fa
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

رفتن به کانال در Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

نمایش بیشتر
2 918
مشترکین
-1524 ساعت
+287 روز
+37030 روز
آرشیو پست ها
በርካታ የመከላከያ አመራሮች ወደ ፋኖ ተቀላቀሉ የመረጃ ደህንነት፣ፐርሶኔል፣የሰው ሀይል እና ሬጅመንት ቲም መረውን ጨምሮ ============================= .......ሰኔ 17/2018 ዓ
+9
በርካታ የመከላከያ አመራሮች ወደ ፋኖ ተቀላቀሉ የመረጃ ደህንነት፣ፐርሶኔል፣የሰው ሀይል እና ሬጅመንት ቲም መረውን ጨምሮ ============================= .......ሰኔ 17/2018 ዓ.ም 25ኛ ክፍለ ጦርን ያለ አንድ ጥይት ጩኸት እያፈራረስነው እንገኛለን በዛሬው እለትም የመከላከያ አመራሮች 201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉ ሲሆን፦ 1.መዲ ታደሰ..... ፐርሰኔል ከድጎ ፅዮን 2.ቻይና ሰርኳ ....ሲራሮ ከድጎ ፅዮን 3.አሸናፊ አበራ ...የሰው ሀይል 4.ጉተማ አብዱ...ሬጅመንት ቲም መሪ 5.ም/አስር አለቃ ዳኔል ጌታነህ..መረጃና ደህንነት 6.ጣሂር ሀሮ ... መሠረታዊ ወታደር ጦሩ ምንም አይነት የመዋጋት ስነልቦና የሌለው መሆኑን የተቀላቀሉት አባሎች አስረድተዋል በ54ኛ ክፍለ ጦር አመራሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጓላቸዋል። የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

የድርጅታችን አፋብን መሪ ራስ አረበኛ ዘመነ ካሴ የተሳደበ ግለሰብ 64ኛ ክ/ጦር በቁጥጥር ስር ዋለ!! 64ኛ ክ/ጦር ሰኔ 17/2018 ዓ.ም ~~~ 64ኛ ክ/ጦር በደረሰው መረጃ መሰረት የድርጅታችን አፋብን መሪ ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴን የተሳደበ ምዕራፍ/በቅፅል ስሙ ዛምራ የተባለ ግለሰብ በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እያረደገ ይገኛል። የትግላችን ምልክት እና የአማራ ህዝብ እንደ አይን ብሌን የሚሳሳለት የድርጅታችን አፋብን መሪ ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ ስም በመጥቀስ ምዕራፍ/በቅፅል ስሙ ዛምራ የተባለ ግለሰብ በTiktok ገፁ ላይቭ በመግባት የተሳደበ ሲሆን ሰኔ 17/2018 ዓ.ም 64ኛ ክ/ጦር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያካሄደ ይገኛል። ክ/ጦሩ በደረሰው መረጃ መሰረት በቁጥጥር ስር የዋለው ምዕራፍ/በቅፅል ስሙ ዛምራ የተባለ ግለሰብ የ64ኛ ክ/ጦር አመራርም አባልም ያልነበር መሆኑን እየገለፅን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ በፊክ አካውንቶች ልጁን ከ64ኛ ክ/ጦር ጋር አየይዘው እያሰራጩት ያለው የሐሰት ወሬ መሆኑንን እናሳውቃለን። የመቶ አመት ክስተት ከሚባሉት መሪዎች ውስጥ አንዱ የሆነው የድርጅታችን አፋብን መሪ ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ በአማራ ህዝብ ላይ የወደቀበትን የጭቆና ቀንበር ለአንዴ እና ለመጨረሻ ግዜ ለማንሳት ትግሉን  በማቀጣጠልና በመምራት እንደ ወርቅ በሳት ተፈትኖ ትግሉን እዚህ ያደረሰ የቁርጥ ቀን ጀግና መሪያችን ነው። ለዚህም እኛ ተመሪዎቹ ብቻ ሳይሆን በጠላት ላይ ያደረስነው ድል ምስክር ነው። መሪያችን ራስ አረበኛ ዘመነ ካሴን በሚዲያም ሆነ በማናቸውም መንገድ የሚደረግን የስም ማጥፋት ዘመቻ አምርረን የምንፀየፍ እና ይህንን ስራ የሚሰሩ የተኛውም አካላት ከጠላት እኩል አድርገን የምናያቸው መሆኑን የደጅ አዝማች በላይ ዘለቀ ልጆች 64ኛ ክ/ጦር እናሳውቃለን።   ድል ለአማራ ህዝብ! ድል ለአማራ ፋኖ!! አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!                  ሰኔ 17/2018 ዓ.ም   አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር

ፋኖ ከተማ ውስጥ በመግባት የተሳካ ኦፕሬሽን አካሔደ‼️ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ክንፍ የሆነው 14ኛ ክፍለ ጦር #ዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን #ጋዝጊብላ ወረዳ #ላልኪው ከተማ ላይ በመግባት የተሳካና ውጤታማ ኦፕሬሽን ሰርተዋል። የካቲት 16 ቀን 2018 ዓ/ም የብልፅግና ሰራዊት መነሻውን ከአዲ-በር ተነስቶ ጥቅር ቢዚ-በር በጭማው አቅጣጫ፣ በቀጭን ወይሎን አቅጣጫ አድርጎ እንዲሁም በላልኪው ፊት ለፊት ጥርጊያውን አድርጎ በሦስት አቅጣጫ መዳረሻውን ዘውማርያም ቢያደርግም ቀድሞ መረጃው የደረሰው የፋኖዎች የመረጃ ክፍል በሰራው ስራ መሰረት ጠላት ባሰበው ሳይሆን ባልጠበቀው ሁኔታ ላልኪው ከተማ በመግባት በተሰራው ኦፕሬሽን #ከጠላት_ካምፕ በርካታ #ቁሳዊ_ግብዓቶች ሲገኙ ከሃዲዎችና የብልፅግና #ካድሬዎችም_ተማርከዋል። በዚህ ኦፕሬሽን የጠላትን የሎጅስቲክ ካምፖች ሰብሮ በመግባት እርጥብ እና ብዛት ያለው ደረቅ ሬሽን ማለትም 👉አራት ኩንታል በርበሬ 👉ሰባት ኩንታል ሽሮ 👉24 ኩንታል ፊኖ ዱቄት 👉 አራት ካርቶን ባለ አምስት ሊትር ዘይት 👉በርካታ ጫማዎችና ሚሊተሪ ልብሶች እንድሁም ቤት ለቤት በተደረገው ፍተሻ በግለሰብ ቤት ደብቀው ያስቀመጡት #አራት_ሳጥን_የክላሽ_ተተኳሽና የጨፍጫፊው ስርዓት አስፈፃሚ የሆኑ #ሦስት_ካድሬዎች እና እንዲሁም ፋኖ ነኝ በሚል የብልፅግናን ስራ እየሰራ የነበረ መረጃው እየተደረሰበት መሆኑን ቀድሞ ሲያውቅ ወደ ብልፅግና ገብቶ የነበረ አንድ ባንዳ በ14ኛ ክፍለ ጦር ፋኖዎች ተማርኳል ሲል የ303ኛ አሳምነዉ ኮር ህዝብ ግንኙነት መረጃዉን አድርሷል።    መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ©የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!!   ሰኔ:- 17/ 2018 ዓ/ም

ጉና ክፍለ አንዳቤት ብርጌድ በሰነዘረው መብረቃዊ ጥቃት የጠላት ሃይል ድባቅ ተመታ። ====================== ሰኔ 17/2018 ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ስር ጉና ክፍለ ጦር አናብስ
+1
ጉና ክፍለ አንዳቤት ብርጌድ በሰነዘረው መብረቃዊ ጥቃት የጠላት ሃይል ድባቅ ተመታ። ====================== ሰኔ 17/2018     ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ስር ጉና ክፍለ ጦር አናብስቶች አንዳቤት ብርጌድ በአንዳቤት ወረዳ መካነ-ስላሴ፣ ውቤ ከተማ፣ ጉልት፣ አፋፍ፣ ጎመለል፣ ወሰንጃ፣ወይበይኝ፣ ቤተ-ማርያም ተራራ ማማ ግርጊ በእነዚህ ምድር አገዛዙ ውጊያ ለማድረግ ቢሞክርም በጀግናው ፋኖ ከበባ ውስጥ ገብቶ አከርካሪውን በመስበር ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል።       ወራሪው ሃይል በሜካናይዝድ እና በእግርኛ ታጅቦ ሲግተለተል የዋለው የጨበጣ ውጊያ ቢከፍትም በአናብስቶችን በደረሰበት ብርቱ ምት ከፍተኛ የሆነ ሰብአዊ፣ ቁሳዊ እና ስነ-ልቦናዊ ኪሳራ ያስተናገደው የጠላት ሃይል የንፁሃንን ሃብት ንብረት ዘርፎል፤ የማህበራዊ ተቋማትን አውድሟል።      ከእነዚህም ውስጥ፦ 👉 ዳሳሽ አበበ ዳኘ = 55000 የተወሰደባት፣ 👉 ክንዱ መንገው አንድ አብራራው ጠመንጃ የተወሰደበት፣ 👉የመካነ-ስላሴ ቀበሌ የእንስሳት ህክምና  መሰጫ ሙሉ ቁሳቁስ ወድሟል፣ 👉 የመካነ-ስላሴ ቀበሌ የማህበራት ሰነድ ሙሉ በሙሉ የወደመ፣ 👉 የመካነ-ስላሴ አንደኛ ደረጃ ሙሉ ሳይክል ትምህርት ቤት የር/መምህሩ ቢሮ፣ የትምህርቱ ቤቱ የመምራን ማርፍያ የተሰባብሩ፣ 👉 የትምህርት ቤቱን የገቢ ማሰባሰብያ ደረሰኝ ከጥቅም ውጭ አድረገውታል። 👉ሶስት Tecno ስልክ የግለሰቦች ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ የተባሉ የተወሰደባቸው፣ ይህ ዘራፊ ሃይል በገሃድ ማህበረሰብ ጥል መሆኑን አሳይቷል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ሜ/ጀኔራል ውባን አባተ፩ኛ ኮር ጉና ከፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ

ጎንደር ነኝ ስላቸው እየመርራቸው ጎጃም ነኝ ስላቸው እየነደዳቸው ሽዋ ነኝ ስላቸው ሲከነክናቸው ወሎ ነኝ ስላቸው ሲያርመጠምጣቸው የአማራ ልጅ ሁኘ ተገኜሁባቸው ይሄ ስብስብ በቅርቡ አራት ኪሎ ላይ እደ
ጎንደር ነኝ ስላቸው እየመርራቸው ጎጃም ነኝ ስላቸው እየነደዳቸው ሽዋ ነኝ ስላቸው ሲከነክናቸው ወሎ ነኝ ስላቸው ሲያርመጠምጣቸው የአማራ ልጅ ሁኘ ተገኜሁባቸው ይሄ ስብስብ በቅርቡ አራት ኪሎ ላይ እደሚደገም አልጠራጠርም🙏 ድል ለመላው የአማራ ፋኖ🔥✊ ድል ለተገፋው የአማራ ህዝብ💚💛❤️ይብላኝ ሚዲያ ከፍታችሁ እርስ በእርስ ለምታባሉ ድኩማን ጎጠኞች

የይፋት ምድር ያበቀለችው የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ!! የታሪክ ማኅደር ሲገለጥ፣ የጀግኖች ስም በወርቅ ቀለም ሲጻፍ፣ ከይፋት እስከ አማራው ግዛት አውራጃ ስሙ ጎልቶ የሚሰማ አንድ ስንቅ የሆነ የቁርጥ ቀን ልጅ አለ። እርሱ የጦር ሜዳ አንበሳ ብቻ አይደለም፤ እርሱ የዕውቀትና የጥበብ ማማ፣ በአማራነቱ የማይደራደረውና ለሕዝቡ ነፃነት ሕይወቱን አሳልፎ የሰጠው ፋኖ አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ ነው። ሙህርነትና ጥበብን ያገረሰሰው ጀግንነት ​አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ በጦር ሜዳ ጥይትና ቆራጥነት ብቻ ሳይሆን፣ በመብሰልና በጥበብ የተሞላው አስተዋይነቱ ልዩ ያደርገዋል። “ጥበበኛው ፋኖ” አለቃ እየተባለ የሚጠራው ያለ ምክንያት አይደለም። ወታደራዊ ስልቶችን የሚነድፍበት፣ የጠላትን አቅጣጫ ቀድሞ የሚያስነብብበት መላውና ጥበቡ የይፋትን ታጋዮች ሁልጊዜም ወደ ድል የሚያሸጋግር ነው። እርሱ ዕውቀትን ከጉልበት፣ ብልሃትን ከጥበብ ጋር አጣምሮ የያዘ የወቅቱ ሙህር መሪ ነው። በአማራነቱ የማይደራደረው ጽኑ ዓለት ​ስለ ማንነቱና ስለ ሕዝቡ ክብር ሲነሳ አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ የማያወላውል፣ እንደ ሰንደቅ ዓላማ ቀጥ ብሎ የቆመ ጽኑ ዓለት ነው። በማንነቱ ላይ የሚመጣን ማንኛውንም ዓይነት ተፅዕኖ በድርድር የማይቀበል፣ ለሕዝቡ መብት መከበር እስከ መጨረሻው የደም ጠብታ ለመቆም የወሰነ ቆራጥ ታጋይ ነው። ይህ አቋሙ በወዳጆቹ ዘንድ ኩራትን፣ በባላጋራዎቹ ዘንድ ደግሞ ታላቅ መፈራትን ጥሎባቸዋል። ​ሁሌም የአንበሳውን ድርሻ የሚወስደው ግንባር ቀደም ​ትግሉ መሪ በሚፈልግበት፣ ሜዳው በፈተና በሚናወጥበትና አስቸጋሪ በሆኑ ወቅቶች ሁሉ፣ ኢሳያስ ወደኋላ አይልም። ሁልጊዜም በግንባር ቀደምትነት በመሰለፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ለጓዶቹ ጋሻ፣ ለሕዝቡ ደግሞ ተስፋ በመሆን በይፋትና እንዲሁም በመላው ሽዋ በአካባቢው ታሪክ የማይረሳው ደማቅ አሻራን እያሳረፈ ይገኛል። ​“ኢሳያስ ማለት የይፋት ኩራት፣ የአማራ ልጅ ፋኖ ያውም ጥበበኛው፣ በማንነቱ የማይደራደረውና ሁሌም በድል አደባባይ የአንበሳውን ድርሻ የሚወስደው የቁርጥ ቀን አርበኛ ነው!” ተፃፈ #በዳዊት #ተመስገን

ምሁር እና ወታደር (ከመሐል አማራ ሣይንት ሰማይ ስር)፤ ፋኖ አብርሃም ፍሰሀ ይባላል፤ ወደ ህልውና ትግሉ ከመቀላቀሉ በፊት በመሐል አማራ ሳይንት ወረዳ የእንግሊዝኛ መምህር ነበር:: የአማራ ህዝብ ህ
ምሁር እና ወታደር (ከመሐል አማራ ሣይንት ሰማይ ስር)፤ ፋኖ አብርሃም ፍሰሀ ይባላል፤ ወደ ህልውና ትግሉ ከመቀላቀሉ በፊት በመሐል አማራ ሳይንት ወረዳ የእንግሊዝኛ መምህር ነበር:: የአማራ ህዝብ ህልውና አደጋ ላይ ወድቆ ሳለ የኔ ጋወን ለብሶ መንገዋለል ምን ዋጋ አለው! ይልቁንስ ሬንጀር ለብሼ ጠብመንጃ ልንከስ ብሎ ወሰነ:: በዚህም መሰረት ጥቅምት 16 ቀን 2016 ዓ.ም በመሐል ሳይንት ግንባር ፋኖን ተቀላቀለ:: የቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው አደራ ተሸካሚ እና የፋኖ ቁልፍ ሰው ነው:: በእሳት የተፈተነ ጀግና ነው:: ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም ቁስለኛ እና መሳሪያ ሊያወጣ ሲሞክር 2 ቦንብ ቢጣልበትም ቁስለኛውን እና መሳሪያውን በድፍረት ማውጣት ችሏል:: አብርሽ እጅግ በጣም ደፋር ወታደር እና ጥንቅቅ ያለ ምሁር ነው:: በእውቀት እና በእውነት ትግሉ እንድቀጥል የራሱን ድርሻ እየተወጣ ያለ ወንድማችን ነው:: በዚህ ትግል ሂደት ይጠቅማሉ ብለን ከምናምንባቸው ታጋይ አታጋዮች መካከል አንዱ ነው:: ለአንድነት ያለው ቀናኢነት እና ለህዝብ ያለው መቆርቆር ልዩ ነው:: አስተዋይ እና የልጅ ሽማግሌም ነው:: በነገራችን ላይ ፋኖ አብርሃም የአ ፋ ብ ን ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክፍለ ጦር አስተዳደር ነው:: በሰራዊቱ እና በህዝብ ዘንድ እጅጉን ተወዳጅ ነው:: እንደ እሱ ያሉ ወንድሞችን ያብዛልን!🙏 Lji Abrham በርታልን ወንድምአለም!!

መነሻቸውን ከመቄት፣ ከላስታና ጋዝጊብላ ወረዳ ያደረጉ መከላከያ አባላት አፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ አሳምነው ኮር ውስጥ ባሉ ክፍለ ጦሮችን ተቀላቀሉ ! ሰኔ 17/2018 ዓ.ም ሰኔ 16 እና
+2
መነሻቸውን ከመቄት፣ ከላስታና ጋዝጊብላ ወረዳ ያደረጉ መከላከያ አባላት አፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ አሳምነው ኮር ውስጥ ባሉ ክፍለ ጦሮችን ተቀላቀሉ ! ሰኔ 17/2018 ዓ.ም ሰኔ 16 እና 17 ቀን 2018 ዓ/ም የተቀላቀሉት መሰረታዊ ወታደር በላይነህ አለበል ላልኪው ከሚንቀሳቀሰው ከ38ኛ ክፍለ ጦር አራተኛ ሬጅመንት በመውጣት 30ኛ ክፍለ ጦርን፣ አንድ እግረኛ፣ ሁለት ድሽቃ ምድብተኛ በድምሩ ሦስት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላልኪው ከሚንቀሳቀሰው 38ኛ ክፍለ ጦር ስድስተኛ ሬጅመንት 14ኛ ክፍለ ጦርን እንዲሁም መሠረታዊ ወታደር ሙሉ ገብሬ፣  አስር አለቃ ጌታሁን እንዳለው፣ አስር አለቃ ክንዱ ፈንታሁን እና አስር አለቃ ገብርዬ አክሊሉ ከመቄት በመነሳት 81ኛ ክፍለ ጦርን በጥቅሉ ስምንት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ፋኖን ተቀላቅለዋል። የመከላከያ አባላቱም  ሁሉም ጥቁር ክላሽ በመያዝ የገቡ ሲሆን በጥቅሉ ስምንት ጥቁር ክላሽ፣ ስድስት የክላሽ ካዝና ከነተተኳሹ፣ አራት የደረትና የወገብ ትጥቅ፣ ስድስት የእጅ ቦምብ ይዘው ተቀላቅለዋል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር  ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! አፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ  ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!

👉 የዳዊት ድንጋይ፤ ጎልያድን የመሰለ ትልቁን እንቅፋት በትልቅ እምነቱ ጥሏል!! =======================> ​በሕይወትዎ ፊት ለፊት የቆመው ችግር ግዙፍ መሆን የውድቀትዎ ምልክት አይደለም፤ ይልቁኑ እግዚአብሔር በእርስዎ ሕይወት ውስጥ የሚያደርገውን ትልቅ ድል ለዓለም የሚያሳይበት መድረክ ነው! 🤌 ​እስራኤላውያን በሙሉ በጎልያድ ግዙፍነት ተፈራርተውና ተሸማቀው ሳለ፣ እረኛው ወጣት ዳዊት ግን ያየው የጠላትን ግዝፈት ሳይሆን የአምላኩን ታላቅነት ነበር። በሰዎች እይታ ዳዊት ያልሰለጠነና ያልታጠቀ ህጻን ይመስል ነበር፤ ሳኦልም የራሱን ከባድ የጦር ትጥቅ ሊያ አልብሰው ሞከረ። ዳዊት ግን የሰዎችን ልማዳዊ አካሄድ አልተቀበለም፤ ትጥቁን አውልቆ ጣለ። በለመደው የቁምጥና እምነቱና በወንጭፉ ብቻ ወደ ጦርነቱ ገባ! 👉 ​ብስለት ማለት የችግርህን ታላቅነት እያዩ መፍራት ሳይሆን፣ በችግርህ ፊት ቆመህ የአምላክህን ታላቅነት ማወጅ ነው! አጥፊዎች አንተን ለመጣል ለመጨፍጨፍ የጦር መሣሪያና ተንኮል ይዘው ቢመጡ፣ አንተ ግን በውስጥህ ባለው የእግዚአብሔር ማንነት ትጋፈጣቸዋለህ። ያንተ የሆነውን ድል ማንም ሊቀማህ አይችልም!!! ​ማንም ሊጋፈጠው ያልደፈረውን ግዙፍ ችግር (ዕዳ፣ በሽታ፣ ወይም የአስተሳሰብ አጥር) ለመስበር መነሳት ለሰዎች ስንፍና ሊመስል ይችላል። ነገር ግን እውነተኛ ስኬት የሚመጣው የሰዎችን ፍርሃት ጥሶ መውጣት ሲቻል ነው። ዳዊት የወረወራት አንዲት ትንሽ ድንጋይ ግዙፉን ጠላት መሬት አስደፋችው። ታሪክህን የሚወስነው የችግሩ ግዝፈት ሳይሆን ለአምላክህ ያለህ አመለካከት ነው! ​"አንተ እብሪተኛ ሁነህ ሰይፍና ጦር ይዘህ ትመጣብኛለህ፤ እኔ ግን... በሠራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ስም እመጣብሃለሁ" (1 ሳሙኤል 17:45) ​ የአማራ ህዝብ ትግልም ይሄው ነው ። አጥፊዎች በእብሪት ተወጥረው ታንኩም፣ባንኩም፣መድፉም፣ድሮኑም፣አየር ሃይሉም፣ባህር ሃይሉም፣ልዩ ሪፐፕሊካን ኃይሉም አቀናጂቶ ሙሉ የመካናይዝድ ጦርን በእግረኛ ሰራዊት አሰማርቶ የአማራን ህዝብ ለማጥፋትና ለመጨፍለቅ አገዛዙ በእብሪት ተወጥሮ በህዝብ ላይ ያወጀው የዘር ማጥፋት ጦርነት ቀጥሏል። የጦርነት እብሪቱና የዘር ጭፍጨፋው በአገዛዙ በኩል ከአርብ ኤምሪትስ ልዩ ተወንጫፊ የአጥፍቶ ጠፊ ድሮኖችን እየተቀበለ በአማራ ህዝብ ላይ ዘግናይ የጭካኔ ግፍ እየፈፀመ ቢገኝም ቅሉ ግን ወርደትን እያስተናገደ ይገኛል ። ማንነትንና እምነትን ሊያጠፋ የተነሳው ጨፍጫፊው አገዛዝ ቃል ለሰማይ ቃል ለምድር ብለው እምነታቸውን ቋጥረው ክርስቶስ ፍረድ ብለው ማንነታቸውንና እምነታቸውን ከጥፋት ለመታደግ የአማራ ፋኖ ነፃ አውጪ ሃይሎች በየ አህጉራቸው ተሰባስበው የታወጀባቸውን የህልውና ጥቃትን መክተው እብሪተኛውን የአገዛዙን ቡድን ታንኩን ነጥቀው፣መድፉንም ጨብጠው ሰራዊቱንም አንገቱን አንቀው በአለም አደባባይ ላይ አሳፍረውታል ። የዳዊትን መንፈስ የታጠቁ የአማራ ፋኖ ነፃ አውጭ ኃይሎች እብሪተኛውን ጨቋኝ አገዛዝ ክንዱን እየሰበሩ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ተክለ ቁመናውንም ሰባብረው የነፃነትና የፍትህ ሚዛንን በአለም አደባባይ ላይ ትይንትን ፈጥረዋል ። እብሪተኞች ተሸንፈዋል !! የነፃነት አብዮታችን በድል እየገሰገሰ ይገኛል። የአማራ ህዝብ ከውጫዊ የፖለቲካ መጋጋጥ ወጥቶ ከነፃነት ተፋላሚ የፋኖ ኃይሎች ጋር መሰለፍ ወቅቱ የሚጠይቀው የመጨረሻው ምዕራፍ ነው ። የነፃነት ተፋላሚ ቡድኑም ከእርስ በርስ መቆራቆዝና የትክሻ መለካካት ተላቆ የጀመረውን የማንነት ክብሩን ለማስመለስ በጋራ በመቆም አንድ ጥይት በአንድ ጠላት ላይ ብቻ በመተኮስ አጥፊውን የአፓርታይድ አገዛዙ በአፈጢሙ ለመትከል ከነፃነት አብዮቱ የሚጠበቅ ጥንቅቅ ያለ አብዮታዊ አንድነት ዕዝና ሰንሰለት የተዘረጋ ተቋምን ማክበር ይጠይቃል ። የነፃነት ኃይሉ ውስጣዊ የሃይል አሰላልፎችን ከቀበሌ፣ከሰፈር፣ከመንደር፣ከዘመደ አዝማድና ከቀበሌኛ አስተሳስቦች ፈልቅቆ ማውጣት አለበት። የነፃነት ተፋላሚ ኃይሉ ከቀጠናዊ እሳቤ በመራቅ አሻጋሪና እውቀት መር ወታደራዊና ፖለቲካዊ መሪዎችን በመተካት የነፃነት አብዮታዊ ግባችንን እንድናሳካ ከወደቅንበት የኋላቀር ወንዜኛ አሰላልፍ እንላቀቅ።!!! 👉ድል ለነፃነት ተፋላሚው የአማራ ህዝብ!!#Dawit Amhara

የፀሐፊ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የፖለቲካ መኮንኖች ማሠልጠኛ ማዕከል የ3ኛ ዙር ሰልጣኞቹን አስመረቀ! በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሥር የሚገኘው የፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የፖለቲካ መኮንኖች ማሠልጠኛ ማዕከል፣ የ3ኛ ዙር ሰልጣኞቹን በደመቀ ሁኔታ አስመረቀ። ማዕከሉ የፖለቲካ መኮንኖችን አሠልጥኖ ያስመረቀው ከዕዙ 105ኛ ኮር ከተውጣጡ የፋኖ አባላት ሲሆን፣ ቁጥራቸው 27 የሆኑት እነዚህ የፖለቲካ መኮንኖች ከሚያዝያ 27 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለባለፉት 49 ቀናት (ለ1 ወር ከ19 ቀናት) ከፍተኛ ሥልጠናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ናቸው። ተመራቂዎቹ በማዕከሉ ቆይታቸው ከወሰዱት ሰፊ የንድፈ-ሐሳብ ትምህርት ባሻገር፣ በምዕራብ ወሎ ቀጠና በተለያዩ አካባቢዎች እየተዘዋወሩ በርካታ ተግባራዊ የሕዝብ ግንኙነትና የንቅናቄ ሥራዎችን ሲያከናውኑ የቆዩ መሆናቸው ታውቋል። በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ያለው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ በትጥቅ የተደገፈ የፖለቲካ ትግል መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ መሬት ላይ ከሚደረገው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ጎን ለጎን በጠላት ላይ የሐሳብና የፕሮፓጋንዳ የበላይነትን መውሰድ እጅግ አስፈላጊ ነው። ይህንን ክፍተት ለመሙላት ታስቦ የሠለጠኑት የዛሬዎቹ ተመራቂ መኮንኖች፣ የታላቁን የጄኔራል አሳምነው ጽጌን ታሪካዊ ቃልና አደራ አንግበው ሕዝብን የማስተማር፣ የማደራጀት እንዲሁም የማታገል ከፍተኛ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። ተመራቂዎቹ በማሠልጠኛ ማዕከሉ በነበራቸው ቆይታ በተለያዩ ርዕሰ-ጉዳዮች ዙሪያ የላቀ ግንዛቤ እንዲጨብጡ የተደረገ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል፦ ፖለቲካ፣ መንግሥት እና የመንግሥት መሠረታዊ ግዴታዎች፣ ሕገ-መንግሥት፣ ሀገረ-መንግሥት እና ርዕዮተ-ዓለም፣ የአማራ ብሔርተኝነት፣ የጦርነት ፕሮፓጋንዳ እና የፋኖነት ፍልስፍና፣ በትግሉ ሂደት የተስተዋሉ ተጨባጭ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው የሚሉትን ያካተተ ጥልቅ ሥልጠና ወስደዋል። ከዚህም በተጨማሪ ተመራቂ መኮንኖቹ በሥልጠናቸው ማጠናቀቂያ ላይ በተግባር ሕዝባዊ መድረኮችን እንዲመሩና የሰራዊት ግንባታ ሥራዎችን በብቃት እንዲሠሩ ተደርገው የተዘጋጁ በመሆናቸው፣ ወደ ቀጣዩ የትግል ምዕራፍ ሙሉ ዝግጁነት ይዘው መሸጋገራቸውን ማዕከሉ በኩራት አስታውቋል። መዳረሻው ድልና ነጻነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ሕልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ! ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም.

በስቦ ማስከዳቱ ስምንት የመከላከያ ሰራዊት አባላት 303ኛ አሳምነው ኮር ውስጥ ባሉ ክፍለ ጦሮች ውስጥ ተቀላቀሉ! መነሻቸውን ከመቄት፣ ከላስታና ጋዝጊብላ ወረዳ ከሚንቀሳቀሰው የብልፅግና ሰራዊት ከተለያዩ አሀዶቻቸው ያደረጉ መከላከያ አባላት ስርዓቱን በመፀየፍና በመጥላት በየአቅራቢያቸው ከሚገኙ ወንድሞቻቸው የፋኖ አደረጃጀት ተቀላቅለዋል። ሰኔ 16 እና 17 ቀን 2018 ዓ/ም የተቀላቀሉት መሰረታዊ ወታደር በላይነህ አለበል ላልኪው ከሚንቀሳቀሰው ከ38ኛ ክፍለ ጦር አራተኛ ሬጅመንት በመውጣት 30ኛ ክፍለ ጦርን፣ አንድ እግረኛ፣ ሁለት ድሽቃ ምድብተኛ በድምሩ ሦስት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላልኪው ከሚንቀሳቀሰው 38ኛ ክፍለ ጦር ስድስተኛ ሬጅመንት 14ኛ ክፍለ ጦርን እንዲሁም መሠረታዊ ወታደር ሙሉ ገብሬ፣  አስር አለቃ ጌታሁን እንዳለው፣ አስር አለቃ ክንዱ ፈንታሁን እና አስር አለቃ ገብርዬ አክሊሉ ከመቄት በመነሳት 81ኛ ክፍለ ጦርን በጥቅሉ ስምንት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ፋኖን ተቀላቅለዋል። የመከላከያ አባላቱም  ሁሉም ጥቁር ክላሽ በመያዝ የገቡ ሲሆን በጥቅሉ ስምንት ጥቁር ክላሽ፣ ስድስት የክላሽ ካዝና ከነተተኳሹ፣ አራት የደረትና የወገብ ትጥቅ፣ ስድስት የእጅ ቦምብ ይዘው ተቀላቅለዋል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር  ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! አፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ  ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!        ሰኔ:- 17/ 2018 ዓ/ም

​የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከሰም ኮር ድል ተቀዳጀ!! ​       ሰኔ 17/2018 ዓ.ም ​የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮር ስር የሚገኙ ሦስቱ ክፍለ ጦሮች በቅንጅት በወሰዱት ወታደራዊ እርምጃ፣ በከሰም ቀጠና ከፍተኛ ድል ማስመዝገቡን የግንባር መረጃችን አስታውቋል። ​​የአገዛዙ  ጥምር ጦር በ42 ተሽከርካሪዎች የተጫነ የሰው ኃይል በማጓጓዝ የፋኖን ሰራዊት እደመስሳለሁ በሚል ቀቢፀ -ተስፋ በስድስት አቅጣጫዎች ተንቀሳቅሶ ነበር። ይሁን እንጂ ጀግናው ሰራዋታችን በደረሰው ቅድመ መረጃ መሰረት በሦስት አቅጣጫዎች ስልታዊ ጥቃት ሰንዝረውበታል። የቡልጋ ክፍለ ጦር፣የነበልባል ክፍለ ጦር እና የኃይለማርያም ማሞ ክፍለ ጦርጦሮች ከአክርሚት ተነስቶ ወደ ሰቃዎጩ አቅጣጫ ይጓዝ የነበረውን ኃይል በመክበብ ከፍተኛ ወታደራዊና ቁሳዊ ኪሳራ እንዳደረሱበት የኮሩ ህዝብ ግንኙነት ክፍል ገልጿል። በጥቃቱም በርካታ ቁጥር ያላቸው የአገዛዙ ጥምር ጦር አባላት መደምሰሳቸውንና ቀሪው የቆሰለና የተበታተነ ኃይል ወደ ተራራማ ቦታዎች በመሸሽ ተጨማሪ ድጋፍ በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል። ​የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከሰም ኮር  ያደረሰበትን ከባድ ምት መቋቋም ያቃተው የአገዛዙ ጥምር ጦር በአካባቢው በሚገኙ አራት ቀበሌዎች ማለትም በስቻት ፣በጎርፎ፣በአክርሚት እና በሰቃጮ ቀበሌ ላይ ጥቃትና ዘረፋ ፈጽሟል። ​በእነዚህ ቀበሌዎች በሚገኙ የአርሶ አደርና ነጋዴ መኖሪያ ቤቶች፣ ሱቆችና ግሮሰሪዎች ላይ በከባድ መሣሪያ (ዲሽቃ) ተኩስ የከፈተ ሲሆን፤ ወርቅ፣ ልዩ ልዩ ጌጣጌጥ፣ እንዲሁም የምግብ እህሎች (ሽሮ፣ በርበሬ፣ ዘይትና ዱቄት) መዘረፋቸውን የአካባቢው ማህበረሰብ ጠቅሷል። በተጨማሪም በመንገድ ላይ የተገኙ ከዘጠኝ በላይ የቤት እንስሳት (ፍየሎች) መታረዳቸውን የኮሩ ህዝብ ግንኙነት በላከው የግንባር መረጃ አስታውቋል።    ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ! ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

በምስራቅ ወለጋ መጠነ-ሰፊ ወታደራዊ ጥቃት መከፈቱና በንጹሃን ላይ የጅምላ ፍጅት ስጋት መጋረጡ ተገለጠሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (አዲስ አበባ)፦ በምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ እና በአካባቢው በሚገኝ ታዳጊ ከተማና ቀበሌዎች ላይ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች በምድር እግረኛ ጦር፣ በሜካናይዝድ ክፍለ-ጦር እና በአየር ኃይል የታገዘ መጠነ-ሰፊ ወታደራዊ ጥቃት መክፈታቸውን ከአካባቢው የተገኙ መረጃዎች አመለከቱ። በትናንትናው እለት ብቻ በተፈጸሙ ተከታታይ የአየር ላይ ድብደባዎች በርካታ ንጹሃን ዜጎች ህይወታቸውን አጥተዋል። ​ጥቃቱ በዋነኝነት ያረፈው አንዶዴ ዲቾ ከተማን ጨምሮ በአሊ፣ በዋጃ እና በጉልማ ቀበሌዎች ላይ ሲሆን፣ በጥቃቱ ሳቢያ በርካታ ቁጥር ያላቸው አርሶ አደሮችና ነጋዴዎች ሰለባ መሆናቸው ተረጋግጧል። በአሊ ቀበሌ በትናንትናው እለት ብቻ በሁለት የጦር ሄሊኮፕተሮች እና በሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮኖች) የታገዘ የ42 ጊዜ ድብደባ የተፈጸመ ሲሆን፣ በዛሬው እለትም የሄሊኮፕተር የቅኝት በረራዎች ቀጥለው መዋላቸው ታውቋል። በጥቃቱ ማግስት ዛሬ ሰኔ 17 ቀን የማዕከላዊ ዕዝ ጦር የኦሮሚያ ሚሊሻን፣ የአድማ ብተናንና የገዳ ኮማንዶን መንገድ መሪነት በማድረግ፣ በርካታ በቆንጨራና በቢለዋ የታጠቁ ወጣቶችን አስከትሎ ወደ አሊ ቀበሌ መግባቱ የተገለጸ ሲሆን፣ ይህም በአካባቢው በሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ላይ የታቀደ የጅምላ ፍጅት ለመፈጸም ነው የሚል ከፍተኛ ስጋት በአካባቢው ላይ ጥሏል። ​በተመሳሳይ ሁኔታ በአንዶዴ ዲቾ ከተማ በትናንትናው እለት በረፋዱና በአመሻሹ ላይ የጦር ሄሊኮፕተር በከፈተችው አውቶማቲክ የተኩስ ጥቃት በእለት ተእለት እንቅስቃሴ ላይ የነበሩ በርካታ ነጋዴዎችና አርሶ አደሮች ተገድለዋል። በዋጃ ቀበሌ ደግሞ በአንድ ዙር የጄት ድብደባ፣ በሶስት ዙር የሄሊኮፕተር ጥቃት እና በታንኮች የታገዘ ከባድ ድብደባ የተፈጸመ ሲሆን፣ በጉልማ ቀበሌ በበኩሉ ከ5 ጊዜ በላይ የሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃት ተፈጽሟል። ​ከጥቃቱ ሰለባ አካባቢዎች በ30 እና 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው የነቀምቴ (ኡኬ) አየር ማረፊያ የሲቪል በረራዎች ሙሉ በሙሉ የተቋረጡ ሲሆን፣ አየር ማረፊያው ትናንትና ዛሬ የሙሉ ሰዓት የወታደር ማመላለሻ፣ የሄሊኮፕተር፣ የድሮን እና የጦር ጄቶች ማኮብኮቢያ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በአካባቢው መደበኛ የኮሙኒኬሽንና የኔትዎርክ አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ መቋረጣቸው ተረጋግጧል። ​በሌላ በኩል፣ መንግስት በምስራቅ እና ምዕራብ ወለጋ ዞኖች አዋሳኝ፣ ከአርጆ ጉደቱ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኘውንና በደርግ ዘመን ተገንብቶ ከአገልግሎት ውጭ የነበረውን የደዴሣ አየር ማረፊያ መልሶ በማፅዳትና በማደስ በአዲስ መልኩ ስራ ማስጀመሩ ታውቋል። ይህ ስፍራ በቄለም ወለጋ (ደምቢዶሎ) በኩል በረራ ሲለካ ለሱዳን ድንበር ቅርብ በመሆኑ፣ የጄነራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይል (RSF) እንደ ድሮን ጣቢያ ሊጠቀምበት እንደሚችል የደረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ። ​የደዴሣ ካምፕ አካባቢ ከ1950ዎቹ እና 60ዎቹ ጀምሮ በርካታ ቁጥር ያላቸው የአማራ ተወላጆች የሰፈሩበት ስፍራ ነው። አካባቢው በ2013 እና 2014 ዓ.ም የጅምላ ጭፍጨፋ ከተፈጸመበት የጊምቢ (ቶሌ) አካባቢ በ10 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ብቻ የሚገኝ ሲሆን፣ አሁንም በቶሌ፣ ጊምቢ፣ አርጆ ጉደቱ፣ ጨዋቃ፣ ኤፍሬም እና ዲጋ አካባቢዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአማራ ማህበረሰብ ይኖራል። ካምፑ ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በሎ-ጂጋንፎይ ወረዳ ጋር የሚዋሰን ሲሆን፣ የአየር ማረፊያው በአዲስ መልኩ መዋቀር በአካባቢው ባለው ሰፊ ህዝብ ላይ የወደፊት የአየር ጥቃቶችን ለመፈጸም እንደ አመቺ ሁኔታ ሊያገለግል ይችላል የሚል ስጋት ማሳደሩን ከአካባቢው የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ።