fa
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

رفتن به کانال در Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

نمایش بیشتر
2 931
مشترکین
-124 ساعت
+1487 روز
+38530 روز
آرشیو پست ها
​በአንፆኪያ ገምዛ የፋኖን ወቅታዊ ቁመናና የትግሉን ገፊ ምክንያቶች የገመገመ ታላቅ የህዝብ መድረክ ተካሄደ!! ​ ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም። በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ፣ አንፆኪያ ገምዛ ክላስተር፣ በአሰለሌ ቀለበት ወንበር ቀበሌ የፋኖን ወቅታዊ የትግል ቁመና እና የወቅታዊ የጠላትን አቋም የገመገመ ታላቅ የህዝብ ስብሰባ ተካሂዷል። "በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር የፋኖ ወቅታዊ ቁመና እና የትግሉ ገፊ ምክንያቶች" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ የአካባቢው ማህበረሰብ በነቂስ ወጥቶ ተሳትፏል። ​በመድረኩ ላይ የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ፣ የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር እና የአስቴ ጉማ ተራራ ክፍለጦር ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የቀጠናው ህዝባዊ አስተዳደር ሃላፊዎች ተገኝተዋል። ​በዕለቱ በተካሄደው ሰፊ ውይይት የትግሉ መነሻ የሆኑ መሰረታዊ ገፊ ምክንያቶች በዝርዝር ቀርበዋል። የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር ወታደራዊ ቃል አቀባይ ፋኖ መምህር መንግስቱ፤ አገዛዙ በአንፆኪያ ገምዛ ቀጠና ላይ አቅዶና አስልቶ ያደረሰውን ዘርፈ-ብዙ ጥፋት በማንሳት ለማህበረሰቡ ማብራሪያ ሰጥቷል። ​የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ በበኩሉ፣ የፋኖን ወታደራዊ ግስጋሴና በየግንባሩ የተመዘገቡ ድሎችን አብራርቷል። በተለይም "በዘመቻ አንሻ ሰይድ" አማካኝነት በአካባቢው ሊከናወን የታሰበውን ምርጫ ሙሉ በሙሉ ማስተጓጎል መቻሉ የትግሉ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጾ፤ በአንጻሩ የጠላት ጦር መዋቅር እየፈረሰና ኃይሉ በየግንባሩ እየተበተነ መምጣቱን አስታውቋል። ​ይህ ህዝባዊ መድረክ የትግሉን ቀጣይ አቅጣጫዎች ከማስቀመጥ ባለፈ፣ ማህበረሰቡ ለነፃነት ትግሉ እያደረገ ያለውን አስተዋፅኦ ያበረታታበት ነበር። አርበኛ አበበ ሙላቱ በቁርጠኝነታቸው ለሌሎች አርአያ የሆኑ ግለሰቦችን መርጦ ልዩ የዕውቅና ሽልማት አበርክቷል። ​ከዚህ በተጨማሪም በትግሉ ነፃ የወጡ አካባቢዎችን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅና የህዝብ አገልግሎትን ለማስቀጠል የሚያስችል አዲስ የቀበሌ መዋቅርና የአስተዳደር አመራሮች ሹመት በይፋ ተከናውኗል። ​በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ አርበኛ አበበ ሙላቱ ባደረገው ንግግር፣ የፋኖ የትግል ጉዞ በታላቅ ድል እንደሚጠናቀቅ በልበ-ሙሉነት ገልጿል። ​"የአንድነታችን ውጤት ወደፊት በስራ እና በተግባር የምናየው ይሆናል" በማለት የህዝብና የፋኖ የጋራ ክንድ ያለውን የጎላ ሚና ያብራራው አርበኛው፤ ለአሰለሌ ቀለበት ወንበር ቀበሌ ህዝብም "ጠንካራ ናችሁ በርቱ" በማለት የላቀ ምስጋናውንና አክብሮቱን አቅርቧል። ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!!   ድል ለአፋብን!!  ድል ለአማራ ህዝብ!!  ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!    ስር-ነቀል ለውጥ በተባበረ ክንዳችን!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ  ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም።

አየር ወለድ ኮማንዶ የነበረው ወጣት ዛሬ ደግሞ በፋኖነት ታሪክ እየሰራ ነው:: ገና ትግሉ ሲጠነሰስ እሱ በፒካፕ ተሳፍሮ ሲጓዝ ጠላት ሊያፍነው መንገድ ላይ ደፍጦ ጠብቆ ተኩስ ሲከፍትበት ከመኪናይቱ ላ
አየር ወለድ ኮማንዶ የነበረው ወጣት ዛሬ ደግሞ በፋኖነት ታሪክ እየሰራ ነው:: ገና ትግሉ ሲጠነሰስ እሱ በፒካፕ ተሳፍሮ ሲጓዝ ጠላት ሊያፍነው መንገድ ላይ ደፍጦ ጠብቆ ተኩስ ሲከፍትበት ከመኪናይቱ ላይ እንደ ወፍ በመብረር ዘሎ በመከረባበት ጠላት መሀል ገብቶ በታትኗቸው ሀገር ጉድ አስብሏል:: የተለያዩ አውደ ውጊያዎች ላይ ተሳትፏል:: ጥይት አሁን ድረስ ሰውነቱ ውስጥ አለ:: ትግሉ ሲያልቅ እታከማለሁ ብሎ ጥርሱም ነክሶ እየታገለ እና እያታገለ ነው:: በርካታ ወጣቶችን አሰልጥኗል:: አሰልጣኝ የማይመረቅ ሰልጣኝ ነው እንድሉ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል የሰለጠነ የሰው ሀይል በማፍራቱ ሂደት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው:: እየነገርኳችሁ ያለሁት ስለ መካነሰላሙ ጀግና ኮማንዶ ጀንበሩ ጌታቸው ነው:: አየር ወለድ በራሪ ነብር የሚል ፅሁፍ ልብሱ ላይ ይታያል:: በራሪ ነብር መሆኑን እኛም እንመሰክራለን:: ጀንቤ በርታ ወንድምሰው:)

በአንፆኪያ ገምዛ የፋኖን ወቅታዊ ቁመናና የትግሉን ገፊ ምክንያቶች የገመገመ ታላቅ የህዝብ መድረክ ተካሄደ!! ​ ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም። በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ፣ አንፆኪያ ገምዛ ክላስተር፣ በአሰለሌ ቀለበት ወንበር ቀበሌ የፋኖን ወቅታዊ የትግል ቁመና እና የወቅታዊ የጠላትን አቋም የገመገመ ታላቅ የህዝብ ስብሰባ ተካሂዷል። "በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር የፋኖ ወቅታዊ ቁመና እና የትግሉ ገፊ ምክንያቶች" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ የአካባቢው ማህበረሰብ በነቂስ ወጥቶ ተሳትፏል። ​በመድረኩ ላይ የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ፣ የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር እና የአስቴ ጉማ ተራራ ክፍለጦር ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የቀጠናው ህዝባዊ አስተዳደር ሃላፊዎች ተገኝተዋል። ​በዕለቱ በተካሄደው ሰፊ ውይይት የትግሉ መነሻ የሆኑ መሰረታዊ ገፊ ምክንያቶች በዝርዝር ቀርበዋል። የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር ወታደራዊ ቃል አቀባይ ፋኖ መምህር መንግስቱ፤ አገዛዙ በአንፆኪያ ገምዛ ቀጠና ላይ አቅዶና አስልቶ ያደረሰውን ዘርፈ-ብዙ ጥፋት በማንሳት ለማህበረሰቡ ማብራሪያ ሰጥቷል። ​የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ በበኩሉ፣ የፋኖን ወታደራዊ ግስጋሴና በየግንባሩ የተመዘገቡ ድሎችን አብራርቷል። በተለይም "በዘመቻ አንሻ ሰይድ" አማካኝነት በአካባቢው ሊከናወን የታሰበውን ምርጫ ሙሉ በሙሉ ማስተጓጎል መቻሉ የትግሉ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጾ፤ በአንጻሩ የጠላት ጦር መዋቅር እየፈረሰና ኃይሉ በየግንባሩ እየተበተነ መምጣቱን አስታውቋል። ​ይህ ህዝባዊ መድረክ የትግሉን ቀጣይ አቅጣጫዎች ከማስቀመጥ ባለፈ፣ ማህበረሰቡ ለነፃነት ትግሉ እያደረገ ያለውን አስተዋፅኦ ያበረታታበት ነበር። አርበኛ አበበ ሙላቱ በቁርጠኝነታቸው ለሌሎች አርአያ የሆኑ ግለሰቦችን መርጦ ልዩ የዕውቅና ሽልማት አበርክቷል። ​ከዚህ በተጨማሪም በትግሉ ነፃ የወጡ አካባቢዎችን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅና የህዝብ አገልግሎትን ለማስቀጠል የሚያስችል አዲስ የቀበሌ መዋቅርና የአስተዳደር አመራሮች ሹመት በይፋ ተከናውኗል። ​በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ አርበኛ አበበ ሙላቱ ባደረገው ንግግር፣ የፋኖ የትግል ጉዞ በታላቅ ድል እንደሚጠናቀቅ በልበ-ሙሉነት ገልጿል። ​"የአንድነታችን ውጤት ወደፊት በስራ እና በተግባር የምናየው ይሆናል" በማለት የህዝብና የፋኖ የጋራ ክንድ ያለውን የጎላ ሚና ያብራራው አርበኛው፤ ለአሰለሌ ቀለበት ወንበር ቀበሌ ህዝብም "ጠንካራ ናችሁ በርቱ" በማለት የላቀ ምስጋናውንና አክብሮቱን አቅርቧል። ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!! ድል ለአፋብን!! ድል ለአማራ ህዝብ!! ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!! ስር-ነቀል ለውጥ በተባበረ ክንዳችን!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም።

በበላይ ዘለቀ ሻለቃ መከበቡን ያረጋገጠው ጠላት ከዚህ በፊት በደረሰበት ምት ሊደገም መሆኑን ሲያውቅ በሌሊት ጓዙን ጠቅልሎ አምልጧል። በሁሉም ግንባር ሽንፈት እየተከናነበ የሚገኘው ጠላት በገባበት ሁሉ እየተደመሰሰ ይገኛል። ቴዎድሮስ ዕዝ ባደረጋቸው ማጥቃት በበርካታ ቦታዎች ከነ አመራሩ ስለተደመሰሰ በማቻከል ወረዳ ግራ ቅዳምን የነበረው ጠላትም ጓዙን ጠቅልሎ አምልጧል። ሰኞ ዕለት በደረሰበትን ምት መቋቋም ያቃተው እና አመራሮችን ያጣው ጠላት በፋኖ መከበቡ ሲገባው ከሌሊቱ 5:00 እየቧጨረ ወጦ አድሯል። በገባበት ገብተው ከነ ሙሉ ትጥቁ ለመረከብ ጀግኛች ስራቸውን እየሰሩ ይገኛሉ። አዲስ ትውልድ ፣አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ ! ቴዎድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 26/2018ዓ.ም

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ቴዎድሮስ እዝ በ44ኛ ክፍለጦር ላይ ወታደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ ​ በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ስር የሚንቀሳቀሰው ቴዎድሮስ እዝ በ44ኛ ክፍለጦር ውስጥ ባደረገው ወታደራዊ እንቅስቃሴ፣ ለሰሜን ግንባር ታጭቶ የነበረ የኮማንዶ እና የፖሊስ ሃይል ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ከጥቅም ውጭ ማድረጉን አስታወቀ። ​የዕዙ የኮሙኒኬሽን ምንጮች እንደሚያመላክቱት፣ ለሰሜን ግንባር ስምሪት ተዘጋጅቶ የነበረውን የኮማንዶና የፖሊስ ሃይል ኢላማ በማድረግ በ44ኛ ክፍለጦር ውስጥ የተቀናጀ ወታደራዊ እርምጃ ተወስዷል። ​በተያያዘ ዜና፣ የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) በሀሙስ ገበያ የተደረገውን ውጊያ አስመልክቶ «የመከላከያ ሰራዊት የፋኖ አባላትን ደመሰሰ» በማለት ያሰራጨው ዘገባ መሰረተ ቢስ መሆኑን እዙ ገልጿል። ሚዲያው ተሰውተዋል በማለት በስም የዘረዘራቸው እነ አወቀ ደሴ፣ አሳየ ደሴ እና መንግስቴ የተባሉ የቴዎድሮስ እዝ የፋኖ አባላት በአሁኑ ሰዓት ሙሉ በሙሉ በህይወትና በሰላም እንደሚገኙ ተረጋግጧል። ​በሌላ በኩል፣ በቅንባባ በኩል ወደ ባህር ዳር የተሸኙት የመንግስት ታጣቂ ሚሊሻዎች ቁጥር 17 ብቻ መሆኑ የተረጋገጠ ሲሆን፣ ቀደም ሲል ከፋኖ አሰላለፍ የወጡ ወይም የከዱ ግለሰቦችን በተመለከተም ቁጥራቸው በቀላሉ ሊሰላ የሚችልና በትግሉ ላይ የሚያመጣው ምንም አይነት ተፅዕኖ እንደሌለ የደረሰን መረጃ ያመላክታል።

ጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር 12ኛ ክፍለጦር 6ኛ እና 4ኛ ሻለቃ ቃኝ በጋራ በሰዋ ሜዳ ሰርገው በመግባት በአገዛዙ ሰራዊት ላይ የማያዳግም እርምጃ ወሰዱ። የ102ኛ ኮር 12ኛ ክፍለጦር  ዛሬ ሰኔ 25/2018ዓ/ም በሰሜን ወሎ ዞን በጉባላፍቶ ወረዳ ከወልዲያ ከተማ በቅርብ ርቀት ልዩ ስሙ ሰዋ ሜዳ በተባለ አካባቢ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ከወትሮ በተለየ ሁኔታ  የደፈጣ ጥቃት ፈፀሙ ። ጥቃቱን የፈፀሙት የ12ኛ ክፍለጦር አናብስቶች ሲሆኑ በዚህም  ማጥቃት 10 የአገዛዙ ሰራዊት እስከ ወዲያኛዉ ሲሸኙ 17 የሚሆኑት ደግሞ በከፍተኛ ጉዳት ወልዲያ ሆስፒታል መግባታቸውን የውስጥ መረጃዎቻችን ገልፀውልናል። ጨፍጫፊውና እብሪተኛው የብልፅግና አገዛዝ በመላው አማራ ህዝብ በደረሰበት የፖለቲካ ኪሳራ ከፍተኛ ውዝግብ ላይ መሆኑ ይታወቃል። በመጨረሻም በዛሬው እለት በ12ኛ ክፍለጦር በ6ኛና 4ኛ ሻለቃ ቃኝ  የተማረከ የጠላት ንብረትና ኪሳራ በዝርዝር እንደሚከተለው እንገልፃለን። 1ኛ. Ak ክላሽን ኮፍ መሳሪያ-------7 2ኛ. የክላሽ ጥይት ተተኳሽ--------400 3ኛ. F 1 ቦንብ-- ----------------------10 4ኛ.የወገብ ትጥቅ-------------------6 5ኛ. የክላሽን ኮፍ ካዝና-------------9 6ኛ. የተደመሰሰ---------------------10 7ኛ.የቆሰለ--------------------------17 መሆናቸዉን የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!!          ሰኔ:- 25/ 2018 ዓ/ም።

የፊስቡክ አካውንታችን አሁንም ዋርኔግ እየሰጠን ይገኛል ፍሪ ሚታ በማለት ከዚህ በታች ያለውን የፊስቡክ ሊንክ በመንካት ሸር ጆይን በማድርግ ይወዳጁን https://www.facebook.com/share/1JVuJ9cNyB/

የአዲሱ ትውልድ ቁጭትና የነገን ዕጣ ፈንታ በራሱ እጅ የመወሰን ፍላጎት ነፀብራቆች! በዚህ ምስል ላይ የሚታየው የአማራ ፋኖ ኮማንዶ የምርቃት ትዕይንት፣ ተራ ወታደራዊ ምርቃት ሳይሆን በአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ ውስጥ ትልቅ አንድምታ ያለው የመሠረታዊ እይታ ለውጥ ማሳያ ነው። ፋኖ ከአነስተኛ የሽምቅ ተዋጊነት መንፈስ ወጥቶ ወደ ተደራጀና ወደ ሰለጠነ ልዩ የኮማንዶ ኃይል መሸጋገሩ፣ የትግሉን ወታደራዊ ብስለት ያሳያል። ታሪክ እንደሚያስረዳው፣ የአንድ ትግል አሸናፊነት የሚለካው በመሣሪያ ብዛት ሳይሆን በሞራል ልዕልና ነው። የአማራ ፋኖ አሸናፊነት ምስጢር የሚያካሂደው ውጊያ የህልውና ትግል በመሆኑ፣ ተዋጊው ለዓላማው ያለው ፅናትና ታማኝነት ከማንኛውም መደበኛ ጦር ይበልጣል። ይህ የቪዲዮ ምስል የሚያሳየው ወጥ የሆነ ስነ-ስርዓትና ፋኖ በምስራቅ አፍሪካ ክስተት የሆነ የራሱን ኃይል እያደራጀ በኃይልም ሆነ በዲፕሎማሲ እየተመነደገ ያለ፣ እጅግ ፈጣን የሆነ የጠመንጃ አቢዎትን ያነገበ፣ ትውልዱ ታሪኩን እየፃፈበት ያለ ትግል መሆኑን ነው። ከአማራ ፋኖ ድል አድራጊነት በስተጀርባ የሰለጠነ የተደራጀ እና የሚታገልለትን ዓላማ ጠንቅቆ የተረዳ ኃይል በመኖሩ በዘመናዊ የጦርነት ስልት ውስጥ እጅግ ድንቅ የሆነውን የውጊያ ስልት በብቃት እየተገበረ ይገኛል። ይህ ደግሞ በቴክኖሎጂ የበልፅገናል የሚለው የአብይ አህመዱን የብልፅግናን ስርዓት ሳይቀር በቆራጥነትና በህዝብ ትብብር የማሸነፉ ምስጢር ነው። የፋኖ ትግል መነሻው በኢትዮጵያ ለዘመናት የቆየው የፖለቲካ መዋቅር አማራን ያገለለና ለጥቃት ያጋለጠ ስር የሰደደ ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ህልውናውን ሊያጠፋው ስለሆነ ነው። በቪዲዮ ምስሉ ላይ የሚታዩት የፋኖ ኮማንዶ ተመራቂዎች፣ የአዲሱን ትውልድ ቁጭትና የነገን ዕጣ ፈንታ በራሳቸው እጅ የመወሰን ፍላጎት ነፀብራቆች ናቸው። የቀይ ቦኔት ለባሾቹ የኮማንዶ ተመራቂዎች፣ የአማራ ህዝብ ከዚህ በኋላ ተጠቂ ሳይሆን በፋኖ የመጫወቻ ሜዳው እንደተቀየረ ማሳያ መሆኑን ያበስራሉ። የአማራ ፋኖ ትግል በጊዜያዊ ስሜት የሚነዳ ሳይሆን፣ በስልጠና የታገዘ፣ በዓላማ የፀና እና በታሪክ የተቃኘ ግዙፍ ኃይል ነው። የአሸናፊነቱ ምስጢር በፍትህና ህልውና ጥያቄው ላይ በተገነባው የማይበገር ስነ-ልቦና እና በህዝባዊ መሰረቱ ላይ የተመሰረተ ነው። ይህ ደግሞ የኢትዮጵያ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ከአማራ ፋኖ ውሳኔ ውጭ ሊሆን አይችልም። ቋሚ ምስል፦የጀግናው ሻለቃ አንሙት ያዛቸው ልጆች የኮማንዶ ምርቃት

ሰበር የድል ዜና ጎንደር‼💪 የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ /አፋብን/ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 305ኛ ጎቤ መልኬ ኮር የአገዙዛን ሀይል ደምስሷል! ✅52ኛ ክ/ጦር ✅የ76ኛ ክ/ጦር የአካል የሆ
ሰበር የድል ዜና ጎንደር‼💪 የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ /አፋብን/ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 305ኛ ጎቤ መልኬ ኮር የአገዙዛን ሀይል ደምስሷል! ✅52ኛ ክ/ጦር ✅የ76ኛ ክ/ጦር የአካል የሆነችው 3ኛ ሬጅመንት ✅የኮሩ ልዩ ተወርዋሪ ሀይል በቀን 24/10/2018 ዓ/ም  ከሌሊቱ 8:00ስዓት ጀምሮ የአገዛዙ ሰራዊት የወገንን ሀይል አፍናለው ብሎ ሲከለከል የወገን ሀይል በደረስ መረጃ መሠረት ሌሊቱን በደፈጣ ሲጠብቅ በማደር ከንጋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ ከጠላት ጋር ፊት ለፊት ከራማ በተባለች ቦታ የተገናኘን ሲሆን አወደውጊያው ከእስከ ምሽቱ 12:00ስዓት ውሏል። ✅የጠላት ሀይል ሙሉ የ53ኛ ክ/ጦር ሬጅመንቶች የተሠለፊበት ሲሆን በጠያይሞቹ የአርማጭሆ ፈርጦች በአራት አቅጣጫ ተከቦ ውሎውን ሲገረፍ ከዋለ በኃላ የተረፈው የጠላት ሀይል የእግሬን አውጭኝ ፍርጠጣውን ተያይዞት ወደመጣበት ተመልሷል። በዚህ አወደውጊያ የተገኙ ድሎች 1ኛ ከ50በላይ ክላሽን ኮፕ 2ኛአንድ ብሬን እስከ ሙሉ ሸንሸል 3ኛ 15ኤፎን ቦንብ 4ኛ 10የካላሽ ካዝና 5ኛ የተደመሠሠ ሻለቃ መሪውን ጨምሮ  ከ50በላይ 6ኛ የቀሠለ የጠላት ሀይል ከ125 በላይ ከባድና ቀላል ቁስል በመሆን ላይመለስ የተሸኘ ሲሆን በወገን ሀይል በኩል ምንም አይነት ጉዳት አላስተናገድነም። ✅መረጃውን ያዘገየነው በኔቶርክ ምክንያት ሲሆን የቀሩ መረጃዎችን የምናጋራ መሆኑን አንገልፃለን!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! ፋኖ መ/ር አስፋው አደራጀው አማረ የ305ኛ ኮር ም/ህዝብግኑኝነት ክፍል

የጀብደኛው 206ኛ ኮር አዳኝ ቡድን በደብረ ማርቆስ ከተማ ከሌሊቱ 5:30 በፈፀመው የቦምብ ጥቃት 14 ጠላት ሙትና ቁስለኛ ሁኗል። ሰኔ 25/2018 ዓ.ም ===========================
የጀብደኛው 206ኛ ኮር አዳኝ ቡድን በደብረ ማርቆስ ከተማ ከሌሊቱ 5:30 በፈፀመው የቦምብ ጥቃት 14 ጠላት ሙትና ቁስለኛ ሁኗል። ሰኔ 25/2018 ዓ.ም ============================+++===++=== የጀብደኛው 206ኛ ኮር አዳኝ ቡድን ከሌሊቱ 5:30 በደብረ ማርቆስ ከተማ ከጎተራ ወደ ወንቃ አቅጣጫ ጥምር ጦር ጭና ስትንቀሳቀስ በነበረች ኮድ (4) ሰሌዳ 75423 ኦባማ የጭነት ማመላለሻ ተሽከርካሪ ላይ በፈፀመው የቦምብ ጥቃት 5 የሚሆኑት ህይወታቸው ሲያልፍ ከሞት የተረፉት 3 ከባድ 9 ቀላል ቁስለኛ ቁስለኛ መሆናቸው ታውቋል። በተመሳሳይ ስዓት በምስራቅ ጎጃም ዞን አስተዳደር ቢሮ ላይ በነበሩ የጠላት ኃይል ላይ የተወረወረው ቦምብ በሰው ኃይል ላይ ጉዳት ባያደርስም የጠላት መገልገያ ቁሳቁሶች ወድመዋል። አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ! የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

የብልፅግናው አገዛዝ የሃይማኖት ግጭት ለመጫር በስውር የገዳይ ቡድኖችን እያሰማራ መሆኑ ተጋለጠ አገዛዙ ህዝቡን እርስ በእርስ በማጋጨት ስልጣኑን ለማራዘም የሃይማኖት አባቶችን ኢላማ ያደረገ አደገኛ የግድያ ሴራ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል። በኢትዮጵያ ለዘመናት በወንድማማችነት እና በመከባበር አብሮ የኖረውን ህዝብ በሃይማኖት ሽፋን እርስ በእርስ ለማጋጨት፡ የብልፅግናው አገዛዝ በስውር ያደራጃቸው ገዳይ ቡድኖች የሃይማኖት አባቶችን በመግደል ላይ መሆናቸው ተጋልጧል። ይህ መሰሪ አካሄድ አገዛዙ የህዝቡን አንድነት ለመበተን እና በሀገሪቱ ውስጥ ያልተረጋጋ ሁኔታን በመፍጠር ስልጣኑን ለማቆየት የሚጠቀምበት የመጨረሻ የጥፋት ካርድ መሆኑ ታውቋል። ሰሞኑን በተለያዩ የአማራ ክልል አከባቢዎች የተፈጸሙት ግድያዎች የዚህ የሴራ መረብ አካል ናቸው። ሰኔ 17/ 2018 ዓ.ም በወሎ ቤተ-አማራ ባቲ ከተማ የጓሃፅባህ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት ቀሲስ ፍሬው ሀብታሙ መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ እንዳሉ በታጠቁ ኃይሎች ተገድለዋል። በተመሳሳይ በምዕራብ አማራ ጎጃም ቀጠና ዳንግላ ከተማ የኹጥባ መስጂድ ኢማም የሆኑት ሸይኽ ሱፍያን ሙሀመድ ከመስጂድ ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ እያሉ በጥይት ተመትተው ህይወታቸው አልፏል። የብልፅግናው አገዛዝ ከዚህ ቀደም በአርሲና በተለያዩ አከባቢዎች እምነትን መሠረት አድርጎ ያደረሰው ግድያና መፈናቀል፡ እንዲሁም በጦርነት ሽፋን በአብያተ-ክርስቲያናት እና በመስጂዶች ላይ ያደረሰው ውድመት ለዚህ የጥፋት ተልእኮው ማሳያዎች ናቸው። አገዛዙ ፍትህ የጠየቁ ንፁኋንን በማሰር እና የሃይማኖት ተቋማትን በማዳከም፣ በእምነት አባቶች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት በቸልታ በማለፍ ለጥፋቱ አጋር መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል። አገዛዙ የሃይማኖት ግጭትን እንደ መሣሪያ በመጠቀም ህዝቡን ለማሰቃየትና ለመከፋፈል እያደረገ ባለው እንቅስቃሴ ጥቃቱ በአሁኑ ወቅት የሃይማኖት አባቶችን ኢላማ በማድረግ ተባብሶ መቀጠሉን ነው ጣቢያችን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ የቻለው። ከእንደዚህ አይነቱ የብልፅግና ሴራ ህዝቡ በንቃት ተደራጅቶ ራሱን እምነቱን እና የሀገሪቱን የዘመናት የወንድማማችነት እሴት ሊጠብቅ እንደሚገባ መረብ ያነጋገራቸው የሃይማኖት አባቶች ጥሪ አቅርበዋል። በተደራጀ የጥፋት ኃይሎች እየተፈጸመ ያለው ይህ የጭካኔ ተግባር፡ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እና የእስልምና እምነት ተከታዮችን እርስ በእርስ ለማጋጨት የታለመ በመሆኑ ህዝቡ የጥፋት ሴራውን በመረዳት አንድነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ነው የሃይማኖት አባቶቹ ያሳሰቡት።

"አይቀመሴ ክንዳችን ለጠላት ያስደነግጣል!" – ፶ አለቃ ስማቸው ቢሻው (ዝግባው) ​የንጉሥ ተክለሃይማኖት ሻለቃ ጀግኖች የአማራ ፋኖ የትጥቅ ትግል ጅማሮ 3ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በወኔ ታጅበው አከበሩ! ​የህልውና ትግሉ የጀመረበትን 3ኛ ዓመት አስመልክቶ በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ፣ 206ኛ ኮር፣ 14ኛ ክፍለ ጦር ስር የሚገኘው "ንጉሥ ተክለሃይማኖት ሻለቃ" የትግሉን ጽናትና የጀግኖችን ወኔ በሚያሳይ ሁኔታ በደማቅ አከበረ። ​የአማራ ሕዝብ የነጻነት ተስፋና የአብራኩ ክፋይ የሆነው የአማራ ፋኖ ትግል፣ ከሶስት ዓመት በፊት የጀመረውን የቆራጥነት ጉዞ፣ የንጉሥ ተክለሃይማኖት ሻለቃ አባላት፣ የሻለቃ አመራሮች ፣ የህዝባዊ መንግስት አመራሮች እና የትግሉ አርበኞች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተዘክሯል።​መርሃ ግብሩ የተጀመረው ለሕዝብ ነጻነት ሲሉ ህይወታቸውን የገበሩትን የጀግኖች ስም በክብር በማስታወስ ነው። በህሊና ጸሎት የታጀበው ይህ አፍታ፣ የትግሉን ዋጋ እና የሰማዕታትን አደራ በአባላቱ ልቦና ውስጥ ያቀጣጠለ ነበር። ​በመድረኩ ላይ የተገኙት የሻለቃዋ የቀድሞ አባላትና አመራሮች ባስተላለፉት መልዕክት፣ የሕልውና ትግሉ ትናንት የጀመረ፣ ዛሬ የቀጠለ እና ነገ በድል የሚቋጭ የጋራ አደራ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። "ከእኛ የሚጠበቀው የአባቶቻችንን ጀግንነት በተግባር ማሳየት ብቻ ነው" ያሉት አመራሮቹ፣ የንጉሥ ተክለሃይማኖት ልጆች ከቶውንም የማይበገሩ፣ በጠላት ላይ የማይደፈሩ መሆናቸውን በድጋሚ አረጋግጠዋል። ​​የጀግኖች መመኪያ የሆነው  ፶ አለቃ ስማቸው ቢሻው (ዝግባው)፣ መድረኩን በሚያነቃቃ መልኩ ባስተላለፈው  መልዕክት፣ የጠላትን ደረት የሚሰብር፣ ተራራን የሚያንቀጠቅጥ የፋኖን ክንድ አሳይቷል። ​፶አለቃ ስማቸው አያይዞም "ጠላት በታሰበውና ባልታሰበው ስፍራ ሁሉ የአይቀመሴ ክንዳችንን ጣዕም ያጣጥማል። ያንን የሚያስፈራ፣ ከግርማ ሞገስ ጋር የተዋሃደ ጀግንነታችንን ለደጀን ህዝባችን ማሳየት የዘወትር ተግባራችን ነው። እኛ የነጻነት አንባዎች ነን!" በማለት የሰጠው አድማጭን የሚያነቃቃ ቃል፣ መድረኩን  በጭብጨባና በፉከራ አናግቶታል። ​በዓሉ በቃላት ብቻ ሳይሆን በባህልና በታሪክ መግለጫዎችም ደምቆ ነበር የዋለው። የአማራ ሕዝብ የጀግንነት መገለጫዎች የሆኑት ፉከራና ቀረርቶ በመድረኩ ላይ ሲሰሙ፣ የጠመንጃ አረር የሚበሩበትን የጦር ሜዳ ወኔ በመድረኩ ላይ  የፈጠሩ ሲሆን፣ የንጉሥ ተክለሃይማኖት ሻለቃ አባላት ለታሪካቸውና ለወገናቸው ያላቸውን የጸና ቃል ኪዳን ደግመውበታል። ​የንጉሥ ተክለሃይማኖት ሻለቃ፤ በታሪክ አደባባይ ላይ አዲስ ምዕራፍ እየጻፈ፣ የሕዝቡን ድል እየቃረበ ነው። ​አዲስ ትውልድ‼️ አዲስ አስተሳሰብ‼️ እስቲበል ዓለሙ

የስምጥ ሸለቆው እንባ፡ የአጣዬ ሰቆቃ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ኤፍራታ ግድም ዛሬም ልብ የሚያደማ ንፋስ ይነፍሳል። ነገር ግን የሚሸተው የለመለመው መስክ ጠረን አይደለም፤ የቆሰለ ታሪክ፣ የነደደ ቤትና የባከነ እንባ ጠረን እንጂ። ​አይ አጣዬ...! ያቺ በሽዋ ስምጥ ሸለቆ እቅፍ ውስጥ የበቀለችው ምርጧ ከተማ። ምነው ስቃይሽ በዛ? ምነው ሰቆቃሽ የዘመን ጠባሳ ሆነ? ​ስንትና ስንት የአማራ ጀግኖች አጥንታቸውን የከሰከሱባት፣ ክብሬን ለባዕድ አልሰጥም ብለው ደማቸውን ያፈሰሱባት ያቺ ምድር፣ ዛሬ በገዛ ልጆቿ ክህደት ታጥባለች። ታሪክ የማይረሳቸው፣ ህሊናቸው በባዕድ አምልኮ የደነዘዘው የብአዴን ቅጥረኞች፣ በአረመኔያዊ አብይ አህመድ ትዕዛዝ የአጣዬን የመጨረሻ ቀይ መስመር አጠፉት። በዋቂ ፈቻ የቅዠት ባንዲራ ስር፣ በንጹሃን ደም የከተማዋን ታሪክ አደፈኑት። ክህደት በልማት ስም ​ይህ ነው ወርቅ ለአበዳሪ የሚባለው? ይህ ነው ባለውለታን ማረድ? ​አማራን ለማጥፋት፣ ከምድረ ገጽ ለማክሰም ብዙ ዶለቱ፣ ብዙ ፎከሩ። አልሳካ ሲላቸው ግን የክፋት ስልታቸውን ቀየሩ። ሰማዩም የእኛ ነው፣ መሬቱም የእኛ ነው እያሉ የትዕቢት መርዝ የሚረጩ የኦሮሞ ሊቅ ተባዮች፣ ዛሬ የከተማዋን ስም ቀይረው፣ በ“ኮሪደር ልማት የይስሙላ መጋረጃ ሸፍነው፣ አጣዬን በቁም እየገፈፏት ይገኛሉ። ልማት ሳይሆን የማንነት መደምሰስ! ልማት ሳይሆን የታሪክ ዘረፋ! ይህቺ ከተማ የቆመችው በድንጋይ ላይ አልነበረም ፤ ከአራቱም ማዕዘን በመጡ የአማራ ልጆች ፋኖዎች ነበር፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ስጋቸውን በገበሩ የአማራ ልጆች ደምና አጽም ላይ እንጂ! ​ዛሬ በአጣዬ ምድር የሚታየው ትዕይንት የሰውን ህሊና ያደማል፣ ልብን ይሰብራል ትናንት ከተማዋን በጥፍራቸው የቆፈሩ፣ ጥረው ግረው ያሳደጉ ስንት ባልንጀሮች ዛሬ በገዛ ምድራቸው ላይ ስደተኛ ሆነው ፊታቸውን አዙረው ያለቅሳሉ የልጆቻቸውን ደምና አጥንት የበላችው መሬት፣ ዛሬ በፖለቲካ ቁማርተኞች እጅ በሆዳም አማራ ለኦሮሞ ስትሸጥ የሚያዩ እናቶች እጃቸውን ወደ ሰማይ ዘርግተው ይጮኻሉ። ​የጀግኖች መቃብር ፈረሰ ለሀገራቸው የወደቁላት ጀግኖች አጽም ዛሬ በባዕዳን ኮቴ ሲረገጥ ማየት፣ የሰውን ልጅ ህሊና ከማንኛውም ነገር በላይ ያሳምማል። አጣዬ ዛሬም ታዝናለች። ሰማዩ በሀዘን ተክዟል፣ ምድሪቱም አልቅሳለች። ታሪክ በደማቅ ቀለም የጻፋትን ከተማ፣ ዛሬ በባዕዶ አለም ሰዎች ስትነጠቅና ስትሸጥ ማየት ህሊና ላለው ሰው ሁሉ የዘላለም የቁም ስቃይ ነው። ​ነገር ግን... መሬት የፈሰሰ ደም ዛሬ ባይናገር፣ ነገ ታሪክ ይፋረዳል! የአጣዬ እንባ መሬት ላይ አይቀርም! #Dawit #Amhara