ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
رفتن به کانال در Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
نمایش بیشتر2 936
مشترکین
+1424 ساعت
+3877 روز
+38530 روز
آرشیو پست ها
የአማራ ልጅ ፋኖ የጽናትና የጀግንነት ተምሳሌት ነው። የታሪክን ሚዛን የሚያስተካክል፣ የወደቁትን የሚያነሳ፣ የታሰረውን የሚፈታ የነፃነት መንፈስ ነው! ይኸው መንፈስ ነው በችግር ውስጥ ጥንካሬን፣ በመከራ ውስጥ ድልን የሚያበቅለው።
አሸናፊነት ማለት መሰናክል አለመኖሩ አይደለም፤ ይልቁንም መሰናክሉን ሁሉ አልፎ ለዓላማ መቆም ማለት ነው! የአማራ ልጅ ፋኖም በመንገዱ ላይ የተደቀነውን እሾህ ሁሉ በትዕግስትና በወንድምነት አልፎ፣ የነገዋን ሰላማዊትና ፍትሃዊት ምድር ለመገንባት በቆራጥነት ይጓዛል።
ታሪክ በእንባ አይጻፍም በጽናት እንጂ! ድል ደግሞ የጽኑአን ዘውድ ናት!
የ54ኛ ክ/ጦር የፋኖ ሰራዊት በሰዴ ወረዳ በእነጌታየ መንበሩ መዝገቡ ዋለልኝ እና ተፈራ ዳምጤ የትውልድ ቀየ ከርኒ ከ600 በላይ ፋኖወች በደማቅ ሁኔታ አስመረቋል።
እንደራጃለን፣ እንሰለጥናለን፣ እንታጠቃለን የአማራን ህዝብ ከአረመኔው አገዛዝ ነፃ እናወጣለን።
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!
ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም
ሁሉም አማራ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ወሳኝ መልዕክት! 🚨
በአሁኑ ወቅት በማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መስኮች እየታዩ ያሉቱ ሁነቶች በአማራ ህዝብ ህልውና፣ ደህንነት እና የወደፊት እድል ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እያሳደሩ ይገኛሉ። እያንዳንዱ ማኅበረሰብ አካል ሊገነዘበውና ትኩረት አደገኛው የብልፅግና ሴራ‼️
ከላሊበላ ከተማ በተወረወረ መድፍ ኩልመስክ ደብረፀሐይ ከተማ የሚኖሩ ንፁሐንና ንብረት ላይ ጉዳት አደረሰ!
የአማራን ህዝብ እንደ ህዝብ ከሚኖርበት እናት ሐገሩ እንዲሳደድና እንዲጠፋ አስቦና አልሞ ታክቲካዊ በሆነ ዘዴ እየሰራ የሚገኘው ብልፅግና መሬት ላይ የሚታየውን እኩይ ተግባሩን በወንበር አስጠባቂው ምስለኔ የጁላ ሰራዊት እያስፈፀመ ይገኛል።
እንደ ኦስትሮጎስና ቫንዳን ህዝቦች ከምድረ ገፅ እንዲጠፋ የተፈረደበት የአማራ ህዝብ በሰሜን ወሎ አስተዳደር ዞን ላሊበላ ከተማ ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ/ም ከረፋዱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ የአገዛዙ ሜካናይድ ሰራዊት በዘፈቀደና በግዴለሽነት ወደ ኩልመስክ ደብረ ፀሐይ ከተማ ተከታታይ ሦስት መድፍ የወረወረ ሲሆን ንፁሐንና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።
በተወረወረው የመድፍ አረር ሁለት ህፃናትና አንዲት ልጃገረድ ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን ኤል-ሸፕ ዘመናዊ ቤት ከነ ሙሉ የቤት ዕቃው ወድሟል፤ ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!!
ሐምሌ:- 21/ 2018 ዓ/ም
ለተከታታይ 4(አራት) ወራቶች ሲሰለጥኑ የነበሩ የ54ኛ ክ/ጦር የፋኖ ሰራዊት በሰዴ ወረዳ በእነጌታየ መንበሩ መዝገቡ ዋለልኝ እና ተፈራ ዳምጤ የትውልድ ቀየ ከርኒ ከ600 በላይ ፋኖወች በደማቅ ሁኔታ አስመረቋል።
ሐምሌ 21//2018 ዓ.ም
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦር ለተከታታይ 4(አራት) ወራት ያሰለጠናቸውን 600 (ስድስት መቶ) የፋኖ አባላት ሐምሌ21/2018 ዓ.ም በሰዴ ወረዳ በጀግኖች መንበሩ ጌታየ ቀየ ከርኒ አካባቢው በደማቅ ሁኔታ አስመረቋል።
በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ስር የሚገኘው አንጋፈው 54ኛ ክፍለ ጦር የፋኖ ሰራዊት ለማስመረቅ በክብር የተገኙት የኮሩ ሰብሳቢ አረበኛ ላይችሉም ገበየሁ የኮሩ ጦር አዛዥ ኮረኔል አደመ የኮሩ ዘመቻ ሻለቃ ላመስግን አለነ እንዲሁም የ54ኛ ክፍለ ጦር አመራሮችና የክብር እንግዶች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የአካባቢው ማህበርሰብ በተገኙበት በሰዴ ወረዳ ከርኒ በደማቅ ሁኔታ ተመርቀዋል።
የጠላትን ቅስም የሰበረው የመንበር ጌታየ ቅየ አላስደፍርም በማለት ጠላትን መቀመጫ ያሳጠው ግዙፉ 54ኛ ክ/ጦር የሀገርን ዳር ድንበር መጠበቅ የሚያስችል የሰለጠነ የፋኖ ሀይል መገንባቱ ይቀጥላል።
እንደራጃለን፣ እንሰለጥናለን፣ እንታጠቃለን የአማራን ህዝብ ከአረመኔው አገዛዝ ነፃ እናወጣለን።
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!
ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም
የ54ኛ ክፍለ ጦር ከ600 በላይ የፋኖ ሰራዊት አባላትን አስመረቀ
ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ቴዎድሮስ ዕዝ፣ 201ኛ ኮር ስር የሚገኘው አንጋፋው 54ኛ ክፍለ ጦር፤ ለተከታታይ 4 (አራት) ወራት በጽናት ሲያሰለጥናቸው የቆያቸውን ከ600 (ስድስት መቶ) በላይ የመሰረታዊ ውትድርና የሰለጠኑ የፋኖ አባላቱን በዛሬው ዕለት ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም. በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል።
ይህ ታሪካዊ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት የተካሄደው በሰዴ ወረዳ፣ የጀግኖች እነ መንበሩ ጌታየ፣ መዝገቡ ዋለልኝ እና ተፈራ ዳምጤ የትውልድ ቀየ በሆነችው ታሪካዊቷ ከርኒ አካባቢ ነው። በዚሁ የምረቃ መርሃ-ግብር ላይ በክብር እንግድነት የ201ኛ ኮር ሰብሳቢ አርበኛ ላይችሉም ገበየሁ ፣የኮሩ ጦር አዛዥ ኮሎኔል አደመ፣ የኮሩ ዘመቻ ሻለቃ አርበኛ ላመስግን አለነ እንዲሁም የ54ኛ ክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የደመቀው የአካባቢው ማህበረሰብ በሙሉ ተገኝተው የሰራዊቱን ወታደራዊ ዝግጁነትና የስነ-ስርዓት ትርኢት በደስታ ተከታትለዋል።
የጠላትን ቅስም በመስበር «የመንበሩ ጌታየ ቀየን አላስደፍርም!» በማለት የሚታወቀው ግዙፉ 54ኛ ክፍለ ጦር፤ የሀገርንና የህዝብን ዳር ድንበር ማስከበር የሚያስችል የበቁና የሰለጠኑ የፋኖ ኃይሎችን የመገንባት ሂደቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል በዚህ አጋጣሚ ያረጋግጣል።
«እንደራጃለን! እንሰለጥናለን! እንታጠቃለን! የአማራን ህዝብ ከአረመኔው አገዛዝ ነፃ እናወጣለን!»
አሻራ ሚዲያ የአይበገሬዎቹ ልሳን
ኃይሌ ሙሉ /ሪፖርተር
ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም
ከላሊበላ ከተማና ሹምሽሃ (ላሊበላ አየር ማረፊያ) በሁለት አቅጣጫ የተንቀሳቀሰው የብልፅግና ጦር በደፈጣ ተመታ!
ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ/ም መነሻውን ከላሊበላ ከተማና ሹምሽሃ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ አድርጎ ወደ ብልባላ ከተማና ቡግና ወረዳ አይና ከተማ ሲንቀሳቀስ የነበረው የብልፅግና ወንበር አስጠባቂ ጦር በተለምዶ 06 ቀበሌ ሶርባ ተብሎ ከሚጠራው ቦታ ላይ በአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር አካል በሆነው 30ኛ (ማረጉ ተማረ) ክፍለ ጦር በተውጣጡ ፋኖዎች በደፈጣ ጥቃት ተመታ።
በዚህ የታቀደና የተናበበ የደፈጣ ጥቃት 17ቱ እስከ ወዲያኛው ሲሸኙ ከ20 በላይ ቁስለኛውን በማንጠባጠብ በሞርታርና አየር መቃወሚያ (ዙ-23) ሽፋን ተሰጥቶት ተራፊው እግሬ አውጭኝ ብሎ ወደ መጣበት ፈርጥጧል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!
ሐምሌ:- 21/ 2018 ዓ/ም
የጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ አሃድ የሆነዉ 303ኛ አሳምነው ኮር 19ኛ ክፍለ ጦር ዋግሹም ብርጌድ ድሐና ወረዳ በሚገኝ የጠላት ኃይል ላይ አኩሪ ድል ተቀዳጀ!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር 19ኛ (ዋግሹም) ብርጌድ በዋግህምራ ዞን ድሃና ወረዳ አገዛዙ በተለምዶ ጥምር ጦር ወይም ሰላም አስከባሪ ብሎ የሚጠራውን ሚሊሻና ፓሊስ 04 ቀበሌ አርቢት ላይ አይቀጡት ቅጣት ቀጥተውታል።
አናብስቶቹ ዋግሹም ብርጌዶች የተከማቸበትን የጠላትን ምሽግ ቀድመው በማጥናት እና ቁልፍ ቦታወችን ቀድመው በመዝጋት በአገዛዙ ዘብ ጠባቂ ሚሊሻና ፖሊስ ላይ የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ ድል ተቀዳጅተዋል ።
ውጊያው ሐምሌ 20/2018 ዓ/ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 11:30 ሰዓት ግለቱን የጠበቀ ሲሆን ከዋግ ህምራ ዞን ከተለያዩ ወረዳዎች ተወጣጥተው ድሃና ወረዳ 012 ቀበሌ ሲልዳ አለኝ የሚለውን የተጠናከረ ምሽግ በተወሰኑ የብርገዷ የዋግሹም ፍሬዎች ክንደ ብርቱነት ሙሉ በሙሉ አስረክቦ ወጥቷል ።
በነበረው አውደ ውጊያ 7 ሚሊሻና 2 የወረዳው ፖሊሶች እስከ ወዳኛው ሲሸኙ ከ11 በላይ ቁስለኛውን እያንጠባጠበ ወደ መደበቂያው አምደወርቅ ከተማ ተመልሷል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!
ሐምሌ 21/2018 ዓ/ም
ሽንፈትና ውርደት የተከናነበው የስርአቱ ወታደሮች ዝርፉያና እገታ!!!
አፋብን ወለጋ /ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ በተለያዩ ግንባሮች ለየት ለየት ያሉ አውደ ውጊያዎችን ለተከታታይ ቀናቶች በማድረግ በርካታ የአገዛዙ ሰራዊትና በሰው ደም የበለፀጉ ካድሬዎች ጨምሮ የተወገዱበት የጥላት አከርካሪና ቅስሙን የሰበርንበት አንፀባራቂ ድል ተመዝግቧል።
እደተለመደው የፈሪ ዱላውን ከፖለቲካው ነፃ የሆኑ በአማራነታቸው ብቻ ንፁሃን ላይ እያሳረፋ ይገኛል።
ለዛሬ አደሩን በምስራቅ ወለጋ ዞን ጉቶ ጊዳ ወረዳና በጉዳያ ቢላ ወረዳ በሁለቱ ወረዳዎቺ ላይ በምትገኘው ጊወርጊስ ከተማ ላይ ተደጋጋሚ የጀት ድብደባ በመፈፀም ንፁሃንን ሲገል እደተለመደው ህዝቡ ተበራጎ ቦታውን ሰለቅለት ወደ ቦታዋ በመግባት የህዝብ መገልገያ ወፍጮ እና ቤቶችን በማቃጠል እድሁም በመዝረፍና ከጥቅም ውጭ በማድረግ የተለመደውን ፀያፍ ድርጊቶችን እየከወነ ይገኛል።በዚሁ ከተማ ሁለት መነኮሳት እና በእድሜ ገፋ ያለ አበትን ጨምሮ በውል ያልታወቁ ንፁሃኖቺን ይዞ ወጥቷል።
ይህ በእድህ እዳለ በምስራቅ ወለጋ ዞን አንገር ጉትን ከተማ ሚካኤል ሰፈር ልዩ ቦታው 15ቁጥር አከባቢ በመጫወት ላይ ያሉ ሁለት(2) የሰባት አመት እና የዘጠኝ አመት ልጂ በመምታት የሰባት አመቱ ልጂ ህይወቱ ሲያልፍ የዘጠኝ አመቱ ደግሞ በሞትና በህይወት ውስጥ ይገኛል።
በመጨረሻም ከሌሎች ወድሞች ጋር ይህንን አገዛዝ እስከወዳኛው
ለመስወገድ ወታደራዊ አቅማቺንን እያጎለበትንና አደረጃጀቶችን እያዘመን እንገኛለን።
ግፍ የወለደን: ግፈኞቺን የምቀጣ
የአንሻ ሰይድ ወድሞች ነን!!!
አፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ
ሐምሌ21/2018ዓም
ሰላም ጓዶች እንዴት ናችሁ?
✍️አንድ የቢሆን ሀሳብ ለማቅረብ ፈልጌ ነው:-
በትግል ውስጥ ብዙ ፈተናዎች እያስተናገድን ቆይተናል፣ አሁንም እያስተናገድን ነው ትግላችን በመስዋዕትነት የታጀበ በመሆኑ ከቤታችን የወጣንበት አላማ ነውና ያለ መስዋዕትነት የሚገኝ ድል አይኖርም። ይሁን እንጅ ድል ማለት በትንሽ ወይንም በዜሮ መስዋዕትነት የተሻለ የውጊያ የበላይነትን ማሳያት እና አመርቂ ውጤት ማስመዝገብ ማለት ሊሆን ይችላል። ይሁን እንጅ ትግል ነውና ድል ሁልጊዜም ቢሆን ባሰብነው መስመር ልክ ሊሆንም ላይሆንም ይችላል።
በመሆኑም በውጊያ ወቅት ውድ የህይዎት መስዋዕትነትን የሚቀበሉ ወንድም/እህቶቻችንን ፎቶግራፍ ገና ውጊያው እንኳን ሳይጠናቀቅ እንዲሁም የተከበረው የመስዋዕትነት አስክሬን እንኳን ተነስቶ በክብር ሳያርፍ ውስጣዊ የሀዘኑ ስሜት እኩል የሁላችንም ነውና፣ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገፆች ላይ በተለይ በTiktok በተለያዩ አካላት (አንዳንዶቹም የጠላት page በሆኑ) በሰፊው እየተሰራጨ መሆኑን በተደጋጋሚ ጊዜ እያየን እንገኛለን። ለአማራ ህዝብ ሲባል መስዋዕትነት የከፈለን ታጋይ ለክብሩ በሚመጠን መልክ ወቅቱን ጠብቆ ቀኑን አስቦ መዋል፣ቤተሰቡን እንደ ድርጅት መጎብኘት፣ከምንም በላይ ደግሞ ብዙዎቻችን በየተራ የምንወድቅለትን ትግል ዳር ለማድረስ በየወቅቱ ቃልኪዳናችንን በማደስ በእልህና በቁጭት መስራት ከድል በኋላም እንደ ድርጅት የሚወሰኑ ነገሮችን ወጥ በሆነ መልኩ መተግበሩ የነገ የሁላችንም ዕጣ ፈንታ ሊሆን ስለሚችል በዚሕ አግባብ ጉዳዩ ቢታይ የተሻለ ይመስለኛል።
ከዛ ውጭ በዛ ፍጥንነት መስዋዕትነት የተቀበለን የታጋይ ፎቶግራፍ ወደ ሚዲያ በተለይ በTiktok ማሰራጨቱ ለወገን ሀይል የሚያስገኝለት ጥቅም ምንድን ነው? እኔ በግሌ ያለ አይመስለኝም!
✅የሰራዊታችንን ሞራል ያላሽቃል
✅ለጠላት ሀይል እንደ ማረጋገጫ ይጠቀምበታል
✅የፋኖ ደጋፊ በሆኑ ወገኖች ላይ የሚፈጥረው የሞራል ስብራት ይኖራል
✅አዲስ ተተኪ የፋኖ አባላት ላይ የሚፈጥረው ጫና
✅ባጠቃላይ ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል።
በመሆኑን በዚሕና መሰል ጉዳዮች ላይ የዕዙ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ተወያይቶ ለዕዙ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ (PR) ውሳኔ በማስተላለፍ ከአመራር እስከ የሰራዊት አባላት እንዲሁም በደጋፊ አካላት ላይ የሚተገበር አጭር መመሪያ አውጥቶ በአስገዳጅ ሁኔታ ተፈፃሚ እንዲሆን ቢያደረግ መልካም ነው የሚል ምልከታ አለኝ።
ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!
21/11/2018ዓ.ም
ሰበር#_13አድማብተና ዲሽቃ ተኳሽ እና ሬዲዮ ኦፕሬተሮች ሚሊሻወች ፋኖን ተቀላቀሉ የብልፅግና ቤት መፈራረሱን ቀጥሏል።
============================
.........ዛሬ ሐምሌ በ20/11/2018 ዓ.ም
ከመርጡ ለማርያም ከተማ እና ደ/ወረቅ ከተማ በመውጣት ሙሉ ትጥቃቸውን ይዘው 201ኛኮር 74ኛ ክ/ጦርን የተቀላቀሉ ሲሆን ጀብድ በመስራት ሁለት ሽጉጥ እና አንድ አይኮን ሬዲዮ መገናኛ በመያዝ ታሪክ የሰራች ጀግና ሴት የምትገኝ ስትሆን እና ሁለት ክላሽ በመያዝ የወጣው ዲሽቃ ተኳሹ የተገኙበት ሲሆን ከእነዚህም መካከል አባላት፦
1.ያብባል ታዴ......አድማ ቲም መሪ
2.ጌትነት ደሴ........አድማ የሻለቃ አጃቢ
3.አበበ ጌትነት.........አድማብተና
4.ኤፍሬም እሸቴ.........አድማብተና
5.እባበይ አቅለው .....ዲሽቃ ተኳሽ 2ክላሽ ይዞ የወጣ
6.ሀይማኖት አበበ.....አድማ ሴት ሬድዮ ኦፕሬተር 2 ሽጉጥ እናአንድ ሞቶሮላ መገናኛ ይዛ የወጣች
7.መሌ......... ፓራ ኮማንዶ
8.ዋና ሳጅን ዳምጠው እባቡ..ከደ/ወርቅ
9.ብርሐን......0ሚሊሻ
10.አዱኛው...........ሚሊሻ
11.ያሳቡ............ሚሊሻ
12..ንጉስ ታመነ......አድማ ብተና
13.ደስተው ጓሌ..........ሚሊሻ ሲሆኑ በዛሬው እለት ከጠላት ጋር ወግነው የነበሩ ሲሆን ዘግይተንም ቢሆን ቀሪ ጊዜያችን ህዝባችን ለመካስ ተዘጋጅተናል በማለት ተናግረዋል።
አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
ሰበር#_13አድማብተና ዲሽቃ ተኳሽ እና ሬዲዮ ኦፕሬተሮች ሚሊሻወች ፋኖን ተቀላቀሉ የብልፅግና ቤት መፈራረሱን ቀጥሏል።
============================
.........ዛሬ ሐምሌ በ20/11/2018 ዓ.ም
ከመርጡ ለማርያም ከተማ እና ደ/ወረቅ ከተማ በመውጣት ሙሉ ትጥቃቸውን ይዘው 201ኛኮር 74ኛ ክ/ጦርን የተቀላቀሉ ሲሆን ጀብድ በመስራት ሁለት ሽጉጥ እና አንድ አይኮን ሬዲዮ መገናኛ በመያዝ ታሪክ የሰራች ጀግና ሴት የምትገኝ ስትሆን እና ሁለት ክላሽ በመያዝ የወጣው ዲሽቃ ተኳሹ የተገኙበት ሲሆን ከእነዚህም መካከል አባላት፦
1.ያብባል ታዴ......አድማ ቲም መሪ
2.ጌትነት ደሴ........አድማ የሻለቃ አጃቢ
3.አበበ ጌትነት.........አድማብተና
4.ኤፍሬም እሸቴ.........አድማብተና
5.እባበይ አቅለው .....ዲሽቃ ተኳሽ 2ክላሽ ይዞ የወጣ
6.ሀይማኖት አበበ.....አድማ ሴት ሬድዮ ኦፕሬተር 2 ሽጉጥ እናአንድ ሞቶሮላ መገናኛ ይዛ የወጣች
7.መሌ......... ፓራ ኮማንዶ
8.ዋና ሳጅን ዳምጠው እባቡ..ከደ/ወርቅ
9.ብርሐን......0ሚሊሻ
10.አዱኛው...........ሚሊሻ
11.ያሳቡ............ሚሊሻ
12..ንጉስ ታመነ......አድማ ብተና
13.ደስተው ጓሌ..........ሚሊሻ ሲሆኑ በዛሬው እለት ከጠላት ጋር ወግነው የነበሩ ሲሆን ዘግይተንም ቢሆን ቀሪ ጊዜያችን ህዝባችን ለመካስ ተዘጋጅተናል በማለት ተናግረዋል።
አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
