fa
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

رفتن به کانال در Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

نمایش بیشتر
2 918
مشترکین
-1524 ساعت
+287 روز
+37030 روز
آرشیو پست ها
ታሪክን ገልጣችሁ እዩ… ማህደሩን መርምሩ! በታሪክ ፊት… አማራ ጀምሮ ያልጨረሰው፣ ታግሎም ድል ሳያደርግ ያቆመው ምንም ዓይነት የህልውና ተጋድሎ የለም። የጀመረውን ማጠናቀቅ፣የወጠነውን ዳር ማድረስ የአባቶቹ ታሪካዊ አሻራ ነው!" ​"አማራ ማለት… ለዚች ታላቅ ሀገር፣ ለኢትዮጵያ መፅናት ዋልታና ማገር ነው! እርሱ ሲቆም ሀገር ይቆማል፤ እርሱ ሲጠነክር የሀገር ክብር ይለመልማል። የኢትዮጵያ ትከሻ፣ የማትናወጠው የፅናት ተራራ ነው አማራ!" ​ ​"እናም… ያ የታሪክ አደራ የደረሰው፣ የነፃነትና የክብር ትርጉም፣ የፅናት ማማ የሆነው የአማራ ልጅ… እነሆ ፋኖ!#Dawit #Amhara

በአልሞ ተኳሹ ጀግናው ፋኖ ሠራዊታችን የቆሰሉ የአገዛዙ Special Force (SF) አባላት ህክምናቸውን አጠናቀው ኮሩ ለቤተሰቦቻቸው ሲያስረክብ፣ የሚሊሻ አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ፋኖን ተቀላቀሉ!! ሰኔ 19 ቀን 2018ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር ግንቦት 23 ቀን 2018ዓ.ም በአገዛዙ የምርጫ አስፈፃሚ የጦር ሀይሎች ላይ ከዕዙ አጋር ኮሮች ጋር በቅንጅት በተሠራው የተቀናጀ ዘመቻ በአልሞ ተኳሾቹ የራንቦ ክፍለ ጦር አናብስቶች የመጀመሪያው ሹተር በተማረከበት አውደ ውጊያ በብሬን የቀኝ እግሩ ተመቶ የተማረከው የአገዛዙ Special Force አባል የሆነው ፲ አለቃ ቸሩ ደገፋ ሂርጳ እና ሌሎች ቁስለኛ ምርኮኞች ለተከታታይ ሶስት (3) ሳምንታት በዕዙና በኮሩ የህክምና ባለሙያዎች ክትትል ሲደረግላቸው ቆይቶ የቅርብ ቤተሰቦቻቸው በተገኙበት ወደ ትውልድ አካባቢው በሰላም የሸኘ ሲሆን ዕዙ ቁስለኛው ከቤቱ መድረሱን አረጋግጧል። ፲ አለቃ ቸሩ ደገፋና ቤተሰቦቹ ለተደረገላቸው ህክምናና መልካም ሰብዓዊ እንክብካቤ ና የደህንነት ዋስትና የአፄ አምደጽዮን ኮርና የዕዝ አመራሮችን ከቤተሠቦቻቸው ጋር ሆነ አመስግነዋል። አገዛዙ የአማራን ህዝብ በጠላትነት ፈርጆ ከምድረ ገፅ ለማጥፋት በእግረኛና አየር ሀይል ታግዞ፣መድፍ፣ ዙ-23፣ታንክና ድሮን ታጥቆ ቢመጣም ግፍና መከራ የወለደው በጀግናው ፋኖ ሠራዊታችን የተማረኩ የስርዓቱ ወንበር አስጠባቂዎችን ከአባታችን የአፄ ምንኒልክ የርህራሄ የሰውነት ጥግ ባህሪ በወረስነው ውርስ የአገዛዙን ተልዕኮ ተቀብለው ሊገድሉን የመጡትን በውጊያ ውስጥ የቆሰሉ የብልፅግናው Special Force አባላትን በሚገባ አሳክመንና ተንከባክበን የትራንስፖርት ወጫቸውን ከፍለን ወደ ትውልድ አካባቢያቸው በሰላም ልከናል ሲል የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ገልጿል። በመሆኑም የአማራ ፋኖ እያደረገ ባለው የህልውና ተጋድሎ ከአንባገነኑ የብፅግና መራሹ ቡድን ውጭ የትኛውንም ብሔር በጠላትነት የፈረጀው አካል አለመኖሩን በሚገባ ታውቆ ሀሰተኛ መርዘማ የፖለቲካ ትምህርት ተግተው የስርዓቱ ዙፋን ጠባቂ ሆነው ውድ የህይወት መስዋዕትነት ለሚከፍሉ የአገዛዙ ሰራዊት ዛሬም እንደ ትላንቱ የፋኖ የምህረት እጆች የተዘረጉ መሆኑን እንገልፃለን ሲል ዕዙ መልዕክቱን ለአገዛዙ ሀይሎች በአፅንኦት አስተላልፏል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ከብልፅግናው ስርዓት ጋር አብረው ተሰልፈው የነበሩ የታጠቁ ሀይሎች በየቀኑ ፋኖን እየተቀላቀሉ ሲሆን፣ ዛሬ ሰኔ 19 ቀን 2018ዓ.ም ሶስት (3) የሚሊሻ አባላት የንጋቷን የፀሀይ ጮራ በፋኖ መንደር ከወንድሞቻቸው ጋር አሳልፈዋል ሲል ኮሩ ገልጿል። የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አሃድ የሆነውን ምኒልክ ክፍለ ጦርን ከነሙሉ ትጥቃቸው የተቀላቀሉ የሚሊሻ አባላት ስም ዝርዝር:- 1ኛ. አቶ ዳንኤል አመነሸዋ ከመንዝ ማማ ወረዳ 2ኛ. አቶ ጌታባለው ዳምጠው ከመንዝ ቀያ ወረዳ 3ኛ. አቶ ደምሰው አልታየ ከመንዝ ቀያ ወረዳ​ ተነስተው የህዝብ ልጅ የሆነውን ጀግናው የአማራ ፋኖን መቀላቀላቸውን የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል በምስል አስደግፎ በላከው የግንባር መረጃ ገልጿል።      ''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!"    "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!" የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ሰበር ዜና!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ  102ኛ ኮር የቀድሞው ዞብል አምባ ክፍለጦር የአሁኑ 12ኛ ክፍለጦር 1ኛ ሻለቃና 3 ሻለቃ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ መብራቃዊ ጥቃት ፈፀሙ። የ102ኛ ኮር የጥንካሬ ምልክት የሆነው የ12ኛ ክፍለጦር ሰኔ 18/2018ዓ/ም በተለያየ አቅጣጫ የመጣውን የአገዛዙ ሰራዊት ቀለበት ውስጥ በማስገባት ደመሰሰ። የጨፍጫፊውና የአምባገነኑ ስርዓት ያለ የሌለ ሀይሉን በመያዝ ውጊያ የከፈተባቸው ቀጠናዎች በዞብልና በራማ በኩል በተለምዶ  ፅሀይ መግቢያ ድረስ አሰላለፍ በማድረግ እንቅስቃሴ ያደረገ ቢሆንም የ12ኛ ክፍለጦር  አናብስቶች በመልሶ ማጥቃትና መከላከል በሁሉም ግንባር  ጥቃት በመፈፀማቸው በሽንፈት ተመልሷል። የ12ኛ ክፍለጦር 1ኛና 3ኛ ሻለቃ ረመጦች ከቀዩ ጋሪያ ቡኩ እስከ ጎቡ ጋሪያ በመዘርጋት በወሰዱት እርምጃ የጠላትን ሀይል ቀለበት ውስጥ በመግባቱ ከስናይፐርና መትረየስ አልሞ ተኳሾች  የተረፈው  ሙትና ቁስለኛውን ሳያነሳ ወደ መንደፈራ ቀበሌ እየፈረጠጠ ተመልሷል። ጠላት በዚህ አውደ ውጊያ የራሱን የሻለቃና የሻምበል አመራሮችን አስከሬን ሳያነሳ በመሸሹ ምን ያክል ጨካኝና ክብር የለሽ መሆኑን በገሀድ  ያሳየበት ተራ የወንበደ ቡድን መሆኑን አሳይቷል። በተጨማሪ የቀድሞው ታጠቅ ክፍለጦር የአሁኑ 65ኛ ክፍለጦር የጠላትን የሀይል ሚዛን በማዛባት ሞርተር 82 በመጠቀምና ሻለቃዎችን ከኮባ ወደ ጎለሻና ዳልቻ   በማስጠጋት ጠላት ባልጠበቀውና ባላሰበው ሁኔታ በመብረቃዊ ጥቃት በመመታቱ ወደ ኋላ እንዲያፈገፍግ ተገዷል። የወገን 65ኛ ክፍለጦር ረመጦች ጠላትን አንዳንቀሳቀስ በማድረግ ከሀብሎ መንደር  እስከ ጎቡ ጋሪያ  በመዘርጋት ዋጋ አስከፍለውታል።            በተመሳሳይ ሁኔታ የ102ኛ ኮር ቃኝ በዋልካ መንደር  በኩል በመግባት አሰፍስፎ የመጣውን ጠላት አከርካሪ የሰበሩ ሲሆን እንድሁም የ101ኛ ኮር የ11ኛ ክፍለጦር 1ኛ ሻለቃ አናብስቶች ወንድሞቻቸውን በማገዝ በአርበኛ ጌታየ ከበደ እየተመሩ ወደ ጮቢ በርና ከላይ የተጠቀሰውን ቦታ በመሸፈን ታሪካቸውን በቀይ ቀለም ፅፈዋል። ጠላት 3 መድፍና አንድ ዙ=23 እንድሁም አንድ 120 ሞርተር በማሰለፍ  ሆርማትና መንደፈራ ከባድ መሳሪያ በማስወንጨፍ ሙሉ አቅሙን የተጠቀመ ቢሆንም የ102ኛ ኮር ክንደ ብርቱዎቹን መቋቋም ባለመቻሉ ካለበት ቦታ እንዳይንቀሳቀስ በማድረግና የገባውን ሀይል አንዳይወጣ አድርገውታል። በመሆኑም የጠላት ግትልትል ሰራዊት በሁሉም አቅጣጫ ወደ ኋላ በመመለስ ወታደራዊ መረጃና ኦፒ የሌለው የብልፅግና መራሹ አምባገነኑ ስርዓት በግምትና በቸልተኝነት የከባድ መሳሪያ ድብደባ በማድረግ በአማራ ህዝብ ላይ በአድስ ቅኝና በጃሮታ ቀበሌዎች ላይ ግብሩ የሆነውን ጦርነቱ የማይመለከታቸውን 4 ሲቪል አርሶ አደሮች ህይወት ቀጥፏል። ከሞቱት ሲቪሎች መካከል የ80 አመቱ ሽማግሌ የ04 ጃሮታ ቀበሌ አቶ ጉብሳ ገብረ ሂይወትና ዘሀራ ኡመር የ8ዓመት ህፃን እንድሁም የ05 አድስ ቅኝ ቀበሌ አቶ ሙሀመድ ኩቢ 50 ዓመትና አለምነሽ እያሴ የ43 ዓመት እድሜ  ይገኙበታል። የአንድ ቤተሰብ አባል የአቶጉብሳ ገብረ ሂይወት ልጅ ድርብ ጉብሳ፣ ሙሉ ቢሰጠኝ እንድሁም የአቶ ሙሀመድ ኩቢ ባለቤትና ልጆች በሙሉ ከፍተኛ ቁስለኛ በመሆን በሞትና በህይወት መካከል ይገኛሉ። በመጨረሻም በዛሬው እለት በ12ኛ ክፍለጦር በዚህ አውደ ውጊያ የተገኙ የጥላት ንብረትና ኪሳራ በዝርዝር እንደሚከተለው እንገልፃለን 1ኛ. Ak ክላሽን ኮፍ መሳሪያ-----28 2ኛ. የክላሽ ጥይት ተተኳሽ-----670 3ኛ.የመትረየስ ጥይት ተተኳሽ-- 1834 4ኛ.የብሬን ሸንሸል-------------------6 5ኛ.የድሽቃ ጥይት ተተኳሽ---------434 5ኛ. አይኮም /icom ----------------1 6ኛ. ወታደራዊ ሻንጣ---------------38 7ኛ. ሬን ኮት/የዝናብ ልብስ---------42 8ኛ.ወታደራዊ የውሀ ኮዳ-----------32 9ኛ. F1 ቦንብ------------------ ---18 10ኛ.የተደመሰሰ የጥላት ሰራዊት--89 11ኛ.የተማረከ የጠላት ቁስለኛ ሰራዊት----60 መሆኑን የኮሩ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!! ሰኔ 19/2018 ዓ.ም

በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር የ55ኛ ክ/ጦር ዛሬ ሰኔ19/2018 ዓ.ም የጠላት አልባሳትን ጭኖ ሲንቀሳቀስ የነበረ ተሽከርካሪን ከነ ሙሉ ጭነቱ ጭነቱ በቁጥጥር ስር ማዋል ችሏል። በሰሜን አቸፈ
+2
በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር የ55ኛ ክ/ጦር ዛሬ ሰኔ19/2018 ዓ.ም የጠላት አልባሳትን ጭኖ ሲንቀሳቀስ የነበረ ተሽከርካሪን ከነ ሙሉ ጭነቱ ጭነቱ በቁጥጥር ስር ማዋል ችሏል። በሰሜን አቸፈር ወረዳ ለሚገኘው ሆድ አደር  የሚኒሻና አድማ ብተና ጥምር ጦር ለማድረስ መነሻውን ባህርዳር ያደረገ 157 ሚሊተሪ አልባሳትን ጭኖ ሲንቀሳቀስ የነበረ አባዱላ በ55ኛ ክ/ጦር ፋኖዎች በተደረገ ጥብቅ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል ። ለዚህ ክትትል ከፍተኛ ድጋፍ ያደረጉትን ቀኘ የውስጥ አርበኞቻችንን በክፍለ ጦራችን ስም እናመሰግናለን ሲል ክፍለጦሩ በሕዝብ ግንኙነት ክፍሉ በኩል ባወጣው መረጃ አስታውቋል።

ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ: ደጋዳሞት ላይ ታሪክ ተደግሟል ደጋ ዳሞት ፈረስ ቤት ለመግባት ለቀናት የሞከረው የጠላት ኃይል ዛሬ አነጋግ ከዚህ በፊት ደማቅ ታሪክ የተፃፈባት ሐሙ
ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ: ደጋዳሞት ላይ ታሪክ ተደግሟል ደጋ ዳሞት ፈረስ ቤት ለመግባት ለቀናት የሞከረው የጠላት ኃይል ዛሬ አነጋግ ከዚህ በፊት ደማቅ ታሪክ የተፃፈባት ሐሙስ ገበያ ላይ የ109ኛ 99ኛ ክፍለ ጦር ከ206ኛ ኮር 24ኛ ክፍለ ጦር፣ 201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦር ጋር በመቀናጀት የጠላትን ኃይል ዲሽቃ እና ሞርተሩን ተረክበውታል። ብሬኖች፣ ስናይፐሮች እና በርካታ ክላሽ ገቢ ተደርጓል። የእግረኛውንም የኮሎኔሎችም፣ የተተኳሽም ዝርዝር ከቆጠራ በኋላ እንመጣለን። ይቀጥላል...

ሰበር እጅ የሚያርቆረጥም የድል ዜና አለን ሸርና ጆይን በማድርግ ይወዳጁን!!

የአብይ አህመድ መራሹ ስርዓት የመጨረሻው ምዕራፍና የግባተ መሬቱ መቃረቡን የሚያሳዩ ፍንጮች እየታዩ ይገኛል ። ስርዓቱ በፈጠረው ጥልቅ የፍርሃት መንፈስ ምክንያት፣ በመላው አዲስ አበባ እና በዙሪያዋ ባሉ የኦሮሚያ ክልል ቦታዎች ላይ ከፍተኛ የወታደርና የደህንነት ኃይል ማሰማራቱ አሰማርቷል። ከቦታው ከሚወጡ መረጃዎች መረዳት እንደተቻለው፣ በኦሮሚያ ክልል ከሚገኙ የተለያዩ ገጠራማ አካባቢዎች የመጡ፣ ከተማውንና ባህሉን በቅጡ የማይረዱ በርካታ የደህንነት አባላት በመዲናዋ መላው አቅጣጫዎች ላይ ተሰማርተዋል። እነዚህ የጸጥታ ኃይሎች በአሁኑ ወቅት የአማራ ተወላጆችን ለይቶ የማሳደድ፣ የማዋከብና የማሰር ዘመቻ እያካሄዱ ይገኛሉ። ​ይህ መጠነ-ሰፊ የክትትልና የማሳደድ እርምጃ እየተተገበረባቸው ያሉ ዋና ዋና የአዲስ አበባ ከተማ ቦታዎች የሚከተሉት ናቸው፦ ​አራት ኪሎ (የቤተ-መንግሥቱ አካባቢ) ​መስቀል አደባባይ፥​መገናኛ ፥​ፒያሳ ​እና የከተማዋ ዋና መውጫ በሆነው በቃሊቲ መግቢያዎች ላይ ከፍተኛ ፍተሻና ጭቆና እየተካሄደ ይገኛል። ​ ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ከአዲስ አበባ ወጣ ብለው በሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞችና ስልታዊ መስመሮች ላይም እንዲሁ ተመሳሳይ የፍርሃት መንቀጥቀጥና የወታደር ክምችት ይታያል። በተለይም በ​ሱሉልታ፥​ቡራዩ ​እና በቢሾፍቱ መስመሮች ላይ የመንግሥት ጦር በከፍተኛ ጥንቃቄ ላይ ቢገኝም፣ የስርዓቱን መፈራረስ ሊያስቆም የሚችል አለመሆኑ ​በተቃራኒው፣ ግፍና መገለልን ወደ ፅናት የለወጡት የቁርጥ ቀን የአማራ ልጆች ፋኖዎች በአገሪቱ በአራቱም ማዕዘናት ታሪካዊ ድሎችን እየተጎናጸፉ ይገኛሉ። በተለይም በቤዛሞ ቀጠና እና በሌሎችም የውጊያ ግንባሮች የፋኖ ኃይሎች የመንግሥትን የጦር መዋቅር በመስበር አንጸባራቂ ድልን እያቀዳጁ ወደ ፊት እየገሰገሱ መሆኑ ታውቋል። ይህም የአገዛዙን የመጨረሻ ፍፃሜ እያፋጠነው ይገኛል።

በከላላ ወረዳ ፋኖን አፍናለሁ በሚል ቅዥት ተንቀሳቅሶ የነበረው የአገዛዙ ጦር በእጅ አዙር በፋኖ ቀለበት ውስጥ ገብቶ ከባድ ኪሣራ መከናነቡ ታወቀ። የፋኖን ክንድ መቋቋም ያልቻለው የአገዛዙ ጦር፡ "ሁሉም አማራ ፋኖ ነው" በሚል በአንድ መንደር ብቻ 21 ጊዜ የሞርታር ድብደባ በመፈፀም በንፁሃንና በቤት እንስሳት ላይ እንዲሁም በሕዝብ ተቋማት ላይ ከባድ ጉዳት አድርሷል። በወሎ ቤተአማራ ቀጠና ከላላ ወረዳ ልዩ ስማቸው ወርቄ እና ባሪ በተባሉ ሁለት ቦታዎች ላይ ፋኖ አፍናለሁ በሚል ቅዠት በሞርታርና በአየር መቃዎሚያ ሽፋን ታግዞ በተንቀሳቀሰው የጠላት ጦር ላይ ነው ፋኖ ስልታዊ የስቦ መምታት የጦር ታክቲክ በመጠቀም አስደንጋጭ እርምጃ መውሰዱን ክፍለጦሩ  በላከው መረጃ አሳውቋል። በአፋብን ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 71ኛ አባናደው ክፍለ ጦር ስር ከ3ኛ ነብሮ ሬጅመንት የተወጣጡ የፋኖ ኮማንዶዎች በወሰዱት ስልታዋ እርምጃ የጠላት ጦርን አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት አንፀባራቂ ድል ተቀዳጅተዋል። የፋኖ ኮማንዶዎቹ የስቦ መምታት የጦር ታክቲክን በመጠበም በወሰዱት እርምጃ በጠላት ላይ ከደረሰው ሰብዓዊና ቁሣዊ ኪሳራ በተጨማሪ ቁልፍ የጦር ስፍራዎች በጀግኖቹ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ነው ጣቢያችን  ከክፍለጦሩ ለማረጋገጥ የቻለው። ትናንት ሰኔ 17/2018 ዓ/ም እስከ ንጋት በተደረገው ተጋድሎ፡ ሰባት፣ የመከላከያ አባላት ሦለት የሚኒሻ አባላት በድምሩ አሥር የአገዛዙ ወታደሮች ሲገደሉ፡ 11 ወታደሮች ደግሞ በፁኑ መቁሰላቸው ታውቋል። የአገዛዙ ጦር የክንደ ነበልባሎቹን ምት መቋቋም ሲያቅተውና ሲፍረከረክ፣ በሞርታር የታገዘ ከባድ መሣሪያ ወደ መንደር በማስወንጨፍ በንፁሃንና በንብረት ላይ አስከፊ መፈጸሙ ተጋልጧል። ይሄው ፀረ አማራና ነውረኛ የአገዛዙ ኃይል በመካናይዝድ የታገዘ ጥቃት በመክፈት፡ በሰላማዊ ነዋሪዎች መንደር ላይ 21 ጊዜ የሞርታር ድብደባ ፈፅሟል። ይህ የተኩስ እሩምታ በንፁሃን ዜጎችና በቤት እንስሳት ላይ ሞትና ጉዳት ያደረሰ ሲሆን፣ የተለያዩ የህዝብ ንብረቶችንም አውድሟል። ይህ ድርጊት አገዛዙ በአማራ ህዝብ ላይ እያካሄደ ያለውን የዘር ጭፍጨፋ፣ እንዲሁም ማህበረሰቡን ስነ-ልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ በሆነ መንገድ ለማድቀቅ እያደረገ ያለውን የጭካኔ ተግባር በግልፅ የሚያሳይ መሆኑን ክፍለ ጦሩ በኔትዎርክ ምክኒያ ዘግይቶ  በላከው መረጃ አመላክቷል።

የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የውስጥ አንድነቱን አጠናከረ፤ ታሪካዊው የመርሐቤቴ አውራጃ የውይይት መድረክ በስኬት ተጠናቀቀ ​ ሰኔ 19/2018 ዓ.ም ​በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር የሚንቀሳቀሱ አራት ታላላቅ ክፍለ ጦሮች፣ የድርጅት እና የዕዝ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ለተከታታይ 5 ቀናት ሲካሄድ የነበረው ታሪካዊ የምክክርና የተሀድሶ መድረክ በታላቅ የጋራ መግባባትና በአዲስ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት ተጠናቋል። ​ይህ ውይይት በሰራዊቱ፣ በአመራሩና በህዝቡ ዘንድ በከፍተኛ ጉጉት ሲጠበቅ የነበረው መድረክሲሆን፤በውስጥ አንድነት ላይ የነበሩ ስጋቶችን ያስወገደ፣ ህዝባዊ ዓላማን ያስቀደመ ፣ የጠላትን ቅስም የሰበረ እና በህዝብ ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመመከት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ታሪካዊ ክስተት መሆኑ ተገልጿል። ​የውይይቱ አላማዎች እና የተደረሱ ስምምነቶች ​በመድረኩ ላይ የአፄ ዘረያዕቆብ ኮር (ናደው እና በፍቃዱ በላይ ክፍለ ጦሮች) እንዲሁም የአፄ አምደ ጽዮን ኮር (አፄ ዳዊት እና ራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦሮች) አመራሮች በትግሉ ሂደት ላይ ያጋጠሙ ውስጣዊና ውጫዊ ተግዳሮቶችን በግልጽነትና በድርጅታዊ ስነ-ምግባር በጥልቀት ገምግመዋል። ​ውይይቱ “ቁጭትን ወደ አቅም፣ መለያየትን ወደ አንድነት፤ ለሕዝባችን ታላቅነት፣ ለጠላታችን ሞት!” በሚል መሪ ቃል የተመራ ሲሆን፣ የሚከተሉትን 4 መሰረታዊ ነጥቦች መሰረት በማድረግ ሀሳብና አስተያዬት ተሰጥቶባቸዋል፦ 1. በትግሉ ላይ ከጎጠኝነት የጠራ የውስጥ አንድነት እና ጓዳዊነትን አስመልክቶ :- ከየትኛውም ዓይነት ወንዛዊ አስተሳሰብና አመለካከቶች በመራቅ፣በጋራ አላማ ላይ ብቻ በማተኮር በጠንካራ የሸዋ የውስጥ አንድነት ፤ቀጣይ ዓላማውን ጠንቅቆ የሚያውቅና ለወጣለት አላማ የሚተጋ ሰራዊት ና አመራር በመፍጠር በአንድነት በመተባበር ጠላታችንን ቅስሙን መስበር ይገባናል ። ይህ የአንድነት መንፈስም እስከ ሰራዊት አባልና ህዝብ ድረስ እንዲሰርጽ በትኩረት ይሰራልም ተብሏልም። 2. ህዝባዊ ውግንና እና በደልን በተግባር መካስን አስመልክቶ ትግሉ ያለ ህዝብ ሙሉ ድጋፍና ተሳትፎ ስኬታማ ሊሆን እንደማይችል በመገንዘብ፣ ባለፉት ጊዜያት የተፈጠሩ ክፍተቶችንና በህዝብ ላይ የደረሱ በደሎችን በተግባር በመስራትና ህዝብን በታማኝነት በማገልገል ለመካስ ቃል ተገብቷል። 3. የዕዝ ሰንሰለትን ማክበር እና ብልሹ አሰራርን መታገል:- ማንኛቸውም ብልሹ አሰራሮች እና መርህን ያልጠበቁ አካሄዶች በድርጅታዊ አሰራር መስመር እንዲይዙ አቅጣጫ ተቀምጧል። የዕዝ ሰንሰለትን በአግባቡ ጠብቆ የተሰጠውን ግዳጅ በብቃት መወጣትና ማንኛውንም አፍራሽ ተግባራት በወቅቱ ማረም የሁሉም አመራርና የሰራዊት አባል ግዴታ መሆኑ ተረጋግጧል። 4. ትግሉ ፖለቲካ መር ትጥቅ ትግል እንደመሆኑ መጠን ወታደራዊ ብቻ ሳይሆን ሰፊ ፖለቲካዊ ና ህዝባዊ መሰረት ያለው በመሆኑ፣ በሰራዊቱ ውስጥ ጥልቅ ግንዛቤ መፍጠርና የወደፊት የግዳጅ አፈፃፀሞችም የዕዝ ሰንሰለትን በጠበቀ መልኩ በተናበበ፣ በተቀናጀ እና ስልታዊ በሆነ መንገድ እንዲመሩ እና የህዝብ አደረጃጀቶችም በሚገባ ተሰርተው ዕዙ የሚያወርደውን ጥልቅ ስልጠና በመሰልጠን ህዝብን ሊያረኩ የሚችሉ ስራዎች መሰራት እንዳለባቸው ስምምነት ላይ ተደርሷል። ​በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የክፍለ ጦር አመራሮቹ እንደገለጹት፣ ይህ የ5 ቀናት ሰፊ ውይይት በህዝቡና በሰራዊቱ ዘንድ የነበሩ ጥያቄዎችን የመለሰ፣ ልዩነቶችን ያረመ እና መጠራጠሮችን በማስወገድ ፍፁም ወንድማማችነትን ያጠናከረ በመሆኑ ለመሪ ድርጅታችንም ሆነ ለሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አመራሮችና ህዝብ ኩራት ነው ብለዋል። ​የመሪዎቻችን፣ የጀግናው ሰራዊታችን እና የህዝባችን ሞራል ከመቼውም ጊዜ በላይ የገነባ እና በትግሉ ላይ የሚነሱ ብዢታዎችን ያጠራ በመሆኑ፤ እየደረሰ ያለውን የጥፋት እርምጃ በመስበር ወደፊት ለመግፋት ዝግጁ ነን። ከአንድነት፣ ከዕርቅ እና ከህዝብ ጥቅም ውጭ ሌላ ምርጫ የለንም! በማለት ሀሳባቸውን ገልፀዋል። በመጨረሻም፣ የመድረኩ መሪ አመራሮች በአስተያዬታቸው:- እንደ አማራ የውስጥ አንድነትን ማጥበቅ፣ ጥያቄዎችን ሁሉ ተቋማዊ በሆነ መንገድ በማቅረብና በመፍታት ሁልጊዜም አይናችሁም ልባችሁም ትግሉ ላይ አድርጉ ያሉ ሲሆን እኛም ለሚጠዬቁ ጥያቄዎች በየደረጃው ምላሽ በመስጠት እና ለህዝብ እና ድርጅታችን የገባነውን ፅኑ ቃል በመጠበቅ የጀመርነውን የህልውና ትግል ከግብ እናደርሳለን በማለት ስብሰባውን አጠናቀዋል። ''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት'' ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን '!! ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

የጥምር ጦር ጋንታ መሪው ፓሊስ እና ፓራ ኮማንዶወች የመከላከያ አባሎች ፋኖን ተቀላቀሉ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ......ሰኔ 18/2018 ዓ.ም የፋኖን ምት መቋቋም ያልቻለው የአብይ አ
+2
የጥምር ጦር ጋንታ መሪው ፓሊስ እና ፓራ ኮማንዶወች የመከላከያ አባሎች ፋኖን ተቀላቀሉ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ......ሰኔ 18/2018 ዓ.ም የፋኖን ምት መቋቋም ያልቻለው የአብይ አህመድ ወንበር ጠባቂ ስብስብ እየፈራረሰ ከአገዛዙ ሀይል ጋር ወግነው የነበሩ በርካታ የፀጥታ ሀይሎች ፋኖን ተቀላቅለዋል፦ 1.አበበ አንላይ ......ፓራ ኮማንዶወደ 74ክ/ጦር 2.አብርሀም አየልኝ.....ፓሊስ ጋንታ መሪ ወደ 74ኛክ/ጦር 3.ምስጋነው ስመኝ.....መከላከያ ወደ /54ኛ ክ/ጦር ከእነማይ ወረዳ ከጠልማ ንዑስ ከተማ እና ግንደወይን ከተማ ጥምር ጦር ብሎ ከሚጠራዉ የጠላት ሀይል በመውጣት 201ኛ ኮር 74ኛ እና 54ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉ ሲሆን በአመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። አልረፈደም አሁንም ወደ ትክክለኛ ማንነታቹህ ተመለሱ ‼️ የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

የአብይ አህመድ አረመኔያዊ ስርዓት የአማራን ህዝብ ህልውና ለመቅጨትና ከምድር ገፅ ለማጥፋት የጥፋት ማኒፌስቶ ቀርጾ ሌት ተቀን እየሰራ መሆኑን ገና በጠዋቱ የተረዱት የቁርጥ ቀን ልጆች ጥቂት ነበሩ። በዚያ የጭንቅና የፈተና ሰዓት ግን ህዝቡ በባርነትና በጭንቀት እንዳይገዛ፣ የጀግኖች አባቶቹን ወኔ አንግቦ የተነሳ አንድ ትንታግ ጋዜጠኛ የታሪክን ገፅታ የቀየረው፣ የትግሉን የመጀመሪያ ቹቦ የለኮሰውና ለዛሬው ታላቅ የፋኖ ፍሬ መብቀል መሰረት የጣለው ጋዜጠኛ አዲሱ ደርቢ አንዱ ነበር! ​ ታሪክ ወደ ኋላ ይመለሳል። ትናንት ፍርሃት አገሩን በከበበበት፣ የጥፋት ደመና በወገን ላይ በደቀነበት ወቅት፣ አዲሱ ደርቢ ብዕርህንና ድምፅን እንደታጠቀ ጀግና ጠላት በስውር የሸረበውን የዘር ማጥፋት ሴራ በመግለጥ፣ ለህዝብህ መነቂያና መከታ መሆኑን ታሪክ ያስታውሰናል ። ያኔ የለኮስካት የትግል ቹቦ ዛሬ መላውን የአማራ ተራራዎችና ሸለቆዎች የሚያበራ ታላቅ የነፃነት እሳት ሆናለች። ​ዛሬ ላይ ትግሉ አድጎ፣ ፍሬ አፍርቶ እዚህ ደረጃ ላይ ደርሷል። የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች በሙሉ ያንተንና መሰል ጀግኖችን ፈለግ ተከትለው ለህልውናቸው እየተፋለሙ ይገኛሉ። ጠላት ሊያጠፋው ያዘጋጀው ማኒፌስቶ በፋኖ ክንድ እየተቀደደ፣ የጀግኖች ታሪክ በአዲስ ምዕራፍ እየተፃፈ ነው።