fa
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

رفتن به کانال در Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

نمایش بیشتر
2 936
مشترکین
+1424 ساعت
+3877 روز
+38530 روز
آرشیو پست ها
ወደ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋት አውራጃ ለከበባ የገባው የጠላት ኃይል በፋኖ ወታደራዊ ጥበብና ብልሀት በከበባ እየተመታ ይገኛል!! ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መ
+2
ወደ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋት አውራጃ ለከበባ የገባው የጠላት ኃይል በፋኖ ወታደራዊ ጥበብና ብልሀት በከበባ እየተመታ ይገኛል!! ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር ወደ ሸዋ ምድር ሲግተለተል የገባን የአገዛዙን ጥምር ጦር በወታደራዊ ብልሃትና ጥበብ በገባበት እዳይወጣ አድርጎ እየመታው ይገኛል። በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ቀወትና ቆሎሚያ አካባቢዎች የገባው የጠላት ኃይል፣ በአርበኞቹ የደጃዝማች ተሰማ እርገጤ ክፍለጦር  ከገጠመው ጽኑ ምት የተነሳ ማምለጫ አጥቶ ወደ ሸዋሮቢት ለማፈግፈግ ተገዷል። ሆኖም ከገባበት ለመውጣት የተቸገረው ጠላት በቀወት/በኩርብሪና በዋጮ አካባቢዎች በሚገኙ (3) ንጹሃን አርሶ አደሮች ላይ  አሰቃቂ ግድያ ፈፅሟል ።በሌላ ግንባር ከመዘዞ አያበር ቀበሌ እስከ መሶቢት ተራራ ድረስ ባለው መሬት ላይ በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር አስቻለው ደሴ ክ/ር ከበባ ውስጥ የወደቀው የጠላት ጦር፣ ውድቀቱን በመስጋት ከሸዋሮቢት ተጨማሪ የሰው ኃይል ለማስገባት ቢሞክርም፡ ነገር ግን በሸዋሮቢት ቆቦና ውስቴንቧይ በሚገኙ በአርበኛ ታደለ ወርቁ ብርጌድ የአርበኞች ፋኖ ጦር በደፈጣ በመጠበቅ በጠላት ላይ ከባድ ጉዳት ያሳረፈ ጥቃቶችን በመፈፀም በርካታ የጠላት ኃይል መደምሰሳቸው ታውቋል። በተመሳሳይ ሰዓት፣ የአስቻለው ደሴ ክፍለ ጦር ባካሄደው የተቀናጀ ወታደራዊ ስልት፣ የጠላትን ጦር ሙሉ በሙሉ መውጫና መግቢያ በማሳጣት በእሳት ወጥመድ ውስጥ እንዲወድቅ አድርጎታል።በዚሕም የተነሳ ጠላት ጦር በአርበኞቹ የደፈጣ ጥቃት ክፉኛ የሰውና ቁሳዊ ኪሳራ ማስተናገዱ ተረጋግጧል ። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!   ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!

ታሪክ የማይረሳው የቁርጥ ቀን ልጅ! ታሪክን ፈሪዎች አይጽፉትም፤ ታሪክን የሚጽፉት በፈተና ወቅት ህዝባቸውን ከፊት ሆነው የሚመሩ አርበኞች ናቸው! ​ህዝባቸው በታሪኩ አይቶት በማያውቀው አስጨናቂ ፈተና ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ ከህዝባቸው ጎን በመቆም ደማቅ ታሪክ እየጻፉ ያለው አርበኛ ዮሃንስ ንጉስ ሙጨ! ​በጎንደር አንድነት የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሰብሳቢ የሆነው ይህ ቆራጥ መሪ፤ የአማራን ህዝብ ከአብይ አህመድ አረመኔያዊና ጨቋኝ ስርዓት ነፃ ለማውጣት ያልከፈለው መስዋዕትነት፣ ያላየው መከራ የለም! ​ላመነት አላማ፣ ለህዝባቸው ነፃነትና ክብር ሲሉ ህይወቱን በግንባር ቀደምትነት ለመስጠት የወጣው አርበኛ ዮሃንስ፤ ዛሬም የብዙዎች የፅናትና የብረት እምነት ምልክት ሆነው ቀጥለዋል። የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሰብሳቢ አርበኛ ዮሐንስ ንጉስ ሙጨ ከትግል ጓዶቹ ጋር በጎንደር ሰማይ ስር!! ​ነፃነት በዋጋ የሚገኝ እንጂ በነፃ የሚሰጥ አይደለም! #Dave #Amhara

የማይበገር ፅናት (ለ) የድል አዋጅ!! በጦርነት መካከል ድሮን፣ ሚግ(ጄት)፣ መድፍ፣ BM ሮኬት በሚዘንብበት ምድር ለአማራ ህዝብ ዘብ የሚቆም ተጨማሪ ሰራዊት ማሰልጠን ፤ በክህሎት፣ በአካል ብቃት፣ በውጊያ ስልት፣ ብቁ የሆኑ ኮማንዶዎችን በተለያዩ ኮርሶች ማብቃት የማይበገረው ፅናት (ለ)ድል አዋጅ መሆኑን የሚያስመሰክር ነው። የድል አዋጁ ዕለት በዕለት በምናስመዘግበው ድልና ስኬት የሚረጋገጥ ሲሆን የማይቋረጠው ወታደራዊና ፖለቲካዊ ስልጠና በጠላት ላይ ያለንን የስነ ልቦና ብልጫ፤ የማድረግ አቅም፤ የዓላማና ፅናት፤ የአሸናፊነት መንፈስና የበላይነት የሚያሳይ ስትራቴጂካዊ ድል ነው። ሽፍታ አድርገናቸዋል፤ በትነናቸው ተስፋ ቆርጠዋል በሚሉበት ቅፅበት "እኛ" ሰራዊት አሰልጥነን ለማስመረቅ የመጨረሻ ዝግጅት ላይ ነበርን። * ስልጠና፦ በጠላት ላይ ያስመዘገብናቸውን ድሎች በማስጠበቅ ለመጨረሻው ድል ግዙፍ ኃይል በመገንባት የምንቀጥልበት ስልት ነው። * ስልጠና፦ ቀጠናውንን በዘላቂነት በመቆጣጠር አስተማማኝ አቅም መፍጠራችንን ያስመሰክራል። * ስልጠና ፦ ትግሉ ብቁ በሆነ መዋቅራዊ ሰንሰለት ተዋረዳዊ አንድነት በአለው ድርጅት የሚመራ መሆኑን ይመሰክራል። * ስልጠና፦  ትግሉ ግልፅ ሁኖ ለተቀመጠለት ፖለቲካዊ ግብ የሚደረግ እና ዓላማውን የማይለቅ ታጋይና አታጋይ የሚመራ ድርጅት መኖሩን በድጋሚ ያረጋግጣል። * ስልጠና ፦ ዘመኑን በዋጀ በሰለጠነ የሰው ኃይል የሚደረገው ትግል ስርዓትና ህግ የሚያከብርና የሚያስከበር ኃይል መፍጠሩን ያሳያል። * ስልጠና፦ በጠላት ላይ የወሰድነው ስትራቴጂካዊ ድል ነው። * ስልጠና ፦ ብቁ በሆኑ የወታደራዊና የፖለቲካዊ አሰልጣኞች የሚሰጥ በመሆኑ ሰልጣኞች የሚታገሉለትን አላማ ማወቃቸውን ያሳያል። * ስልጠና፦ በቀጠናው ላይ ያለንን ተደማጭነት ከፍ ያደረገና ትግሉን በፊታውራሪነት በመምራት ሌሎች ኃይሎች የትግላችንን ጥንካሬ ተመልክተው ትግሉን እንዲቀላቀሉ መነሳሳትን ፈጥሮላቸዋል። * ስልጠና ፦ የመጨረሻው የድል አዋጅ አሸናፊ ፋኖ መሆኑን ለዓለም ያሳያል። ያለ ዕረፍት በሁሉም ቦታ እንሰራለን፤ እናሰለጥናለን እናስታጥቃለን ፣በፈተናዎች ሳንበገር በፅናት ለአማራ ህዝብ ህልውና ዘብ እንቆማለን። የዚህ ዘመን! የመጭውም ዘመን! የኃይል ማሽኖች እኛ ነን!! አዲስ ትውልድ ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ! የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

በሰሜን ኸዋ ሀገረ ስብከት በጻድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ድንገት በተከሰተ ርዕደ መሬትና የመሬት መንሸራተት አደጋ የ14 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ በ5 ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ሀገረ ስብከቱ አስታወቀ ። ምሥራቅ ሐረርጌ ,ኢትዮጵያ ሐምሌ ፳ ፯ ፳ ፻ ፲ ፰ ዓ/ም በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በታላቋ ገዳም ደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ገዳም ከክረምቱ መግባት ጋር ተያይዞ በተከሰተው ከፍተኛ የዝናብና የመባርቅት ድምፅ በደረሰ ርዕደ መሬትና የመሬት መንሸራተት ለጸበል ፣ ለሱባኤና ለመሳለም ከአራቱም አቅጣጫ በተሰበሰቡ በጻድቃኔ ማርያም ልጆችና ወዳጆች ላይ የደረሰው ድንገተኛ አደጋ እጅግ አስደንጋጭና ልብ ሰባሪ ኃዘን መኾኑ ተገልጧል። በዚህ ድንገተኛ አደጋም የ14 ወገኖቻችን ሕይወት ሲያልፍ በ5 ወገኖቻችን ላይ ከፍተኛና በ2 ወገኖች ላይ መለስተኛ ጉዳት መድረሱም ተመላክቷል። የሀገረ ስብከቱ ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቀሌምንጦስ በስፍራው በመገኘት ለሞቱ ወገኖቻችን ጸሎተ ፍትሐት ለተጎዱት ጸሎት ላዘኑ ወገኖቻችን የማጽናኛ ትምህርተ ወንጌልና አባታዊ ቃለ በረከት በመስጠት ላይ ይገኛሉ ። © የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት አቡቀለምሲስ ሚዲያ ለፈጣን እና ተአማኒ መረጃ ነው

የማከብርው መሪዬ የእኔ ጀግና ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ፦ የጽናት፣ የድፍረትና የአማራ አልፎም የኢትዮጵያ ህዝብ ክንድ! ራስ ​አርበኛ ዘመነ ካሴ በቃላት ብቻ የሚገለፅ መሪ ሳይሆን፣ በእሳት ውስጥ አልፎ ለህዝቡ ጋሻና መከታ የሆነ የእውነተኛ ጀግንነት ማሳያ ነው። ​የእሱ ጀግንነትና የጀግናነት ግርማ እንዲህ መግለፅ ባይቻልም ​ያልተበረዘ ጽናትና ቁርጠኝነት፦ ዘመነ ማለት እሱ ባመነበት ህዝባዊ ዓላማ ላይ እንደ ድንጋይ የፀና፣ በምንም ዓይነት ውሽንፍር፣ ዛቻና የእስራት ዘመን የማይወላወል የብረት ያህል ጠንካራ ስብዕና ያለው አርበኛ ነው። ​የተፈጥሮ ግርማና የመሪነት ግንባታው መድረክ ላይ ሲቆም በንግግሩ ወጣቱንና ህዝቡን በአንድ ላይ የሚያንቀሳቅስ፣ ተስፋ ባጣው ዘንድ ተስፋን የሚዝራ፣ በፍርሃት በተሸበበው ዘንድ ደግሞ ወኔንና ድፍረትን የሚሰራ የአማራ ህዝብ አለኝታችኝ ነው። ​ለህዝብ ፍቅር አደጋን የመጋፈጥ ድፍረት፦ የራሱን ምቾት፣ ሰላምና ህይወት አሳልፎ በመስጠት የህዝቡን መብት፣ ክብርና ደህንነት ለመጠበቅ ወደ ግንባር የወጣ፣ ከችግርና አደጋ ፊት ቀድሞ የሚቆም ሳያስበው የሚያስቡለት ጀግና ነው። ​በመርህ ላይ የተገነባ አቋም፦ ዘመነ ካሴ የጥቅም ወይም የወንበር ሰው አይደለም፤ ለቆመለት ህዝባዊ እውነትና ፍትህ ሲል ብቻ በማንኛውም ፈተና ውስጥ የሚያልፍ፣ መርሁንና ክብሩን ለምንም ነገር አሳልፎ የማይሰጥ የማህበረሰቡ ጋሻ ​ባጠቃላይ፦ ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ ማለት በቁርጠኝነት የሚያስደምም፣ በህዝባዊ ወገናዊነቱ የሚያስከብር፣ በጽናቱ ደግሞ ለትውልድ አርአያ የሚሆን የጽናትና የጀግንነት ከባቶቻችን የወረሰ የአማራ ህዝብ የመኖር ዋስትናችን ጭምር እንጅ! #Dave #Amhara

​እነዚህ አርበኞች ያደራጁትን ወታደር በእውቀት፣ ባካበቱት ልምድ እና በተፈጥሮ በታደሉት የማስተዋል ብቃት አዋህደው፤ የጦር ስልቶችን በማቀናጀት የላቀ መሪነታቸውን አስመስክረዋል። በዚህም የጥንካሬያቸውና የልዩ አመራር ብቃታቸው ማረጋገጫ በሆነው የፋኖ ትግል ውስጥ ከአባልነት እስከ አመራርነት ድረስ በመመደብ ሰራዊቱን በላቀ ዲስፕሊን፣ በሁለገብ እውቀትና ብቃት መምራት ችለዋል። አንድነት ናፋቂ የነበሩት እነዚህ የጦር አዛዦች እና አመራሮች፣ የጎንደር ፋኖ አንድነት እንዲመጣ በቀጠናው ያደረጉት በጎ አስተዋፅኦ እጅግ አስተውሎትን የተላበሰና አሻጋሪ አመራርነት ነበር።​አርበኛ ጌታሰው በሬ፣ ሻለቃ ተመስገን አብርሃም እና ከእነርሱ ጋር በጀግንነት የወደቁት የፋኖ አባላትና አመራሮች በሙሉ አንደበተ-ቁጥብ፣ ትሁት፣ ንግግራቸው የታሰበበትና በተግባር የሚያምኑ ሁለገብ መሪዎች ነበሩ። የጀግንነታቸውን ታሪክ በቃላት ሳይሆን በውጊያ ሜዳ ላይ በሚፅፏቸው እውነተኛ ገድሎች የሚናገሩ፣ ለትግል አጋሮቻቸው አለኝታ፣ ለጠላቶቻቸው ደግሞ የማይበገር አጥር ሆነው ያለፉ ህያው የታሪክ ማህደሮች ናቸው። ​አርበኛ ጌታሰው በሬ፣ አርበኛ አማኑኤል ተረፈ፣ አርበኛ ዮናታን/ዮኒ እና ጓዶቻቸው አንድነቱን ጨርሰው በእንቅስቃሴ ላይ እያሉ በፀረ-አንድነት ኃይሎች በተቃጣባቸው ጥቃት ወንድሞቻቸውን ተከላክለው ከጓዶቻቸው ጋር አብረው መስዋዕትነት የከፈሉ ሲሆን፤ ሻለቃ ተመስገን አብርሃምን ጨምሮ አርበኛ ሳሌ አስራት (ቄሴ)፣ አርበኛ ጌታለም እና ሌሎች አርበኞች ደግሞ ራስ ጋይንት ምድር ከጠላት ጋር እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ አድርገው ለአማራ ህዝብ ክብር ሲሉ ሐምሌ 26/2018 ዓ.ም በክብር ተሰውተዋል። ​ስለሆነም በወንድሞቻችን መስዋዕትነት የሚቀለበስም ሆነ የሚገታ ትግል ስላልጀመርን፣ የአገዛዙን ስርዓትም ሆነ የፀረ-አንድነቶችን ሴራና ተንኮል በማፍረስ የህዝባችንን መከራ እናሳጥራለን። ​ክብርና ሞገስ ለተሰው ሰማዕታት! አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ! ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም

Ashara Media - አሻራ ሚዲያ: ​አማራነትን በቃል ሳይሆን፤ በደማቸው ጽፈው ያለፉ እንቁዎች! ​የአማራ ሕዝብ ከ1983 ዓ.ም የሥርዓት ለውጥ በኋላ ተከታታይና ህልቆ-መሣፍርት ግፎችን እያስተናገደ ይገኛል፡፡ «ይህ የህዝብ እልቂት ከዚህ በላይ ሊቀጥል አይገባም» ብሎ የተነሳው የአማራ ፋኖ፤ በደሙና በላቡ የአማራን ሕዝብ ተራዛሚ መከራ ለማሣጠር ብርቱ ትግል እያካሄደና ውድ ዋጋም እየከፈለ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ ​የአማራን ህዝብ ከቁጥር ማጉደል፣ ከማዕድ መቀነስ፣ ከእርስት ማሳነስ እና ከክብር በታች ማድረግን ዓላማ ያደረገው ስርዓቱ፤ ቀን አልፎ ቀን በመጣ ቁጥር የጥላቻ ፖሊሲዎቹን ከመተግበር ወደኋላ ብሎ አያውቅም፡፡ የአማራ ፋኖ መርህ-መር በሆነ መንገድና በአንድነት ለአንድ ዓላማ ተማምኖ ትግል ማድረጉ ይህን ክፉ እቅዳቸውን እንደሚያከሽፍባቸው ሲረዱ ደግሞ፣ የፋኖ አንድነት እውን እንዳይሆን የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም ትግሉን ሲያጓትቱት ቆይተዋል፡፡ ​የጎንደር ፋኖ አንድ ባለመሆኑ ምክንያት፣ የፋኖን ትግል በሦስት አቅጣጫ የሚያዋክበው ኃይል ሊነሳበት ችሏል፡፡ የጠላቶቻችን ብዛት ቀጠናውን ለትርምስ፣ ህዝብን ለስቃይ፣ ታጋዩንም ተስፋ ወደ ማስቆረጥ ሲዳርገው ቆይቷል፡፡ «ይህ ሁኔታ እስከየት ያደርሰናል?» ብለው በቁጭት የተነሱ ጥቂት የማይባሉ እውነተኛ የህዝብ ልጆች ደግሞ መሪዎቻቸውንና ሠራዊቱን ጎትጉተው የፋኖን አንድነት እውን እንዲሆን አደረጉ፡፡ አንዳንዶቹ በአንድነቱ ዋዜማ በክብር ሲወድቁ፤ እንደ አርበኛ ጌታሰው በሬ፣ አርበኛ ተመስገን አብርሃም፣ አርበኛ አማኑኤል ተረፈ፣ አርበኛ ሳሌ አስራት (ቄሴ) እና ሌሎች ደግሞ የአንድነቱን ህብስት እንደቆረሱ ሳይጎርሱት በክብር ተሰውተዋል፡፡ ​የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ በቅርቡ መዋሀዱን ተከትሎ ጠላቶቻችን እጅጉን ተቆጡ፤ «አንድነቱን ያመጡ ታጋዮች መወገድ አለባቸው» ብለው የሴራና የክፋት እቅዳቸውን ወጥነው ተነሱ፡፡ ሊፈትኑንም ሊያንገዳግዱንም የቻሉትን ሁሉ ሞከሩ። ​«ጀግና ታሪክ እንጂ፤ እድሜ የለውም!»​የአማራ ህዝብ ትግል እልፍ ጀግኖችን የገበረበት፣ የጀግኖች የደም አሻራ ያረፈበት፣ ህያውነት ያለው የመኖር ተስፋን ያነገበና አልፋና ኦሜጋ የሆነ የማንነት ማስከበር ትግል ነው። በዚህ መራራ ህዝባዊ ትግል ውስጥ እንደ አርበኛ ጌታሰው በሬ፣ ሻለቃ ተመስገን አብርሃም እና ሌሎችም አብረዋቸው ለወደቁ የፋኖ አባላትና አመራሮች ያሉ የፅናት፣ የጀግንነት፣ ለህዝብና ለሀገር ያላቸውን ጥልቅ ፍቅር አርአያ ያደረጉ መሪዎችን ማጣት ትርጉሙ እጅግ ከባድና ዘርፈ-ብዙ ነው። ​ነገር ግን «ጀግና ታሪክ እንጂ እድሜ የለውም» እንዲሉ፣ እያንዳንዳቸው ታሪካቸውንና የከፈሉትን ዋጋ ለተከበረው የአማራ ህዝብ ሲሉ በደማቸው ፅፈው አልፈዋል፡፡ ​አርበኛ ጌታሰው በሬ መናገሻ ጎንደር ከተማ ተወልዶ፣ መደበኛ ትምህርቱን በሚገባ ተከታትሎ፣ በጅጅጋ ዩኒቨርሲቲ በኮምፒዩተር ሳይንስ ተምሮ በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቀ የቀለም ቀንድ ነበር፡፡ ከጥብቅ ሃይማኖታዊ ሥርዓት ተከታይ ቤተሰብ የተገኘው አርበኛ ጌታሰው በሬ፤ በህይወት ጉዞውም መርህ፣ ዲሲፕሊን፣ የበዛ ሥነ-ሥርዓት፣ ሰው አክባሪነትና ለአደራ መታመን የህይወቱ ቁልፍ መመሪያዎች ነበሩ፡፡ እነዚህን የህይወት መርሆች አስተምረው በሥነ-ሥርዓት ያሳደጉት ደጉ አባቱ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ነበር ያረፉት፡፡ የአባቱን ሞት አስመልክቶ ባስተላለፈው መልዕክትም፦ ​‹‹አባቴ፤ በሕይወቴ ያሰረፅከው ተስፋ እና ኃይል እስከ መጨረሻዬ ይመራኛል። እንደምታስተምረኝ እንድሆን፣ የምትፈልገውን ያን ጥሩ ሰው ለመሆን እጥራለሁ። በአካል ብትርቅም መንፈስህ አይለየኝም፤ በልቤ ለዘላለም ትኖራለህ። በእንባዬ ውስጥ ፍቅርህን እሸከማለሁ። እስከምንገናኝ ድረስ ሰላም ተኛ አባቴ፤ እወድሃለሁ፣ ሁልጊዜም እናፍቅሃለሁ››​ሲል ነበር የገለጸው፡፡ የአባቱ ናፍቆት ምን ያህል እንደከበደው ማሳያው አባቱ ባረፉ በ88ኛ ቀናቸው ተከትሏቸው መሄዱ ነው፡፡ ​ጀብደኛው አርበኛ ተመስገን አብርሃም በበኩሉ፤ የልጅ አዋቂ፣ አስተዋይ፣ ደፋር፣ ጀግና እና የበዛ የዋህነት የተላበሰ ወጣት ነበር፡፡ በአማራ ልዩ ኃይል አባልነት የዲሽቃ ተኳሽ የነበረው ትሁቱ አርበኛ ተመስገን አብርሃም፣ የ«ሻለቃ» ማዕረግተኛ የነበረ ሲሆን፤ ከቄሳር ሹመት ይልቅ የህዝቤ እልቂት ያሳስበኛል ብሎ ለአማራ ሕዝብ የትግል አደራ ታምኖ ወደ ትግል የገባ የቁርጥ ቀን ልጅ ነበር፡፡ ​በውጊያ ላይ ፍርሃት አልባ መሆኑን ለመግለጽ ‹‹ልበ ደንዳና›› የሚል ስም የተሰጠው አስተዋዩ የራስ ጉና ክፍለ-ጦር ዋና አዛዥ አርበኛ ተመስገን አብርሃምም ሆነ፤ «በሁለት በኩል የተሳለ ሰይፍ» የሚባለው አርበኛ ጌታሰው በሬ፤ ለአማራ ሕዝብ ህልውና ሲሉ ለትግል ከወጡበት ጊዜ ጀምሮ በክብር እስከተሰውበት ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በትግል አጋሮቻቸው የተወደዱ፣ በቀጠናው በሚንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል የተፈሩ፣ ወልዶ ባሳደጋቸው ማህበረሰብ ዘንድ ደግሞ የተመሰገኑ ታማኝ የህዝብ ልጆች ነበሩ፡፡ ሁለቱ ታማኝ ታጋዮችና አብረዋቸው የተሰውት የፋኖ አመራሮችና አባላት፣ በትግሉ ውስጥ እልፍ ጀብዶችን የፈጸሙ ሁለገብና ባለሁለት ወገን ሚና የነበራቸው ጀግኖች ነበሩ። ​በተዋጊነታቸው እንደማንኛውም የአማራ ልጅ ጀግና በግንባር ተሰልፈው እስከ መጨረሻው የሚፋለሙ የቁርጥ ቀን ተዋጊዎች ሲሆኑ፤ በአዋጊነታቸው ደግሞ የጦር መሪነትንና ወታደራዊ ስልትን ከቀደሙት የቁርጥ ቀን የፋኖ መሪዎች ከአርበኛ ውባንተ አባተ እና ከአርበኛ ከፍያለው ደሴ በብቃት የተማሩና የቀሰሙ ነበሩ። ​በጅጅጋ ዩኒቨርሲቲ በኮምፒውተር ሳይንስ ትምህርት ዘርፍ ተመርቆ የወጣው አርበኛ ጌታሰው በሬ፤ በጎንደር ከተማ ህዝባዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ጉልህና አሸናፊ ድርሻ የነበረው የወቅቱ ንቁ ታጋይ ነበር። ፖለቲካን ከውትድርና ሳይንስ ጋር አጣምሮ የያዘው ይህ አርበኛ፤ በነበረው ከፍተኛ ወታደራዊ ስልትና የፖለቲካ ብቃት የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ የስልጠና መምሪያ ኃላፊ ሆኖ በማገልገል ሰራዊቱን በእውቀትና በስልት እንዲያንጽ ተመድቦ ነበር። ​እጅግ ታማኝ፣ ጽኑ፣ አደራ ተቀባይ እና አንድነትን ፈላጊ የነበረው አርበኛ ጌታሰው በሬ፤ ለአንድነት ምሥረታውም በወንድሞቹ አስከሬን ላይ ተረማምዶ አንድነትን ያጸና ታጋይ ሲሆን፣ በትናንትናው ዕለት በክብር ተሰውቷል፡፡ አርበኛ ጌታሰው በሬ አንድነቱን ጨርሶ በእንቅስቃሴ ላይ እያለ፣ በፀረ-አንድነት ኃይሎች በተቃጣበት ጥቃት ወንድሞቹን ተከላክሎ ከጓዶቹ ጋር አብሮ መስዋዕትነትን ከፍሏል፡፡ ​በሌላ በኩል፣ ቀደም ሲል በክልሉ ልዩ ኃይል ውስጥ በነበረው የዲሽቃ ተኳሽነት የላቀ የውጊያ ማዕረግና የታወቀ ጀብደኝነት የሚታወቀው ሻለቃ ተመስገን አብርሃም በበኩሉ፤ አገዛዙ የአማራ ልዩ ኃይልን በበተነበት ወቅት የፋኖ አደረጃጀት እንዲጎለብትና ወደ ተደራጀ የህዝብ ሰራዊትነት እንዲሸጋገር የመሪነትና የግንባር ቀደምትነት ድርሻውን በመወጣት፣ በቀጠናው ለተፈጠረው ሚዛን አስጠባቂ ሰራዊት ይገነባ ዘንድ አይተኬ የላቀ አሻራውን አስቀምጦ አልፏል።

የማከብርው መሪዬ የእኔ ጀግና ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ፦ የጽናት፣ የድፍረትና የአማራ አልፎም የኢትዮጵያ ህዝብ ክንድ! ራስ ​አርበኛ ዘመነ ካሴ በቃላት ብቻ የሚገለፅ መሪ ሳይሆን፣ በእሳት ውስጥ አልፎ ለህዝቡ ጋሻና መከታ የሆነ የእውነተኛ ጀግንነት ማሳያ ነው። ​የእሱ ጀግንነትና የጀግናነት ግርማ እንዲህ መግለፅ ባይቻልም ​ያልተበረዘ ጽናትና ቁርጠኝነት፦ ዘመነ ማለት እሱ ባመነበት ህዝባዊ ዓላማ ላይ እንደ ድንጋይ የፀና፣ በምንም ዓይነት ውሽንፍር፣ ዛቻና የእስራት ዘመን የማይወላወል የብረት ያህል ጠንካራ ስብዕና ያለው አርበኛ ነው። ​የተፈጥሮ ግርማና የመሪነት ግንባታው መድረክ ላይ ሲቆም በንግግሩ ወጣቱንና ህዝቡን በአንድ ላይ የሚያንቀሳቅስ፣ ተስፋ ባጣው ዘንድ ተስፋን የሚዝራ፣ በፍርሃት በተሸበበው ዘንድ ደግሞ ወኔንና ድፍረትን የሚሰራ የአማራ ህዝብ አለኝታችኝ ነው። ​ለህዝብ ፍቅር አደጋን የመጋፈጥ ድፍረት፦ የራሱን ምቾት፣ ሰላምና ህይወት አሳልፎ በመስጠት የህዝቡን መብት፣ ክብርና ደህንነት ለመጠበቅ ወደ ግንባር የወጣ፣ ከችግርና አደጋ ፊት ቀድሞ የሚቆም ሳያስበው የሚያስቡለት ጀግና ነው። ​በመርህ ላይ የተገነባ አቋም፦ ዘመነ ካሴ የጥቅም ወይም የወንበር ሰው አይደለም፤ ለቆመለት ህዝባዊ እውነትና ፍትህ ሲል ብቻ በማንኛውም ፈተና ውስጥ የሚያልፍ፣ መርሁንና ክብሩን ለምንም ነገር አሳልፎ የማይሰጥ የማህበረሰቡ ጋሻ ​ባጠቃላይ፦ ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ ማለት በቁርጠኝነት የሚያስደምም፣ በህዝባዊ ወገናዊነቱ የሚያስከብር፣ በጽናቱ ደግሞ ለትውልድ አርአያ የሚሆን የጽናትና የጀግንነት ከባቶቻችን የወረሰ የአማራ ህዝብ የመኖር ዋስትናችን ጭምር እንጅ! #Dave #Amhara

በሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ ደብረ- ዘቢጥ ክላስተር የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሰፊ የሕዝብ ንቅናቄ መድረክ አካሔደ። በንቅናቄ መድረኩ ከማህበረሰቡ ጋር ሰፊ የወይይት መድረክ የተደረገ ሲሆን ሕዝቡም በመቄትና አካባቢው ካሉ የፋኖ ኃይሎች ጋር የተጀመረው ትስስር እና አንድነት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አውንታዊና ጠንካራ ምክር-ሃሳቦችን የሰጠ ሲሆን ፋኖ የአማራ ሕዝብ ስርዓት ወለድ በሆነ መንገድ የገጠመውን ሁለተናዊ የሕልውና አደጋ ለመቀልበስ የሚያደርገውን ፖለቲካዊ ትጥቅ ትግል በሙሉ ልብ ሁለተናዊ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን በመድረኩ ቃል ተገብቷል። ማህበረሰቡ በትግሉ ተደራሺነትና ቅቡልነት ዙሪያ እንዲሁም በድርጅታዊ ዕድገትና የዲፕሎማሲ ስራዎች ዙሪያ ጠንካራ ሃሳቦችን ሰንዝሯል።  ሰራዊቱ ፍፁም ለትግሉ የታመነ ፣ በጥሩ ሰነ-ምግባር የታነፀ ፣ ለጓዱና ማህበረሰቡ ክበር ያለው እንዲሆን ድርጅቱ አበክሮ መሰራት እንዳለበት ማህበረሰቡ ያሳሰበ ሲሆን በድርጅታዊ ዕደገትና ዓለም አቀፍ ተቀባይነትን ድርጅቱ በእጅጉ ማሳደግ አለበትም ብሏል። ሌላው ፋኖ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች የትምህርት ፣ የጤና ፣ የግብርና እና ሌሎች አገልግሎቶች በአግባቡ እንዲፈፀሙ ፋኖ እያደረገ ያለውን አዎንታዊ ድጋፍ አድንቀው በህዝብ ሀብት የተገነቡ ተቋማትን ማህበረሰቡም ይሁን ፋኖ መጠበቅ እንዳለበት በመድረኩ ማህበረሰቡ ገልጿል። በመድረኩ  የአማራ ፋኖ ብራሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የአደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አሰፋ መሰለ ፣ የዕዙ ዕቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አራጋው ያለው እና የዕዙ ም/ሕዝብ አስተዳደር ኃላፊ አርበኛ ጋሻው ሙሉጌታ እና የ303ኛ ኮር ሕዝብ አስተዳደር ኃላፊ አርበኛ 50 አለቃ መንግስቱ ካሳ እንዲሁም የ303ኛ ኮር 81ኛ ክፍለ ጦር እመራሮችና የ16ኛ(106) ኮር 22ኛ ክፍለ ጦር አመራሮች  የተገኙ ሲሆን ለንቅናቄ መድረኩ የሚመጥን በሁሉም ዘርፍ ማብራሪያ ተስጥቷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቄናቄ  ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!! ቀን 27/11/2018 ዓ.ም

45ኛው (መብረቅ) ክፍለ ጦር በተቆጣጠረው ቀጠና ታላቅ ህዝባዊ መድረክ አካሄደ! ​አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 45ኛ (መብረቅ) ክፍለ ጦር በተቆጣጠረው ጎረጅ ቀጠና ላይ ታላቅ ህዝባዊ መድረክ አካሄደ። ​በመድረኩ ላይ፡ ከፍተኛ የዕዝ ፣የኮር እና የክፍለ ጦሩ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። ​በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አርበኛ ንጉሴ ሀሚድ፤ ጎረጅ ከተማ በጠላት እጅ ከስድስት ወር በላይ ተይዛ ስትቆይ የአገዛዙ ወንበር አስጠባቂ ሠራዊት በማህበረሰቡ ሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሲያሳድር መቆየቱን አውስተዋል። በመቀጠልም "የመብረቅ አናብስቶች ከተማዋን ለመቆጣጠር በጠላት ምሽግ ላይ ተደጋጋሚ የማጥቃት ውጊያ በመክፈት ይዟት የነበረችውን ከተማ ለቆ እንዲወጣ አድርገናል፤ በዚህም በልጆቻችሁ ልትኮሩ ይገባል" በማለት የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላፍለዋል። ​በመድረኩ ላይ የተለያዩ አጀንዳዎችን በማንሳት ሰፊ ትንታኔና ማብራሪያ የሰጡት አርበኛ ዘላለም ኑርዬ የፋኖን አላማና አሁናዊ ቁመና በተመለከተ ሰፊ ገለፃ አድርገዋል። እንደ አርበኛው አገላለፅ፡ ​"ፋኖ የሚኖረው በህዝብ ነው፤ የሚኖረውም ለህዝብ ነው። ፋኖ ህዝባዊ ነው፤ ፋኖ ለአማራ አልፎም ለኢትዮጵያ ህዝቦች የቆመ ብቸኛው የነፃነት ታጋይ የህዝብ ልጅ ነው" ብለዋል። ​በመቀጠልም አርበኛ ዶ/ር ሚካኤል ጋሻው እንደገለጹት ከሆነ የአማራ ፋኖ እየታገለ ያለው የአማራ ህዝብን የህልውና አደጋ ለመታደግ እና የአብይ አህመድን ዘራፊና ጦርነት ጠማቂ ስርዓት ለማስወገድ መሆኑን ገልጸዋል። ​በዚህም የውይይት ሂደት ከታዳሚዎች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተዋል። ለአብነት ያህል ፋኖ ወደ ከተማ ሲገባ ምንም አይነት የተኩስ ድምፅ ሳያሰማ መግባቱ እንዲሁም ከማህበረሰቡ ጋር ያለው መስተጋብር ታማኝነትና ቅንነት በተሞላበት መልኩ መሆኑ እፎይታ እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል። ነገር ግን የአብይ ወንበር አስጠባቂ ሠራዊት በማህበረሰቡ ላይ "ፋኖን ትደግፋላችሁ" በሚል ከፍተኛ አካላዊና ሥነ-ልቦናዊ ጉዳት ማድረሱን ተናግረዋል። በተጨማሪም በከተማዋ ውስጥ ራሱን "ጥምር ጦር" ብሎ የሚጠራው ሠራዊት ሴቶችን መደፈሩን፣ በርካታ የግል መሳሪያዎችን መውሰዱን፣ ተቋማትን ማውደሙን እንዲሁም ሱቆችንና የህል መጋዘኖችን መዝረፉን ገልጸዋል። ​በተለይ ራሱን "ወሎ ህብረት" ብሎ የሚጠራው የአብይ አህመድ የፖለቲካ ክንፍ የሃይማኖት ካባ ባለበሳቸው ግለሰቦች አማካኝነት ማህበራዊ እሴቶችን (ማለትም ዕድር፣ ደቦ፣ ሠርግ፣ ለቅሶ እንዲሁም መውሊድ በመሳሰሉት ላይ) ከማህበረሰቡ ወግና ባህል ባፈነገጠ መልኩ መተሳሰብና መረዳዳት እንዳይኖር ትልቅ አሉታዊ ተፅዕኖ ፈጥሮብናል ብለዋል። ​ከመድረኩ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ማብራሪያ የሰጡት አርበኛ ዘላለም ኑርዬ፤ ስርዓቱ ያሰማራቸው ዘራፊ ቡድኖች በከተማዋ ላይ ያደረሱትን ችግር አውግዘዋል። በተለይም "ወሎ ህብረት" የአማራን ባህላዊ እሴቶች ለማጥፋትና እርስ በእርስ እንድንገዳደል የሚሰራ፣ ምንም አይነት ሃይማኖታዊ አስተምህሮ የሌለው በመሆኑ በጋራ ልንታገለው ይገባል ብለዋል። አርበኛው አክለውም የፈረሱ ዕድሮች በአስቸኳይ ወደ ነበሩበት እንዲመለሱና የ"ወሎ ህብረት" አባል የሆኑ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ በአፅንዖት ተናግረዋል። ​በመጨረሻም የምኒሊክ ዕዝ ከፍተኛ አመራር የሆኑት አርበኛ ኑራዲን አበበ ማህበረሰቡ በመከባበርና በመተማመን በአንድነት ከፋኖ ጎን በመሰለፍ ይህንን ጄኖሳይደር አገዛዝ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማሸነፍ በጋራ መሰለፍ አለብን ሲሉ ተደምጠዋል። ​መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!! ​ሐምሌ 27 / 2018 ዓ.ም

በታሪካዊው ካራምሽግ ስም "ካራ ምሽግ ብርጌድ " የአርበኞች ጦር ተመሰረተ!! ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ በአፄ ዓምደ ጽዮን ኮር የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በሚ
+4
በታሪካዊው ካራምሽግ ስም  "ካራ ምሽግ ብርጌድ "  የአርበኞች ጦር ተመሰረተ!!               ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ በአፄ ዓምደ ጽዮን ኮር የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በሚንቀሳቀስበት ቀጠና  «ካራ ምሽግ ብርጌድ»  የአርበኞች ጦር ሰራዊት ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም በይፋ መመስረቱን የአፄ ዓምደ ጽዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል በምስል በተደገፈ የግንባር መረጃው አስታውቋል። በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ ሬማ ክላስተር በተካሄደው በዚህ የምስረታ ስነ-ስርዓት ላይ፦ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች፣ የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር አመራሮች፣ የክላስተርና የቀበሌ አመራሮች፣ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ልዩ ልዩ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ብርጌዱ ተመስርቷል። በዚሁ የምስረታ መድረክ ላይ የሰራዊቱን የውስጥ አደረጃጀት፣ ወቅታዊ ቀጠናዊና ጂኦፖለቲካዊ ሁኔታዎችን፣ የሰራዊቱን የስነ-ልቦና ዝግጅት እንዲሁም የወደፊት የትግል አቅጣጫዎችን አስመልክቶ በየደረጃው ከሚገኙ አመራሮች ሰፊ ምክረ-ሐሳቦች ተነስተው የጋራ ውይይት ተደርጎባቸዋል። ውይይቱን ተከተሎ አዲስ የተመሰረተው የካራ ምሽግ ብርጌድ በተሟላ አደረጃጀት ወደ ስምሪት መግባቱን የኮሩ መረጃ ያመላክታል። ለብርጌዱ የኮማንድ አመራሮችም ተመርጦ መርሀ ግብሩ በነባር ቱባ ባሕል ኪነትና ልዩ ልዩ አዝናኝ ፅሑፎች ሊጠናቀቅ ችሏል። በመጨረሻም የተሠየሙት አመራሮች ህዝቡንና አካባቢያቸውን በቅንነት፣ በታማኝነት፣ በፍትሃዊነትና በጽናት ለማገልገል በህዝቡ ፊት ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።       " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!     " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

በደላንታ ወረዳ የወገልጤና ከተማ ነዋሪዎች የፀረ-አማራውን ብልፅግና አገዛዝ የመጨረሻ ቀብር ለመፈፀም ሙሉ ቁርጠኝነታቸውን ገለፁ! በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምኒልክ ዕዝ ሙሉ በሙሉ በተቆጣጠረውና እጅግ ስትራቴጂካዊ የጦር ቀጠና በሆነው ደላንታ ወረዳ ዛሬ ሐምሌ 26/2018 ዓ/ም የነዋሪውን ሕዝባዊ ወገንተኝነትና የትግል ቁርጠኝነት የበለጠ ያጠናከረ ታላቅ ሕዝባዊ መድረክ አካሂዷል። ይህ ታሪካዊ የውይይት መድረክ የተካሄደው የደላንታ ወረዳ መቀመጫ በሆነችው በወገል ጤና ከተማ ሲሆን በመድረኩ የምኒልክ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች፣ የኮርና የክፍለጦር አመራሮች እንዲሁም ማዕረግተኛ ወታደራዊ አዛዦች ተገኝተው መድረኩን በብቃት መርተዋል። በውይይቱ ወቅት ለበርካታ አሥርት ዓመታት በአማራ ሕዝብ ላይ ሲፈፀም ስለነበረው ስልታዊና ቀጥተኛ የዘር ማፅዳት እንዲሁም በአሁኑ ወቅት ተባብሶ መንግሥት-መር በሆነ መልኩ ስለቀጠለው ዘር ጭፍጨፋ በዕዙ ትምህርትና ስልጠና መምሪያ ኃላፊ በአርበኛ ፍቅሩ ፈንታው ሰፊና አጠቃላይ ገለጻ ተደርጓል። የሕልውና ትግሉን መነሻና መድረሻ በሚመለከት ደግሞ ሰፊ ማብራሪያ ያቀረበው የዕዙ ፖለቲካ መምሪያ ምክትል ኃላፊ አርበኛ ስንታየሁ ተስፉ ትግሉ ሕዝብን ከእልቂት የማዳንና ፍትሕ ርትዕ የማስፈን ራስ በቅ ትግል መሆኑን አፅንዖት ሰጥቶ አብራርቷል። አርበኛ ስንታየሁ አክሎም ፋኖ ከሌሎች አጋር ኃይሎች ጋር የሚያደርገው ትብብርና ወታደራዊ አጋርነት እስከ ምን ድረስ ሊሆን እንደሚችልና የጋራ ግቡን በሚመለከት ግልፅና ተጨባጭ ማብራሪያ ሰጥቷል። ሌሎች የዕዙና የኮር ከፍተኛ አመራሮችም በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያና ገለፃ ባደረጉበት በዚህ መድረክ የወረዳው ነዋሪዎች ከመድረኩ አመራሮች ለቀረቡት ማብራሪያዎች ያላቸውን አክብሮትና ሙሉ ድጋፍ በታላቅ ወኔና ቁርጠኝነት ገልፀዋል። ሕዝቡ ለሕልውና ትግሉ ያለውን የፀና አቋም ሲያረጋግጥ የብልፅግና አገዛዝም ተገርስሶና የፋኖ ፍትሐዊ ትግል መቋጫ አግኝቶ በምድሪቱ ላይ ፍትሕና ርትዕ እስኪሰፍን ድረስ ከፋኖ ጎን ቆሞ እንደሚዋጋና እንደሚያዋጋ በይፋ ገልጿል። በተጨማሪም ነዋሪው ለትግሉ ያለውን ጥልቅ አጋርነት ገልፆ በሕልውና ትግሉ ዙሪያ ወደፊት በሚደረጉ የውጊያና የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ላይ መሻሻል አለባቸው ያላቸውን ወሳኝ ጉዳዮች ነቅሶ በማውጣት ገንቢ አስተያየቶችን ሰጥቷል። በትግሉ ውስጥ የበለጠ ሊጠናከሩና ሊበረታቱ የሚገባቸውን የሕዝብና የፋኖ አንድነት፣ የደጀንነት ሚና እና የደህንነት ጥቃቅን ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ አዎንታዊ ሃሳቦችን ሰጥቷል። ይህ በደላንታ ወረዳ የተካሄደው ታላቅ ሕዝባዊ መድረክ የአማራ ሕዝብ ለነፃነቱና ለሕልውናው ያወጀውን መራራ ትግል ወደ ተሟላ ድል ለማሸጋገር ያለው ዝግጁነት ከምንጊዜውም በላይ በከፍተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በግልፅ ያሳየ ሆኗል። መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል ሲል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሀምሌ 26/2018 ዓ/ም

የአማራ ልጅ ፋኖ ማለት እኮ፦ ​የአማራ ልጅ ፋኖ ማለት እኮ፤ለእውነት የቆመ፣ ለፍትሕ የዘመረ፣በሀገሩ ፍቅር የታነፀ፣ ለክብሩ ያደረ። ይሉኝታን አውልቆ፣ መከራን ተጋፍጦ፣የወገኑን እንባ፣ በጽናት አብሶ፤ የታሪክ ባለቤት፣ የጽናት አርበኛ፣ ለነፃነት የቆመ፣ የፍትሕ ዘበኛ። ​ ወገን ሲበደል፣ አርፎ የማይቀመጥ፣ ለቃሉ ፀንቶ፣ ፍጹም የማይለወጥ፤ የአባቶቹን አደራ፣ በልቡ አዝሎ፣ በነፃነት መንገድ፣ ወደፊት የሚጓዝ በሞራል ተሞልቶ። ​ የአማራ ልጅ ፋኖ ማለት እኮ፤ የጀግንነት ምሳሌ፣ የሀገር አለኝታ፣ ለበደል የማይበረከክ፣ የጽናት አለታ! Dave Amhara

እኛን የሚገልፀን አንድ ታላቅና የማይናወጥ እውነት አለ... ​እኛ የዚች ታሪካዊት ምድር ኩሩ የአማራ ልጆች ነን! በራሳችን ሰማይ ስር በፍቅር፣ በክብርና በሰላም መኖርን እንጂ፣ የሰውን ክፉ መመኘትም ሆነ የሌላውን ድንበር መድፈር በተፈጥሯችን የለም። ተፈጥሮ በውበት፣ በንጽሕናና በጽናት የሰራችን የእውነት ሕያው እንቁዎች ነን! ​​ክብራችንን የሚነካ፣ ማንነታችንን የሚደፍርና ሰላማችንን የሚያደፈርስ ማንኛውም እጅ ሲመጣ በጭራሽ አንታገስም! የፍቅራችንን ያህል ቁጣችን ታላቅ፣ የትዕግስታችንን ያህል እሳታችን የበረታ ነው! በታሪካችን ታይቶ በሚታወቅ ዳግማዊ ድልና የበላይነት እንጂ፣ በሽንፈት የሚባል ጥቁር ጥላ ማንነታችን ላይ እንዲያርፍ አንፈቅድም። ​ማንነታችን ንጹሕና የወርቅ ያህል የጠራ ነው፤ ጽናታችን ደግሞ ተራራ የሚያናውጥ፣ ከድንጋይ የጠነከረ ነው! የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላት #Dave #Amhara