fa
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

رفتن به کانال در Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

نمایش بیشتر
2 936
مشترکین
-324 ساعت
+3667 روز
+38130 روز
آرشیو پست ها
አንድ ሻለቃ በአራት ጀነራሎችና በሰባት ኮሎኔሎች ላይ!! "የጎልያድና የዳዊት ትንቅንቅ" ​የጀግንነት መፍለቂያ በሆነችው በደጋ ዳሞት ምድር፣ ዛሬ ታሪክ ዳግም በደማቅ ቀለም እየተጻፈ ነው! የአራት ኪ
አንድ ሻለቃ በአራት ጀነራሎችና በሰባት ኮሎኔሎች ላይ!! "የጎልያድና የዳዊት ትንቅንቅ" ​የጀግንነት መፍለቂያ በሆነችው በደጋ ዳሞት ምድር፣ ዛሬ ታሪክ ዳግም በደማቅ ቀለም እየተጻፈ ነው! የአራት ኪሎው አገዛዝ ያለ የሌለ ኃይሉን አሰባስቦ፣ በርካታ መድፎችንና ከባድ መሣሪያዎችን አስታጥቆ የላካቸውን 4 ጀነራሎች እና 7 ኮሎኔሎችን (በአጠቃላይ 11 የጦር መኮንኖችን) የአማራ ፋኖ ኩራት በሆነው በጀግናው ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው የሚመራው የቴዎድሮስ ዕዝ ጀግኖች እያንቀጠቀጧቸው ይገኛል። ​የጦር ሳይንስንና መደበኛ ውትድርናን ብቻ ሳይሆን፣ የሕዝብን እውነተኛ የነጻነት ስሜትና ወኔ አንግቦ የተነሳው ሻለቃ ዝናቡ፣ በደጋ ዳሞት ቆራጥ ሕዝብ ደጀንነት የታገዘ ተአምረኛ አመራሩን በተግባር እያሳየ ነው። አራት ጀነራልና ሰባት ኮሎኔል ተደምረው በአንድ የፋኖ መሪ ፊት መቆም አቅቷቸው ሲጨነቁና ሲጠበቡ ማየት፣ የትግሉን የሞራል የበላይነትና የፋኖን ድል አድራጊነት በግልጽ ያሳያል። የደጋ ዳሞት ምድር ዛሬም ነገም የጀግኖች መቃብር እንጂ የፈሪዎች መፈንጫ አትሆንም፤ የጀግናው ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው ክንድ ነገም ታሪክ መስራቱን ይቀጥላል!! ​ድል ለአማራ ፋኖ! ክብር ለደጋ ዳሞት ጀግና ሕዝብና ለሻለቃ ዝናቡ ልንገረው!!

ሰበር  ዜና❗❗ 7/ለ70 ክፍለ ጦር  በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ የአገዛዙን ታማኝ መረጃ አቀባይ  እስከወዲያኛው ማሰናበቱን አስታወቀ!!          ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ 7ለ70 ክፍለ የኦፕሬሽን  ስራ በመስራት የጠላትን የመረጃ መረብ በመበጣጠስ ላይ ይገኛል።ክፍለ ጦሩ በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ኤፍራታና ግድም ክላስተር አላላ ከተማ ላይ በልዩ ኦፕሬሽን የአገዛዙ መረጃ የነበረ ተከፋይን ማለትም  ''ሰይዶ'' በሚል ስም የሚታወቀው ባንዳ ላይ  እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል። ግለሰቡ በተደጋጋሚ በክ/ጦሩ ማስጠንቀቂያና ምክር ቢሰጠውም ሊሰማ ባለመቻሉ፣ በናሁሰናይ ሻለቃ የቅኝት ቡድን አማካኝነት ዘልቆ በመግባት  እስከወዲያኛው ሊሰናበት እንደቻለ የክ/ጦሩ ሪፖርተር ከግንባር በላከው መረጃ አመልክቷል። አክለውም የአገዛዙ አስገዳይ ተከፋይ ባንዳ ላይ እንድህ አይነት የማያዳግሙ እርምጃዎች ተጠናክረው ስለሚቀጥሉ ሌሎች ተላላኪዎች ከዚህ ተማሩ ብሏል ። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት"! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ሰበር ዜና!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር 12ኛ ክፍለጦር 3ኛ ሻለቃ መንደፈራ ቀበሌ በአገዛዙ ላይ መብረቃዊ የደፈጣ ጥቃት ፈፀሙ። የ102ኛ ኮር 12ኛ ክፍለጦር 3ኛ ሻለቃ የሰራዊት አባላት ዛሬ ሐምሌ11/2018ዓ/ም በሰሜን ወሎ ዞን በራያ ቆቦ ወረዳ ከቆቦ ከተማ በቅርብ ርቀት ልዩ ስሙ መንደፈራ በተባለ አካባቢ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ የደፈጣ ጥቃት ወሰዱ ። ጥቃቱን የፈፀሙት የ12ኛ ክፍለጦር 3ኛ ሻለቃ የሰራዊት አባላት የአገዛዙ ሰራዊት ከጮሬና ቀዩ ጋሪያ መነሻውን በማድረግ በቀዩ ጋሪያና መንደፈራ መካከል ያለውን ወታደራዊ ገዢ መሬት ለመያዝ በመጓዝ ላይ እያለ በከበባ ውስጥ በማስገባት ነው። በመሆኑም የ12ኛ ክፍለጦር የ3ኛ ሻለቃ ነበልባሎች ጠላት አዘውትሮ የሚውልበትን ምሽግ በሌሊት ተስቦ በመያዝ በወሰዱት ማጥቃት 15 የመከላከያ ሰራዊት ሲገደሉ 18 የሚሆኑት ደግሞ በከፍተኛ ጉዳት ወደ ቆቦ ሆስፒታል መግባታቸውን የውስጥ መረጃዎች በዝርዝር ገልፀዋል። በጥቃቱ የጠላት ሻምበሏን ጠርንፎ ሲመራ የነበረ ሻምበል መሪ እና ግዳጅ የተሰጣት ሙሉ የሰራዊት አባል ተደምስሰዋል። በተጨማሪም አገዛዙ በዚሁ ቀጠና በተለያዩ የሀገሪቱ ትምህርት ቤቶች በአፈና ሰብስቦ ያመጣቸው አድስ ወታደራዊ ሰልጣኞች በስልጠና ላይ እያሉ ወደ ውጊያ እንድገቡ በመደረጋቸው ምክኒያት የገፈቱ ቀማሽ ሆነዋል። ጨፍጫፊውና እብሪተኛው የብልፅግና አገዛዝ በመላው አማራ ህዝብ በደረሰበት የፖለቲካ ኪሳራ ከፍተኛ ውዝግብ ላይ መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም ለሴቴና ህፃናት እንድሁም ከተማ ለሚኖሩ አዛውንት ሲቪሊያን የማይጨነቀውና በደረሰበት የንስሮቹ ፈጣን የደፈጣ ጥቃት የተወዛገበው የብልግና ሰራዊት ዛሬም እንደ ትናንቱ የቁጣ ማብረጃቸው ምስኪን የአማራ ገበሬ ላይ የከባድ መሳሪያ ድብደባ አድርገዋል። በዚህ ምክኒያት በርካታ ንፁሀን አርሶ አደሮች መሰዋትነት የከፈሉ ሲሆን ግሚሱ በከፍተኛ ጉዳት ላይ እንደሆኑ የአካባቢው ማህብሰብ ገልጿል። እንድሁም የአማራን ህዝብ ጭፍጨፋ እውን ለማድረግ የመጣው አገዛዙ በከባድ መሳሪያ ድብደባ የአቶ ተመስገን መለሰ 7 ከብት እና የአቶ ታደሰ መርሻ 5 ከብት በድምሩ 12 የቁም እንስሳት በመግደልና በርካታ የአርሶ አደር ሰብል አቃጥሏል። በመጨረሻም በዚህ የደፈጣ ጥቃት የደረሰ የጥላት የሰባዊና ቁሳዊ ኪሳራ 1ኛ.Ak ክላሽን ኮፍ መሳሪያ------10 2ኛ. F1 ቦንብ--------------------- 9 3ኛ. የተደመሰሰ ---------------------15 4ኛ.የቆሰለ ----------------------------18 መሆኑን የ12ኛ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ገልጿል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ(ቤተ-አማራ) ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም

ለተከበረው የሸዋ ደራ ህዝብ የቀረበ የህልውና ጥሪ ሰላም የተከበርከውና ውድ የሸዋ ደራ ህዝብ ሆይ፤ እንደሚታወቀው ሁሉ፣ በደራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው የማፈን፣ የመግደል፣ የማፈናቀል እና ያለ ም
+1
ለተከበረው የሸዋ ደራ ህዝብ የቀረበ የህልውና ጥሪ ሰላም የተከበርከውና ውድ የሸዋ ደራ ህዝብ ሆይ፤ እንደሚታወቀው ሁሉ፣ በደራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው የማፈን፣ የመግደል፣ የማፈናቀል እና ያለ ምንም ፍርድ የህይወትና የንብረት ብዝበዛ እጅግ አሳሳቢና መራራ ደረጃ ላይ ደርሷል። ይህ በወገናችን ላይ የተደቀነ የህልውና አደጋ እያደር እየከፋ መጥቷል። ይሁንና አሁን እየታየ ያለው አዲስና አደገኛ አካሄድ ሸኔ የነገ ተስፋችን የሆነውን ወጣቱን ከየአቅጣጫው እያፈኑ ወደ ስልጠና ተቋማት በማስገባት ለጥፋት ማዘጋጀታቸው ነው። ይህ ድርጊት ነገ የራስህ ልጅ በአንተ ላይ እንዲነሳና የገዛ ወላጁን አንገት እንዲያርድ እያሰለጠኑት መሆኑን በጥልቀት ልንረዳውና ልንነቃበት ይገባል። ስለሆነም፣ ይህንን የጥፋት ሴራ ቀድመን ለማክሸፍ ወጣቱም ሆነ ጎልማሳው በአንድነት በመነሳት፣ ወደ ፋኖ በመቀላቀል ሀገሩንና ወገኑን ሊታደግ ይገባል። ባለሀብቱም ቢሆን ዛሬ እጅህን አስገብተህ፣ ተግተህ ሰርተህ ባለሀብት የሆንክባትን፣ በነጻነት ወጥተህ ወርደህ የምትኖርባትን ሀገርህን ለማዳን የምትረባረብበት ወሳኝ ወቅት አሁን ነው። ይህንን የጥፋት ኃይል ከደራ መሬት ላይ ሙሉ በሙሉ ነቅለን ለመጣል እያንዳንዱ ሰው በየተሰማራበት ዘርፍና በየፊናው ተግቶ በመስራት ውድ ሀገረ ደራን ከጥፋት እንታደጋት! ድል ለተበደለው ለተገፋው ህዝባችን! የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህግ መምሪያ አርበኛ ሽመልስ ንጉሴ

ሰላም ሰላም ቤተስብ አዳዲስ መረጃዎችን በአራቱም ማዕዘን ጎልጉለን እያወጣን እንገኛለን የቴሌግራም ሊንካችን ሸርና ጆይን በማድረግ ይወዳጁን፦ https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk

ከአፋብን ሸዋ ጠ/ግ አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮር ኃይለማርያም ማሞ ክፍለጦር ለሚሊሻ እና ለአድማ ብተና ፖሊስ አባላት የተላለፈ ጥሪ። የተከበራችሁ የሚሊሻ እና የአድማ ብተና ፖሊስ አባላት፤ እናንተ ከዚሁ ማህበረሰብ ማህፀን የወጣችሁ፣ ወላጆቻችሁ፣ እህትና ወንድሞቻችሁ እንዲሁም ልጆቻችሁ ከዚሁ ህዝብ ጋር አብረው የሚኖሩ የሀገራችን ወገኖች ናችሁ። ዛሬ አገራችን ያለችበት ወቅታዊ ሁኔታ እና አምባገነኑ ስርዓት እናንተን ከገዛ ወገኖቻችሁ ጋር ለማጋጨትና ለስልጣኑ ማራዘሚያነት ሊጠቀምባችሁ የሚሄድበት መንገድ እጅግ አደገኛ ደረጃ ላይ ደርሷል። በገዛ ወገን ላይ እጅ ማንሳት፣ ንፁሃንን ማጥቃት እና የህዝብን ደህንነት ለአደጋ ማጋለጥ የታሪክም ሆነ የህሊና ተጠያቂነትን ያስከትላል። ስልጣንና የአምባገነኖች መመሪያ ጊዜያዊ ናቸው፤ ከህዝባችሁ ጋር አብሮ የመኖር ዘላቂ እጣ ፈንታችሁ ግን መቼም አይቀየርም። ስለሆነም ክፍለጦራችን ኃይለማርያም ሞሞ ክፍላጦር የሚከተለውን ታሪካዊና ወንድማዊ ጥሪ ያቀርብላችኋል፦ ፩) ከህዝባችሁ ጎን ቁሙ፦ የአምባገነኑን ስርዓት ህዝብን የመጨፍለቅ እና የማጥቃት እኩይ ትዕዛዝ "አሻፈረኝ" በማለት ከወገናችሁ ጎን እንድትቆሙ እና የህዝብን ደህንነት እንድታስጠብቁ ጥሪ እናደርጋለን። ፪) የሙሉ ደህንነት ዋስትና፦ ስርዓቱን ጥላችሁ ከህዝባችሁ ጋር ለመቀላቀል ለምትወስኑ ለእያንዳንዳችሁ አባላት ሙሉ የደህንነት ጥበቃ፣ ክብር እና ማህበራዊ ዋስትና እንደሚደረግላችሁ በይፋ ቃል እንገባለን። ፫) የይቅርታ እና የመደጋገፍ መርህ፦ከዚህ ቀደም የተፈጠሩ አለመግባባቶች አልፈው ማህበረሰባችን በይቅርታና በክብር እንደሚቀበላችሁ እናረጋግጥላችኋለን። ከእንግዲህ ከአምባገነኑ አገዛዝ አፈንግጦ ወደ ክፍላጦራችን የሚመጣ የሚሊሻ አድማ ብተና ወይም የፖሊስ አባል ምንም አይነት እርምጃ እንደማይወሰድበት ዋስትናችን የጸና ነው። ፬) የጋራ ጥበቃ፦ከአምባገነኑ ስርዓት የሚሰነዘርባችሁን ማንኛውንም አይነት የደህንነት ስጋት ከህዝቡና ከእኛ ጋር በመሆን በጋራ እንከላከላለን። ፭) የጋራ ኮሚቴ ማቋቋም፦ ከዚህ በፊት በተሳሳተ መረጃ ምክንያት  ስህተቶች ተፈጥረዋል ለወደፊቱ መሰል ስህተቶች እንዳይደገሙ ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከሃይማኖት አባቶች እና ከማህበረሰቡ ተወካዮች ጋር በጋራ የሚሰራ የክትትል ኮሚቴ ይቋቋማል። ወንድሞቻችን ሆይ! ታሪክ እና ህዝብ ትክክለኛውን ውሳኔ የምትወስኑበትን ታሪካዊ ቀን እየጠበቁ ነው። የወጣችሁበት ህዝብ ደህንነቱ እንዲጠበቅ እና የወገን ደም እንዳይፈስ ምርጫችሁን ከህዝባችሁ ጎን አድርጉ። ክብር እና ደህንነት ለህዝባችን! አፋብን ሸዋ ጠ/ግ አሳምነው ዕዝ ከሰም ፪ኛ ኮር የኃይለማርያም ማሞ ክፍላጦር ሪፖርተር

#‎የአረመኔው አብይ አህመድ 55 ውሸቶች ‼️ ‎ ‎1/ ሳናጣራ አናስርም ‎2/ ጊዜ ስለሌለኝ ከኖቬል ሽልማት ፕሮግራም ላይ አልገኝም ‎3/ አንዲት ፈረንሳዊ ላግባህ ብላኝ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ ‎4/ በተከልነው ችግኝ የሀሮማያ ሀይቅ ወደ ነበረበት ተመልሷ ‎5/ ነዳጅ ማውጣት ጀምረናል ‎6/ በእኔ ዘመን አሳዳጅና ተሳዳጅ አይኖርም ‎7/ ወደ ትግራይ አንድ ማስክ እንጅ አንዲት ጥይት አልክም ‎8/ እመኑኝ አሻግራችኋለሁ ‎9/ የኤርትራ ሰራዊት በጦርነቱ አልተሳተፈም ‎10/ ስንዴ ኤክስፖርት ልናደርግ ነው ‎11/ ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ምርጫ አይራዘምም ስላቸው ስልክ ጆሮየ ላይ ዘጉብኝ ‎12/ በአፍሪካ እንደኔ ብዙ ደጋፊ ያለው መሪ የለም ‎13/ 5 ቢሊዮን ችግኝ የአሜሪካ መንግስት ልትከል ቢል አይችልም፣ እኛ አድርገንዋል ‎14/ እንዲህ አይነት ፋውንቴንም ሆነ አበባ ዱባይ እና ላስቬጋስ እንኳ የላቸውም ‎15/ እያንዳንዱን የመንግስት ስብሰባበ ቀጥታ ለህዝብ እናስተላልፋል ‎16/ ሲሚንቶ በ600 ብር ይሸጣል ‎17/ ከኖቤል ሽልማት የኢትዮጵያ እናቶች የሚመርቁኝ ይበልጥብኛል ‎18/ ሚዲያ ዘግቶ፣ ተፎካካሪ አስሮ፣ ሃሳብ ዘግቶ የመንደር አለቃ መኮን ይቻላል እንጅ ‎የሀገር መሪ መሆን አይቻልም እኔም አላደርገውም ‎19/ ሀጫሉን ማንም ሳያውቀው ለ10ዓመት ያክል ጓደኛዬ ነበር ‎20/ ገዱን እና እኔን የሚለየን ሞት ነው ‎21/ ሱፊና ሰለፊ አብረው መስገድ የጀመሩት እኔ ከመጣሁ ነው ‎22/ የዘይት ገብያው ተረጋግቷል ‎23/ የወለጋ ህዝብ ውሃ ብትጠይቁት ወተት የሚያጠጣ ነው ‎24/ ፍትሀዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንድካሄድ አደርጋለሁ ‎25/ ስናጠፋ ቆንጥጡን ‎26/ ባለፉት 2 ዓመታት በአማራ ክልል ብቻ 28000 ት/ቤቶች አስገንብተናል ‎27/ የጨረባ ምርጫን ለማስቆም መንግስት ይገደዳል ‎28/ በ7 ዓመቴ የኢትዮጵያ ንጉስ እንደምሆን አውቅ ነበር ‎29/ በባድሜ ጦርነት ወቅት ቦንቡ ሲፈነዳ ጓደኞቼ ሞተው እኔ ብቻ ቀረሁ ‎30/ መግደል መሸነፍ ነው ‎31/ ሸህ አላሙዲንን ከሳውዲ አስፈትቼ አመጣቸዋለሁ ‎32/ አሳምነው ፅጌን ከእስር ያስፈታሁት እኔ ነኝ ‎33/ በእኔ ምክንያት አንድ ሰው ከሞተ ስልጣኔን እለቃሁ ‎34/ ለማ መገርሳ ትላንት በግልፅ ዛሬ በድብቅ አለቃዬ ነው! ‎35/ ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞት ኢትዮጵያ ‎36/ ጠቅላይ ሚሚንስቴር እንደምሆን መለስ ዜናዊም ያውቁ ነበር ‎37/ ልጅ ሁኘ በሻሻ ላይ ጓደኞቸ ጠቅላይ ሚኒስተር እንደምሆን ይነግሩኝ ነበር! ‎38/ ተቃዋሚዎች በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ ‎39/ የአማራ ፋኖ ከቆሰሉ መከላከያ ሰራዊት ጥቁር ክላሽ ቀምቷል ‎40/ የኢትዮጵያ እናቶች ይፀልዩልኛል ‎41/ አዲስ አበባ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የኦሮሞ ጥላቻ አለ ‎42/ ኦሮሞ በእኔ ስልጣን ዘመን ያለውን ተነጠቀ እንጂ እላፊ አልወሰደም ‎43/ ኢትዮጵያ የጋዝ ምርትን ወደ ገበያ ልታቀርብ ነው። በቅርቡ የራሷን የተፈጥሮ ጋዝ ለገበያ ልታቀርብ ነው! ‎44/ ጎጃም ውስጥ ዝናብ አዝንበናል ‎45/ መንግስታችን ተነካ ብለው ከቡራዩ ፣ ከለገዳዲ . . . እየመጡ ነበር ‎46/ አሳምነው ፅጌንና የአማራ ክልል አመራሮችን እኔ አልገደልኩም ‎47/ ዶክትሬት ዲግሪ አለኝ ‎48/ 300 % ደመወዝ ጨምሬአለሁኝ ‎49/ የዛሬ 5 አመት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሮቦት ይኖረዋል ‎50/ በ2100 በአለም ላይ ኢትዮጵያ 2ኛዋ ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ ትሆናለች ‎51/ ኢትዮጵያ ውስጥ እድገት አይደለም ያለው ሚራክል ነው ‎52/ የድሮን ፋብሪካ አስመርቄያለሁ ‎53/ ለፈጣሪ ምን ይሳነዋል ወደብ አገኝን ‎54/ ወያኔ ዱቄት ሆኗል አየር ላይ እንደ

የአገዛዙን ተልዕኮ ተቀብለው በስርቆትና በእገታ እኩይ ድርጊት በተሰማሩ ወንጀለኞች ላይ ፋኖ በወሰደው መጠነ-ሰፊ የማፅዳት ዘመቻ በርካቶችን ሲደመስስ በርካቶችን ደግሞ በቁጥጥር ስር ማዋሉ ታወቀ። በአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ 305ኛ ኮር የኮሩ ልዩ ዘመቻን ጨምሮ በኮሩ ስሩ የሚገኙ ክፍለ ጦሮች ከሕዝቡ ጋር በመቀናጀት  በቀጠናው ከአገዛዙ ተልዕኮ ተቀብለው በስርቆት እኩይ ድርጊት በተሰማሩ ወንጀለኞች ላይ ከወትሮው የተለየ ጥብቅ እርምጃ እንዲወስዱ አቅጣጫ ማስቀመጡን ተከትሎ ዘመቻው በድል ታጅቦ መቀጠሉን  ኮሩ ካወጣው መረጃ ተመልክቷል። ከፋኖ ጋር ፊትል ለፊት ገጥሞ ማሸነፍና ከወደ ፋኖ የሚሰነዘርበትን መብረቃዊ ምት መቋቋም ያልቻለው የብልፅግናው አገዛዝ፡ በፋኖ ስም ሕዝቡን ለመዝረፍ የራሱን የአድማ ብተና አባላትን ጨምሮ ሌሎች ሆድ አደሮችን በመመልመል በመከላከያ ሠራዊት ሽፋን ሰጭነት በየአከባቢው አሰማርቶ መንገደኞችን በማገትና የሕዝቡን ሃብት ንብረት በማዘረፍ አስፀያፊ ድርጊት ሲሰራ ቆይቷል። ማን ሕልውናውን እንደሚያስከብርለትና ማን እንደሚገድለው እንዲሁም ማን እንደሚዘርፈው ጠንቅቆ የሚያውቀው ሕዝቡ፡ በአንዳንድ ከተሞች ላይ አገዛዙ በሚያዘጋጀው መድረክ ላይ ተገኝቶ "ዘራፊዎቹ ከመንግስት መዋቅር ጋር የተሳሰሩ ናቸው" በሚል ቢናገርም ሰሚ ከማጣቱም በላይ፡ የፅንፈኛ ተልዕኮ ተሸካሚ በሚል በአገዛዙ ኃይሎች ለዳግም ጥቃት ሲዳረግ ቆይቷል።    በዚህም፡ በበላይ ዕዝ 305ኛ ኮር የኮሩ ልዩ ዘመቻን ጨምሮ በኮሩ ስሩ የሚገኙ ክፍለ ጦሮች ከሕዝቡ ጋር በመቀናጀት በቀጠናው ከአገዛዙ ተልዕኮ ተቀብለው በስርቆት እኩይ ድርጊት ላይ በተሰማሩ ወንጀለኞች ላይ ከወትሮው የተለየ ጥብቅ እርምጃ እንዲወስዱ አቅጣጫ ማስቀመጡን ኮሩ በሕዝብ ግንኙነት ክፍሉ በኩል ካወጣው መረጃ ተመልክቷል። ከወልቃይት ጠገዴ ጀምሮ በአርማጭሆ፣ ከአዳኝአገር ጫቆ እስከ መተማ በተለይ በጠረፉ አካባቢ ተጠናክሮ በቀጠለው የማፅዳት ዘመቻ በርካታ ቁጥር ያላቸው የአገዛዝ ወንበዴዎች እርምጃ የተወሰደባቸው ሲሆን፡ በርካቶች እጅ ከፈንጅ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው ይገኛል። እጅ ከፈንጅ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው ከሚገኙ ዘራፊዎች የተገኘው መረጃ የሚያመላክተው፡ እገታና ዝርፊያው እንዲፈፀም ትዛዝ የሚሰጡት የፌደራል መረጃና ደህንነት ክፍል እና የዞንና ከወረዳ ፓለቲካ አመራሮች እንዲሁም የመከላከያ ሠራዊት አዛዦች ናቸው። 305ኛ ኮር በስሩ ከሚገኙ ክፍለጦሮች የተወጣጡ አሃዶችን አስተሳስሮ ከማህበረሰቡ ጋር በማቀናጀት ፀረ አማራው የብልፅግና ቡድን ባሰማራቸው ዘራፊና አጋች ወንበዴዎች ላይ የሚወስደው እርምጃ በድል ታጅቦ ተጠናክሮ መቀጠሉን ኮሩ በሕዝብ ግንኙነት ክፍሉ በኩል ካወጣው መረጃ ተመልክቷል።

የማይደበዝዝ እውነት!! ​"ጊዜ የሰጠው ቅል ጋን ይሰብራል አሉ...ኦሮሞ ሰው ሆኖ ዛሬ እዚህ ደረጃ ላይ እንዲደርስና ትልቅ የታሪክ ምዕራፍ እንዲይዝ ያደረገው የአማራ ህዝብ የከፈለው መስዋዕትነትና የዋለው ውለታ እንዴት በአንድ ጀምበር ተረሳ? በታሪኬ እኔ ኦሮሞ ሆኜ ባለመፈጠሬ ፈጣሪን ከሚያመሰግኑት ጥቂት ሰዎች አንዱ እኔ ነኝ" ምክንያቱም አብሮነትንና ሰብአዊነትን የረሱ፣ ሰው ሆኖ መፈጠር የተሳናቸው አንዳንድ የኦሮሞ ልሂቃን ዛሬ ለሀገር የሚያበረክቱትን የጥፋት መርዝ ሲያይ፣ "ባይፈጠሩ ይሻላቸው ነበር" ብሎ ከማሰብ ውጪ ሌላ ማስተንፈሻ አላገኘም። የአማራን ህዝብ እውነተኛ ማንነትና ለሀገር የከፈለውን ዋጋ በሰራ የምድር አለማት ባልበቁት እውነቱን እንዲህ ነው። ​አማራ ማለት ለዚህች ውድ ሀገር... ​የሉዓላዊነት ጽኑ ምሰሶ ዳር ድንበሯ እንዳይደፈር፣ ክብሯና ነፃነቷ ተጠብቆ ለትውልድ እንዲሻገር ደሙን ያፈሰሰ፣ አጥንቱን የከሰከሰ የወርቅ ግንብ ነው። ​የአብሮነት ማህተም ራሱን ዝቅ አድርጎ ሀገርን ከፍ ያደረገ፣ በታሪኩ ማንም ሳይለይ ሁሉንም ወገኖቹን እቅፍ አድርጎ የያዘ የትዕግስትና የፍቅር ተምሳሌት ነው። ​የማንነት አሻራ የባህል፣ የፊደል፣ የሥነ-ጽሑፍ እና የክብር መሰረትን የጣለ፣ ውለታው በማንኛውም የታሪክ ማህደር የማይፋቅ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው።​በመጨረሻም ታሪክ ጊዜያዊ ማዕበል ቢመታውም፣ እውነት ግን ለአፍታ እንጂ ለዘላለም ተቀብራ እንደማትቀር ልብ ልትሉት ይገባል። Dave Amhara

ከተፈጥሮም የተጣላው ብልፅግና❗️ አሁን ከመሸ 1:00 ላይ በሸዋ ተጉለት ቀጠና ሠላ ድንጋይ ከተማ ፆድቃኔ ማሪያም አካባቢ ዝናብ መዝነቡን ተከትሎ በጣለው የመብረቅ አደጋ የሚሊሻ አባላት መሞታቸው ሲገ
ከተፈጥሮም የተጣላው ብልፅግና❗️ አሁን ከመሸ 1:00 ላይ በሸዋ ተጉለት ቀጠና ሠላ ድንጋይ ከተማ ፆድቃኔ ማሪያም አካባቢ ዝናብ መዝነቡን ተከትሎ በጣለው የመብረቅ አደጋ የሚሊሻ አባላት መሞታቸው ሲገለፅ የቆሰሉ እንዳሉም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር መረጃና ደህንነት ክፍል በመረጃው አረጋግጧል። እውነት ሁሌም ከተበዳዮች ጎን ናት!

በተወሰደው የሰርጎ ገብ ኦፕሬሽን አራት የሚሊሻ አባላት ከፍተኛ ጥቃት ደርሰ!! 64ኛ ክ/ጦር ሀምሌ 10/2018 ዓ.ም ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ በሸበል በረንታ ወረዳ የዕድውሃ ከተማ
+1
በተወሰደው የሰርጎ ገብ ኦፕሬሽን አራት የሚሊሻ አባላት ከፍተኛ ጥቃት ደርሰ!! 64ኛ ክ/ጦር ሀምሌ 10/2018 ዓ.ም ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ በሸበል በረንታ ወረዳ የዕድውሃ ከተማ ልዩ ስሙ ገበሬ ማህበር ሀምሌ 09/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ምሽግ ላይ በነበሩ የአገዛዙ ቅጥረኛ የሚሊሻ አባላት ላይ 64ኛ ክ/ጦር በወሰደው የሰርጎ ገብ ጥቃት አራት የሚሊሻ አባላት ላይ ከባድ ጉዳት አድረሶል። ጥቃት ከደረሰባቸው የአገዛዙ ቅጥረኛ ሰራዊት አባላት ውስጥ 1ኛ.ሚሊሻ ሸጋው 2ኛ.ሚሊሻ ደረጀ አሸነፍ 3ኛ.ሚሊሻ ደሴ ፈንታ እና 4ኛ. ..................... ስሙን ለግዜው ማግኘት ያልቻልነው የሚሊሻ አባል ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደረሶባቸው ቢቸና፣ ደጀን የመጀመረያ ደረጃ ሆሲፒታል እና ደ/ማርቆስ ሪፈራል ሆሲፒታል ገብተው በሞት አፋፍ መሆናቸው ተረጋግጦል። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ ተስፋ፣ አዲስ አስተሳሰብ!!                 ሀምሌ 10/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት

በድጋሚ የወጣ አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ መልእክት! ​ከነበልባል ክፍለ ጦር  👉👉​ከዚህ ቀደም ባወጣነው መግለጫ እንዳሳወቅነው፤ የቦታ ምሪትና በከተማ ውስጥ የሚከናወኑ የቀበሌ ቦታዎች፣ እንዲሁም «በቦታ ትክና» እና «በጨረታ» ሰበብ የሚደረጉ የቦታ መቀራመቶችን እንደማንቀበለው  አሳውቀናል። 👉👉 በእኛ በኩልም እንደማይፀድቁና እንደሚወረሱ የነበልባል ክፍለ ጦር የያዘውን ፅኑ አቋም መግለጻችንም የሚታወስ ነው። 👉👉​ነገር ግን ይህንን ማስጠንቀቂያና ማሳሰቢያ ቸል በማለት፣ የመሬት ወረራውና መቀራመቱ አሁንም እንደቀጠለ መሆኑን ደርሰንበታል። ​ 👉👉​ማንኛውም ግለሰብም ሆነ ቡድን፣ በእኛ በነበልባል ክፍለ ጦር በኩል የቦታ ምሪትን እና ከላይ የጠቀስናቸውን የከተማ ውስጥ የመሬት ወረራዎች አጥብቀን የምንቃወም መሆናችንን ሊያውቅ ይገባል። 👉በዚህ ጉዳይ ላይ ምንም ዓይነት ይሉኝታ የማንሰጥ መሆኑን አውቃችሁ፣ ከእነዚህ መሰል ህገ-ወጥ ተግባራት እራሳችሁን እንድታቅቡና በ«ምሪት» ሰበብ የሚደረገውን ያልተገባ የመሬት ወረራ በጋራ እንድትከላከሉ በጥብቅ እናሳስባለን። ​ 👉​ከጦርነት አዙሪት መውጣት ያቃተው ድኩማኑ የብልፅግና ገዢ ቡድን፣ በቅርቡ ለመጀመር ካሰበው የሰሜኑ ጦርነት ጋር ተያይዞ ሚሊሻውን በቦታ ለመደለል አቅዷል። 👉 ለዚህም የምሪት ቦታ ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁንና ከሚሊሾች 30,000 (ሰላሳ ሺህ) ብር በመቀበል፣ ቀሪውን ደግሞ በባንክ ብድር በመሙላት ሊሰጥ እንደሆነ ደርሰንበታል። 👉👉​በተጨማሪም ከሚሊሻዎች ጋር በመዳለል እና ለሚሊሾች የተወሰነ ትርፍ በማትረፍ፣ ቦታውን በግላችሁ ለማድረግ የምትሯሯጡ ጥቂት «ሆድ አደር» ግለሰቦችም እንዳላችሁ ደርሰንበታ። 👉ህይወታችሁን ቃብድ አስይዛችሁ መሬቱን ለመቀበል የተዘጋጃችሁ የብልፅግናው ወንበር ጠባቂ ሚሊሾች! ይህ ስርዓት በተወገደ ጊዜ ከእሱ የተበረከተላችሁ ማንኛውም ዓይነት ንብረት በእኛ በፋኖ በኩል የማይጸናላችሁና ሊወረስ የሚችል መሆኑን እናሳውቃለን። ከእናንተ ላይ የሚገዛውም አካል ንብረቱ አብሮ እንደሚወረስበት በጥብቅ ማሳሰብ እንወዳለን። ​✊ ​በመጨረሻም፣ ከስርዓቱ አገልጋይነት ወጥታችሁ የህዝብ ደጀን ወደሆነው ፋኖ በመቀላቀል፣ ህዝባችሁን ከተጋረጠበት የህልውና አደጋ ለመታደግ የበኩላችሁን አስተዋፅኦ እንድታደርጉ በዚሁ አጋጣሚ ጥሪ እናደርጋለን። 👉​ይህ ሳይሆን ቢቀርና ከብልፅግና ጋር በማበር በህዝብ ላይ የሚደርሰውን ግፍና በደል ለግል ጥቅማችሁ ስትሉ ብቻ በቸልተኝነት የምትቀጥሉ ማንኛቸውም አካላት፤ ታሪካችሁን በጥቁር መዝገብ እየያዝን የምንከታተላችሁ መሆኑን፣እና ከድል በኋላም የምንፋረዳችሁና ታሪክም ይቅር እንደማይላችሁ በጥብቅ ማስገንዘብ እንወዳለን! ድላችን በተባበረ ክንዳችን ​አፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ/ከሰም ፪ኛ ኮር ነበልባል ክፍለ ጦር ኮሙኒኬሽን

ምኒልክ ዕዝ 105'ኛ ኮር 45'ኛ/መብረቅ ክፍለጦር       ከወግዲ ሰማይ ስር ታላቅ ጀብድ ተሰርቷል!!💪 ለጥላቱ መብረቅ ለወገን መከታ፣ በቆላ በደጋው በድል እንደረታ። 💪 በምዕራብ ቤተ-አማራ ግንባር ወግድ ወረዳ ውስጥ የሚንቀሳቀሰው 45ተኛ (መብረቅ) ክፍለ ጦር ከወግድ ባሻገር ወደ አጎራባች ወረዳዎች እና ወንዝ ተሻግሮ ጎራ ዞሮ ጭምር ወደ ደራ እንዲሁም መርጦለማርያም በመጓዝ ከወገን ኃይል ጋር እየተቀናጀ የጠላትን አከርካሪ የሚሰብር ሰራዊት ያለበት ክፍለ ጦር ነው:: "መብረቅ በጠላት ላይ መብረቃዊ ጥቃት ለመፈፀም ያሥችላት ዘንድ የሰለጠነና የበቃ ሰራዊት ገንብታ ከአመት እስከ አመት በድል ጎዳና እንደተጓዘች ነው። የናዚ ጀርመኑ መሪ አዶልፍ ሂትለር ድፍን አውሮፓን በወራት ጊዜ ውስጥ ያንበረከከበት አንድ የሚታወቅበት ስልት አለ፡፡ ‹‹ብሊትዝክሪዬግ›› ይባላል፡፡ ብሊትዝክሪዬግ ደረቅ ቃሉ መብረቅ ማለት ነው፡፡ የመብረቅ እሳት እንደማለት ነው፡፡ ሂትለር ለአውሮፓውያኑ ባላንጣዎቹ የሆነባቸው ያልታሰበ ነጎድጓዳማ የመብረቅ እሳት ነበር፡፡ እና ጦርነት አንዴ ከተለኮሰ ፣ ድል እንዲቀናህ ፍጥነትን በመላ አካልህ ተላበስ፡፡ ሠራዊትህ መብረቃዊ ይሁን፡፡ በጠላትህ ላይ እንደ ድንገተኛ መብረቅ ውረድበት። ጓዙንና ካዝናውን ለመሰብሰብ እንኳ ጊዜ እንዳይኖረው አድርገህ ጠላትህን አዋክበው። መብረቅ እንደወረደበት በድንጋጤ እንዲበረግግ አድርገው፡፡ ከፍጥነትህ የተነሳ በምትፈጥረው ድንገተኛነትህ ጠላትህን ፍርሃትን ልቀቅበት፡፡ በእውር ድንብሩ ሲውተረተር ለብዙ ስህተቶች እንዲጋለጥ አድርገው፡፡ ጥ- ይት የተተኮሰባት ሚዳቆ በፍርሃት እንደምትደነብረው ጠ- ላትህን በስሜት አናውጠው። በፍርሃት ናጠው፡፡ ጠ- ላትህ በድንጋጤ ሲውሸለሸል እንደ መብረቅ ትኩስ እሳት ጎርሰህ ፣ ነጎድጓዳማ እሳት ለብሰህ እንደተዋከበ ወገብ ዛላውን ብለህ ምታው። እንደ መብረቅ ክፍለጦር አፈር አስግጠው። የግዙፉ 105ኛ ኮር ክንፍ የሆነችውና በወግዲ ቀጠና የምትንቀሳቀሰው የቀድሞዋ መብረቅ ክፍለጦር/45'ኛ ታላቅ የጦር ሜዳ ጀብድ ፈፅማለች። እንደዚህ ነው እንጅ መታየት ዘንጦ፣ ሽር እያሉ መዝለቅ ከሌሎቹ በልጦ።😍 ጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ ግዙፉ 105'ኛ ኮር 45'ኛ መብረቅ       ከወግዲ ሰማይ ስር!!

ጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር መብረቅ ክ/ጦር ታዓምራዊ ጀብዶዎችን ፈፅሟል። በውጊያው ሰብአዊ እና ቁሳዊ ሃብትም ተገኝቶበታል። ምርኮኛው የብልፅግና ስራዊት ሙት እና ቁስለኛው በመሆን ብትንትኑ ወ
ጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር መብረቅ ክ/ጦር ታዓምራዊ ጀብዶዎችን ፈፅሟል። በውጊያው ሰብአዊ እና ቁሳዊ ሃብትም ተገኝቶበታል። ምርኮኛው የብልፅግና ስራዊት ሙት እና ቁስለኛው በመሆን ብትንትኑ ወጥቷል❤🙏 በምዕራባዊ ቤተ-ዐማራ አካባቢ ከፍተኛ መነቃቃት ተፈጥሯል። ዝንታለም አማራ ወይራው አማራ