ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
رفتن به کانال در Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
نمایش بیشتر2 938
مشترکین
+1424 ساعت
+3877 روز
+38530 روز
آرشیو پست ها
15 የፓሊስ አባላት አገዛዙን በመክዳት ከካምፕ መሰወራቸው ታወቀ!!
ሰሞኑን የፋሽስቱ አብይ አህመድ መንግስት ከየወረዳዎች ሚሊሻና ፓሊስ መልምሎ ወደ አንድ ማዕከል እያጓጓዘ መሆኑ ይታወቃል። ከአጭር የለብለብ ስልጠና በኋላ ወደ መከላከያ ይቀላቀላሉ የተባሉት ሚሊሻና ፓሊሶች በየእለቱ በመክዳት ላይ ናቸው። ከዚሁ ጋር ተያይዞ ከመካነሰላም ተጭነው ወደ ጊምባ ማዕከል ከተወሰዱት መካከል 8 የፓሊስ አባላት ዛሬ ሌሊት ከካምፕ መጥፋታቸው ተረጋግጧል:: ስም ዝርዝራቸው እንደደረሰን የምናሳውቅ ይሆናል።
በተመሳሳይ መልኩ ከመቅደላ ወረዳ 7 ፓሊሶች የጠፉ ሲሆን በድምሩ 15 የፓሊስ አባላት አገዛዙን ከድተዋል።
ከመቅደላ ወረዳ ፓሊሶች መካከል:-
ምክትል ሳጅን ሙላት ባይጨክን
ምክትል ሳጅን ሞገስ
ዋና ሳጅን አቡሽ ሰይድ
ምክትል ሳጅን ጀማል
ምክትል ሳጅን ፀጋዬ
ሳጅን ኮስትር ዘመነ
እና አንድ ስሙ ለጊዜው ያልታወቀ ፓሊስ ከካምፕ ሲጠፉ ሳጅን እንድሪስን ጨምሮ 3 ፓሊሶች ደግሞ ሊከዱ ነው በሚል ጥርጣሬ ታስረው ይገኛሉ::
አማራን በአማራ አጠፋለሁ ብሎ ጦርነት ያወጀው የፋሽስቱ አብይ አህመድ መንግስት በመንገድ መሪነት እና በጥይት ማብረጃነት እየተጠቀመባቸው ያሉት የክልሉ ሚሊሻ እና ፓሊስ አባላት በጦርነቱ ግንባር ቀደም ተጎጅዎች መሆናቸው ይታወቃል። የመከላከያ ሰራዊት አባላት የማድረግ አቅም ሲቀንስ እና የሰራዊቱ ቁጥርም በብርሀን ፍጥነት ሲመነምን አሁን ላይ ሚሊሻ እና ፓሊስን እንደ አማራጭ ተጠቅሞ ወደ መከላከያ ሰራዊት ለመቀላቀል ቢያስብም ሁኔታው እንደተጠበቀው ሳይሆን ቀርቶ በየቀኑ እየከዱት የወገን ኃይልን እየተቀላቀሉ ነው።
ይህን ተከትሎ የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር በበኩሉ ከአገዛዙ ከድተው ለሚመጡ ሁሉ በልዩ ሁኔታ ወገናዊ አቀባበል እና እንክብካቤ እንደሚያደርግ በዚሁ አጋጣሚ እናሳውቃለን ሲል የኮሩ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!
ሀምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም
+5
ሰበር መረጃ!
በአፋብን ወለጋ/ቢዛሞ ቀጠና የተመዘገበ አንጸባራቂ ድል!*
በአንሻ ሰይድ እዝ ስር የሚገኙት ጀግኖቹ ➨አበጀ ጥበቡ ነበልባል ክፍለጦር፣
➨አንገር ጉትን ክፍለጦር እና
➨ጌጤ ግርማ ክፍለጦር ባደረጉት የተቀናጀ እና መብረቃዊ የጥምረት ዘመቻ አስደናቂ ወታደራዊ ድል ተቀዳጅተዋል!
በዚህ የተሳካ ኦፕሬሽን የተመዘገቡ ዋና ዋና ውጤቶች
- ስትራቴጂካዊ መስመሮች በቁጥጥር ስር ውለዋል
- ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው ትልቁ የጉትን
ነቀምት መስመር፤ እንዲሁም ከቱሉ ጋና ወደ ጉትን የሚያስኬደው ቁልፍ መንገድ ሙሉ በሙሉ በጀግኖቹ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
በተደረገው የተቀናጀ ማጥቃት የጠላት አከርካሪ የተሰበረ ሲሆን፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኃይልም ተደምስሷል።
በዘመቻው በርካታ የጦር መሳሪያዎች እና ተተኳሾች በምርኮ የተገኙ ሲሆን፤ እጅ መስጠት የመረጡ የጠላት ኃይሎችም በህይወት በቁጥጥር ስር መዋላቸው ታውቋል።
የጀግኖቹ ጥምረት፣ ቆራጥነት እና ጽናት ይህንን ደማቅ ታሪክ ጽፏል!
ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም
በብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን ስም ዘረ ፈጁ አገዛዝ ያዘጋጀውን የብልጽግና እና ጀሌዎቹ ጉባኤ አስመልክቶ ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ
ለልዩነት እና ለጦርነት ምክንያት በሆኑ አጀንዳወች ላይ አካታች ብሔራዊ ውይይት እና ምክክር ማድረግን በተመለከተ የኢትዮጵያ ህዝብ ለዘመናት ሲያቀርበው የቆዬ ጥያቄ መሆኑ ይታወቃል።
ሀቀኛ ብሔራዊ ምክክር ማድረግ ለሀገር ዘላቂ ሰላም አስፈላጊ የመሆኑን ያህል የብሔራዊ ምክክር ሂደት በተለይም የምክክር ሂደቱ አካታችነት፣ የሚካሄድበት ነባራዊ ሁኔታ፣ ሂደቱን የሚመራው ተቋም አወቃቅር እና ተቋማዊ ገለልተኝነት፣ አሳታፊነት እና ሌሎችም ሁኔታወች በአግባቡ ካልታዩ ነባር ችግሮችን እና ቅራኔወችን ከማስፋት እና ከማወሳሰብ ያለፈ ፋይዳ አይኖረውም።
በብልፅግና አገዛዝ ጦረኝነት እና ዘረ-ፈጅ የቀውስ አገዛዝ ምክንያት ዓመታትን የተሻገረ እና የሚሊዮኖችን ሕይወት ያመሰቃቀለ ደም አፋሳሽ ጦርነት ውስጥ ያለችው ሀገራችን፣ ይህን በህዝብ ላይ የተከፈተዉን ጦርነት ያወጀው አገዛዝ ጦርነትን ለማቆም ምንም አይነት ፍላጎት ባላሳየበት ሁኔታ ውስጥ የሚደረግ የምክክር ድግስ በጀት ከማባከን እና ለአገዛዙ የገጽታ ግምባታ ከመስራት ያለፈ ፋይዳ አይኖረውም።
ባለፉት አመታት በዳበሳ ከሚታወቁ የሀገሪቱ እውነቶች መካክል ጦርነት ፣ ስደት፣ መፈናቀል ጅምላ ጭፍጨፋና ማንንነት መሰረት ያደረጉ ግልፅ ጥቃቶች በአገዛዝ ስፖንሰርነት እየተፈፀሙ ነው:: በብልፅግና የቀውስ አገዛዙ ምክንያት ሚሊዮኖች ተሰደዋል፣ በርካቶች በአገዛዙ የፀጥታ መዋቅር ንብረታቸዉን ተዘርፈዋል::
አማራ ክልልን ጨምሮ ከፊሉ የሀገሪቱ ክፍል በወታደራዊ አገዛዝ ስር ከወደቀ ሶስት አመታትን አስቆጥሯል። አገዛዙ በቀጥታ የእርስ በእርስ ግጭቶችን እና ጦርነቶችን በማዋለድ እና አለመተማመን እንዲነግስ በማድረጉ አብዛኛው የሀገሪቱ ክፍል ቀውስ ውስጥ ይገኛል። ይኸው ወታደራዊ አገዛዝ ምርጫ ለማድረግ የሚያበቃ የሰላም ሁኔታ ሳይኖር ራሱ ተመራጭ፣ ራሱ ታዛቢ፣ ራሱ መራጭ እና አስመራጭ በመሆን ትልቅ የፖለቲካ እና የዲሞክራሲ ክንዉን በሆነው የምርጫ ሂደት ላይ መቀለዱን ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡም የመሰከረው እና የታዘበው ሐቅ ነው። ይህንንም ተከትሎ የ2018 ምርጫ ክንዉን አለመካሄዱን እና ብልፅግናም በምርጫ ያገኘው ቅቡልነት እንደሌለ ተረጋግጧል።
አገዛዙ ይህንን በምርጫ ድግስ ያጣውን ቅቡልነት በምክክር ለማግፕት ጥረት እያደረገ ቢሆንም የብሔራዊ ምክክር ሂደቱን ለማሰናዳትም ሆነ በባለቤትነት ለማስኬድ የሚያበቃ የህግ መሰረት ግን የለዉም።
ሀቀኛ ብሔራዊ ምክክርን መምራት የሚችል ኮሚሽን በኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ ተፋላሚ ኃይሎች ይሁንታ የተሰጠው፤ ስቪክ ማህበራትን ጨምሮ በሁሉም ኃይሎች ተሳትፎ የተቋቋመ እና ገለልተኛነቱም የተረጋገጠ መሆን ይገባዋል። የወቅቱን የብሔራዊ ምክክር ጉዳይ እመራለሁ የሚለው ኮሚሽን ከአገዛዙ በስተቀር በየትኛውም የፖለቲካ ኃይል እውቅና እና ይሁንታ ያልተሰጠው ከመሆኑ ባሻገር የብልፅግናን በተለይም የጠቅላይ ሚኒስትሩን የግል ፍላጎት የብሔራዊ ምክክር ውጤት አድርጎ ይዞ ለመቅረብ የተዘጋጀ፣ ሂደቱ የሚመራበትን አሰራር የሚወስን ህግ እንኳን እንዲወጣ ያላደረገ የጏዳ ወዳጆችና የፖለቲካ ደላሎች ስብስብ ነው። ገለልተኛ ባልሆነ ተቋም የሚመራ ምክክር ደግሞ የብልፅግና ካድሬወች ውይይት እንጅ ብሔራዊ ምክክር አይሆንም። ለሀገሪቱ ችግርም ዘላቂ ሰላምም አያመጣም።
ላለፉት በርካታ ዓመታት ሀቀኛ ወኪል ሳይኖረው በመቅረቱ እጣ ፋንታውን ሌሎች የፖለቲካ ኃይሎች ሲወስኑለት የቆዬው የአማራ ህዝብ በዚህ የምክክር ጉባኤም ተመሳሳይ ሂደት ውስጥ ይገኛል። በአብን እና በአማራ ብልፅግና ስም ከየጎሬው ተለቃቅመው በጉባኤው አማራን ወክለን እንሳተፋለን የሚሉትም በአማራው ላይ ይፋዊ ጦርነት ያወጀውን ዘረ ፈጅ አገዛዝ የተቀበሉ የብልፅግና ወኪሎች እንጅ ለአማራ ህዝብ መብት እና ጥቅም ቅንጣት ታክል አስተዋፅኦ ማድረግ የማይችሉ በመሆናቸው ይህ የምክክር ጉባኤ የአማራ ህዝብ ያልተወከለበት እና የማይሳተፍበት መሆኑ በታሪክ ፊት ተመዝግቧል።
የአማራን ህዝብ ብቻ ሳይሆን ከብልፅግና አገዛዝ ጋር ይፋዊ ጦርነት ውስጥ ያሉ የፖለቲካ ኃይሎችን ያገለለ የምክክር ጉባኤ በመሆኑም ከአማራ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ሌላው ኢትዮጵያዊም ቢሆን በዚህ ጉባኤ በትክክለኛ ወኪሎቹ አማካኝነት እየተሳተፈ ነው ብለን አናምንም።
በመሆኑም ድርጅታችን አፋብን ለአማራ ሕዝብ፣ ለኢትዮጵያ ሕዝቦች እና ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚከተለውን ጥሪ ያቀርባል:-
1. ለአማራ ሕዝብ -
ይህ ምክክር ተብሎ በአገዛዙ የሚደረገው እንቅስቃስ የአማራ ህዝብ ያልተወከለበት እና ትክክለኛ ወኪሎቹ የህልውና ትግል ላይ በመሆናቸው፣ ትግሉን ጫፍ በማድረስ ስር ነቀል ለውጥ በማምጣት ህልውናውን አረጋግጦ ለወደፉቱ ከሌሎች ህዝቦች ወኪሎች ጋር በግልፅ ተነጋግሮ ሀገራዊ እውነተኛ እርቅና ምክክር ለማምጣት እንዲቻል አሁን ላይ ሁሉንም አቅሞች አሰባስቦ በበለጠ ቁርጠኝነት እንዲታገል ጥሪ እናቀርባለን፤
2. ለኢትዮጵያ ሕዝብ:-
ይህ የምክክር የተባለው ክሹፉና አስመሳይ ሂደት የአማራን ሕዝብ ጨምሮ ሌሎች ጥያቄ ያላቸው የፖለቲካ ኃይሎችም የተሳተፉበት አለመሆኑን፣ የሀገሪቱን አንድነት የበለጠ አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን፣ የእርስ በርስ ጦርነቱን የማያስቆምና የሚያባብስ መሆኑን፣ የአንድ ግለሰብ እና የገዢ ቡድን ፍላጎት ለማሳካት እየተደረገ ያለ መሆኑን በማመን ከአማራ ሕዝብ ጎን ቆሞ ስርዓቱን መታገል ይገባል:: በቀጣይ በጋራ የሽግግር መንግስት መስርተን ሀገራችንን ማፅናት እንችል ዘንድ ብሎ እውንተኛ ምክክርና እርቅ እንፈፅም ዘንድ በተባባረ መልኩ ፀረ አገዛዝ ትግል እንዲደረግ ጥሪ እናቀርባለን፤
3. ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ:-
እንደሚታወቀው በትክክለኛው መንገድ የማይካሄድ ብሄራዊ እርቅና ምክክርን ሂደቱ ካለ መኖሩ የከፋ ሀገራዊ ችግርን ያስከትላል። ብሄራዊ ምክክር ከከሸፈ አንድ ሀገር የምትገባበት ቀውስ እጅግ ከባድና በአዙሪት የተሞላና የማይገመት ይሆናል:: የብዙ ሀገራት ብሄራዊ እርቅና ምክክር የተኮላሸው ገለልተኛነትና አሳታፊነት የሌለውን ሂደት በመከተላቸው እንደሆነ ብዙ ምሳሌና ተሞክሮዎች አሉ:: የአሁኑ የአገዛዙ ብሔራዊ ምክክር የተባለው ሂደትም የህዝብ ቅቡልነት የሌለው፣ እውነተኛ ችግር ፈች ምክክር ሳይሆን ብልጽግና እና ደጋፊዎቹ የአገዛዙ ስልጣን ማጽኛ እንደሆነ እና ሀገሪቱን እንዲሁም የቀጣናውን ሰላም ከድጡ ወደማጡ የሚያስገባ መሆኑን ተገንዝባችሁ ለሀቀኛ ሽግግር እና ዘላቂ ሰላም እንድትሰሩ ጥሪ እናቀርባለን።
4. የአማራ ህዝብ ወኪል ነን ለምትሉ የሂደቱ ተሳታፊወች:-
ከዚህ ቀደም እንደሆነው ሁሉ የአገዛዙ ተላላኪ በመሆን እና ተገቢው የአማራ ህዝብ ውክልና ሳይኖራችሁ በሂደቱ የምትሳተፉ ግለሰቦች እና ቡድኖች በብሔራዊ ምክክር ስም በሚካሄድ የብልፅግና ጉባኤ በመሳተፍ ታሪካዊ ስህተት ከመፈፀም እንድትታቀቡ እያሳሰብን ይህን ማሳሰቢያ ችላ በማለት የምታደርጉት ሂደት የአማራን ህዝብ ጥያቄወች ለሌላ ምዕራፍ ለማዳፈን ለምታደርጉት ያልተገባ ተግባር ኃላፊነት የምትወስዱ መሆኑንም በህዝብ እና በታሪክ ፊት እናሳውቃለን።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ
የአፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ናደው ክፍለ ጦር ለወራት ያሰለጠናቸውን አዲስ ምልምል የፋኖ ኮማንዶ ሰልጣኞችን በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ።
ሀምሌ 18/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር የሚገኘው የአፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ናደው ክፍለ ጦር ለወራት ያህል ሲሰጥ የቆየውን ጠንካራ የንድፈ-ሀሳብ እና የተግባር ስልጠና ሲከታተሉ የቆዩ አዲስ ምልምል የኮማንዶ ሰልጣኞቹን ሐምሌ 16 ቀን 2018ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል።
በዚሁ የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ የዕዝ እና የኮር ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች እንዲሁም የአካባቢው የቀበሌ እና የክላስተር አመራሮች ተገኝተዋል።
የዕለቱ መርሃ-ግብር የተጀመረው በተመራቂ ሰራዊት አባላት የክብር ሰላምታ እና ወታደራዊ ሰልፍ ማሳያ ነው። ተመራቂዎቹ በስልጠና ወቅት ያገኟቸውን የአካል ብቃት፣ የትእዛዝ አቀባበል፣ የአሰራር ዲሲፕሊን እንዲሁም ልዩ ልዩ ታክቲክና ክህሎቶችን የሚያሳዩ ትርኢቶችን ለታዳሚው አቅርበዋል።
በዕለቱ የዕዙ ከፍተኛ አመራር አርበኛ ዳዊት ቀፀላ ባደረጉት ንግግር፤ የምረቃ ፕሮግራሙ የፅናት፣ የዲሲፕሊንና የመስዋዕትነት ውጤት መሆኑን ገልጸው፣ ተመራቂዎች በስልጠናው ወቅት ያሳዩት ወታደራዊ ክህሎት የተጣለባቸውን ታሪካዊ አደራ ለመሸከም ዝግጁ መሆናቸውን ያረጋገጡበት ነው ብለዋል። አክለውም ሰራዊቱ ህዝቡን እንደ አይኑ ብሌን እንዲጠብቅና የተሰው ጀግኖችን አደራ እንዲያስቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
በሰራዊት ምርቃት መርሀ-ግብሩ ላይ የተገኙት የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ፶ አለቃ እሸቱ ኃ/ሚካኤል በበኩላቸው፤ ዲሲፕሊን፣ ታማኝነት እና ለህዝብና ለአላማ በፅናት መቆም የሰራዊታችን ዋና መሰረት ናቸው ሲሉ የተናገሩ ሲሆን፤
የኮሩ ዋና መሪ አርበኛ እዮብ ለማ በበኩላቸው የሰራዊቱ ጥንካሬ በህዝብ ደጋፊነት እና በህብረት ላይ የተመሰረተ መሆኑን በማስገንዘብ፣ ተመራቂዎች እስከ መጨረሻው የድል ግብ ድረስ ትግሉን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ለተመራቂ ሰራዊት መልእክት አስተላልፈዋል።
በስልጠናው ወቅት በዲሲፕሊን፣ በስልጠና ውጤት፣ በአካል ብቃት እና በትእዛዝ አፈጻጸም ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂ ሰልጣኞች እና አሰልጣኞች ታላቅ የምስጋና እና የክብር እውቅና ተሰጥቷቸዋል።
ከተመራቂዎች መካከል አስተያየታቸውን የሰጡ አባላት በስልጠናው ወቅት ያገኙት ልምድ ለቀጣይ ስራቸው ትልቅ አቅም እንደሚሆናቸው በመግለጽ፣ የተጣለባቸውን ህዝባዊ እና ድርጅታዊ ሀላፊነት በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠው፤የምረቃ ስነ-ስርዓቱ በተመራቂዎች የቃለ-መሀላ ስነ-ስርዓት ከተካሄደ በኋላ በደማቅ ሁኔታ ተጠናቋል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት !
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
🔥ተጠናክሮ የቀጠለው አፋብን ወለጋ /ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ ክፍለጦሮቺ በጥላት ላይ ድል ተቀዳጁ‼️
ከመጠየፍ ያልቆጠሩት የከባድ መሳርያ ፍንዳታን አራተኛ(4) ቀኑን የያዘው ከአራቱም ክፍለጦሮቺ የተውጣጡ የአንሻ ሰይድ አናብስቶች በምስራቅ ወለጋ ዞን ስቡ ስሬ ወረዳና ጉቶ ጊዳ ወረዳ የህልውና ተጋድሎው እደቀጠለ ሲሆን፦
በተጨማሪም አድማሱን በማስፋት በምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ በመንደር 4 እና በመደር 3 ላይ እድሁም በሆሩ ጉድሩ ወለጋ ዞን አቤደንጎሮ ወረዳ ቱሉጋና ከተማን በመቆጣጠር አንፀባራቂ ድል ተቀዳጁ።
ሐምሌ 17ቀን2018ዓ.ም ከጠዋቱ 1:00ሰአት ላይ በመናበብ አበጀ ጥበቡ ነበልባል ክፍለጦር በመንደር 4 በመግባት ጥላትን ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ከአከባቢው አጥረግርገው በማስወጣት፤በተጨማሪም አንገር ጉትን ክፍለጦር መንደር 3 ቀበሌ ላይ በመግባት አንድ የጥላት ፓትሮል ኃይል ከነተሽከርካሪው ሲመታ በሁለቱም ቀበሌዎች የተናበበ የሁለቱ ክፍለጦሮች ጥምረት ከከተሞች በማስወጣት እግር በእግር እየተከታተሉ ሙትና ቁስለኛውን በመጣል አንገር ጉትን ከተማ መዘጋጃ ውስጥ በፍርሐት ከትሞ ይገኛል።
በሌላኛው በሆሩ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አቤደንጎሮ ወረዳ ቱሉጋና ከተማን ታፈረ አለሙ ሳተናው ክፍለጦር በልዩ ኦፕሬሺን ከተማዋን ተቆጣጥሯል።
በዚህምከባድ አውደ ውጊያ ምርኮ የተገኙ 31 ክላሺ እኮቭ ሲማረክ አንድ በሲብል ሲቀሳቀስ የነበረ ደህንነት ፖሊስ ጨምሮ 4 የኦሮሚያ ልዩ ኃይል በመማረክ በከፍተኛ የበላይነት መቆጣጠር ተችሏል።
ግፍ የወለደን :ግፈኞችን የምቀጣ የአንሻ ሰይድ ወድሞች ነን!!
©አፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ!
17/11/2018 ዓ.ም
የምስራቅ ወለጋ ዞን ከፍተኛ አመራር ርምጀ ተወሰደበት‼
የድሮው የሀሮ ሊሙ ወረዳ አስተዳዳሪና የአሁኑ የምስራቅ ወለጋ ዞን ወጣቶችና ስፖርት ጽፈት ቤት ሀላፊው አቶ ደቻሳ ገነቲ በዛሬው ዕለት ምስራቅ ወለጋ ዞን አንገር ጉትን ከተማ አስተዳደር ምሃል ከተማ ላይ በፋኖ የማያዳግም ርምጃ ከተወሰደባቸው የብልጽግና አመራሮች መካከል አንዱ ይህ ሰው ነው።
ሐምሌ 17/2018ዓ.ም
ቢዛሞ ሚዲያ
ተራሮቹን ያናወጠው የባሩድ ድምፅ
የሐምሌው ሰማይ በከባድ ደመና ተሸፍኗል፤ ነገር ግን ከሸዋ ሰማይ ስር፣ ከባሽና፣ ከሞፈር ውሃ እና ከቆብ አስጥል ተራሮች የሚወጣው ጭስ የክረምት ጉም አልነበረም የነጻነት፣ የጽናት እና የብረት እሳት እንጂ!
መነሻቸውን ከመንዝ አውራጃ—ከሞላሌ፣ ከወገሬ፣ ከመሀል ሜዳና ከዘመሮ አድርገው በአራቱም አቅጣጫዎች ለዘረፋና ለአጥፊ ግስጋሴ ወደ "መዘዞ" ያመሩት የጠላት 112ኛ እና 104ኛ ጥምር ጦሮች፣ ምድሪቱን በደም ሊያጨማልቋትና ንጹሃንን ሊያጋዩ ተንቀሳቅሰው ነበር። ነገር ግን በዚያ የፈተና ሰዓት፣ የተራሮቹ ዘበኞች እና የአማራ ህዝብ የቁርጥ ቀን ልጆች፣ የጠላትን ህልም አፈር ድሜ አብልተውት ውለዋል።
በጀግናው በአርበኛ ኢሳያስ ደመቀ (የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ምክትል ወታደራዊ አዛዥ)፣ ከዕዝ እና ከኮር አመራሮች ጋር በመሆን የጠላትን እንቅስቃሴ አስቀድሞ በመቃኘት የጦር ስልቱን በመንደፍ የአሳምነው ዕዝ 7/ለ70 ክፍለጦር አመራሮች ከጣርማበር እና ከሰላድንጋይ ተነሥቶ በሞፈር ውሃ ጅረት በኩል ሊያጠቃ የመጣውን የጠላት ኃይል በገደላማው መንገድ ላይ አፍነው በመያዝ ቅንድቡን እንዲመታ አድርገውታል።
የመሐመድ ቢሆነኝ ኮር ወንዱ አስቻለው ደሴ ክፍለጦር ከአመራር እስከ ታች ድርስ እስከ አሉ የፋኖ አባላት ድርስ የተሳተፉበት ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ በባሽና ከተማ ዙሪያና በቆብ አስጥል መስመር ከባድ ምት በመሰንዘር፣ የጠላትን ጥምር ጦር መውጫና መግቢያ አሳጡት። የሞፈር ውሃ እና የባሽና እሳት መጥመቂያ ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ላይ ምድሪቱ በከባድ መሣሪያ ድምፅ ተናወጠች። የጠላት ጥምር ጦር በቁጥር የበላይነት ለመግፋት ቢሞክርም፣ በአርበኛ ኢሳያስ ደመቀና በኮር እና በክፍለጦር አመራሮቹ ቀጥተኛ መመሪያ የፋኖ ተዋጊዎች ምሽጋቸውን ጥሰው እንደ አንበሳ በመነሳት ድባቅ መተውት ከቆብ አስጥል እስከ መዘዞ ከተማ መግቢያ፣ ከጣርማበር እስከ ሰላድንጋይና ሞፈር ውሃ ጅረት... እያንዳንዱ ሜዳና ሸንተረር ለጠላት ሰራዊት መውጫ የሌለው የእሳት አጥር የቆራጥነት ወኔ፣ የአማራ ልጅ ፋኖዎች የሜኒልክን ትንፋሽ ስንቅ አድርገው የጠላትን ሰራዊት እንደ ቅጠል ያራግፉት ጀመር።
የጠላት መደምሰስና የድል አበሳ በሞፈር ውሃና በባሽና ዙሪያ የተካሄደው ከባድና ታሪካዊ ትንቅንቅ በፋኖዎች ሙሉ የበላይነት የተጠናቀቀ ሲሆን የጠላት ሰራዊት እዳመጣጡ ተመቶ በርካታ ሙትና ቁስለኛ አስተናገደ፤ የተረፈውም ኃይል ተበትኖ ወደ ኋላ እንዲፈረጥጥ ተገዷል። በመጨረሻም የደረሰበትን ከባድ ምት መቋቋም ያቀተው የጠላት አዛዥ፣ በአርበኛ ኢሳያስ ደመቀና በጀግኖቹ የሽዋ ጠቅላይ ግዛት የፋኖ አመራሮች የታነቀበትን እሳት ማጥፋት አቅቶት፦ "ተጨማሪ ደጋፊ ኃይል በአስቸኳይ ከደብረ ብርሃን ላኩልን!" ሲል ሲማጸን ውሏል።
በጀግናው አርበኛ ኢሳያስ ደመቀ ብልሃተኛ አመራር፣ በኮር በክፍለጦር አመራሮቹ ቅንጅት እና በፋኖዎች የማይበገስ ጽናት፣ የመዘዞና የባሽና ምድር የጠላትን አላማ አክሽፋውት ውለዋል! #Dave #Amhara
+4
የአማራ ልጅ ፋኖ በታሪክ የጀመረውን የማንነት እና የህልውና ትግል ሳይጨርስና አላማውን ሳይመታ የቀረበት አንድም ታሪካዊ አጋጣሚ የለም። ፋኖ የሕዝብ ብሶትና የፍትህ ጥያቄ ወላጅ እንጂ የሥልጣን ፍላጎት ውጤት አይደለም።
በአሁኑ ወቅት የአማራን ሕዝብ በማንነቱ ምክንያት አንገት ለማስደፋት፣ የዘር ፍጅት ለመፈጸም እና የኢኮኖሚና የማህበራዊ መዋቅሩን ለማፍረስ አልሞ የተነሳው የአገዛዙ ሥርዓት፣ በአራቱም ማዕዘናት መካናይዝድ፣ የከባድ መሳሪያ እና የአየር ኃይል በመጠቀም ሰፊ ወረራ ሲፈጽም ሰንብቷል።
ሆኖም ግን የሕዝቡን አደራ እና አገራዊ ኃላፊነት የተሸከሙት፦
የቴዎድሮስ ዕዝ
የሚኒልክ ዕዝ
የበላይ ዘለቀ ዕዝ እና
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ጽጌ ዕዝ
በተቀናጀና በተደራጀ የተወርዋሪ ኃይሎቻቸው ምት የጠላትን ረጅም እጅ በመቁረጥ፣ የጠበቀውን የጦር ስልት በማክሸፍ ቅንድቡን መተው በመውተርተር ላይ ጥለውታል፤ የሜዳውን የበላይነትም ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥረውታል።
በግንባር የተከናነበውን መራራ ሽንፈት ለመሸፈን፣ የብልፅግና የሳይበር ሰራዊትና የፕሮፓጋንዳ በ#AI በመጠቀም የሐሰት ወሬዎችን እና የተቀናበሩ ምስሎችን በመንዛት ሕዝቡን ለማደናገርና ለማስደሰት ሲጣጣሩ ማየት ያስቃል። ይህ ዓይነቱ የሳይበር ሽብርና የሐሰት ፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ሥርዓቱ በወታደራዊው መስክ ሙሉ በሙሉ መሸነፉን እና የመጨረሻው የውድቀት ማበቂያ ላይ መድረሱን የሚያሳይ ግልጽ ማረጋገጫ ነው። Dave Amhara
ድል ለተበደለው የአማራ ሕዝብ!
ድል ለፋኖ!
ሰበር ዜና ‼️
ወደ " መዘዞ " ከአራት አቅጣጫ ለዘረፋ የተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ክፉኛ ተመታ!!
ሐምሌ/17/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ 7/ለ70 እና የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር አስቻለው ደሴ ክፍለጦሮች ወደ መዘዞ በተለያየ አቅጣጫ የተንቀሳቀሰውን የጠላት ኃይል በጋራ በመሆን፡ በመዘዞ ዙሪያ፣ በባሽና እና በሞፈር ውሃ አካባቢዎች ከፍተኛ ትንቅንቅ እያካሄዱ ይገኛሉ።
መነሻውን ከመንዝ አውራጃ ሞላሌ፣ወገሬ ፣መሀል ሜዳና ዘመሮ ያደረገውን የጠላት ኃይል፡ የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር ወንዱ አስቻለው ክፍለጦር ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ጀመሮ ከባሽ ከተማ ዙሪያ ከፋተኛ ትንቅንቅ እያደረጉ ይገኛል ከቆብ አስጥል እስከ መዘዞ ከተማ ድረስ ሁለቱም ክፋለጦሮች በቅንጂት ገጥመው ሲያራግፈው፡ የ112ኛ እና የ104 ጥምር ጦር አስካሁን ድረስ በከባድ ትንቅንቅ ላይ ይገኛሉ።
በሌላ ግንባር ማለትም፦ ከጣርማበር እና ከሰላድንጋይ በሞፈር ውሃ ጅረት ወደ መዘዞ የተንቀሳቀሰውን የጠላት ኃይል 7ለ70 ክፋለጦር እና መሐመድ ቢሆነኝ ኮር ወንዱ አስቻለው ደሴ ክፍለ ጦር ጠላትን እዳመጣጡ አያራገፉት ይገኛሉ። በዚሕ ከባድ ትንቅንቅ ጠላት ብዙ ሙትና ቁስለኛ ያስተናገደ ሲሆን ተጨማሪ ኃይል ከደብረ ብርሀን መጠየቁ ተሠምቷል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ !!
ፋኖ የጁምአ ሶላት ላይ!
ምድር ቃጤ በሆነችበት ውጊያ መኃል ቢሆኑም ሰዓቱ ከደረሰ የዝሁር፣ የፈጅር፣ የአሱር፣ የኢሻና የመግሪብ ስግደት ዝንፍ የማይልባቸው እነዛ ከምሽግ ምሽግ እየተወረወሩ የጠላትን ላንቃ የሚዘጉት፣ እነዛ ፍትሕ ርዕት አስፋኞች ኃያላን ፋኖዎች የሕዝባቸውን መከራ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማስቆም 11ኛው ሰዓት ላይ ደርሰዋል!!!!!
ፋኖ ...የሕልውና አደጋ ተጋርጦበት ለሚገኘው የአማራ ሕዝብ ብቻ ሳይሆን...በዚህ ፋሺስታዊ ኦህዴድ መር አገዛዝ በባርነት ስር የወደቀ ነፃነት ናፋቂ ትውልድ ሁሉ በጉጉት ይጠብቀዋል።
👉የአማራ ሕዝብን ሕልውና ያረጋግጣል፣ የሌሎች ኢትዮጵያውያንን መብት ባልተጋፋ መልኩ ጥቅምና መብቱን ያስከብራል።
👉በዚህ ፀረ ሕዝብ የአገዛዝ ስርዓት የመከራ ቀንበር የወደቀበት ኢትዮጵያዊ ሁሉ በጉጉትና በስስት ይጠብቀዋል።
👉የምስራቅ አፍሪቃን ጨምሮ የቀጠናውን መረጋጋት የሚፈልጉ ኃይሎች ሁሉ ተስፋ ያደርጉታል።
#ተስፋፊነትና ወራሪነት፣ ጥቅመኝነትና ጎጠኝነትን እንደአንድ መርህ ለሚጠቀመው እንዲሁም ለጥቂት ግለሰቦች ጥቅም ሲባል ብቻ የሚሊየን ድሀዎችን ጉሮሮ መዝጋት እንጂ ሀገር መምራት ያልቻለው የኦህዴድ ብልፅግና...በዚኸው የፋኖ ኃይል ብርቱ ክንድ ተቀጥቅጦ እንጦሮንጦስ ይወርዳል።
ተከሳሾች ከማረሚያ ቤት ባለመቅረባቸው በእነ ዮሐንስ ቧያሌው መዝገብ ላይ ብይን ለመስጠት ለጥቅምት ተቀጠረ
ዓርብ፣ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዮሐንስ ቧያሌው የክስ መዝገብ ላይ ተከሳሾች እንዲከላከሉ ወይም በነፃ እንዲሰናበቱ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጥሮ የነበረ ቢሆንም፣ የተወሰኑ ተከሳሾች በችሎት ባለመገኘታቸው ብይኑን ለማንበብ ለጥቅምት 6 ቀን 2019 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን የተከሳሾች ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለአዲስ ማለዳ ገለጹ።
ፍርድ ቤቱ ባስቻለው ችሎት የብይኑ ውሳኔ ተዘጋጅቶ የደረሰ ቢሆንም፣ ከማረሚያ ቤት መቅረብ የነበረባቸው የተወሰኑ ተከሳሾች ባለመገኘታቸው ምክንያት ብይኑ ሳይነበብ ቀርቷል።
ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ እንዳሉት፣ ተከሳሾቹ ወደ ችሎት ያልቀረቡበት ምክንያት ያልተገለጸ ሲሆን፤ በዕለቱ በችሎት ካልተገኙት መካከል ዶ/ር ዘሪሁን፣ ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ፣ መርጌታ በላይ አዳሙ እና ተከሳሽ ታደለ ይገኙበታል።
በሌላ በኩል፣ የዶ/ር ካሳ ተሻገር እና የጋዜጠኛ ቴዎድሮስን የስልክ ቁጥር “ሌላ ሰው እየተጠቀመበት ነው” በሚለው ክስ ላይ ኢትዮ ቴሌኮም ማጣራት አድርጎ በዕለቱ ምላሹን ለችሎቱ አቅርቧል።
ኢትዮ ቴሌኮም ለፍርድ ቤቱ በላከው ምላሽ፤ የሁለቱ ተከሳሾች የስልክ ቁጥሮች አገልግሎት ጊዜያቸው በማለፉ ምክንያት በተቋሙ ሕግና ደንብ መሠረት ለሦስተኛ ወገን መተላለፋቸውን ገልጾ፣ ቁጥሮቹን የተቀበሉትን ሰዎች ሙሉ ስም ከአያት ጋር አያይዞ ማሳወቁን ጠበቃ ሰለሞን አብራርተዋል።
በዚህም መሠረት ፍርድ ቤቱ በእነ ዮሐንስ ቧያሌው መዝገብ ላይ የቀረበውን ብይን ለማንበብ ለጥቅምት 6 ቀን 2019 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
በራያ ቆቦ ወረዳ ከ ሶስት ቀበሌ ማህበረሰብ ጋር ህዝባዊ ዉይይት ተደረገ!
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ እዝ በራያ ቆቦ ወረዳ ቃሊም ንዑስ ወረዳ ስር የሚገኙ የሦስት ቀበሌ ነዋሪዎችን በመሰብሰብ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ የህዝብ ውይይት አካሄድ።
በቀን 16/11/2018 ዓ.ም በተካሄደው በዚህ ህዝባዊ መድረክ፤ በወቅታዊ የፖለቲካ እና የጸጥታ ሁኔታዎች፣ በአማራ ህዝብ ታጋዮች ዓላማዎች እንዲሁም የብልፅግና አስተዳደር በህዝቡ ላይ እያደረሰ ባለው እና ሊያደርስ ባቀደው መጠነ-ሰፊ የዘር ማጥፋት ጭቆና ዙሪያ ከህዝቡ ጋር ጥልቅ ውይይት ተደርጓል።
የህዝቡ ጥያቄዎችና የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች
በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የአካባቢው ነዋሪዎች የገጠሟቸውን በደሎችና ያሉባቸውን ስጋቶች ያነሱ ሲሆን፣ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አንስተዋል።
ያነሷቸዉ ሃሳቦችም :-የብልፅግና አስተዳደር እያደረሰ ያለው በደል በተግባር እየታየ መሆኑን የጠቀሱት ነዋሪዎች፤ በቅርቡ በአዋስ ቀበሌ አርሶ ከመብላት ውጭ ምንም የማያውቁ ንጹሃን አርሶ አደሮችን ከቤተሰቦቻቸው ፊት ያለ ርህራሄ መረሸናቸውን እና ንብረታቸውንም ዘርፈው መሄዳቸውን በምሬት ገልጸዉ "አሁን የምንፈልገው ሁላችንንም አስታጥቁን፤ ይህን ስርዓት ዘር አጥፊና ዘራፊ አስተዳደር በአንድነት እንታገለው" በማለት ሙሉ ዝግጁነታቸውን ገልጸዋል።
የሰርጎ-ገቦች ጉዳይ፦ በመካከላቸው የሚገኙ የጠላት ሰርጎ-ገቦች ለህዝቡም ሆነ ለፋኖ ድርጅት ትልቅ ፈተና መሆናቸውን በመጥቀስ፤ ህዝቡና ታጋዩ በጋራ በተቀናጀ መልኩ በመያዝ አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድባቸው ጠይቀዋል።
በዚህም ከማህበረሰቡ ለተነሱት ጥያቄወች እና ጥቆማ የመድረኩ መሪዎች ህዝቡ ለትግሉ ያሳየውን ባለቤትነትና የቆራጥነት ስሜት ያከበሩ ሲሆን፣ የብልፅግና መንግሥት "ድርድር እና ምክክር" በሚሉ የማደናገሪያ አጀንዳዎች ህዝቡን ለማወናበድ የሚሰራውን ስልት ህዝቡ ነቅቶ ሊጠብቀው እንደሚገባ አሳስበዋል።
የመድረኩ መሪወች አክለውም የህዝቡ የህልውና ዋስትና ከሆነው ከፋኖ ጎን በመሰለፍ፣ የተጀመረውን የህልውና ትግል ከግብ ለማድረስ በቁርጠኝነትና በፅናት መታገል እንደሚገባ በመጠቆም መድረኩ አጠናቀዋል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!
አፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!
ሐምሌ17/11/2018ዓ'ም
ጋንታ መሪውን ጨምሮ የአገዛዙ ወታደሮች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ምኒልክ ዕዝን ተቀላቀሉ!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር በሚንቀሳቀስባቸው ቀጠናዎች ከውጊያ ጎንለጎን የጠላትን ሃይል ስቦ ማስከዳቱን አጠናክሮ ቀጥሏል ።
መነሻቸውን ሰሜን ወሎ ዞን ላስታ ወረዳ ሹምሽሃ/ ላሊበላ አየር ማረፊያ/ከተከማቸው የአፓርታይዱ አብይ አህመድ እና የምርኮኛው ብርሃኑ ጁላ ስብስብ ተስፋ ቆራጩ ወታደር በመነሳት 3 መሰረታዊ ወታደሮች አምስት ጥቁር ክላሽ ፣6 ኤፍዋን የእጅ ቦንብ፣ 3 የደረት ትጥቅ እና 840 የክላሽ ተተኳሽ በመያዝ 303ኛ አሳምነው ኮር 19ኛ(እሸት )ክፍለጦርን ተቀላቅለዋል።
ጋንታ መሪው የራሱን አንድ ጥቁር ክላሽ እና ዋርድያ ላይ የነበሩትን የሁለት ጓዶቹን ጥቁር ክላሽ ጨምሮ አጠቃላይ በድምሩ 3 ጥቁር ክላሽ በመያዝ ወደ ፋኖ በመግባት ትልቅ አርአያነትን ለሌሎች ቀሪ የአገዛዙ ወታደሮች አሳይቷል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መረጃውን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!
አፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!
ሐምሌ17/11/2018ዓ'ም
