fa
Feedback
Puritans pool

Puritans pool

رفتن به کانال در Telegram

Now that we have all this sound doctrine,we need to see it applied and worked out in our head and our hearts and in our hands,and we need to see it worked out in our homes, in our Churches,and our communities,and live in accordance with it everywhere.

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
417
مشترکین
+424 ساعت
+67 روز
+1730 روز

در حال بارگیری داده...

کانال‌های مشابه
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '26
+9
در 1 کانال‌ها
ژوئن '26
+45
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+282
در 2 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '260
در 5 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+107
در 3 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
12 ژوئیه0
11 ژوئیه+4
10 ژوئیه0
09 ژوئیه0
08 ژوئیه+1
07 ژوئیه+1
06 ژوئیه0
05 ژوئیه0
04 ژوئیه+1
03 ژوئیه0
02 ژوئیه+2
01 ژوئیه0
پست‌های کانال
"God hath appointed one day in seven to be a Sabbath, that our souls may be refreshed in Him." "እግዚአብሔር ነፍሳችን በእርሱ እንድትታደስና እንድትበረታ፣ ከሰባቱ ቀናት አንዱን ለሰንበት አድርጎ ሾሞአል።" Thomas Watson

2
ስለ መጨረሻዉ ፍርድ ማስተማር ኃጥኣንን በክርስቶስ ፍርድ ወንበር ፊት መቆም፣ሁሉን በሚያዉቅ፣ሁሉን በሚችል፣ሁሉን በሚያይ በሕያው እግዚአብሔር እጅ መዉደቅ እጅግ አስፈሪ መሆኑን ከማስተማር ባለፈ፤እግዚአብሔርን ለሚፈሩ የመጽናኛና የተስፋ መልእክት ነው። በክርስቶስ ጽድቅ የተሸፈኑ ስለሆኑ፣ የኀጢአተኞች ክፉ ሥራ ፍትሐዊ ፍርድን እንደሚቀበል፣ እነርሱም በእግዚአብሔር ፊት ለዘላለም የተባረኩ እንደሚሆኑ በማወቅ መጽናናትን ያገኛሉ። በዚህ በአሁኑ ሕይወትም መከራዎች መካከል፣ ከዓለም፣ ከሥጋ፣ ከዲያብሎስም የሚመጣባቸውን ተቃውሞ ሲታገሉ፣ በዚህ እውነት እውነተኛ መጽናኛና እረፍት ሊያገኙ ይችላሉ።
316
3
ጽድቅ፣በእግዚአብሔር ዘንድ ያለን ሁኔታ(status) የሚቀየርበት ሲሆን፤ቅድስና ባሕሪያችን የሚቀየርበት ነው። ጽድቅ፣የኃጢአትን ክስ ሲያስወግድ ቅድስና ከኃጢአት ብክለት ነጻ የምንሆንበት ነው። ጽድቅ፣በፍርድቤት ቋንቋ ነጻ መሆናችን የሚታወጅበት(Legal declaration) ሲሆን ቅድስና የግል በሂደት የሚመጣ ለዉጥ(personal transformation) ነው። ጽድቅ፣ከኃጢአተኛው ዉጭ ሲሆን ቅድስና በኃጢአተኛው ዉስጥ ነው። ጽድቅ ፍፁምና ቅጽበታዊ ሲሆን ቅድስና እዚህ ምድር ላይ ፍፁም የማይሆን ሂደታዊ ለዉጥ ነው። ጽድቅ የእግዚአብሔር ብቻ ሥራ ነው፤ ቅድስና የእኛንም ተሳትፎ ይጠይቃል። ለመጽደቅ Righteousness is imputed. ለቅድስና Righteousness is infused. ጽድቅ በአማኞች ሁሉ ዘንድ እኩል ሲሆን ቅድስና ግን እኩል አይደለም። ጽድቅ passive ነው። ቅድስና active ነው። ጽድቅ በdegree አይቀንስም። ቅድስና ግን ሊቀንስ ይችላል። ጽድቅ የመኖር መብትን ሲሰጥ ቅድስና ሕይወትን enjoy and experience እንድናደርግ ያደርገናል። ጽድቅ በእምነት ብቻ ነው። ቅድስና በፍቅር በሚሰራ እምነት እንዲሁም ሕጉን በመጠበቅ ነው። ጽድቅ በመቀደስ የሚገኝ አይደለም። ቅድስና ግን የመጽደቃችን ዉጤት ነው።
116
4
የተባረከውን መካከለኛችንንና ክቡር ሕግ ሰጪያችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር፣ እንክብካቤና ታማኝነት የሚያንቋሽሽ፣ ወይም ከሙሴ ያነሰ ታማኝ እንደሆነ የሚያሳይ፣ እንዲሁም በአዲስ ኪዳን ካሉት ታላላቅ ሥርዓቶች—እንዲያውም ምሥጢራት አንዱ ከብሉይ ኪዳን ማንኛውም ሕግ ወይም ሥርዓት ይልቅ የበለጠ ጨለማና የማይገለጥ እንዲሆን የሚያደርግ ትምህርት፣ ከእግዚአብሔር ሊሆን አይችልም። ‎ነገር ግን፣ የሕፃናት ጥምቀት ትምህርት የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር፣ እንክብካቤና ታማኝነት ያንቋሽሻል፤ ከሙሴም ያነሰ ታማኝ እንደሆነ ያሳያል፤ እንዲሁም በአዲስ ኪዳን ካሉት ታላላቅ ሥርዓቶች—እንዲያውም ምሥጢራት—ከብሉይ ኪዳን ማንኛውም ሕግ ወይም ሥርዓት ይልቅ የበለጠ ጨለማና የማይገለጥ እንዲሆን ያደርጋል። ‎ ‎ስለዚህ፣ የሕፃናት ጥምቀት ከእግዚአብሔር የመጣ ትምህርት ሊሆን አይችልም። ‎ Benjamin Keach
126
5
Then Interpreter took him by the hand, and led him into a very large parlor which was full of dust, because it was never swept. After Christian had contemplated this scene for a little while, the Interpreter called for a man to sweep the room. When he began to sweep, the dust began to so thickly swirl around the room—that Christian began to be choked by it! Then Interpreter said to a maiden who stood nearby, "Bring some water, and sprinkle the room!" After she had done this—the parlor was then swept and cleansed with ease. "What does this mean?" Christian inquired. Interpreter explained, "This parlor is the heart of a man which has never been sanctified by the sweet grace of the Gospel. The dust is his original sin and inward corruptions, which have defiled the whole man. He who began to sweep at first, is the Law . The maiden who brought and sprinkled the water, is the Gospel . "You saw that as soon as the man began to sweep, that the dust thickly swirled around the room, and became even more difficult to cleanse, nearly choking you to death. This is to show you that the Law, instead of cleansing the heart from sin—does in fact arouse sin, giving greater strength to it—and causing it to flourish in the soul. The Law both manifests and forbids sin—but it has no power to subdue sin. "Again, you saw the maiden sprinkle the room with water, upon which it was cleansed with ease. This is to show you, that when the Gospel comes in the sweet and precious influences thereof to the heart—then, I say, even as you saw the maiden subdue the dust by sprinkling the floor with water—just so is sin vanquished and subdued, and the soul made clean, through faith, and consequently fit for the King of glory to inhabit." ‎ከዚያ ፡ በኋላ ፡ አስተርጓሚ ፡ ክርስቲያንን ፡ በእጁ ፡ ይዞት ፡ ወደ ፡ አንድ ፡ ትልቅ ፡ የእንግዳ ፡ መቀበያ ፡ ቤት ፡ ወሰደው ። ይህም ፡ ክፍል ፡ ከቶ ፡ ካለመጠረጉ ፡ የተነሣ ፡ አቧራ ፡ ሞልቶበት ፡ ነበር ። አስተረጓሚውም ፡ ክፍሉን ፡ ለጥቂት ፡ ጊዜ ፡ ከተመለከተ ፡ በኋላ ፡ አንድ ፡ ሰው ፡ ጠርቶ ፡ እንዲጠርግ ፡ አዘዘው ። ሰውየውም ፡ መጥረግ ፡ እንደ ፡ ጀመረ ፡ አቧራው ፡ በብዙ ፡ ስለ ፡ በነነ ፡ ክርስቲያን ፡ ታፍኖ ፡ ሊሞት ፡ ጥቂት ፡ ቀረው ። አንዲት ፡ ቆንጆ ፡ በቅርብ ፡ ቆማ ፡ ነበር ። አስተረጓሚውም ፡ ጠራትና ፡ እንዲህ ፡ አላት ፤ ውኃ ፡ አምጪና ፡ በክፍሉ ፡ ውስጥ ፡ እርከፍክፊበት ። ይህንን ፡ ካደረገች ፡ በኋላ ፡ ቤቱ ፡ ደህና ፡ ሆኖ ፡ ተጠረገ ፤ ንጹሕም ፡ ሆነ ። ክርስቲያንም ፡ አለ ፤ የዚህ ፡ ምስጢር ፡ ምንድር ፡ ነው? አስተርጓሚው ፡ እንዲህ ፡ ሲል ፡ መለሰለት ፤ ይህ ፡ ክፍል ፡ ጣፋጭ ፡ በሆነው ፡ በወንጌል ፡ ጸጋ ፡ ከቶ ፡ ያልተቀደሰ ፡ የሰው ፡ ልብ ፡ ይመስላል ። አቧራው ፡ የሰውየውን ፡ ሁለንተና ፡ ያረከሰው ፡ ከጥንት ፡ የተወረሰ ፡ ኃጢአትና ፡ ውስጣዊ ፡ ርኩሰት ፡ ነው ። መጀመሪያ ፡ መጥረግ ፡ የጀመረችው ፡ ኦሪት ፡ ናት ። ውኃ ፡ አምጥታ ፡ በክፍሉ ፡ ውስጥ ፡ ያረከረከችበት ፡ ቆንጆ ፡ ወንጌል ፡ ናት ። የመጀመሪያው ፡ ሰው ፡ መጥረግ ፡ እንደ ፡ ጀመረ ፡ ትቢያ ፡ መብዛቱ ፡ አንተ ፡ ልትሞት ፡ ጥቂት ፡ እስኪቀርህ ፡ ድረስ ፡ በአቧራ ፡ መታፈንህ ፤ ከዚህም ፡ የተነሣ ፡ ሰውየው ፡ ክፍሉን ፡ ለመጥረግ ፡ አለመቻሉ ፤ አንተ ፡ ይህን ፡ የሚከተለውን ፡ እንድታውቅ ፡ ነው ። ኦሪት ፡ (በሥራዋ ፡) ልብን ፡ ከኃጢአት ፡ አያነጻም ። ኃጢአትን ፡ ይገልጣል ፡ ደግሞም ፡ ይከለክላል ፤ ነገር ፡ ግን ፡ ድል ፡ ለመንሣት ፡ ለመጨፍለቅ ፡ የሚሆን ፡ ኃይል ፡ አይሰጥም ። ኃጢአትን ፡ ያነቃቃል ፡ ብርታት ፡ ይሰጠዋል ፡ በነፍስም ፡ ውስጥ ፡ ያበዛዋል ። ከዚያ ፡ ቀጥሎ ፡ ቆንጆይቱ ፡ በክፍሉ ፡ ውስጥ ፡ ውኃ ፡ ከአርከፈከፈችበት ፡ በኋላ ፡ በሰላም ፡ እንደ ፡ ተጠረገ ፡ አየህ ። ይህ ፡ መደረጉ ፡ አንተ ፡ ይህን ፡ የሚከተለውን ፡ እንድታውቅ ፡ ነው ። በልብ ፡ ላይ ፡ ውኃ ፡ በማርከፍከፍ ፡ ቆንጅዬቱ፡ አቧራውን፡ ጸጥ፡ እንዳደረገችው፡ ሁሉ፡ ወንጌልም፡ ጣፋጭና፡ ክቡር፡ በሆኑት፡ ስሜቶች፡ ወደ፡ ልብ፡ ሲገባ፡ ኃጢአትን፡ያጠፋዋል፡ ደግሞም፡ ይገዛዋል ። ነፍስ፡ ከወንጌል፡ በሚሆን፡ ሃይማኖት፡ ንጹሕ፡ ትሆናለች ፡ ስለዚህም፡ ለምስጋና፡ ንጉሥ፡ የምትገባ፡ መኖሪያ፡ የተዘጋጀች፡ ትሆናለች ። John Bunyan
194
6
Following_God_Fully_An_Introduction_to_the_Puritans_Joel_R_Beeke;.epub
155
7
The Mystery of Providence - John Flavel.epub
156
8
‎You complain that Providence delays to perform to you the mercies you have prayed and waited for, but have you right ends in your desires after these mercies? It may be that this is the cause you ask and receive not (James 4:3). The lack of a good aim is the reason why we lack good success in our prayers. It may be we pray for prosperity, and our aim is to please the flesh. We look no higher than the pleasure and accommodation of the flesh. We beg and wait for deliverance from such a trouble and affliction, not that we might be the more ready and prepared for obedience, but freed of what is grievous to us and destroys our pleasure in the world. Certainly, if it is so, you have more need to judge and condemn yourselves, than to censure and suspect the care of God. ‎ ‎You wait for good, and it does not come; but is your will brought to a due submission to the will of God about it? ‎  ‎  Certainly, God will have you come to this before you enjoy your desires. Enjoyment of your desires is the thing that will please you, but resignation of your wills is that which is pleasing to God. If your hearts cannot come to this, mercies cannot come to you. David was made to wait long for the mercy promised him, yea, and to be content without it before he enjoyed it. He was brought to he 'as a weaned child' (Psalm 131:2), and so must you. ‎ John Flavel
168
9
Discovering God's will: ‎ ‎(1) Get the true fear of God upon your hearts. Be really afraid of offending Him. God will not hide His mind from such a soul. 'The secret of the LORD is with them that fear him; and he will show them his covenant' (Psalm 25:14). ‎ ‎(2) Study the Word more, and the concerns and interests of the world less. The Word is a light to your feet (Psalm 119:105), that is, it has a discovering and directing usefulness as to all duties to be done and dangers to be avoided. It is the great oracle at which you are to inquire. Treasure up its rules in your hearts, and you will walk safely. 'Thy Word have I hid in mine heart that I might not sin against thee' (Psalm 119:11). ‎ ‎(3) Reduce what you know into practice, and you shall know what is your duty to practice. 'If any man do his will he shall know of the doctrine' (John 7:17). 'A good understanding have all they that do his commandments (Psalm 111:10). ‎ ‎(4) Pray for illumination and direction in the way that you should go. Beg the Lord to guide you in straits and that He would not permit you to fall into sin. This was the holy practice of Ezra: 'Then I proclaimed a fast there at the river Ahava, that we might afflict ourselves before our God, to seek of him a right way for us, and for our little ones, and for all our substance' (Ezra 8:21). ‎ ‎(5) And this being done, follow Providence so far as it agrees with the Word and no further. There is no use to be made of Providence against the Word, but in subservience to it. And there are two excellent uses of Providence in subservience to the Word. Providences, as they follow promises and prayer are evidences of God's faithfulness in their accomplishment. When David languished under a disease, and his enemies began to triumph in the hopes of his downfall, he prays that God would be merciful to him and raise him up (Psalm 41:10); and by that, he says, he knew the Lord favored him, because his enemy did not triumph over him (verse 11). This providence he looked upon as a token for good, as elsewhere he calls it (Psalm 86:17). Also providences give us loud calls to those duties which the command lays upon us and tell us when we are actually and presently under the obligation of the commands as to the performance of them. Thus when sad providences befall the Church or ourselves, they call us to humiliation; and let us know that then the command upon us to humble ourselves at the feet of God is in force upon us. 'The LORD's voice crieth unto the city, and the man of wisdom shall see thy name. Hear ye the rod, and who hath appointed it' (Micah 6:9). The rod has a voice, and what does it speak? Why, now is the time to humble yourselves under the mighty hand of God. This is the day of trouble, in which God has bid you to call upon Him. And on the contrary, when comfortable providences refresh us, it now informs us this is the time to rejoice in God, according to the rule: 'In the day of prosperity be joyful' (Ecclesiastes 7:14). These precepts bind always, but not to always. It is our duty therefore and our wisdom to distinguish seasons, and know the proper duties of every season; and Providence is an index that points them out to us. John Flavel
155
10
https://youtu.be/3VeYO6hmKGs?si=Qv5iOLWnVqVUGebS
127
11
ማቴዎስ 5:3 [3] “በመንፈስ ድኾች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፤ መንግሥተ ሰማይ የእነርሱ ናትና።" ኢሳይያስ 55:1-2 [1] “እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ ኑ፤ እናንተ ገንዘብ የሌላችሁ፣ ወደ ውሆች ኑ፤ ኑና ግዙ፤ ብሉም! ኑና ያለ ገንዘብ፣ ያለ ዋጋ፣ የወይን ጠጅና ወተት ግዙ።"
172
12
The Marrow Theology ‎1. True saving faith has assurance in it, but it may be clouded by accompanying doubts. Thus, sinners should be called to assuredly trust in Christ to cover their sins through His shed blood, to give them a title to heaven and to dwell in them by His Spirit. ‎ ‎2. The atonement is limited to the elect alone, but the power of Christ's death is sufficient for all so that Christ and His death may be offered to all. This is good Dortian theology: sufficient for all; efficient for the elect. ‎ ‎3. The covenant of grace has no conditions that sinners must meet prior to entering the covenant and it has no conditions that could disinherit anyone from the covenant. Effectual calling brings sinners into the covenant of grace, giving them faith, and the Spirit preserves believers in the covenant. Faith is a blessing of the covenant of grace, not a precondition of entering or condition of continuing. ‎ ‎4. Sinners should trust in Christ, not only for justification but also *for* repentance. Repentance is by faith in Christ. No one should be told that they must first change and then they can have Christ and His benefits because change (sorrow for sin, hating and forsaking it) is itself one of Christ's benefits. ‎ ‎5. Holiness and good works are neither a ground nor a means of entering into heaven. Rather, holiness is necessarily present in those who enter into heaven. It is necessary as a fruit of salvation, and it is necessary in those being saved, but we should avoid language that says holiness is "necessary for salvation" (though some orthodox use it, but not the confessions) so as not to imply that we have to do good works to save ourselves. Tom Hicks
231
13
በክርስቶስ ሞት እና ትንሣኤ ከጠላቶቻችን ሁሉ ማለትም:- ከኃጢአት ክስና ኩነኔ፣ከእግዚአብሔር ቁጣ፣ከሕግ እርግማን፣አሁን ካለንበት ክፉ ዓለም፣ከሰይጣን እስራት፣ከኃጢአት አገዛዝ፣ከመከራ ክፋት፣ከሞት ፍርሃትና ባርነት፣ከመቃብር ኃይል፣ከዘላለም ጥፋት አምልጠናል። እግዚአብሔርንም በጽድቅ እና ቅድስና እናመልክ ዘንድ ነጻነት አግኝተናል። ‎ ‎ ሉቃስ 1:74-75 ‎[74] ከጠላቶቻችን እጅ አውጥቶ፣ ያለ ፍርሀት እንድናገለግለው፣ [75] በዘመናችንም ሁሉ በቅድስናና በጽድቅ በፊቱ ሊያቆመን ነው።
157
14
Working as a calling Puritans secular workን(ምድራዊ/ዓለማዊን ሥራ) የሚያዩበት መንገድ theologically rich ነው። ልክ እንደ ቤተክርስቲያን አዳሾቹ የእግዚአብሔር ጥሪ(vocation/calling) እንደሆነ በፅኑ ያምናሉ፣ያስተምራሉ። ለPerkins ምድራዊ ሥራ በእግዚአብሔር ኃይል እና ጌትነት ላይ የተመሠረተ ነው፤ይህንም ሲፅፍ እንዲህ ብሏል “A vocation (or calling) is a certain kind of life, ordained and imposed on man by God for the common good.” ለቤተክርስቲያን አገልግሎትም ይሁን ለምድራዊ ሥራ የሰው ጥሪ መጀመሪያውና መነሻው እግዚአብሔር ነው። ‎Perkins እግዚአብሔር የአንድን ሰው መጠራት በመወሰን ረገድ ያለውን ሚና ከጦር ጄኔራል ጋር ያነጻጽረዋል። "አንድ ጄኔራል ለእያንዳንዱ ሰው ቦታውን እና ማዕረጉን እንደሚመድብ ሁሉ፣ እግዚአብሔርም ለእያንዳንዱ ሰው መጠራትን (ሙያን) ይመድባል። እናም አንድ ወታደር በተመደበበት የጦር ግንባር “ሊኖርና ሊሞት” እንደሚገባው ሁሉ፣ እያንዳንዱም ሰው ጄኔራሉ (እግዚአብሔር) የሚለቅበት ጊዜ መድረሱን እስኪነግረው ድረስ በተጠራበት መጠራት ውስጥ ጸንቶ ሊቆይ ይገባል። ስለዚህ፣ አንድ ክርስቲያን ሥራውን በድንገተኛ አጋጣሚ ወይም በሰው ምርጫ ብቻ እንደደረሰበት ነገር አድርጎ ሊመለከተው አይገባም፤ ይልቁንም እያንዳንዱ ሙያ በእግዚአብሔር የተወሰነና የተደነገገ ነው።" ‎እግዚአብሔር ልጆቹን ለተለያዩ የሥራ ዓይነቶች አዘጋጅቷቸዋል። ብቁም እንዲሆኑ አስታጥቋቸዋል። አንዳንዶች የጠለቀ ዕውቀት የተቸሩ በመሆናቸው ለምሁራዊ/ለአእምሮ ሥራዎች ብቁ ሲሆኑ፣ ሌሎች ደግሞ ልዩ ጥንካሬና ብቃት ከእግዚአብሔር ስለተቸሩ የጉልበት ሥራዎች ላይ ይሰማራሉ። በእነዚህ ሁሉ ልዩ ስጦታዎች፣ የአጽናፈ ዓለሙ ጥበበኛ ገዥ ለእያንዳንዱ ሰው ተስማሚ ቦታውንና ሥራውን መድቧል፤ ከራሳቸው ድንበር (ክበብ) ውጭ ለሚንቀሳቀሱትም ከሽልማት ይልቅ ተግሣጽን ይሰጣቸዋል። እግዚአብሔር በመግቦቱ ፍጥረቱን ተመጋጋቢ አድርጎ ያስተዳድራል። የሰው ልጅ ድርሻ ተስማሚ የሆነውን የሥራ መስኩን ማግኘትና በሥራውም እግዚአብሔርን ማክበር ነው። ሉተር፣ቤተክርስቲያን መድረክ ላይ ቆሞ የሚሰብክ እና መንገድ የምትጠርግ ሴት በእግዚአብሔር ዘንድ ያላቸው ድርሻ እኩል ነው ይላል። ለእግዚአብሔር ክብር እስካደረጉት ድረስ። ‎እግዚአብሔር በአንድ በተወሰነ መጠራት (የሥራ መስክ) ውስጥ እንድንኖርና እንድንሠራ ስለጠራንና ስለፈጠረን፣ Puritans አንዴ ይህንን መጠራታችንን ካወቅን በኋላ እግዚአብሔር ሌላ ነገር ካልነገረን በቀር በዚያው መጽናት እንዳለብን ያስተምሩ ነበር። ከአንድ የሥራ መስክ ወደሌላ የሥራ መስክ ለመዘዋወር ከመሻት፣ ወይም በሌላው ሰው የሥራ መስክ ከመቅናት ይልቅ፣ አንድ ሰው ለእግዚአብሔር ክብርና ለጋራ ጥቅም ሲል በትጋት በዚያ በተመደበበት የሕይወት ስፍራ መሰማራት አለበት። ‎በሰው አካል ውስጥ የተለያዩ ክፍሎችና ብልቶች አሉ፤ ከእነዚህም እያንዳንዱ የአካል ክፍል ለራሱ ሳይሆን ለጠቅላላው አካል ጥቅም የሚሆን የየራሱ የተለየ አገልግሎትና ተግባር አለው። ይህንን ጉዳይ በዚህ መነጽር ስንረዳው፣ የሰው ልጅ ሥራ አዲስ ትርጉም ይይዛል። የአንድ ሰው ሥራ እግዚአብሔርን ከማክበር ባለፈ፣ በዙሪያው እና በአካባቢዉ ያሉ ሰዎችን ይጠቅማል። የምንሰራው ሥራ ህጋዊ እና ከእግዚአብሔር ሕግ ጋር የማይጣረስ(lawful and just) እስከሆነ ድረስ የእጆቻችንን ሥራ ይባርካል። ‎ ‎የልጆችን ጥሪ የመለየት ኃላፊነት የነበረባቸዉ ወላጆች ነበሩ ነገርግን እንደ አህጉር providentially አለመታደል ሆኖ ብዙዎቻችን ጥሪያችንን የመለየቱ ጉዳይ የእኛ ድርሻ ሆኗል። ጥሪያችንን  ወይም የሥራ መስካችንን ያላገኘን ሰዎች ካለን Puritans ሁለት ዋና ዋና መመዘኛዎችን ይጠቁሙናል፤ እነሱም፦ ስጦታ (ክህሎት) እና ፍላጎት ናቸው። አንድ ሰው በመጀመሪያ፦ ምን ማድረግ እፈልጋለሁ? በልቤስ ውስጥ ምን ለማድረግ አስባለሁ? ብሎ ራሱን መጠየቅ አለበት። በመቀጠልም፦ በምን ነገር ላይ ጎበዝ ነኝ?ምንስ ችሎታ አለኝ? ብሎ መጠየቅ ይኖርበታል። ፍላጎታችንና ስጦታችን ሲጣጣሙ ጥሪያችንን እንለያለን። ‎ 1 ተሰሎንቄ 4:11 ‎[11] ከዚህ በፊት እንዳዘዝናችሁ በገዛ እጃችሁ ሥሩ፤ በጸጥታ ኑሩ፤ በራሳችሁ ጕዳይ ላይ ብቻ አተኵሩ። ‎
176
15
Puritansን እንወቅ Jonathan Edwards(1703_1758) ‎፨ ጆናታን ኤድዋርድስ እ.ኤ.አ ጥቅምት 5 ቀን 1703 በኢስት ዊንድሶር ኮኒክቲከት(East Windsor፣Connecticut) ተወለደ። የኤድዋርድስ አባት እና የእናቱ አባት(አያቱ) ሁለቱም እጅግ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰባኪያን ነበሩ። ኤድዋርድስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን የተከታተለው በአባቱ የሰዋሰው(grammar) ትምህርት ቤት ሲሆን፥በዚያም በreformed theology እና Puritan piety የታነጸና የተኮተኮተ ነበር። በ13 ዓመቱ ወደ ኮሌጂየት በኋላ ዬል/Yale ኮሌጅ ተብሎ ወደተጠራዉ ትምህርት ቤት አመራ። በ1720 ከክፍሉ ከፍተኛ ዉጤት በማስመዝገብ የመጀመሪያ ድግሪውን ያገኘ ሲሆን፥ማስተርስ ድግሪውን ለመቀጠልም በዬል ቆየ። ኤድዋርድስ በልጅነቱ እና በወጣትነቱ የኃጢአት ጥፋተኝነት ስሜት(spiritual conviction) ያጠቃው የነበረ ቢሆንም በ1721 ወደ conversion በመምጣት ፍፃሜውን አግኝቷል። ‎ ‎፨የኤድዋርድስ የአገልግሎት ዘመን የጀመረው በ1722 በ new york city በሚገኝ አንድ የPresbyterian ቤተክርስቲያን ዉስጥ እንዲያገለግል በተጋበዘበት ወቅት ነበር። ሆኖም ወደ ኮኒክቲከት ለመመለስ ከአባቱ ጋር በመስማማቱ ይህ የመጋቢነት ቆይታው ከ8 ወራት አላለፈም። በዬል የማስተርስ ድግሪውን ካጠናቀቀ በኋላ፥በህዳር ወር 1723 በቦልተን ወደሚገኘው parish church የቀረበለትን ጥሪ ተቀብሎ አመራ። በሚቀጥለው ዓመት ኤድዋርድስ በኮሌጁ ዉስጥ በአስተማሪነት ለማገልገል ወደ ኒዉ ሄቨን ተመለሰ። ኤድዋርድስ እስከ 1726 ድረስ እዚያ የቆየ ሲሆን፥በዚያው ዓመት በእድሜ አያቱ ለሚሆኑት ለሰሎሞን ስቶዳርድ እረዳት ሆኖ እንዲያገለግል ከNorthampton፣Massachusetts የሕዝብ ጥሪ ደረሰው። እ.ኤ.አ የካቲት 15 ቀን 1727 በይፋ ተሹሞ አገልግሎቱን የጀመረ ሲሆን፥በ1729 የስቶዳርድ መሞትን ተከትሎ የቤተክርስቲያኑ ብቸኛ መጋቢ ሆነ። ኤድዋርድስ በመንፈሳዊ ግዴለሽነት ዉስጥ እየወደቀ በነበረው ማሕበር መካከል ፈሪሃ-እግዚአብሔርንና ቅድስናን ማስፋፋት ትልቅ ፈተና ሆኖበት ነበር። በዚህም ምክንያት በ1730ዎቹ መጀመሪያ ላይ ስብከቱን በተለየና በተለመዱ ኃጢአቶች ላይ ያተኮረ በማድረግ፥ሕዝቡ ንስሐ እንዲገባና ወንጌልን በእምነት እንዲቀበል አጥብቆ ያሳስብ ነበር። በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ አማካኝነትም፥የእሱ ስብከት ከ1734_1735 በNorthampton ዉስጥ ትልቅ የመንፈስ መነቃቃት እንዲቀሰቀስ አድርጓል። ‎ ‎፨ ሕጻናትን አላጠምቅም በማለቱ፣ከአንዳንድ ወጣቶች አያያዝ ጋር በተያያዘ ከተሰራጨ የሐሰት ወሬዎች እና ከበርካታ የሥነ-ሥርዓት እርምጃዎች ጋር ከተፈጠሩ ዉስብስብ ችግሮች ጋር ተዳምሮ፥የNorthampton ቤተክርስቲያን አባላት በ1750 ኤድዋርድስ ከመጋቢነት እንዲሰናበት በድምፅ ወሰኑ። በሚቀጥለው ዓመት ኤድዋርድስ ከቤተሰቡ ጋር ከNorthampton በመዉጣት ወደ ስቶክብሪጅ አቀና፤በዚያም ለአነስተኛ ማሕበር በመጋቢነት እንዲሁም ለnative Indians በሚሲዮናዊነት አገለገለ። በ1758 ኤድዋርድስ በPrinceton የሚገኘው የኮሌጅ ኦፍ ኒዉ ጄርሲ ፕሬዝዳንት ለመሆን ተስማማ። ይሁን እንጂ በPrinceton ጥቂት ወራትን ብቻ ካሳለፈ በኋላ፥እ.ኤ.አ መጋቢት 22 ቀን 1758 smallpox inoculation ባስከተለበት ዉስብስብ የጤና ችግር ምክንያት ሕይወቱ አለፈ። እጅግ ብዙና ለመረዳት የሚከብዱ ስራዎቹ አሁንም ድረስ በጥልቀት እየተጠኑና እየተመረመሩ ነው። ይህም አንዳንዶች እንደሚሉት እሱ የአሜሪካ የመጨረሻው Puritan እና ምርጡ theologian መሆኑን ማረጋገጫ ነው።
162
16
https://youtu.be/IQsWP0SuKu0?si=VBH6OJ-XtzR6Nuyy
154
17
Puritansን እንወቅ Matthew Henry (1662_1714) ‎ማቴዎስ ሄንሪ የተወለደው እ.ኤ.አ ጥቅምት 18 ቀን 1662 በብሮድ ኦክ ፍሊንትሻየር፣ኢንግሊዝ ዉስጥ ሲሆን፣ይህም የሆነው አባቱ ፊሊፕ ሄንሪ ከኢንግሊዝ ቤተክርስቲያን(Church of England) የአገልግሎት ዘርፍ በተገለሉ ሁለት ወር ባልሞላ ጊዜ ዉስጥ ነበር። ያለ ዕድሜው የተወለደ በመሆኑ ደካማ ልጅ የነበረ ቢሆንም ፣Spiritually እና Intellectually gifted ነበር። በዋናነት የተማረው በአባቱ ሲሆን ፣የግል አስተማሪዎችም እገዛ አድርገዉለታል። ሄንሪ በ1680 በኢስሊንግተን ወደሚገኘው የቶማስ ዱሊትል አካዳሚ ገባ። እዚያም በዱሊትል እና በቶማስ ቪንሰንት ስር ለሁለት ዓመታት የተማረ ሲሆን፣በወቅቱ በነበረው ስደት ምክንያት አካዳሚው ቦታዉን ለመቀየር ሲገደድ ሄንሪ ወደ ፍሊንትሻየር ተመለሰ። ለአገልግሎት የመጠራት ዕድሉ አነስተኛ መሆኑን የተረዳው ሄንሪ፣የሕግ ሙያ ዉስጥ ለመግባት ወሰነ። በዚህም መሠረት በግል የሥነ-መለኮት ትምህርቱን እየተከታተለ፣ሕግ ለማጥናት በ1685 በGray's Inn ተቀባይነት አገኘ። ‎ ‎በ1686 ሄንሪ በአባቱ መኖሪያ መንደር አካባቢ መስበክ ጀመረ። በንግድ ሥራ ጉዳዮች ምክንያትም በ1687 ቼስተር ተዛወረ። በዚያም የአካባቢው አጥቢያ አገልጋይ እንዲሆን እስከ-ተጠየቀበት ጊዜ ድረስ በሰዎች የግል መኖሪያ ቤቶች ዉስጥ ይሰብክ ነበር። እ.ኤ.አ ግንቦት 9 ቀን 1687 በለንደን Ordain ተደረገ፣በቼስተርም ማገልገሉን ቀጠለ። በጥቂት ዓመታት ዉስጥም በጉባኤው የጌታን እራት የሚቆርሱ ሰዎች ቁጥር ወደ 250 አደገ። እ.ኤ.አ በ1687 ሄንሪ ካትሪን ሃርድዌርን(Katherine Hardware) አገባ፤ይሁን እንጂ ከሁለት ዓመት በኋላ በወሊድ ምክንያት ሕይወቷ አለፈ። በ1690 ሄንሪ፣ሜሪ ዋርበርተንን(Mary Warburton) አገባ። አንድ ፊሊፕ የተባለ ወንድ ልጅ እና ስምንት ሴት ልጆች የወለዱ ሲሆን፣ከሴት ልጆቹ መካከል ሦስቱ በሕፃንነታቸው ሕይወታቸው አልፏል። በ1700 በክሩክ ሌይን(Crook Lane) ለሄንሪ የተገነባ የአምልኮ አዳራሽ ተከፈተ። በ1706 ደግሞ ከሄንሪ ጉባኤ ጋር የተቀላቀለ ሌላ ተጨማሪ ጉባኤን ለማስተናገድ እንዲቻል በህንፃው ላይ ሰገነት(ፎቅ መሰል የዉስጥ በረንዳ) ተጨመረ፤ይህም የጌታን እራት የሚካፈሉ ሰዎች ቁጥር ወጀ 350 አሳደገዉ። ሄንሪ፣ከእራሱ የጉባኤ አገልግሎት ሥራ በተጨማሪ፣በአምስት አቅራቢያ ባሉ መንደሮች ዉስጥ ወርሃዊ አገልግሎቶችን ያደርግ የነበረ ሲሆን፣በእስር ቤት ዉስጥ ላሉ እስረኞችም ዘወትር ይሰብክ ነበር። እ.ኤ.አ በ1704 በ42 ዓመቱ፣ሄንሪ በራሱ ገላጭ የስብከት ስልት(expository preaching) እንዲሁም በአገልግሎት ዘመኑ ባከማቻቸዉ ሰፊ የመፅሐፍ ቅዱስ ማስታወሻዎችና ጽሑፎች ላይ የተመሠረተ የመፅሐፍ ቅዱስ ማብራሪያ(commentary) ማዘጋጀት ጀመረ። በልጅነቱ የዕብራይስጥ፣ግሪክ እና ላቲን ቋንቋዎችን የተማረ ሲሆን፣የፈረንሳይኛ የሥራ ቋንቋ እዉቀትም ነበረው። ከእዚህ በተጨማሪ ከፍተኛ የሆነ የመመርመር እና ዶክትሪንን ቀላልና ጥልቅ በሆነ መንገድ የመግለጽ ብቃት ነበረው። ‎ ‎በ1710 ሄንሪ በለንደን አቅራቢያ ከሚገኙት እጅግ በጣም አስፈላጊ ከሆኑት የnonconformist ጉባኤዎች አንዱ ወደሆነው ወደ ሃክኒ(hackney) ተጋበዘ። ወዲያው ባይሆንም እንኳ ለመዛወር ተስማማ። እ.ኤ.አ ግንቦት 11 ቀን 1712 ብዙ እንባ የታጀበዉን የመጨረሻ ስብከቱን በቼስተር አቀረበ። በቀጣዩ ሳምንት በማሬ ስትሪት(Mare street)፣ሃክኒ አገልግሎቱን የጀመረ ቢሆንም፣ይህ አገልግሎቱ ግን ብዙም አልቆዩም። በሰኔ 1714 ወደ ለንደን እየተመለሰ ሳለ ከፈረሱ ላይ የወደቀ ሲሆን፣በቀጣዩም ቀን ሕይወቱ አለፈ። ‎ማቴዎስ ሄንሪ ይበልጥ የሚታወሰው በመጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያው (commentary) ቢሆንም፣ በዋናነት በተግባራዊና መንፈሳዊ ሕይወት (practical godliness) ላይ ያተኮሩ ሠላሳ ተጨማሪ መጻሕፍትንም ጽፏል። የሄንሪ የሕይወትና የአገልግሎት መልዕክት ቀላል ነበር፦ “እግዚአብሔርን በማገልገልና ከእርሱ ጋር ኅብረት በማድረግ የሚያልፍ ሕይወት፣ ማንም ሰው በዚህ ዓለም ላይ ሊኖረው የሚችለው እጅግ በጣም ምቹ ሕይወት ነው።”
203
18
ሰንበት፣በመጽሐፍ ቅዱስ ዉስጥ የተገለጠውን የእግዚአብሔርን ፈቃድ እና እዉቀት የምናዉቅበት፣በእግዚአብሔር ሕይወት ለመኖር ኃይል የምንታጠቅበት፣በረከት የምናፍስበት ዉድ ቀን። በመንፈሱ የተነካች እዉነተኛ ነፍስ፣ይበልጥ ከክርስቶስ ጋር ሕብረት ለማድረግ ትናፍቃለች። መልካም ሰንበት!
277
19
‎ከማይለወጠዉ የምርጫ ድንጋጌ የተነሣ..ከማይቀየረዉ፣ነጻ ከሆነው ከእግዚአብሔር ፍቅር የተነሣ..ውጤታማ ከሆነው ከኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ፣ምልጃ እና ከእርሱ ጋር ካለ አንድነት የተነሣ..ከእግዚአብሔር መሓላ የተነሣ..ለዘለዓለም የመንፈሱ ማደሪያ ከመሆናችን የተነሣ..ከእግዚአብሔር ዘር ከመካፈላችን የተነሣ..ከጸጋው ኪዳን ባሕሪ የተነሣ እስከመጨረሻው እንጸናለን! ‎ ‎ መዝሙር 121:1-8 ‎[1] ዐይኖቼን ወደ ተራሮች አነሣሁ፤ ረድኤቴ ከወዴት ይመጣል? [2] ረድኤቴ ሰማይንና ምድርን ከፈጠረ፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይመጣል። [3] እግርህ እንዲሸራተት አይፈቅድም፤ የሚጠብቅህም አይተኛም። [4] እነሆ፤ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም፤ አያንቀላፋምም። [5]  እግዚአብሔር ይጠብቅሃል፤ እግዚአብሔር በቀኝህ በኩል ይከልልሃል። [6] ፀሓይ በቀን አያቃጥልህም፤ ጨረቃም በሌሊት ጕዳት አታመጣብህም። [7]  እግዚአብሔር ከክፉ ሁሉ ይጠብቅሃል፤ ነፍስህንም ይንከባከባታል። [8]  እግዚአብሔር ከአሁን ጀምሮ እስከ ዘላለም፣ መውጣትህንና መግባትህን ይጠብቃል።
250
20
God hath given us divers ordinances to be exercised in, that if we be dull and weary in one, we may go to another, if you be weary in prayer, you may go to reading; if weary in reading, then go to meditating; if weary in meditation, you may go to conference; if you will spend your self only in one duty, there will dulness and deadness upon you; but if you exercise your self according to that variety which God hath given you, your heart will be kept up with an holy freshness unto things above. ‎ William Bridge
221