውም exercise አድርገዋል። እነሱም occasional(አልፎ አልፎ፣አጋጣሚን መሠረት ያደረገ አሰላስሎት) እና deliberate(ሆን ተብሎ፣አቅዶ የሚደረግ አሰላስሎት) ናቸዉ። occasional meditation ማለት አንድ አማኝ በዓይኑ የሚያየውን፣በጆሮው የሚሰማውን ነገር ሰማያዊ የሆኑ ነገሮችን ለማሰብ ይጠቀምበታል። ዳዊት በመዝሙር 8 ላይ ስለ ጨረቃና ከዋክብት ያደረገው፣ ሰሎሞንም በምሳሌ 6 ላይ ስለ ጉንዳኖች ያደረገው ፣ እንዲሁም ክርስቶስ በዮሐንስ 4 ላይ ስለ ጉድጓዱ ውኃ የተናገረው ይህንኑ ነበር። ከእዚህ በላይ ጠቃሚዉ እና በየዕለቱ ሊተገበር የሚገባው deliberate meditation ነው። ይህን meditation አማኞች እንደሌሎቹ የክርስትና duty(ጸሎት፣የመፅሐፍ ቅዱስ ጥናት) ጊዜ መድበዉ እና አቅደው ሊለማመዱት ይገባል። ይሄንም የmeditation ዓይነት በመፅሐፍ ቅዱስ እዉነት ላይ በመትከልና በጸሎት በማጀብ ክርስቲያኖች ሊለማመዱትና በሁሉም የሕይወታቸው ክፍል ሊተገብሩት ይገባል። መኪና ከእኛ ቁጥጥር ዉጭ ሆኖ ስለሄደ እየነዳን ነው እንደማይባል፣ከቁጥጥራችን ዉጭ የሆኑ እና ድንገት ወደ አእምሮአችን የሚመጡ ሀሳቦች ስላሉ እያሰብን ነው አይባልም። አንድ Puritan እዉነተኛ ተመስጦን እንዲህ ይገልጻል:-"እውነተኛ ተመስጦ ማለት አንድ ሰው ልቡ በክርስቶስ ፍቅር እስከሚቃጠል (እስከሚነካ) ድረስ ስለ ክርስቶስ በጥልቀት የሚያስብበት፣ እንዲሁም ወደ እግዚአብሔር እውነቶች እስኪለወጥ ድረስ ስለ እነዚያ እውነቶች የሚያጠነጥንበት ነው።" meditation ፍሬያማ የሚሆነው፣የምናሰላስለዉ ተጨባጭ የሆነ የጌታ ቃል እዉነት ሲኖረንና ያንን እዉነት በየዕለቱ በሕይወታችን ስንገልጥ ነው።
Thomas Brooks:- 'የላቀ፣ ጣፋጭ፣ ጥበበኛና ጠንካራ ክርስቲያን መሆኑን የሚያስመሰክረው ብዙ የሚያነበው ሳይሆን፣ ይልቁንም አብዝቶ የሚያሰላስለው ነው።'
Puritansን እንወቅ
John Flavel(1628_1691)
፨ ጆን ፍላቨል እ.ኤ.አ. በ1628 በዎርስተርሻየር ግዛት በብሮምስግሮቭ ተወለደ። እሱም የnonconformist አገልጋይ የነበረው የሪቻርድ ፍላቨል ልጅ ነበር። ጆን በአባቱ አማካኝነት የኃይማኖት መንገድ የተማረ ሲሆን፣በመቀጠልም በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን ተከታትሏል። እ.ኤ.አ. በ1650፣በSalisbury በሽማግሌዎች ለአገልግሎት ተሾመ። በዚያም በብዙ መንገዶች እንዲሰረና እንዲቀረጽ ምክንያት ሆኖታል። Joan Randall የተባለችን እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት አገባ፤ነገርግን በ1655 የመጀመሪያ ልጃቸውን ስትወልድ ሕይወቷ አለፈ። ሕፃኑም በተመሳሳይ ሁኔታ ሞተ። ከአንድ ዓመት የኀዘን ቆይታ በኋላ፣ፍላቨል Elizabeth stapellን አገባ፣በዚህም በርካታ ልጆችን ባፈሩበት፣እግዚአብሔርን በሚፈሩና ፍፁም በሆነ የትዳር ሕይወት ተባረከ። በ1656 ፍላቨል ዳርትማዉዝ በተባለችው በልማት ላይ በነበረች የወደብ ከተማ ዉስጥ መጋቢ ሆኖ እንዲያገለግል የቀረበለትን ጥሪ ተቀበለ። በነበረዉም አገልገሎት በርካታ ሰዎች ወደ እምነት ተመልሰዋል።
፨ ፍላቨል nonconformist በመሆኑ እ.ኤ.አ.በ1662 ከአገልግሎት ታገደ፣ሆኖም ግን ከአጥቢያዉ ምዕመናን ጋር በምስጢር እየተገኘ ማምለክን ቀጠለ። በአንድ ወቅት፣ምሥጢራዊ ወደሆነው የመሰብሰቢያ ቦታ ለመድረስ፣ለመስበክና የጥምቀት ሥርዓትን ለመፈጸም ሲል ሴት መስሎ በፈረስ ላይ ሆኖ ተጉዞ ነበር። በሌላ ጊዜ ደግሞ በባለሥልጣናት እየታደነ ሳለ፣ፈረሱን ወደ ባሕሩ ዉስጥ አስገብቶ፣በዓለታማ ቦታዎች መካከል በዋና በማምለጥ ከእስር ሊተርፍ ችሏል። እ.ኤ.አ በ1665 ፍላቨል ወደ Slapton የተዛወረ ሲሆን፣በዚያም ጉባኤዉን ማገልገሉን ቀጠለ። በጫካዎች ዉስጥ በምስጢር ብዙ ቁጥር ላላቸው ሰዎች ይሰብክ ነበር፤አንዳንዴም እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ይቆይ ነበር። በአንድ እንዲህ ባለ አጋጣሚ ላይ ወታደሮች በድንገት እየተመሙ በመግባት ምዕመናኑን በትነዋቸዉ ነበር። ለማምለጥ ከሞከሩት መካከል ጥቂቶቹ ተይዘው የገንዘብ ቅጣት የተጣለባቸው ቢሆንም፣የቀሩት ግን ፍላቨልን ወደ ሌላ የጫካ አካባቢ በመዉሰድ ስብከቱን እንዲቀጥል አድርገዋል። እ.ኤ.አ በ1672 ንጉሥ ቻርለስ ሁለተኛው የነጻነት አዋጅን ያወጁ ሲሆን፣ይህም ለnonconformists የአምልኮ ነጻነትን ሰጣቸው። ፍላቨልም ወደ ዳርትማዉዝ በመመለስ የCongregationalist ፈቃድ አገኘ። ሆኖም በሚቀጥለው ዓመት ይህ አዋጅ ሲሰረዝ፣ፍላቨል በድጋሚ በግል መኖሪያ ቤቶች፣ገለልተኛ በሆኑ አካባቢዎች እና ጥቅጥቅ ባሉ ጫካዎች በድብቅ መስበኩን ቀጠለ። በዚህ የመከራ ጊዜ ዉስጥ የፍላቨል ሁለተኛ ሚስት ሕይወቷ ያለፈ ሲሆን፣እሱም የአንድ መጋቢ ልጅ የነበረችውን Ann downeን አገባ። ለ11 ዓመታት ያህል ደስተኛ የሆነ የትዳር ሕይወት ያሳለፈ ሲሆን፣ሁለት ወንድ ልጆችንም አፍርተዋል። በ1670ዎቹ መገባደጃ እና በ1680ዎቹ መጀመሪያ ላይ፣ፍላቨል አገልግሎቱን በዋናነት በቀጠለበት በጽሑፍ ሥራ ላይ አተኮረ። በእነዚህ ጊዜያትም ዘጠኝ የሚደርሱ መጻሕፍትን አሳትሞ አዉጥቷል። ሆኖም በ1682 በጋ ላይ ለደህንነቱ ሲል ወደ ለንደን ለመሰደድ ተገደደ፤በዚያም በአንድ ወዳጁ አጥቢያ ዉስጥ በአገልግሎት ያግዝ ነበር። በለንደን በነበረበት በዚህ ወቅትም የፍላቨል ሦስተኛ ሚስት ሕይወቷ አለፈ።
፨ ፍላቨል ለአራተኛ ጊዜ ትዳር በመመስረት በ1684 ወደ ዳርትማዉዝ ተመለሰ፤በዚያም በቁም እስር ላይ በመሆኑ፣አገልግሎቱ በገዛ መኖሪያ ቤቱ ዉስጥ ብቻ የተገደበ ሆነ። እዚያም ከባለሥልጣናት የሚሰነዘርበትን ከፍተኛ ተቃዉሞና ጠላትነት ተቋቁሞ፣በየሳምንቱ እሁድ እና በሥራ ቀናት ምሽት ላይ ለሚሰበሰበው ህዝብ ይሰብክ ነበር። በ1687 ንጉሥ ጄምስ ሁለተኛው ለnonconformists ሌላ የምሕረትና የነጻነት አዋጅ ያወጡ ሲሆን፣ይህም ፍላቨል በድጋሚ በአደባባይ እንዲሰብክ ምቹ ሆነለት። የጉባኤውም አባላት ወደ አገልግሎት መድረኩ በክብር መመለሱን በማስመልከት ትልቅ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ገነቡለት። በአደባባይ የሰበከባቸዉ እነዚህ የመጨረሻዎቹ የአራት ዓመታት አገልግሎቱ እጅግ የተባረከ ነበር። ይሁን እንጂ ጤንነቱ በፍጥነት እየተዳከመ መጣ። በሰኔ ወር 1691 ለመስበክ ወደ ኤክስተር ተጉዞ ሳለ፣ፍላቨል በከባድ የስትሮክ(የጭንቅላት ዉስጥ ደም መፍሰስ) ተጠቃ በዚያዉ ዕለት ምሽት በ63 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
Marks of sanctification
(1) መንፈሳዊ ጉድለታችንንና ፍላጎታችንን ማወቅ፤በልባችን መራርነት በኃጢአታችን ሁሉ እግዚአብሔርን በመበደላችን ማዘን።
(2) ከሥጋ መሻት ጋር መጋደል— ማለትም የሥጋን ዓመፀኛ ዝንባሌዎች መቃወምና መጥላት፣ እነዚያንም ዝንባሌዎች እንደ ከባድ ሸክምና አስቸጋሪ ፈተና መቁጠር(ማሰብ)።
(3) የዘላለምን ሕይወት ለማግኘት የእግዚአብሔርን ጸጋና የክርስቶስን የማዳን ሥራ በጽኑ መናፈቅና በታላቅ መሻት መፈለግ።
(4) ይህን የዘላለም ሕይወት ባገኘን ጊዜ፣ እንደ ከበረና እጅግ ውድ እንደ ሆነ ዕንቁ አድርጎ መቁጠር (ፊልጵስዩስ 3፥8)።
(5) የእግዚአብሔርን ቃል አገልጋይ፣ አገልጋይ በመሆኑ ብቻ መውደድ፤ ክርስቲያንንም፣ ክርስቲያን በመሆኑ ብቻ መውደድ—በዚህም ምክንያት፣ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ፣ ከእነርሱ ጋር ደምን እስከ ማፍሰስ (ሕይወትን አሳልፎ እስከ መስጠት) ድረስ ዝግጁ መሆን (1 ዮሐንስ 3፥16)።
(6) እግዚአብሔርን በጽኑ መፈለግ እና መጣራት። ያለ እግዚአብሔር ምንም መሆናችንን፣ባዶነታችንን ማወቅ።
(7) ይህ የኃጢአት ዘመን ፍጻሜ ያገኝ ዘንድ፣ከኀጢአት ኀይል እና ከኃጢአት መገኘት ነጻ ለመዉጣት የክርስቶስን ዳግም ምጽአትና የፍርድ ቀንን በጉጉት መናፈቅና መጠበቅ።
(8) ከኃጢአት አጋጣሚዎችና ፈተናዎች ሁሉ በመሸሽ፣ በአዲስ የሕይወት ሥርዓት ለመመላለስ መጣር።
(9) እስከ መጨረሻዋ የሕይወት እስትንፋስ ድረስ በእነዚህ ነገሮች ላይ መጽናት።
አንድ አማኝ በትንሽ ዲግሪም ቢሆን እነዚህን የጸጋ ምልክቶች ከተለማመደ፣በእግዚአብሔር መንፈስ ለመቀደሱ እርግጠኛ መሆን ይችላል። ምክንያቱም እነዚህ ምልክቶች በበደሉ እና በኃጢአቱ ሙት ለሆነ ሰው alien እና unnatural ናቸው።
ዛሬ በመንገዴ ላይ አንድ በእድሜያቸው ጠና ያሉ አባት "የወንጌል ትራክት" ሰጡኝ። ትራክቱን ሳነበዉ በጣም ደነቀኝ። የፃፉትም ምሳሌያዊ በሆነ መንገድ ነው። ምሳሌውም በአንድ ሕዝቡን በመልካም አስተዳደር የሚመራ ንጉሥ፣በንጉሡም ብቸኛ ልጅ በሆነች እና ንጉሡን ገድለው ስልጣን መቆናጠጥ በሚፈልጉ ጄነራል ታሪክ ዙሪያ ነው የሚያጠነጥነው። ይሄን ትራክት ያዘጋጁት ሰዎች ንጉሡ እግዚአብሔርን፣ልጅቱ የሰው ልጆችን እንዲሁም ጄነራሉ ደግሞ ሰይጣንን እንደሚወክል በመግለፅ "ምስክርነታቸውን" ለመግለጽ ሞክረዋል። የታሪኩም ፍሰት በአጭሩ ልጅቱ የንጉሥ ልጅ እንደሆች፣የአባቷንም ምክር በመስማት የምትኖር እንደሆነ ይናገራል። ከለታት በአንዱ ቀን ግን ንጉሡን በመግደል ስልጣን ቀምቶ መንገስ በሚፈልግ ጄነራል ልጅቱ ተታላ ታገባዋለች። ጄነራሉም በጣም ይጨቁናት፣ይደበድባት ነበር። ይህ ሁኔታ ግራ የገባት ልጅትም አባቷን ማለትም ንጉሡን እንዲረዳት ብትልም አባቷ ግን ፈቅዳ ስለገባችና በእሷ ላይ ስልጣን እንደሌለው በመናገር ምንም ማድረግ እንደማይችል ይገልጽላታል። አባትየው ምንም ማድረግ ባለመቻሉ ምርር ብሎ ያለቅሳል። ልጅቱም ባሏ ከብዙ ሴቶች ጋር እንደሚሆን ስለምታቅ ከዕለታት በአንዱ ቀን እጅ ከፍንጅ በማስረጃ ትይዘዉና ምስክር በማቅረብ ነጻነቷን አወጀች። ዉሏን አፈረሰች።ከጄኔራሉ ተፋታች።እራሷን አዳነች።ድንቅ ነው።
ወገኖች ይሄ ታሪክ እንግዲህ ወንጌልን ያብራራልናል ብለዉ ነው ይህን ትራክት ያዘጋጁ ሰዎች የጻፉት። በጣም የሚያሳዝነው ግን ወንጌልን አቃለዉ፣አበይት የክርስትና አስተምህሮዎችን ተቃዉመዉ ነው የጻፉት። እንዴት ለሚለው ፣የታሪኩ ገፀባሕርያት ማለትም ንጉሡ እግዚአብሔርን ፣ልጅቱ የሰው ልጅን ፣ ጄነራሉ ሰይጣንን ነዉና የሚወክሉት፣እያንዳንዱን ታሪክ በመፅሐፍ ቅዱስ እንመዝነዉ:-
1, "ልጅቱ የንጉሥ ልጅ ነበረች፣የአባቷንም ምክር ትሰማ ነበር"ይላል። ዳግም ልደትን ያላገኘ፣አማኝ ያልሆነ የሰው ልጅ ግን የእግዚአብሔር ጠላት፣የቁጣ ልጅ እንደሆነና በእዚህ ዓለም አለቃ ፈቃድ እንደሚመላለስ መፅሐፍ ቅዱስ ይናገራል።
ኤፌሶን 2:1-3 [1] እናንተም በበደላችሁና በኀጢአታችሁ ምክንያት ሙታን ነበራችሁ፤ [2] በዚህም፣ የዓለምን ክፉ መንገድ ተከትላችሁ፣ በአየር ላይ ላሉት መንፈሳውያን ኀይላት ገዥ ለሆነውና አሁንም ለእግዚአብሔር በማይታዘዙት ሰዎች ላይ ለሚሠራው መንፈስ እየታዘዛችሁ ትኖሩ ነበር። [3] እኛ ሁላችን በአንድ ወቅት የሥጋችንን ምኞት እያረካን፣ መንገዱንም እየተከተልን በመካከላቸው እንኖር ነበር፤ እንደ ሌሎቹም የቍጣ ልጆች ነበርን።
ሮሜ 3:9-12 [9] እንግዲህ ምን እንላለን? እኛ ከእነርሱ እንበልጣለንን? ከቶ አይደለም፤ አይሁድም ሆኑ አሕዛብ፣ ሁሉም ከኀጢአት በታች እንደ ሆኑ አስቀድመን ከስሰናቸዋል። [10] እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፤ “ጻድቅ ማንም የለም፤ አንድ እንኳ፤ [11] አስተዋይ የለም፤ እግዚአብሔርንም የሚሻ አንድም የለም። [12] ሁሉም ተሳስተዋል፤ በአንድነት የማይጠቅሙ ሆነዋል፤ መልካም የሚያደርግ የለም፤ አንድ እንኳ።” 2, ልጅቱ፣የንጉሥ ልጅ ናት። ማለትም ልጅቱ የምትወክላቸዉ የሰው ልጆች ንጉሡ ለሚወክለው ለእግዚአብሔር ልጆች ናቸው እያሉ ነው። በእዚህም justification from eternityን attest እያረጉ ነው። ማለትም እግዚአብሔር ምርጦቹን ዓለም ሳይፈጠር በዘለዓለም ዉስጥ በክርስቶስ ሊያጸድቃቸዉ ስለደነገገ መፅደቃቸዉ እርግጥ ነው፣በዉጤቱም ከእግዚአብሔር እርግማን በታች፣ከቁጣዉ በታች አይደሉም ይልቁን ከዉልደታቸዉ ጀምሮ የእርሱ ልጆች ናቸው የሚል አስተምህሮ ነው። actually ይሄን ትምህርት ያዉቁታል ብዬ አላስብም ግን፣ inadvertently የሚሰራ ኃጢአት ነው። ምክንያቱም አንድ ሰው የመፅደቁ እና በእግዚአብሔር ፊት righteous የመሆኑ እዉነታ በወንጌል ስብከት አማካኝነት መንፈስ ቅዱስ በአማኙ ዉስጥ በሚሰራው የዳግም ልደት ሥራ እና በክርስቶስ ሥራ የተገኙትን ትሩፋቶች apply ሲያደርግ ነው። 3, ልጅቱ የንጉሥ ልጅ ሆና በሰላም እየኖረች ሳለ ነው በጄኔራሉ ተታላ እዳ ዉስጥ የገባችው። ማለትም የእዚህ ትራክት አዘጋጆች እያሉ ያሉት ሰዉ naturally የእግዚአብሔር ልጅ ነው። ሲወለድም innocent ነዉ። በሰይጣን ተታሎ ነው ኃጢአት ዉስጥ የገባው እያሉን ነው። ይሄም አንኳር የሆነዉን የወንጌልን እዉነት የሚፃረር ነው። ሰዉ በሚያደርገው ኃጢአት ነው ኃጢአተኛ(original innocence/ancestral sin)የሚሆነው እያሉ ነዉ።ይህም ሰዉ ኃጢአተኛ ስለሆነ ነው ኃጢአትን የሚያደርገው(original sin) የሚለውን የመፅሐፍ ቅዱስ እዉነት ይክዳል። የአዳም ኃጢአት ዉጤት ብቻ ሳይሆን ለሰው ዘር የተላለፈው የአዳም guilt እና corrupt nature ነው። ምከንያቱም አዳም የሰዉ ዘርን በጠቅላላ በመወከል ነዉ ከእግዚአብሔር ጋር ኪዳን የገባው። በካርቴጅ እና በኤፌሶን የቤተክርስቲያን ጉባኤም ይህ አስተምህሮ የተወገዘ ነው።
ሮሜ 5:12 [12] ስለዚህ ኀጢአት በአንድ ሰው በኩል ወደ ዓለም እንደ ገባ ሁሉ፣ ሞትም በኀጢአት በኩል ገብቷል፤ በዚሁ መንገድ ሞት ወደ ሰዎች ሁሉ መጣ፤ ምክንያቱም ሁሉም ኀጢአትን ሠርተዋል፤
መዝሙር 51:5 [5] ስወለድ ጀምሮ በደለኛ፣ ገና እናቴም ስትፀንሰኝ ኀጢአተኛ ነኝ።
ዘፍጥረት 6:5 NASV [5] እግዚአብሔር አምላክ የሰው ዐመፅ በምድር ላይ የበዛና የልቡም ሐሳብ ዘወትር ወደ ክፋት ብቻ ያዘነበለ መሆኑን ተመለከተ።
ማርቆስ 7:20-22 [20] ቀጥሎም፣ እንዲህ አለ፤ “ከሰው የሚወጣ ያ ሰውን ያረክሰዋል፤ [21] ከውስጥ፣ ከሰው ልብ የሚወጡት ክፉ ሐሳብ፣ ምንዝር፣ ስርቆት፤ ሰው መግደል፣ ዝሙት፣ [22] መስገብገብ፣ ክፋት፣ ማታለል፣ መዳራት፣ ምቀኛነት፣ ስም ማጥፋት፣ ትዕቢት፣ ስንፍና ናቸው። 4, ይህ አስደናቂ ታሪክ ይቀጥልና፣ ልጅቱ ሲጨቁናት ከነበረው ጄነራል በእራሷ ብቃት፣ ምንም ማድረግ ወዳልቻለዉ፤ምንም ማድረግ ባለመቻሉ ስቅስቅ ብሎ ሲያለቅስ ወደነበረዉ፣ ንጉሥ ወደሆነዉ አባቷ እንደተመለሰች ያትታል። እንግዲህ በእዚህ ታሪክ መሰረት ነው ምንም ማድረግ ወዳልቻለዉ "እግዚአብሔር" በኀይላቹ ተመለሱ፣ከሰይጣን አምልጡ እያሉ ያሉት። እጅግ በጣም ያሳዝናል። በሉዓላዊነቱ፣በዘላለም እዉቀቱ፣እንደ ፈቃዱና ምክሩ ሀሳብ ደስ የሚያሰኘውን የሚያደርግን አምላክ ነው እንዲህ አንኳሰዉ ያቀረቡት። በእግዚአብሔር ቃል እና በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ብቻ የሚፈርሰዉን የሰዉን ድንጋይ የሆነ ልብ ነው አሸንፉት የሚሉን። በበደሉ እና በኃጢአቱ የሞተን የሰዉን ልጅ ነው እራስህን አስመልጥ እያሉ ያሉት።
ቈላስይስ 2:13 [13] እናንተም በበደላችሁና የሥጋችሁን ኀጢአታዊ ባሕርይ ባለመገረዝ ሙታን ነበራችሁ፣ እግዚአብሔር ግን ከክርስቶስ ጋራ ሕያዋን አደረጋችሁ፤ በደላችንንም ሁሉ ይቅር አለን፤
1 ቆሮንቶስ 6:11 [11] ከእናንተ አንዳንዶቻችሁ እንደዚህ ነበራችሁ፤ አሁን ግን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስምና በአምላካችን መንፈስ ታጥባችኋል፤ ተቀድሳችኋል፤ ጸድቃችኋል።
2 ጢሞቴዎስ 1:9 [9] እኛ ስላደረግነው አንዳች ነገር ሳይሆን፣ ከዕቅዱና ከጸጋው የተነሣ ያዳነን፣ ወደ ቅዱስ ሕይወትም የጠራን እርሱ ነው። ይህም ጸጋ ከዘላለም ዘመናት በፊት በክርስቶስ ኢየሱስ ተሰጠን፤
Puritansን እንወቅ
John Bunyan (1628_1688)
ጆን ባንያን እ.ኤ.አ በ1628 በቤድፎርድ አቅራቢያ በምትገኘው ኤልስቶዉ(England) ዉስጥ ከቶማስ ባንያን እና ከማርጋሬት ቤንትሊ ተወለደ። ያደገው በድሃ ቤተሰብ ዉስጥ በመሆኑ ፣ ጆን ጥሩ ትምህርት ለማግኘት አልታደለም። እሱም ህግን የማይታዘዝ፣የስድብን ቃል የሚናገር፣እጅግ አመጸኛና blasphemous ሰው ነበር። ነገርግን አልፎ አልፎ የሚሰማው የኃጢአት የጥፋተኝነት ስሜት ያንን አለመታዘዝ በተወሰነ መልኩ ለመግታት ረድቶታል። ጆን ባንያን እድሜው 16 ዓመት ሲሆን፣የ Cromwell's new model armyን ተቀላቀለ፣በዚያም ያንን አመጸኛ የአኗኗር ዘይቤዉን ቀጠለበት። ይሁን እንጂ በኢንግሊዝ የእርስ በእርስ ጦርነት ዉስጥ መዋጋቱ በተለይም ለጥቂት ከሞት ከተረፈበት አጋጣሚ በኋላ ቆም ብሎ በጥልቀት እራሱን እንዲያይ እና እንዲያዝን አድርጎታል። ባንያን በ1646/47 ከጦር ሰራዊቱ ተሰናበተ። ባንያን በ1648 ስሟ እስካሁን የማይታወቅ አንዲት እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት አገባ። የእሷን የPuritan መንፈሳዊ ጽሑፎች ካነበበ በኋላ፣እንደገና የኃጢአተኝነት ስሜት(conviction of sin) ተሰማው። ከዚያም በአካባቢው ወዳለ parish church መሄድ ጀመረ፣ስድብና መሐላን ተወ፣የጌታንም ቀን(ሰንበት) ለማክበር ጥረት አደረገ። ከጥቂት ወራት በኋላ፣ባንያን ስለ ክርስቶስ እና ስለ ዳግም ልደት በደስታ ከሚያወሩ አንዳንድ ሴቶች ጋር ተገናኘ፣የእነሱም ዉይይት እጅግ ማረከው። እሱ እራሱ ግን እንደጠፋና ከክርስቶስ ዉጭ እንደሆነ ሲረዳ፣ያንን ደስታ የራቀዉን ሕይወቱን በሐዘን አሰበው። በመላ ኢንግሊዝ ዉስጥም ከእሱ የከፋ ልብ ያለው ሰው ያለ አልመስል አለው። በ1651 ሴቶቹ ባንያንን በቤድፎርድ የቤተክርስቲያናቸዉ መጋቢ ወደነበረው ወደ John Gifford ወሰዱት። እግዚአብሔርም ባንያንን ወደ ንስሐና ወደ እምነት ለመምራት በgifford ተጠቀመ። በ1655 ባንያን ከባለቤቱና ከአራት ልጆቹ ጋር ወደ ቤድፎርድ ተዛወረ፤የGiffordም ቤተክርስቲያን አባል ሆነ፣ብዙም ሳይቆይ በዲያቆንነት ተሾመ። የእሱም የሕይወት ምስክርነት በከተማው ዉስጥ መነጋገሪያ ሆነ፣ለብዙ ሰዎችም መለወጥ(conversion) ምክንያት ሆነ።
በ1655 ባንያን በቤድፎርድ ዉስጥ በተለያዩ ጉባኤያት መስበክ ጀመረ። እሱንም ለመስማት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ይመጡ ነበር። በሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት ዉስጥም በርካታ መጻሕፍትን ያሳተመ ሲሆን፣ይህም ስመጥር የpuritan ጸሐፊ እንዲሆን አስቻለው። በ1661 መጀመሪያ አካባቢ፣ባንያን ከቤተመንግስት የተሰጠ ይፋዊ ፈቃድ ሳይኖረዉ በመስበኩ ተከሰሰና ታሰረ። ከእንግዲህ ወዲህ ላለማስተማር ቃል ከገባ እንደሚለቀቅ ቢነገረዉም፣"ዛሬ ብፈታ፣ነገ እሰብካለሁ" ብሎ መለሰላቸው። በዚህም የወንጌልን ስብከት ትቶ ለመቀመጥ ፈቃደኛ ባለመሆኑ እና church of Englandን ሐሰተኛ ነሽ በማለት ስላወገዘ ያለምንም ይፋዊ ክስና ሕጋዊ የፍርድ ዉሳኔ ለ12 ዓመት ተኩል በእስር ቤት ማቀቀ። በእስር ቆይታዉም የእስር ቤት ጠባቂዎች አልፎ አልፎ እየወጣ እንዲሰብክ ይፈቅዱለት ነበር። የእስር ዓመታቱ ለእሱ ከፍተኛ የፈተና ጊዜያት ነበሩ በተለይም ከባለቤቱና ከልጆቹ መለየቱ ያስከተለበት ስቃይ እጅግ ከባድ ነበር። ይሁን እንጂ፣እነዚህ ዓመታት ለባንያን ፍሬያማ ጊዜያት ነበሩ። ሳይታክትና በብዛት ይጽፍ የነበረ ሲሆን፣ካሉት በደርዘን ከሚቆጠሩ መጻሕፍቱ መካከል አብዛኞቹን ያዘጋጀው በእነዚህ ዓመታት ዉስጥ ነበር።
በግንቦት ወር 1672፣የቤድፎርድን ጉባኤ በመጋቢነት ለመምራት ከእስር ተፈታ። ለሁለት ዓመታት ያኽል በነፃነት ከኖረ በኋላ፣በመስበኩ ምክንያት እንደገና በከተማው እስር ቤት ዉስጥ ታሰረ። እጅግ ዝነኛ የሆነው "የመናኝ ጉዞ"(pilgrim's process) የተሰኘው መፅሐፉ የመጀመሪያ ክፍልን ጨምሮ በርካታ ሥራዎቹን የፃፈው እዚህ እስር ቤት ዉስጥ እያለ ነበር። በ1677 ከእስር ከተለቀቀ በኋላ፣የቀሩትን የሕይወት ዓመታት በማስተማርና በመፃፍ አሳለፈ። በ1688 ባንያን በጣም ቀዝቀዛ በሆነ አካባቢ እየተጓዘ ሳለ በያዘው ብርቱ ትኩሳት ምክንያት በሳንባ ምች ሕይወቱ አለፈ። በሞት አልጋው ላይ ሳለ፣ትልቁ ምኞቱና ፍላጎቱ ከክርስቶስ ጋር መሆን እንደሆነ ለጓደኞቹ ከነገራቸው በኋላ፣ እጆቹን ወደ ሰማይ ዘርግቶ "ወደ አንተ መጥቻለሁና ዉሰደኝ" በማለት ተጣራ ከዚያም ሕይወቱ አለፈች።
Puritansን እንወቅ
John Owen (1616_1683)
የኢንግሊዝ የሥነ መለኮት ሊቃዉንት ልዑል ተብሎ የሚጠራው ጆን ኦወን፣በኢንግሊዝ ስታድሃም መንደር፣የአካባቢው የpuritan vicar ከነበሩት ከሄነሪ ኦወን ተወለደ። ኦወን ገና በለጋ እድሜው ነበር ለአምልኮተ እግዚአብሔር እና ለሥነ መለኮት ጥናት ዝንባሌ ያሳይ የነበረው። በ12 ዓመቱ በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ኩዊንስ ኮሌጅ (Queens college,Oxford) በመግባት፣በ1632 ዓ.ም በ16 ዓመቱ የመጀመሪያ ዲግሪዉን፣በ1635 ዓ.ም ደግሞ የማስተርስ ዲግሪዉን አግኝቷል። teenage እያለ በቀን ከ18_20 ሰዓታት ያጠና ነበር። ኦወን በ1637 ዓ.ም ኦክስፎርድን ለቆ በመዉጣት፣ private chaplain እና አስተማሪ ሆነ። እነዚህ የ chaplaincy ዓመታት ለጥናት የሚሆን ሰፊ ጊዜ የሰጡት ሲሆን፣እግዚአብሔርም ይህንን ጊዜ በብዙ ባርኮታል። ኦወን በ26 ዓመቱ፣ከ80 በላይ መጻሕፍትን ያበረከተበትንና አርባ አንድ ዓመታት የፈጀውን የጽሕፈት ዘመኑን ጀመረ። ኦወን ከልጅነቱ ጀምሮ የpuritan እምነት እና አቋም የተቀበለ ቢሆንም፣እ.ኤ.አ በ1642 " ማቴዎስ 8:26
[26] ኢየሱስም፣ “እናንተ እምነት የጐደላችሁ፤ ለምን ይህን ያህል ፈራችሁ?” አላቸው፤ ከዚያም ተነሥቶ ነፋሱንና ማዕበሉን ገሠጸ፤ ወዲያውም ጸጥታ ሰፈነ።" በሚለው ጥቅስ ላይ የተመሠረተ ስብከትን እስከሰማበት ጊዜ ድረስ፣በድነቱ ሙሉ እርግጠኝነት እና እምነት(assurance of faith) አልነበረውም። እግዚአብሔር ኦወንን ወደዚህ የድነት እርግጠኝነት ለማምጣት ያንን ስብከት በኀይል ተጠቀመበት።
ኦወን በ1643 የካልቪኒዝምን አስተምህሮ በጥልቀት ያብራራበትና የተከላከለበትን "a display of Arminianism" የተሰኘውን መፅሐፍ አሳተመ። ይህ መፅሐፍ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ከፍተኛ እዉቅናን ያስገኘለት ሲሆን፣በፎርድሃም(Fordham) መንደር ባለ አጥቢያ ፓስተር ሆኖ እንዲሾምም በር ከፍቶለታል። በእዚያም የነበረው አገልግሎት በሰዎች ዘንድ እጅግ የተወደደ ከመሆኑ የተነሳ፣ብዙ ሰዎች እሱን ለመስማት ከተለያየ አካባቢ ይመጡ ነበር። እሱም በመስበክ ብቻ ሳይሆን ምዕመኑን catechize በማድረግ የተዋጣለት ነበረ። ኦወን በፖለቲካዊ ምክንያቶች ከነበረበት የኃላፊነት ቦታ ከተነሳ በኋላ፣1646 በኮግሻል(coggeshall) የሚገኘውና ታዋቂው የኤሴክስ(Essex) ቅዱስ ጴጥሮስ ቤተክርስቲያን መጋቢ ሆነ። በዚህም ጊዜ ነበረ ከ Presbyterianism ወደ Congregationalism የተቀየረው። የአጥቢያ ቤተክርስቲያኑንም በ congregationalism መመሪያዎች መሠረት እንደገና አዋቀረ። በ1640'ዎቹ መገባደጃ፣ኦወን በስብከቱና በጽሑፎቹ አማካኝነት ዝናዉ በፍጥነት የተስፋፋ ሲሆን፣ቀስ በቀስ ግንባር ቀደም የ independent ሥነ መለኮት ምሁራን መሪ ሆነ። Oliver Cromwell፣ኦወን በፓርላማ ፊት ባቀረበው ስብከት እጅግ በመደነቁ፣በዳብሊን የሚገኘዉን የትሪኒቲ ኮሌጅ(Trinity college in Dublin) ጉዳዮችን በበላይነት እንዲከታተልና እንዲመራ አብሮት ወደ Ireland እንዲሄድ አሳምነው። ኦወንም በቆይታው አብዛኛውን ጊዜ ያሳለፈው በስብከት አገልግሎት እንዲሁም ኮሌጁን በ Puritan መመሪያዎችና ሥርዓቶች መሠረት እንደገና በማደራጀት ላይ ነበር። እ.ኤ.አ. በ1651 በኦክስፎርድ የክርስቶስ ቸርች ኮሌጅ(Christ church college,Oxford) ዲን የሆነ ሲሆን፣ከ18 ወራት በኋላ ደግሞ የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ቻንስለር ተደርጎ ተሾመ። በሥነ መለኮት ትምህርቶች እና በበርካታ እትመቶች አማካኝነት፣የተሐድሶ ሥነ መለኮትን(Reformed theology) እና የ Puritansን መንፈሳዊ ሕይወት(Puritan piety) አስፋፋ። የኦወን እግዚአብሔርን የሚፈራና ማዕከል ያደረገ አመራሩ ዩኒቨርሲቲው ለዓመታት በ civil war ምክንያት ከነበረበት ቀዉስ እንዲወጣና ሰላምን፣መረጋጋትና መንፈሳዊ አንድነትን እንዲያገኝ አደረገ።
Cromwellን ልጁ ሪቻርድ ከተካዉ በኋላ፣ኦወን እና ሌሎች አገልጋዮች በቤተክርስቲያን ዉስጥ የነበራቸውን ቦታ በ Presbyterian የሥነ መለኮት ሊቃዉንት አጡ። እ.ኤ.አ በ1660 ኦወን በ Christ church ከነበረው የዲንነት ሃላፊነት በ Edward Reynolds ተተካ። በ1665 በለንደን ትንሽ ጉባኤን በመመስረት አገልግሎቱን ቀጠለ፣ጽሑፎቹንም መፃፍ ቀጠለ። በ1673 ይህ ጉባኤ Joseph Caryl የሚባል ሰው ፓስተር ሆኖ ያገለግልባት ከነበረው ሌላ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ጋር ተዋሐደ። ኦወን በመጨረሻዎቹ የሕይወት ዓመታት በአስም እና በሐሞት ከረጢት ጠጠር በሽታዎች እጅግ የተሰቃየ ሲሆን፣ሕመሙም በተደጋጋሚ ከመስበክ ያግዱት ነበር። ይሁን እንጂ የጽሑፍ ሥራዉን አላቋረጠም ነበር፣ስለ justification፣ spiritual mindedness፣እና the glory of Christ የሚያብራሩ ታላላቅ መጻሕፍትን አበርክቷል። ኦወን ሊመጣ ያለዉን ክብር በሙሉ ደስታ በመናፈቅ እ.ኤ.አ ነሐሴ 24 ቀን 1683 ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
Puritansን እንወቅ
John Eliot(1604_1690)
የህንዶች ሐዋርያ በሚል ስያሜ የሚታወቀው ጆን ኤሊየት እ.ኤ.አ. በ1604 በእንግሊዝ አገር ከባለ ጸጋ ቤተሰብ ተወለደ። ከሕጻንነቱም የጥናት ልማድ የነበረው ሲሆን፣በ1619 በካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ ወደ ሚገኘው ኢየሱስ ኮሌጅ(Jesus college) በመግባት በ1622 የመጀመሪያ ዲግሪዉን አግኝቷል። ከተመረቀም በኋላ በኢንግላንድ ቤተክርስቲያን(church of England) ለአገልግሎት የተሾመ ቢሆንም፣ብዙም ሳይቆይ በቤተክርስቲያኗ ሕጎችና ልማዶች ደስተኛ ሳይሆን ቀረ። እሱን የሚረዳና የሚስማማው የሰበካ ጉባኤ(parish) ለመፈለግ ከመጣር ይልቅ፣ Thomas Hooker ርዕሰ መምህር በነበረበት በኤሴክስ(Essex) በሚገኘው የሰዋሰው ትምህርት ቤት(grammar school) ማስተማርን መረጠ። በሁከር ተፅዕኖ አማካኝነትም ኤሊየት በክርስቶስ ወደ ማመን መጣ። ከconversionኡ ከጥቂት ጊዜም በኋላ ለአገልግሎት ሙሉ በሙሉ መሰጠት እንዳለበት ተሰማው። የሁከር ትምህርት ቤት በመዘጋቱ እና የChurch of Englandን ሕጎችና ልማዶች የመከተል ግዴታ(conformity) እየበረታ በመምጣቱ ምክንያት፣ኤሊየት ወደ ማሳቹሴትስ(Massachusetts) ለመሰደድ ወሰነ። እ.ኤ.አ. ሕዳር ቀን 1631 ቦስተን ደረሰ። በመቀጠልም በሮክስበሪ ማሳቹሴትስ በመኖር፣እዚያ የሚገኘውን ቤተክርስቲያን በመጀመሪያ በአስተማሪነት በኋላም በፓስተርነት ከ50 ዓመታት በላይ አገልግሏል። የመጀመሪያዎቹን 15 ዓመታት ሙሉ በሙሉ እራሱን ለቤተክርስቲያን ሥራ የሰጠ ሲሆን፣በቀጣዮቹ 35 ዓመታት ግን ጊዜዉን ጉባኤውን በመጋቢነት በማገልገል እና በነባር አሜሪካዉያን(native Americans) መካከል በመሥራት ከፍሎታል። ኤሊየት የተዋጣለት ሰባኪ እና አማካሪ በመሆንም ታወቀ።
የአልጎንክዊን(Algonquian) ቋንቋን ለጥቂት ዓመታት ካጠና በኋላ፣ኤሊየት እ.ኤ.አ. በ1646 ለአገሬው ነባር ነዋሪዎች መስበክ ጀመረ። እንደ እግዚአብሔር ባርኮት ኤሊየት "የሚጸልዩ ህንዶች"(praying Indians) የሚባሉባቸዉን ከተሞች መመሥረት ጀመረ። እ.ኤ.አ. በ1674 ወደ 14 የሚጠጉ praying towns የተመሠረቱ ሲሆን፣በነዚህ ከተሞች ዉስጥ የሚኖረው ሕዝብ ቁጥር ወደ 3,600 ገደማ ይገመት ነበር፤ከነዚህም መካከል ወደ 1,100 የሚሆኑት የክርስትናን ፍሬ ያሳዩ ነበሩ። የCongregationalist የአስተዳደር ሥርዓትን የሚከተሉ የህንድ አብያተ ክርስቲያናትን ማቋቋም ጀመረ። በ15 ዓመታት ዉስጥ በርካታ ችግሮችን ከተወጣ በኋላ፣የመጀመሪያው የአገሬው ነባር ነዋሪዎች ቤተክርስቲያን እ.ኤ.አ በ1660 በይፋ የተከለ ሲሆን፣ሌሎችም ብዙም ሳይቆዩ ተከታትለው ተተክለዋል። በዚህ ሁሉ ጊዜ ዉስጥ ኤሊየት መፅሐፍ ቅዱስን የቤይ ስቴት/የማሳቹሴትስ የመጀመሪያ ነዋሪዎች ወደነበሩት የአልጎንክዊን ቋንቋ ለመተርጎም በትጋት እየሠራ ነበር። በኢንግሊዛዉያን እርዳታ የማተሚያ ቤት ያቋቋመ ሲሆን፣በዚህም ማተሚያ ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ በማሳቹሴትስ ቋንቋ አዲስ ኪዳን እ.ኤ.አ በ1661 ታተመ። በ1663 ደግሞ የብሉይ ኪዳን በማሳተም፣በአሜሪካ አህጉር ላይ የታተመው የመጀመሪያው ሙሉ መፅሐፍ ቅዱስ እንዲሆን አድርጎታል።
እ.ኤ.አ በ1675 የንጉሥ ፊሊፕ ጦርነት እስከ ተቀሰቀሰበት ጊዜ ድረስ የኤሊየት ሥራ በጥሩ ሁኔታ እያደገና እየተስፋፋ ነበር። በወቅቱ በርካታ የክርስትና እምነት ተከታይ የሆኑ የአገሬው ነባር ነዋሪዎች ለሕይወታቸው በመስጋት በቦስተን ወደሚገኝ አንድ ደሴት ተዛወሩ። ይሁን እንጂ ብዙዎች እዚያው ሕይወታቸው አለፈ። ይህ አሳዛኝ ሁኔታ በሌሎች ከተሞችም የተደገመ ሲሆን፣በጸሎት ከተሞች ዉስጥ የነበሩት praying Indians በጦረኛ የጎሳ አባላት እና በበቀል በተሞሉ ቅኝ ገዢዎች ተደመሰሱ። በመጨረሻም 14ቱም የፀሎት ከተሞች ሙሉ በሙሉ ጠፋ። ኤሊየት ከጦርነቱ በኋላ እንደገና ለመጀመር ቢሞክርም፣ባደረገው ጥረት ሁሉ እነዚያን ከተሞች ዳግም ሊያቋቁማቸዉ አልቻለም። እ.ኤ.አ ግንቦት 20 ቀን 1690 በ86 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
Holiness is nothing but the implanting, writing, and realizing of the gospel in our souls. just as we are justified by the blood of Christ, so we are sanctified by the blood of Christ. The Holy Ghost,actually communicates the cleansing, purifying virtue of the blood of Christ unto our souls and consciences, whereby we are freed from shame, and have boldness towards God.”
ቅድስና ማለት ወንጌሉ በነፍሳችን ውስጥ ከመተከሉ፣ ከመጻፉና ከመገለጡ በስተቀር ሌላ ምንም አይደለም። በክርስቶስ ደም እንደጸደቅን ሁሉ፥ እንዲሁ በክርስቶስ ደም እንቀደሳለን። መንፈስ ቅዱስም በእፍረት እንዳንኖርና በእግዚአብሔር ፊት ድፍረት እንዲኖረን፥ የክርስቶስን ደም የማንጻትና የማጥራት ኃይል በተግባር ለነፍሳችንና ለሕሊናችን ይገልጣል።
John Owen
Puritansን እንወቅ
Thomas Goodwin (1600_1680)
ቶማስ ጉድዊን እ.ኤ.አ. ጥቅምት 5 ቀን 1600 በሮልስቢ፣ኢንግሊዝ ተወለደ። እግዚአብሔርን የሚፈሩት ወላጆቹ ሪቻርድ እና ካትሪን ጉድዊን ልጃቸዉን በአርዓያነታቸዉ ከመቅረፅ ባለፈ በአካባቢው በሚገኙ ምርጥ ከሚባሉ ትምህርት ቤቶች በአንዱ የተሻለ ትምህርት እንዲያገኝ በማድረግ፣ለአገልግሎት ለማዘጋጀት የተቻላቸውን ጥረት ሁሉ አድርገዋል። ጉድዊን በልጅነቱ tender ሕሊና የነበረው ሲሆን፣ስለ እግዚአብሔርና ስለ ዘላለም ትልቅነት ጥልቅ የሆነ ግንዛቤና ስሜት ነበረው። በ13 ዓመቱ በካምብሪጅ christ college ተመዘገበ። ምንም እንኳ በpuritan ስብከትና ትምህርት የተከበበ ቢሆንም፣ጉድዊን ትኩረቱን የንግግር ጥበብ ማጥናት ላይ በማድረግና የአርሚኒያኒዝምን እምነት በሙሉ ልብ በመቀበል ታዋቂ ሰባኪ ለመሆን ቆረጠ። ጉድዊን እ.ኤ.አ. በ1617 በ17 ዓመቱ ከchrist college በመጀመሪያ ዲግሪ ተመረቀ። በ1619 ትምህርቱን በካምብሪጅ በሚገኘው በቅድስት ካትሪን ሆል የቀጠለ ሲሆን፣በማስተርስ ዲግሪ ከተመረቀ ከአንድ ዓመት በኋላም የኮሌጁ ባልደረባ እና ሌክቸረር ለመሆን በቃ።
በእግዚአብሔር መግቦት፣ጉድዊን በካምብሪጅ በሚገኙና ከንቱ የንግግር ጥበብን እንዲሁም አርሚኒያኒዝምን መከተል ሞኝነት መሆኑን ሊያስረዱት በሞከሩ ሌሎች የኮሌጁ ባልደረቦች ተፈተነ። ከዚህ በተጨማሪ ሪቻርድ ሲብስ እና ጆን ፕሪስተን በኮሌጁ chapel ያደርጉት የነበረው ቀጥተኛና ልብ የሚነካ የወንጌል ስብከት ተፅዕኖ ሊለቀዉ አልቻለም። ጥቅምት 2 ቀን 1620 በሉቃስ 19:41_42 ላይ የተመሰረተ የቀብር ሥነሥርዓት ላይ የተደረገ ስብከት በሰማ ጊዜ፣እግዚአብሔር ጉድዊን ስለ ኃጢአቱ ጥልቅ የሆነ ፀፀት እንዲሰማዉ በማድረግና ኃጢአተኛ መሆኑን እንዲያምን በማድረግ conversion በሕይወቱ ተከሰተ። እራሱንም ከpuritans ሥነ-መለኮት ጋር በማስተሳሰር ጥልቅ፣ተግባራዊና መጋቤያዊ(pastoral) ስብከቶችን መስበክ ጀመረ። በ1628፣ በ27 ዓመቱ የሲብስን እና የፕሪስተንን እግር በመተካት በtrinity ቤተክርስቲያን መምህር ሆኖ ተሾመ። የሊቀ ጳጳስ(Archbishop) ላዉድን(laud) የስምምነት አንቀጾች(articles of conformity) ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመሆኑ ምክንያት ሥራዉን ለመልቀቅ እስከተገደደበት እስከ 1633 ማብቂያ ድረስ እዚያው አገለገለ። በለንደን ዉስጥ ገለልተኛ(separatist) ሰባኪ ሆኖ ማገልገል የጀመረ ቢሆንም፣በስብከት ላይ የሚጣለው ገደብ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመሄዱ ምክንያት ጉድዊን እ.ኤ.አ. በ1639 ወደ ኔዘርላንድስ ተሰደደ። እዚያም በአርንሄም(Arnhem) ከተማ፣ከሊቀ ጳጳስ ላዉድ ስደት አምልጠው የመጡ ከመቶ በላይ የሚሆኑ ሰዎችን በማገልገል ሰርቷል።
እ.ኤ.አ. በ1641 ሊቀ ጳጳስ ላዉድ ከሥልጣን ተወግዶ በተከሰሰ ጊዜ፣ጉድዊን ወደ ኢንግሊዝ እንዲመለስ ከፓርላማ የቀረበለትን ጥሪ ተቀብሎ ተመለሰ። እዚያም እጅግ ከፍተኛ ሚና የተጫወተበት የWestminster assembly አባል ሆኖ ተሾመ። በኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ መምህር ሆነ፣በመቀጠልም የMagdalen ኮሌጅ ፕሬዚዳንት ሆነ። ጉድዊን ይህንን ተቋም በቅዱሳት መጻሕፍት እዉነት እና በተግባር ላይ በተመሰረተ የካልቪኒዝም አስተምህሮዎች ለመቅረጽ ረድቷል። እጅግ የላቀ የትምህርት ብቃትን ይጠይቅ ስለነበር እና ከተማሪዎቹ መንፈሳዊ ሕይወት ጋር ቀጥተኛ በሆነ መንገድ ይሠራ ስለነበር፣በእሱ የpuritan አጽንኦት ባልተደሰቱት ሰዎች "የሕሊና ጠባብነትን" እያስፋፋ ነው በሚል ተከሷል። በእዚህም ወቅት independent church አቋቁሟል። እ.ኤ.አ. መስከረም 29፣1658 ጉድዊን ከበርካታ የindependent church መጋቢዎችና የነገረ መለኮት ምሁራን ጋር በመሆን፣ የሳቮይ የእምነት መግለጫን(Savoy declaration of faith and order) አዘጋጀ። ይህም ለBritish Congregationalism ቋሚ የእምነት ሰነድ ሆነ። ትንሽ ቆይቶም የAmerica Congregationalist's adopt አድርገዉታል። እ.ኤ.አ. በ1660 ዳግማዊ ቻርለስ(Charles II) ወደ ሥልጣን መምጣቱን ተከትሎ የPuritanኦች ሕዝባዊ ተጽዕኖ እየቀነሰ በመሄዱ፣ጉድዊን ኦክስፎርድን ለቆ ለመዉጣት ተገደደ። እሱና ሌሎች ክርስቲያኖች ወደ ለንደን በመሄድ እንደ አዲስ ቤተክርስቲያን ሆነው ሕብረት ማድረግ ጀመሩ። ጉድዊን የመጨረሻዎቹን የሕይወት ዘመኑን ያሳለፈው በስብከት፣በእረኝነት አገልግሎት፣ እና በፅሁፍ ሥራ ላይ ነበር። በ80 ዓመቱም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
Sibbes unpacked this image in a sermon series he preached on the Song of Solomon, showing how Christ, our great Bridegroom, has joined Himself to His bride; taken on Himself our sin, death, and judgment; and imparted to us His life and perfect righteousness. He has become poor that we might receive His riches. In other words, because of our union with Christ, believers are justified and declared righteous in God’s sight with the very righteousness of Christ. Good works will flow as a result not a cause of the Christian’s righteousness. As the bride shares the status of her Bridegroom, so Christians share—or rather, have imputed to them—the righteous status of Christ. It is what Luther called the “joyful exchange.” Christ is one with His people, and so all theirs is His, and all His is theirs.
Joel Beeke
Puritansን እንወቅ
Richard Sibbes(1577_1635)
ሪቻርድ ሲብስ በ1577 የእንግሊዝ Puritanism እምብርት በሆነችው በቶስቶክ፣ሰፎልክ ነበር የተወለደው። Thurston በሚገኘው የአካባቢው የሰበካ ቤተክርስቲያን(parish church) የተጠመቀ ሲሆን፣እዚያው ባለ ትምህርት ቤትም ትምህርቱን ተከታተለ። ልጅ ሆኖም መጻሕፍትን ይወድ ነበር። አባቱ ጳዉሎስ ሲብስ ታታሪ የእንጨት ጎማዎችን የሚሰራና የሚጠግን ባለሙያ እና እግዚአብሔርን የሚፈራ ክርስቲያን የነበረ ቢሆንም፣በልጁ የመጻሕፍት ፍላጎት ይበሳጭ ነበር። የጎማ መሥሪያ መሣሪያዎችን ሥጦታ በመስጠት ልጁ መጻሕፍት የመግዛት ልማዱን እንዲተው ሊያደርገዉ ቢሞክርም፣ብላቴናው ግን ከሃሳቡ ፈቀቅ ሊል አልቻለም። በሌሎች ሰዎች ድጋፍ በ18 ዓመቱ በካምብሪጅ በሚገኘው የቅዱስ ዮሐንስ ኮሌጅ ተቀባይነት አገኘ። በ1599 የመጀመሪያ ዲግሪዉን፣በ1601 የባልደረባነት ማዕረግን፣ እንዲሁም በ1602 የማስተርስ ዲግሪዉን ተቀበለ። በ1603 ሲብስ በወንጌል አባቴ ብሎ በሚጠራው በጳውሎስ ቤይንስ ስብከት ወደ ክርስቶስ መጣ።
ሲብስ በ1608 በኖርዊች ከተማ በኢንግላንድ ቤተክርስቲያን ዉስጥ ለአገልግሎት ተሾመ። ከ1611_1616 በካምብሪጅ በሚገኘው የቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ዉስጥ በመምህርነት አገለገለ። የእሱም ስብከት ካምብሪጅን ፐርኪንስ ከሞተ በኋላ ወድቃበት ከነበረው መንፈሳዊ ድካም ቀስቅሷታል። ሲብስ በ1617 ወደ ለንደን በመምጣት የGray's inn መምህር በመሆን ማገልገል ጀመረ። በ1626 በካምብሪጅ የሚገኘው የቅድስት ካትሪን ኮሌጅ የበላይ ሃላፊ ሆነ። ሲብስ በተሾመ ጥቂት ጊዜ ዉስጥ በካምብሪጅ የዶክተር ኦፍ ዲቪኒቲ ዲግሪዉን ተቀበለ። እግዚአብሔርን ማዕከል ካደረገ ስብከቱና ሰማያዊ ሐሳብ ካለዉ የሕይወት ዘይቤዉ የተነሳ "the heavenly doctor" በመባል ይጠራል። Puritans ሲብስን ክርስቶስን ማዕከል ያደረገና ተግባራዊ ክርስትና የሚሰብክ መሆኑን ይናገሩ ነበር።
ሲብስ ከመሞቱ ከአንድ ሳምንት በፊት የሰበከው የመጨረሻው ስብከቱ
ዮሐንስ 14:2
[2] በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ ይህ ባይሆንማ ኖሮ እነግራችሁ ነበር፤ የምሄደውም ስፍራ ላዘጋጅላችሁ ነው። በሚለው ቃል ላይ ነበር። በመጨረሻዎቹ ቀናት ነፍሱ እንዴት እንደሆነች ሲጠየቅ ሲብስ "በጣም ደህና ነኝ ባልል ኖሮ እግዚአብሔርን እጅግ እበድለዉ ነበር"ሲል ነበር የመለሰው። ሲብስ በሐምሌ 5 ቀን 1635 ባለጸጋ ወደሆነው አዳኙ ሄደ።
Do any of us find decays in grace prevailing in us;—deadness, coldness, lukewarmness, a kind of spiritual stupidity and senselessness coming upon us? Do we find an unreadiness unto the exercise of grace in its proper season, and the vigorous acting of it in duties of communion with God, and would we have our souls recovered from these dangerous diseases? Let us assure ourselves there is no better way for our healing and deliverance, yea, no other way but this alone,—namely, the obtaining a fresh view of the glory of Christ by faith, and a steady abiding therein. Constant contemplation of Christ and his glory, putting forth its transforming power unto the revival of all grace, is the only relief in this case.
John Owen
Puritansን እንወቅ
William Perkins(1558_1602G.C)
ዊሊያም ፐርኪንስ፣አንዳንዴ "the father of Puritanism" በመባል ይጠራል። ከአባቱ ቶማስ እና ከእናቱ አና ፐርኪንስ በ1558 እ.ኤ.አ. በwarwickshire/England ነበር የተወለደው። በወጣትነቱም ግልፍተኛ ባሕሪ የነበረው፣በስድብ እና በስካር የተጠመደ ነበር። ነገር ግን በካምብሪጅ በሚገኘው የክርስቶስ ኮሌጅ(Christ's college) ተማሪ እያለ፣አንዲት ሴት በጎዳና ላይ ሆና ሥነምግባር የጎደለውን ልጇን እንደ "ሰካራሙ ፐርኪንስ" ትሆናለህ ብላ ስትገስፀዉ ይሰማል፣ይህን ጊዜ ነው በፐርኪንስ ሕይወት ዉስጥ ትልቅ መንፈሳዊ ለዉጥ(conversion) የጀመረው። ይህ ክስተት ፐርኪንስን እጅግ ስላሳፈረዉ ክፉ መንገዱን በመተው ድነትን ፍለጋ ወደ ክርስቶስ እንዲሸሽ አደረገው። የmathematics ትምህርቱን እንዲሁም በምስጢራዊ ጥበባት(occult) ላይ የነበረውን ከፍተኛ ፍላጎት በመተው፣የሥነ-መለኮት ትምህርትን መከታተል ጀመረ።
በ1584 የማስተርስ ዲግሪዉን ካገኘ በኋላ በቅዱስ እንድርያስ ቤተክርስቲያን በመጋቢነት አገልግሎ ነበር። በተጨማሪም ከ1584_1594 በክርስቶስ ኮሌጅ ዉስጥ በባልደረባነት ያገለገለ ሲሆን፣በዚያም የመስበክ፣የማስተማር እና ተማሪዎችን የማማከር(mentor) ሃላፊነት ነበረበት። ትኩረቱም የነበረው ከቤተክርስቲያን አስተዳደርና መዋቅር(church polity)ይልቅ የመጋቤያዊ(pastoral) ጉድለቶች፣የመንፈሳዊ ሕይወት ድካሞችና በቤተክርስቲያን ዉስጥ ያሉ ነፍስን የሚያጠፋ ቸልተኝነትን መቅረፍ ላይ ነበር። ፐርኪንስ ቅዱሳት መጻሕፍትን የመተርጎምና የማብራራት ልዩ ስጦታ የነበረው ሲሆን፣መደበኛውን ሰው በቀላል ስብከትና ግልጽ በሆነ የሥነ-መለኮት አቀራረብ ለመድረስ የሚያስችል አስደናቂ ችሎታ ነበረው። የቅድመ ወሰንን(predestination) ትምህርት ከተግባራዊ ክርስትና አኗኗር ጋር(godly living) ማጣመር ዓላማው ነበር። የእግዚአብሔር ሉዓላዊነትና የሰው ሃላፊነት complimentary doctrine ነው ብሎም በጽኑ ያምን ነበር።
ፐርኪንስ ንግስት ኤልሳቤጥ(Queen Elizabeth) ዘመነ መንግሥታቸዉን ከመጨረሻው ጥቂት ቀደም ብሎ፣በ1602 በኩላሊት ጠጠር ሕመም ምክንያት ነበር ሕይወቱ ያለፈው። ፐርኪንስ በሞተበት ጊዜ በእንግሊዝ አገር የነበሩት የእሱ መጻሕፍት ሽያጭ የጆን ካልቭን፣ የቴዎዶር ቤዛ እና የሔንሪ ቡሊንገር መጻሕፍት በጋራ ተደምረው ከነበራቸው ሽያጭ በላይ ነበር። ቶማስ ጉድዊን ከዓመታት በኋላ ወደ ካምብሪጅ ሲገባ፣በፐርኪንስ እግር ሥር ተቀምጠው የተማሩ ስድስት መምህራኑ አሁንም የእሱን ትምህርት እያስተላለፉ እንደነበርና ካምብሪጅም በፐርኪንስ ስብከት ኃይል ተሞልታ እንደነበር ፅፏል። ፐርኪንስ እንደ የንግግር ጥበብ አዋቂነቱ፣መፅሐፍ ቅዱስን በጥልቀት ፈትቶ እንደሚያብራራ፣የሥነ-መለኮት ምሁር እና እረኛ በመሆኑ የpuritan ንቅናቄ አርክቴክት ለመሆን በቅቷል።
The emanation of divine love to us begins with the Father, is carried on by the Son, and then communicated by the Spirit; the Father designing, the Son purchasing, the Spirit effectually working: which is their order. Our participation is first by the work of the Spirit, to an actual interest in the blood of the Son; whence we have acceptation with the Father.
John Owen
ትዕቢት(pride) የመጀመሪያው የእግዚአብሔር ጠላት ነው። በኤደን ገነትም የመጀመሪያው ኃጢአት ነበረ። ትዕቢት ከሌሎች ኃጢአቶች የተለየ ነው። ሌሎች ኃጢአቶች ከእግዚአብሔር ይለዩናል፤ነገርግን ትዕቢት ቀጥታ በእግዚአብሔር ላይ የሚደረግ ጥቃት ነው። ልባችንን ከእግዚአብሔር በላይ እና በእግዚአብሔር ላይ ያነሳሳል፤ Henry smith የሚባል ሰው "pride seeks to dethrone God and enthrone self" ይላል። Jonathan Edwards የትዕቢትን ዉስብስብነት ከሽንኩርት ጋር በማነፃፀር አንዱን layer ስናነሳ ሌላው layer ይቀራል ይላል።
Puritans ዓለማዊያን ትዕቢትን ሲጋቱ፣አማኞች ግን መዋጋት እንዳለባቸው ያስተምራሉ። ለእዚህም የተወሰኑ መንገዶችን ይጠቁማሉ:-
1, በተዋረደዉ ክርስቶስ እና በትዕቢተኛዉ ክርስቲያን መካከል ያለዉን ልዩነት ማሰብ ነው።
2, እግዚአብሔርን በጥልቀት ማወቅ ነው። ባሕርያቱን፣ክብሩን መረዳት። ኢዮብና ኢሳያስም የሚያስተምሩን እግዚአብሔርን ባወቅን ቁጥር እና ስለእርሱ ከፍ ያለ ሐሳብ በኖረን ቁጥር ትሁት እንደምንሆን ነው።(ኢዮብ 42፣ኢሳያስ 6)።
3,በሞትና በፍርድ ቀን እዉነታ እንዲሁም በዘላለም ትልቅነት ላይ meditate ማድረግ። Thomas Watson ስለ eternity ሲናገር እንዲህ ይላል:- "ምድር በአሸዋ ብትሞላና አንድ ወፍ በዓመት አንድ ጊዜ አንድ አሸዋ ብታነሳ ለሰው ልጅ ተስፋ አለው"።
4,በየቀኑ ይህን ቃል ማስተዋል
ምሳሌ 16:18 [18] ትዕቢት ጥፋትን፣ የእብሪት መንፈስም ውድቀትን ትቀድማለች።5, Puritan Richard Mayo የተባለ ሰው በተናገረው ነገር እራስን examine ማድረግ:- “እንደ አንተ ያለ ኃጢአት የሠራ፣ እንደ አንተም ያለ ኑሮ የኖረ፣ ብዙ ዘመንን ያባከነ፣ እጅግ ብዙ ምሕረትን ያላግባብ የተጠቀመ፣ ብዙ ኃላፊነቶችን የተወ፣ እጅግ ታላላቅ የጸጋ መንገዶችን የናቀ ሰው — ሊታበይ ይገባዋልን? የእግዚአብሔርን መንፈስ እጅግ ያሳዘነ፣ የእግዚአብሔርን ሕግ የጣሰ፣ የእግዚአብሔርንም ስም ያዋረደ ሰው — ሊታበይ ይገባዋልን? እንደ አንተ ያለ ልብ ያለው ሰው ሊታበይ ይገባዋልን?”
መዝሙር 46:1-11
[1] አምላካችን መጠጊያችንና ኀይላችን፣ በሚደርስብን መከራ ሁሉ የቅርብ ረዳታችን ነው። [2] ስለዚህ ምድር ብትነዋወጥ እንኳ፣ ተራሮችም ወደ ባሕር ጥልቅ ቢሰምጡ አንፈራም። [3] ውሆች ቢያስገመግሙ፣ ዐረፋ ቢደፍቁም፣ ተራሮችም ከውሆቹ ሙላት የተነሣ ቢንቀጠቀጡም አንደናገጥም። ሴላ [4] የእግዚአብሔርን ከተማ፣ የልዑልን የተቀደሰ ማደሪያ ደስ የሚያሰኙ የወንዝ ፈሳሾች አሉ። [5] እግዚአብሔር በመካከሏ ነው፤ አትናወጥም፤ አምላክ በማለዳ ይረዳታል። [6] ሕዝቦች በዐመፅ ተነሡ፤ መንግሥታትም ወደቁ፤ ድምፁን ከፍ አድርጎ አሰማ፤ ምድርም ቀለጠች። [7] የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ከእኛ ጋራ ነው፤ የያዕቆብም አምላክ መጠጊያችን ነው። ሴላ [8] ኑና የእግዚአብሔርን ሥራ፣ ምድርንም እንዴት ባድማ እንዳደረጋት እዩ። [9] ከዳር እስከ ዳር ጦርነትን ከምድር ያስወግዳል፤ ቀስትን ይሰብራል፤ ጦርን ያነክታል፤ ጋሻንም በእሳት ያቃጥላል። [10] “ዕረፉ፤ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ ዕወቁ፤ በሕዝቦች ዘንድ ከፍ ከፍ እላለሁ፤ በምድርም ላይ ከፍ ከፍ እላለሁ።” [11] የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ከእኛ ጋራ ነው፤ የያዕቆብም አምላክ መጠጊያችን ነው። ሴላ
