fa
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

رفتن به کانال در Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

نمایش بیشتر
2 929
مشترکین
+224 ساعت
+3727 روز
+36730 روز
آرشیو پست ها
የጥንቃቄ መልእክት ለ201ኛ ክ/ እና ለ64ኛ ክፍለ ጦር ቴዎድሮስ ዕዝ ​በድሮማ እና በአካባቢው በሚገኙ የ64ኛ ክፍለ ጦር የመንቀሳቀስ ቀጠናዎች ላይ የአገዛዙ ኃይል ጥቃት ለማድረግ ዝግጅት እያደረገ
የጥንቃቄ መልእክት ለ201ኛ ክ/ እና ለ64ኛ ክፍለ ጦር ቴዎድሮስ ዕዝ ​በድሮማ እና በአካባቢው በሚገኙ የ64ኛ ክፍለ ጦር የመንቀሳቀስ ቀጠናዎች ላይ የአገዛዙ ኃይል ጥቃት ለማድረግ ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ስለተመለከተ፥ በቀጠናው የሚገኙ ሁሉም የወገን ኃይሎች ሊንከባለል የሚችልን ማንኛውንም ግብአት ለመከላከል እና የአካባቢውን ደህንነት ለማክበር ከወዲሁ ከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ እንዲቆሙ፤ የቅኝት ስራዎችን በማጠናከርና የመረጃ ልውውጥን በመቃኝት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ሁሉ አጠናቀው እንዲጠብቁ መረጃውን አዘውትሩ። ​09/12/2018 ዓ. ም

የፋሽስቱ አገዛዝ የ45ኛ የ46ኛ እና የ47ኛ ክፍለ ጦር አባሎች እየፈረሱ ፋኖን እየተቀላቀሉ ነዉ። የአገዛዙ ሰራዊት አባሎች እየፈረሱ የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ(አፋብን) ወሎ ቤተ አምሓራ ሚኒሊክ
+3
የፋሽስቱ አገዛዝ የ45ኛ የ46ኛ እና የ47ኛ ክፍለ ጦር አባሎች እየፈረሱ ፋኖን እየተቀላቀሉ ነዉ። የአገዛዙ ሰራዊት አባሎች እየፈረሱ የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ(አፋብን) ወሎ ቤተ አምሓራ ሚኒሊክ ዕዝ 101ኛ ኮርን እየተቀላቀሉ ይገኛሉ። የ47ኛ ክፍለ ጦር አምስተኛ ሻሐቃ አባል አንድ ጥቁር ክላሽ ከ200 የክላሽ ተተኳሽ ጋር በመያዝ እና ከ45ኛ ክፍለ ጦር አምስተኛ ሻለቃ ሁለት አባሎች ሁለት ጥቁር ክላሽ፣240የክላሽ ተተኳሽ እና አምስት F1 ቦንብ በመያዝ 101ኛ ኮር 15ኛ ክፍለጦርን ሲቀላቀል የ46ኛ ክፍለ ጦር የአንደኛ ሻለቃ የሻለቃ አመራሩ አጃቢ 110 የክላሽ ተተኳሽ አንድ ጥቁር ክላሽ እና የሻለቃውን የመገናኛ ሬድዮ በመያዝ 11ኛ ክፍለጦርን ተቀላቅለዋል። በአጠቃላይ ከ45ኛ፣ከ47ኛ እና 46ኛ ክፍለ ጦሮች አፋብን ወሎ ቤተ አምሓራ ሚኒሊክ ዕዝ 101ኛ ኮርን አራት(4) ጥቋቁር ክላሽ ሶስት መቶ አስር(550)የክላሽ ተተኳሽ አምስት F1 ቦንብ አንድ(1) የመገናኛ ሬድዮ በመያዝ ተቀላቅለዋል ሲል 101ኛ ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃዉን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!! ነሀሴ 09/2018 ዓ.ም

በአማራ ፋኖ ትግልና በሌሎች የትጥቅ ድርጅቶች መካከል ሊደረግ ስለሚችል ትብብርና አጋርነት አዲስ አተያይና ከባድ ትችት ተሰነዘረ። የአፋብን ወሎ ቤተአማራ ምኒሊክ እዝ ከፍተኛ አመራር የሆነው አርበኛ አበበ ፈንታው፣ ሻለቃ ዳዊት ወልደ ጊዮርጊስ ወቅታዊውን የትብብር አካሄድ አስመልክተው የሰነዘሩትን ሐሳብ በመቃወም ሰፊ ማብራሪያ አውጥቷል። ​አርበኛ አበበ ፈንታው እንደገለጸው፣ ሻለቃ ዳዊት ወልደ ጊዮርጊስ በአፋብን ምስረታ ምክክር ወቅት በታዛቢነት ከሁሉም የፋኖ አመራሮች ጋር የመቀራረብና የመተዋወቅ ዕድል ነበራቸው፤ ስለዚህም ጉዳዩን ከአንዳንዶቹ ጋር በቀጥታ የመምከር ወይም የማማከር ዕድሉ ነበራቸው። ​የአርበኛ አበበ ፈንታው ዋና ዋና ትችቶችና ነጥቦች ​የአቀራረብ ክፍተት: ደውሎ ጉዳዩን የማማከር ዕድል ባያገኙ እንኳ፣ ፅሑፍ አዘጋጅተው ለፋኖዎቹ የማጋራት አማራጭ እንደነበራቸው አርበኛው አንስተዋል። ዛሬ የትግል አመራሮች ወጥተው "በኢትዮጵያ ያሉ የትጥቅ ድርጅቶች በሚተባበሩበት አግባብ ላይ እየመከሩ ነው፤ የደረሱበትንም በቅርብ ያሳውቃሉ" ሲሉ፣ አንዲት አጭር አንቀፅ በማኅበራዊ ሚድያ መለጠፍ የተቃውሞ ጩኸቱን ከመቀላቀል ያለፈ አቋም የማስቀየርም ሆነ ግንዛቤ የመፍጠር አቅም እንደሌለው ተመላክቷል። ​የወንጀል ማጠብ ስጋትና ፍትሕ: "በአማራ ላይ ሁለንተናዊ ጥቃት የፈፀሙ ጠላቶች ናቸው" በሚል አውድ፣ የሚፈጸም ትብብርና አጋርነት የተጣማሪ ኃይሎችን "ወንጀል ማጠብ" እንዳይሆንና ተጠያቂነትን በሚያረጋግጥ መልኩ እንዲፈጸም ማሳሰብ ተገቢ መሆኑ ተገልጿል። የአማራ ብሔራዊ ትግል አንዱ ትልቁ አንጓ "ፍትሕና ርትዕን ማረጋገጥ" መሆኑም ተነስቷል። ​የአዋቂ ምክር አስፈላጊነት: ሕዝብ ስለትብብር ትክክለኛ ግንዛቤ እንዲይዝ ከፈለጉ፣ ከአንዲት ብጣቂ ልጥፍ ይልቅ ዕድሜ ልኩን በፖለቲካ የኖረ ሰው ጉዳዩን በጥልቀት ሊያስረዳው ይገባ ነበር ብሏል። በዚህም መሠረት ብድግ ብሎ "ከእገሌ እንዳትተባበር" ከማለት ይልቅ፡ ​ትብብርና አጋርነት ምንድን ነው? ​የፀረ-አገዛዝ ታጋይ ድርጅቶች እና አገዛዙ ምንና ምን ናቸው? ​መተባበርና አለመተባበር ምን ማለት ነው? ​ለድል እና ከድል ማግስት ምን ተጽዕኖ አለው? ምን ሊያስከትል ይችላል? ​ጉዳዩ በምን አግባብና ሁኔታ መታየት አለበት? የሚሉ ሰፋ ያለ አውድ ያላቸው ነጥቦችን የያዘ "የአዋቂ ምክር" ቢቀርብ የቀረውም አንባቢ ግንዛቤ ማግኘት እንደሚያችሁ ተብራርቷል። ​የትብብር አውድና የድል ማግስት እይታ ​የአማራ ትግል በድል ውጤቱ የማንወደውን የፖለቲካ ኃይል ይዞ ትግራይን ከኢትዮጵያ መነጠል እንዳልሆነ አርበኛ አበበ ፈንታው አስገንዝበዋል። አገዛዙ የሕልውና ጥቃት ከፍቶብኛል የሚሉ አካላትን የመታገል መብት ፈቃጅና ከልካይም አለመሆናችንን ጠቅሶ፣ አገዛዙን የሚታገሉ አካላት በጎንዮሽ ቅራኔ አራት ኪሎን ለመቆጣጠር ከመፎካከር ይልቅ መተባበር ጤናማ ሽግግር እንደሚፈጥር አጽንኦት ሰጥቷል። ​አማራው በድል ማግስት አኩራፊ በመፍጠር ወታደራዊ ትጥቅ ትግልን ማስቀጠል ሳይሆን፣ ብዙሃኑን የሚያቀራርብ ፖለቲካዊ አውድ መፍጠርና ቅራኔዎችን ከአገራዊ ቀውስነት በታች ማድረግ እንደሚገባው ተጠቁሟል። የሚኖር ትብብርም "የወንጀል አጠባ" ይሉኝታ የሚፈጥርም አይሆንም የሚል ተስፋ እንዳለው ገልጾ፣ ድሉን የተሟላ የሚያደርገው የሕልውና ጥቃቱን ከመመከት በተጨማሪ ባለፉት ዓመታት ለተፈጸሙ ግፎች ሁሉ ፍትሕ ርትዕን (የወንጀል ፍትሕ፣ የካሳና እርምት ፍትሕን) ከማንም ጋር ሆኖ ማረጋገጥ እንደሆነ አበክሮ አሳስቧል። ​ሰነዱ በውጤታማነት "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!" በሚል መፈክር ተጠናቆ ለአንባብያን ደርሷል። አርበኛ አበበ ፈንታው

አርበኛ ደሳለኝ ሲያስብሸዋ የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዋና ሰብሳቢ

አርበኛ አበበ ሙላቱ የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ !!

አፋብን 1ኛ ምኒልክ ዕዝ ዕዝ የድላታ ወረዳ ጊዚያዊ የሲቪል አስተዳደር መዋቅር በዛሬዉ ዕለት አዋቀረ!! ​አፋብን 1ኛ ዕዝ በተቆጣጠራቸዉ ወረዳወች ጊዚያዊ የሲቪል መዋቅርሮችን እየዘረጋ እና እያቋቋመ የህዝብን ጥያቄ እና አገልግሎቶችን ያለምንም እንከን እንዳይቋረጡበት እየሰራ ይገኛል አሁንም በደላንታ ወረዳ በአካባቢው ህዝባዊ አገልግሎቶችንና አስተዳደራዊ ተግባራትን በላቀ ቅንጅት ለመምራት፣ የህዝቡን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለማስከበር እንዲሁም ዘላቂ አስተዳደራዊ መረጋጋትን ለመፍጠር ያለመው የድላታ ወረዳ ጊዚያዊ አስተዳደር በፋኖ መዋቅር ስር በይፋ በዛሬዉ ዕለት ማለትም በቀን 8/12/2018ዓ.ም ተዋቅሯል። ​ይህ አዲስ የጊዚያዊ አስተዳደር አደረጃጀት በአካባቢው የሚገኙ ህዝባዊና ማህበራዊ ተቋማት አገልግሎታቸውን ያለአንዳች መቋረጥ ለህብረተሰቡ እንዲሰጡ ለማስቻል፣ የህዝቡን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ሰላማዊ ማድረግ እና የልማት፣  እንዲሁም የፀጥታ ስራዎችን በበላይነትና በባለቤትነት ለመምራት የታሰበ ነዉ። የዳለንታ ወረዳ  የጊዚያዊ ሲቪል መዋቅር ሲዋቀር የ11ኛ ምኒልክ ዕዝ ም/ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ስንታየሁ ተስፉ  እና ህዝብ አስተዳደር መምሪያ አርበኛ አበበ ቀዮ ተገኝዋል። የወረዳውን አጠቃላይ እንቅስቃሴ በበላይነት እንደሚመሩ ኃላፊነት የተሰጣቸዉ አመራሮች እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፡ 1. አርበኛ በላይ ሰጠ የጊዚያዊ አስተዳደር መዋቅር ዋና  አስተዳዳሪ 2.አርበኛ መኳንንት ክፍሌ ምክትል አስተዳዳሪ ​3.አርበኛ ወንዶሰን ምክሪ — አስተዳደር ፅህፈት ቤት ሃላፊ ​4. አስር አለቃ ኪዳኑ አስናቀ — አስተዳደር እና ፀጥታ ፅህፈት ቤት ሃላፊ 5. አርበኛ ሲሳይ ጥላሁን — ገንዘብ ፅህፈት ቤት ሃላፊ ​6. አርበኛ ሞላ ጉበና — ከተማ አስተዳደር ፅህፈት ቤት ሃላፊ ​7.አርበኛ ኤፍሬም በቃቢል — ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ሲሆኑ በአዲስ የተዋቀረዉ የደላንታ ወረዳ ጊዚያዊ አስተዳደር መዋቅር የወረዳውን የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ በማጠናከር፣ የአካባቢውን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ በመጠበቅ እና ህዝባዊ ጥያቄዎችንና ፍላጎቶችን በማስተባበር ረገድ የነቃ ሚና እንደሚኖራቸዉ ተግልጿል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!!          ነሀሴ :- 08/ 2018 ዓ/ም

ነሐሴ 08/2018 ዓ.ም አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ​፩ኛ ኮር 23ኛ ነበልባሉ ክፍለ ጦር አመራሮች ከፎገራ ወረዳ ጊዜያዊ አስተዳዳሪዎች ጋር ውይይት አካሄደ ። ነሐሴ 08/2018 ዓ.ም ነበልባሉ 23ኛ ክፍለ ጦር አመራሮች ከፎገራ ወረዳ የሲቪል ጊዜያዊ አስተዳዳሪዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል።በውይይቱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እና የትግሉን ህዝባዊ ደጀንነትን በተመለከተ በጥልቀት ውይይት ተደርጎበታል ። ​በውይይቱ ወቅት የገኙት የወረዳው ጊዜያዊ አስተዳዳሪዎች የሕዝብ ጠላት የሆነውን የብልጽግና ሥርዓት ሙሉ በሙሉ ለመደምሰስ የሚያስችል ጠንካራ የሰራዊት ቁመና ላይ እንዲገኝ የሚያስፈልገውን ድጋፍና ተቋማዊ ዝግጅት እንደሚያደርጉ እና ከዚህ ጎን ለጎን የህዝባችንን የመልካም አስተዳደር ችግር መፍታት በሚያስችል ቁመና ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። ​በውይይቱ ላይ የተገኙት የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ዋና ሰብሳቢ አርበኛ አመኑ አለማንተ በተነሱ ሀሳቦች ላይ አስተያየትና የቀጣይ ተግባራት አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል ሲል መረጃውን ያደረሰን የክፍለ ጦሩ የህዝብ ግንኙነት ነው። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

የፍቅርና የጽናት ህያው ምስክር፦ ጀግናው አበባው ​አንዳንዶች ይሄዳሉ… ነገር ግን አሻራቸውን በልባችን፣ ስማቸውን በታሪካችን፣ ፍቅራቸውን ደግሞ በነፍሳችን ውስጥ ጥለው ያልፋሉ። የዛሬ ዓመት በዚች ዕለት… ሰማይ ከብዶ፣ ምድር አዝና፣ የብዙዎቻችን ልብ በሐዘን የተሰበረበት ዕለት ነበር። የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር አለኝታ፣ የጓዶቹ ጋሻና መኪያ የነበረው አበባው፣ ከራሱ ህይወት ይልቅ የሌሎችን ህይወትና የአማራን ክብር አስበልጦ ውድ ነፍሱን የገበረበትን አንደኛ ዓመት መታሰቢያ የምናስብበት ዕለት ነው። ​የፍርሃት የለሽነትና የፍቅር ጥግ ​አበባው ለሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር አባላት ባልደረባ ወይም ብቻ አልነበረም፤ በጨለማ ውስጥ ተስፋ የሚያበራ ችቦ፣ በደከሙ ጊዜ ደግሞ እጅን ዘርግቶ የሚያነሳ ትልቅ ወንድም ነበር። ​በእሳትና በባሩድ መካከል ሳለ እንኳ የሌሎችን ህይወት ለማዳን ያሳየው ፍርሃት የለሽነት፣ በልቡ ውስጥ የነበረው ጥልቅ የሀገርና የጓዶቹ ፍቅር ውጤት ነበር። እሱ ህይወቱን የሰጠው ስለወደደ ነው። ስለ ሀገሩ ሰላም፣ ስለ ወገኑ ደኅንነት! ጀግና አይሞትም፤ ታሪክ ይሰራል! ​አበባው ዛሬ በአካል ከአጠገባችን አይኑር እንጂ በተከፈለው መስዋዕትነት በምናገኘው እፎይታ ውስጥ አለ፣ በጓዶቹ ትዝታና በታሪክ ድርሳናት ውስጥ በወርቃማ ቀለም ተጽፎ ይኖራል፣ ​በእያንዳንዳችን ልብ ውስጥ ታሪኩ ዘላለም ሲነገር ይኖራል። ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ አሳልፎ ከመስዋት በላይ የሚበልጥ ፍቅር የለም። አበባው ያንን ታላቅ ፍቅር በደም አሻራው አሳይቶናል! ​የክብር ማስታወሻ ​በዚህ የዛሬ ዓመት መታሰቢያው ዕለት፣ ለአበባው ወላጆች፣ ለቤተሰቦቹ፣ አብረውት ለተዋጉት የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር ጀግኖችና ለወዳጆቹ ሁሉ ፈጣሪ መጽናናትን እንዲሰጥ እንመኛለን። ​“አበባው ሆይ… ስምህ በክብር ይጠራል፤ ታሪክህ በትውልድ ይወደሳል፤ አሻራህ ደግሞ በልባችን ውስጥ ዘላለም ሲያንሸባረቅ ይኖራል። ነፍስህ በገነት ትረፍ፤ ጀግንነትህና አጋርነትህ በልባችን ውስጥ ዘላለም ህያው ነው! #Dave #Amhara

በደቡብ ወሎ ዞን ጉሽ ሜዳ ቀበሌ ህዝባዊ ዉይይት ተካሄደ! ​ በጉሽ ሜዳ ቀበሌ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ በተገኘበት አጠቃላይ ህዝባዊ ስብሰባ በዛሬዉ ዕለት ማለትም ነሃሴ 8/2018 ዓ.ም የምኒልክ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተካሂዷል። ​በዚህ አበይት ህዝባዊ መድረክ ላይ የትምህርትና ስልጠና መምሪያ ምክትል ኃላፊ፣ የህዝብ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ እንዲሁም የ11ኛ ኮር ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ጨምሮ  የሲቪል መዋቅር  አመራሮች ተገኝተው ከህዝቡ ጋር ሰፊ ውይይት አድርገዋል። በዕለቱ የተደረገውን ስብሰባ በተመለከተ እንደተገለጸው፣ የህዝቡ አቀራረብና ተሳትፎ እጅግ ከፍተኛ እና በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች በነቃ ሁኔታ ተሳትፈዋል። ​በውይይቱ ወቅት የህዝቡን ስሜትና አቋም ያንጸባረቁ አንድ የአካባቢው አባት እንደገለጹት፣ ቀደም ሲል የነበረውን ሁኔታ በማስታወስ «እስካሁን ድረስ በእንደዚህ አይነት መንገድ ግንዛቤ ተፈጥሮልን አናውቅም» በማለት የተጀመረው የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና ህዝቡ ሁልጊዜም  ከፋኖ ጎን እንደሚቆም ገልጸዋል። ቀደም ሲል የነበረው አሰራር የተበታተነ እንደነበር በማስታወስ፣ የአሁኑ የፋኖ መዋቅር፣ የተስተካከለ የመሪነት ቁመና እና ፖለቲካውን በቅጡና በወርዱ የተረዳ አመራር ያለው መሆኑን በመጥቀስ «ድርጅታችን አፋብን መድኃኒታችን እና መዳኛችን ነው» ሲሉ አደንቀዋል። ​ ሰራዊቱ አሁንም ከማህበረሰቡ ጋር ያለዉን ጥሩ ዲሲፕሊን አሁንም አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። ​በመጨረሻም ህዝቡ በሎጂስቲክስም ሆነ በሌሎች አስፈላጊ ነገሮች ሁሉ  ከሰራዊቱ ጎን በመቆም አብሮ ለመሰለፍ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!!          ነሀሴ :- 08/ 2018 ዓ/ም

በአበሽጌ ወረዳ ዳርጌ ቀበሌ ላይ ወጣቱ ግዛው የተባለ ዜጋ በታጣቂዎች መገደሉ ተሰማ። ግድያው የተፈጸመው ሚሊሻው ከስራ ውሎ ምሽት በሁለት ሰዓት (2:00) ወደቤቱ በሚመለስበት ወቅት ተጠብቆ እንደነበር ታውቋል። የተገደለው ወጣት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሚና የተገደለው ወጣት ግዛው ቤተሰብ የሚያስተዳድር፣ ከራሱ አልፎ ለ12 ዜጎች የስራ እድል በመፍጠር የኢኮኖሚእንቅስቃሴ እንዲፈጠር ድርሻውን እየተወጣ የሚገኝ ታታሪ ወጣት እንደነበር ተገልጿል። ይሁን እንጂ ይህ ተስፈኛ ወጣት በግፍ ሕይወቱ ሲያልፍ፣ ገዳዩ አካል ግን ምንም ዓይነት ጥያቄና ከለላ ሳይደረግበት በነፃነት እንደሚንቀሳቀስ ተመላክቷል። በግፍ የተገደሉ ወጣቶች እና በቤተሰቦች ላይ የሚደርሰው ጫና በአካባቢው በርካታ ንጹሃን ዜጎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን መረጃዎች ያሳያሉ። ከዚህም በላይ አሳዛኙና አስገራሚው ጉዳይ፣ የተጎጂዎች ቤተሰቦች የደረሰባቸውን ሀዘን በነፃነት እንዳይወጡ መከልከላቸው ነው። በቅርቡም ሶስት ወጣቶች በአሰቃቂ ሁኔታ ተጨፍጭፈው ለአውሬ መጣላቸው የተዘገበ ሲሆን፤ የሟቾች ቤተሰቦች “የተገደሉት ‘ሽፍታዎች’ ናቸው ብላችሁ ማስተባበያ ካልሰጣችሁ በእናንተም ላይ እርምጃ እንወስዳለን” ተብለው እየተዛተባቸው እንደሚገኙ ትናንት መሰረት ሚዲያ ዘግቧል። ጉዳዩን አስመልክቶ የሚመለከታቸው አካላት ምላሽ እና የሰብአዊ መብት ጥበቃ ክትትል እንዲደረግበት ጥሪ ቀርቧል።

➤በወለጋ ንፁሃንን ጨፍጭፎ የብሔር ግጭት ለማስነሳት ሞክሯል እንጅ ፋኖ እና OLA ዜሮ አድርገዉታል። ➤ፋኖ ንፁሃን ኦሮሞዎችን አልነካም የወለጋ ፋኖዎችም እዚያው ወለጋ ተወልደዉ ያደጉ ጥሩ የተግባቦት
➤በወለጋ ንፁሃንን ጨፍጭፎ የብሔር ግጭት ለማስነሳት ሞክሯል እንጅ ፋኖ እና OLA ዜሮ አድርገዉታል። ➤ፋኖ ንፁሃን ኦሮሞዎችን አልነካም የወለጋ ፋኖዎችም እዚያው ወለጋ ተወልደዉ ያደጉ ጥሩ የተግባቦት ክህሎት (Good communication skill) ያላቸዉ እና  ኦሮሞኛ የሚናገሩ ናቸዉ። ➤ኢትዮጵያዊን ሲተባበሩ የሚፈርስ ብልፅግና የሚባል ጨቋኝና ገዳይ አገዛዝ እንጅ፤የምትፈርስ ኢትዮጵያ የለችም። ➤እኛ ተለጠፊም ተላላኪም አይደለንም የትብብሩ መሪዎች ነን። አርበኛ አስረስ ማረ ስለትብብሩ የተናገረው

የ7/70 ክፍለ ጦር ተሃድሶ መርሃ ግብርን በተመለከተ የተላለፈ የምስጋና መልዕክት!! ነሐሴ 08/2018 ዓ.ም በቀን 07/12/2018 ዓ.ም ለነበረው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ 7/70 ክፍለ ጦር ሁለንተናዊ የተሀድሶ መርሃ ግብር ለተገኛችሁ በሙሉ፦ ♥️የተከበራችሁ የሀይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች‼️ ♥️የተከበራችሁ የድርጅታችን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) አመራሮች❗️ ♥️የተከበራችሁ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አመራሮች❗️ ♥️የተከበራችሁ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የኮር አመራሮችና የአጋር ክፍለ ጦር አመራሮች‼️ 👏ጥሪ የተደረገላችሁ የተከበራችሁ እንግዶቻችን❗️ ♥️የተከበራችሁ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የ7ለ70 ክፍለ ጦር አመራሮች እንዲሁም የሰራዊት አባሎቻችን በሙሉ በጉጉት ስንጠብቀው ለነበረው ለተበሰረው ልዩ ዝግጅት እንኳን ደስ አላችሁ‼️ 👏ውድ የዚህ ልዩ የተሃድሶፕሮግራም ተሳታፊዎች በሙሉ: ከሁሉ አስቀድሜ እስከ አሁኗ ሰዓት የትግል ቆይታችን ድረስ ለአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ የማይተካ ውድ ህይወታቸውን ለከፈሉ የትግሉ ሰማዕታት ያለኝን ታላቅ አክብሮት በስመ ገናናው 7ለ70 ክፍለ ጦራችን ስም መግለፅ እወዳለን። 👉ትላንት ከጅምሩ አብረን የተዋደቅን የተከበራችሁ ጓዶች፤ ዛሬም በትላቱ መንፈስ ለታላቅ ብስራት ተከስተናል። ➯በአንድ አይነት ተነሳሽነት!! ➯በአንድ አይነት ፍላጎት!! ➯በአንድ አይነት ቅንነት!! ➯በአንድ አይነት ታማኝነት!! ➯በአንድ አይነት ግልፀኝነት!! ➯በአንድ አይነት ተጠያቂነትና ተግባራዊነት መሰዋዕትነት!! ከትግሉ ሰማዕታት የተረከብነው የቃልኪዳን አደራ በመጠበቅ፣ በውድቀቱ ዋዜማ አመሻሽ ላይ የሚገኘውን ይህንን የበሰበሰና የነቀዘን ስረዓት ከሌሎች ወንድም እህቶቻችን ጋር በጋራ አብረን ሆነን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከምድረ ገፅ ነቅለን የምንጥልበት የአድነት መንፈስና መነቃቃት የድል ዜና ያድርግልን ዘነድ ልባዊ መልዕክታችንን መግለፅ አወዳለን። " ክብር ለትግሉ ሰመዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የ7ለ70 ክፍለ ጦር

ነሐሴ 08/2018 ዓ.ም ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 208ኛ ራስ አሞራው ውብነህ ኮር፣ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች፣ የኮር እና ጥሪ የተደረገላቸው የክፍለ ጦር አመራሮች በተገኙበት ስፋትና ጥልቀት ያለው የምክክርና የግምገማ መድረክ አካሂዷል። በዚሁ መድረክ ላይ የዕዙ ልዩ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አስፋው ሰርፀ ፣ የሕዝብ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ንጉሱ አዱኛ፣ የኦዲትና ቁጥጥር መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አለሙ መለሰ እና ሌሎች የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች፣ የ208ኛ ራስ አሞራው ውብነህ ኮር ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ወርቁ እና ሌሎች የኮርና የሦሥት ክፍለ ጦር ስራ አስፈጻሚዎች ማለትም :- ➛ ዘራይ ክፍለ ጦር ፤ ➛አያሌው ብሩ ክፍለ ጦር እና ➛ሰሜን ብርቅዬ ክፍለ ጦር ስራ አስፈጻሚዎች የተገኙ ሲሆን፣ ውይይቱም ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም ይፋ የተደረገውን የጎንደርን አንድነት ለማብሰር የተኬደበትን ዕልህ አስጨራሽና ከፍተኛ መስዋዕትነት የተከፈለበትን ሂደት በመገምገም የተገኘውን አንድነት አጽንቶ ማስቀጠል እና ኮሩ በቀጣይ ሊከውናቸው የሚገቡ ተግባራትን በዝርዝር ማቀድ ላይ ያተኮረ ነበር። ​በውይይቱ ወቅት በተቋሙ ስም የሚደረጉ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን በጥብቅ የተገመገመ ሲሆን፣ በግል ፍላጎትና ጥቅም ተነሳስተው ተቋማዊ ሕግና መርህን ሳይከተሉ በኮሩ ስም የሚሰጡ ማንኛቸውም የግለሰብ መግለጫዎች ኮሩን እንደማይወክሉ አረጋግጧል። ይህን መሰል ስርዓት-አልበኝነትን የሚከተሉ ግለሰቦችን ኮሩ በጥብቅ እንደሚታገላቸው የተገለጸ ሲሆን ፣ ሁሉም በኮሩ ስር ያሉ ክፍለ ጦሮች ለሚሰጣቸው ወታደራዊ ግዳጅ እራሳቸውን ብቁ እንዲያደርጉና ዋጋ የተከፈለበትን ተቋማቸውን እንዲጠብቁ ጥብቅ መመሪያ ተላልፏል። ​በዚህ የውይይት መድረክ የተሳተፉት የዕዙ አመራሮች አንድነታችን በብዙ ጀግኖች መስዋትነት፣ደምና ላብ የተገኘ መሆኑን በመግለጽ፣ ይህን መስዋዕትነት የማያከብሩ፣ ዕዝና ተቋማዊ ሰንሰለትን የማይከተሉ እንዲሁም ከትግሉ ይልቅ የግል ፍላጎታቸውንና ስሜታቸውን የሚያስቀድሙ አካላት ከሰራዊቱ እና ከሕዝቡ ተቃራኒ የቆሙ በመሆናቸው ልንታገላቸው እንደሚገባ አስምረውበታል። በተጨማሪም በተቋማዊ አሰራር ላይ ቅሬታ ያለው ማንኛውም አካል በየቁጥቋጦው ስር ከመግለጽ ይልቅ ድርጅታዊ እና ተቋማዊ መርህን ተከትሎ ቅሬታውን ለዕዙ ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ማቅረብ እንዳለበት እና የመፍትሔ አካል መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። ስለሆነም የሰራዊቱን ወታደራዊ ዝግጅትና ተቋማዊ አወቃቀር ማጠናከርን፣ ለቀጣይ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ግዳጆች ሙሉ ዝግጁነት መፍጠርን እንዲሁም ከሕዝቡ ጋር ያለውን ፖለቲካዊና ማህበራዊ ቁርኝት ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር የተጣለብንን ህዝባዊ ኃላፊነት በብቃት መወጣትን ያካተቱ ወሳኝ የቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተቋጭቷል ። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ