ደራሲው...∞
رفتن به کانال در Telegram
1 350
مشترکین
+124 ساعت
+187 روز
+11430 روز
آرشیو پست ها
1 350
ያኔ ልጅ እያለሁ በጨዋታ መሀልና በጓደኞቼ ወይም ለጓደኞቼ ይሰሙኝ የነበሩት ስሜቶች አዋቂነቴን ይነጥቁኛል ብዬ አስቤያቸው አላውቅም ነበር!😔.....loading
1 350
ያኔ ልጅ እያለሁ በጨዋታ መሀልና በጓደኞቼ ወይም ለጓደኞቼ ይሰሙኝ የነበሩት ስሜቶች አዋቂነቴን ይነጥቁኛል ብዬ አስቤያቸው አላውቅም ነበር!😔.....loading
1 350
ምናልባት ይስሐቅ ልጁን ባይወጋውኮ ሕይወታቸው...
ምናልባት እኔ አሁን የሆንኩትን ባልሆን ኑሮ እራሴን እጠላው ነበር? ወይስ...
ምናልባትም ሕይወትን በAccept እንጂ በAvoid ማሸነፍ አይቻል ይሆናል....
ይታያችሁ እንግዲህ ይሄንን የማስበው maths ፈተና ላይ ቁጭ ብዬ ነው🤦♂
1 350
አሪፍ የሆነ ቻናል ልጠቁማቹ 𝙸𝚗𝚜𝚒𝚐𝚑𝚝 𝚀𝚞𝚘𝚝𝚎𝚜 📖 ይሰኛል አሪፍ የሆኑ የፍልስፍና ሀሳቦች ወጎች አስተማሪ ፁፎች ከመፀሀፍ ውስጥ የወጡ አጫጭር ፁፎች የሚለቀቅበት አሪፍ ቻናል ነው ለመቀላቀል
ከፈለጋቹ አሁኑኑ join በሉ👇
https://t.me/InsightQuotes
https://t.me/InsightQuotes
https://t.me/InsightQuotes
1 350
ምናለ ትንሽ ብፀፀትበት.. እኔን ለመግደል ምን አስቸኮለው... ምናለ ትንሽ አዝኜላት.. ምናለ ይቅር በይኝ እህቴ እህቴ እንድል ትንሽ ደቂቃ ቢሰጠኝ እያልኩ ለመሞት ስዘጋጅ ዘፍ ብሎ የሚወድቅ ነገር ሰማሁ...
ዞር ብዬ ሳይ ባሏ እራሱን በሽጉጥ ገድሏል... ደነገጥኩ ሰራተኛዋና ልጆቹ ይጮሀሉ.. እኔ በድንጋጤ... እዛው ደርቄ እንደቀረሁ... ፖሊሶች ያዙኝ...
ምንም ቢፈረድብኝ ግድ አይሰጠኝም ነበር... አላምንም ያልኩት ይመስል አንዱ ፖሊስ "እነሱን ለበቀል ብለህ እንደገደልካቸው ብታምን ነው የሚሻልህ" እያለ ይደበድበኛል
ፍርድ ቤት ቀርቤ "እኔ አልገደልኳቸውም ሁለቱም እራሳቸውን ነው ያጠፉት ግን አልገደልኩም ብዬ አልከራከርም ምክንያቱም ከዚህ ብወጣም ምንም የምኖርበት ጉዳይ የለኝም!" አልኩኝ ዳኛው እኔ አልገደልኩም ላልኩበት ነገር ማስረጃ ማቅረብ አለመቻሌንና ከዚህ በፊት በግድያ ሙከራ መታሰሬን ጠቅሰው እድሜ ልክ ፈረዱብኝ...
እንደእህቴ ሕይወትንም አልረዳት አልኩ መሰለኝ አጥፍቼ የታሰርኩት አምስት አመት ለድድብናዬ አልበቃት ብሎ እድሜ ልክ በወህኒ ልታስተምረኝ ካለጥፋቴ እስር ቤት አስወረወረችኝ!
አይ ሕይወት እንደ እኔ ደደብ ነገር ናት እንዴ ሰዎችን ለማስተማር ምን አደከማት አሁን.. እኔ የሰናፍጭ ቅንጣት ታክል ትምህርት ጠይቄያት ነበር? ምን እንዲህ ያደርጋታል...
በታሰርኩ በወሩ... በይግባኝ ፍርድ ቤት ቀረብኩኝ... በዳኛው ፊት የእህቴ የቤት ሰራተኛ የነበረችው ሴት መናገር ጀመረች...
በጣቷ ወደፖሊሱ እየጠቆመች "ይሄኛው ፖሊስ ልክ መኝታ ቤት እንደገባ ከመሬቱ ላይ ወረቀቱን አነሳና ትንሽ አንብቦ ይሄንሰ ወረቀት አቃጥይው ብሉ ሰጠኝ.. እኔ በስአቱ ደንግጬ ስለነበር ከሽርጤ ጋር እቃ ቤት ሸጉጬው ወደሚያለቅሱት ሕፃናት ነበር የሄድኩት
በቀደም ለት ቤት ሳፀዳ ነው አግኝቼ ለጎረቤት ሳሳያቸው እግዜር ይስጣቸውና ይግባኝ እንድጠይቅ እንዲሁም ለእነዚህ ሕፃናት ከእሱ የተሻለ ዘመድ እንደሌላቸውና እሱ እንዲያሳድጋቸው እንዲፈታ ጠይቂ ብለው ወደዚህ የሰደዱኝ!" አለች... መፈታቴ አይደለም ግን የእህቴን ልጆች ለማሳደግ የቅርብ ዘመድ እኔ ብቻ መሆኔ አስደሰተኝ አሁን ለመውጣት ጓጓሁ...
ያኔ ብታስሩኝም ግድ የለኝ ያልኩትን አሁን ወጥሬ ማስረዳትና መከራከር ጀመርኩ...
በስተመጨረሻም ዳኛው "ፖሊስ አለሙ እረጋሳ... በተጠርጣሪ ላይ በማስፈረድ ነጥብ ለመሰብሰብ በሚል ሞያቸው በማይፈቅደው መንገድ መረጃን በመደበቅና በማሸሽ ወንጀል ተጠርጥረው ጉዳዩን ፍርድ ቤቱ ሲመረምረው ቆይቶ ተከሳሽ አቶ ይስሀቅ አብርሃም ነፃ መሆኑንና የእህቱን ወይዘሮ እሮዛ አብርሀምን ልጆች ሕፃን ሄለን ብሃይሉንና ሕፃን መቅደስ ብሃይሉን እንደቤተሰብ ሁኖ እንዲያሳድግ ፍርድ ቤቱ የወሰነ ሲሆን በፖሊስ አለሙ እረጋሳ ደግሞ የአባልነት ሰነዱ ተነጥቆ ከ25,0000 ብር የካሳ ቅጣትና ሦስት አመት እስር በይኖበታል... መዝገቡ ተዘግቷል ወደመዝገብ ቤት ይመለስ!" ድሞ!
አቤት እንደዚህች የመዶሻ ድምፅ ደስታን ሰቶኝ የሚያውቅ የለም!
እናንተዬ ሕይወት ትሰክራለች ለካ! ምን ጠጥታ እንደምትሰክር ባላውቅም ግን የሰከረች ለት እንዲህ ሕይወታችንን ብጥብጥ ታደርገውና ልክ ስካሯ ሲለቃት በራሷ ጊዜ መልሳ ትክሰናለች!
ሕይወት የሰከረችበት ሰው ግን ወየውለት!
✍ሌዊhttps://t.me/lewi_derest
1 350
ድምፅ የለኝም ፊቴ ላይም ምንም ገፅታ የለም እንባዎቼ ግን በቀስታ መንከባለል ጀመሩ... ታሳሪ ጓደኞቼ ሊያፅናኑኝ ሲሞክሩ ግን የእንባዎቼ ፍጥነት ጨመረ....
ከዛ ቀን ብኋላ እህቴ ልትጠይቀኝ መታ አታውቅም... መንታ ልጆችን እንደወለደችና ከባሏም ጋር ጥሩ ኑሮ እንደምትኖር ደስተኛም እንደሆነች ሰምቻለሁ... እንዳውም በፍቅራቸው መንደሩ ሁላ ይቀናባቸዋል አሉ!
እህቴ እንደዛ አይነት ኑሮ በመኖሯ ደስ ብሎኛል... ያቺ እናቴ ግን የውስጥ ትግሌን ሳያይልኝ... እንደዛ የምሆነው ዱርዬ ሁኜ ተብቼ ሳይሆን ችግሯን ማየት አቅቶኝ እንደሆነ ሳታውቅልኝ መሞቷ ሁሌም ውስጤን ይመጠምጠዋል...
አምስት አመት ታስሬ በአመክሮ ተፈታሁ... ፖሊሶች እንደምፈታ ነግረዋት ስለነበር... መታ ተቀበለችኝ...
ተቃቀፍን... ሁለታችንም እንባ አልነበሩንም ለምን መጠየቅ እንዳቆመችም የጠየቀና ለማብራራት የሞከረ የለም በቃ ሳናወራ ተግባብተናል...
የሆነ ቤት ወሰደችኝ... ትንሽዬ ክፍል ቤት... ምግብ ማብሰያ ምናምን ያላት ደስ የምትል ቤት...
"ወንድሜ ከዚህ በላይ ላደርግልህ አልችልም... ስራ እንዲቀጥሩህ ያወራሁልህ ሰዎች አሉ ነገ እመጣና አብረን እናወራቸዋለን" ብላኝ ትታኝ ልትወጣ ስትል እጇን ያዝኳትና...
"አልገባኝም ለምን አንቺ ቤት አትወስጂኝም? ልጆችሽንም ባልሽንም ለማየት ጓጉቼ ነበርኮ?" አልኳት
እሱ አሁን አይሆንብ! እኔ ከዚህ በላች ቸግር መሸከም አልችልም በቃ ነገሮች ባሉበት ይቀጥሉ... ቸው" ብላኝ ትታኝ ወጣች
አሁን ማሰብ ጀመርኩ... ቤት ውስጥ ያለውን ነገር በዳቦ ቀባብቼ ከበላሁ ብኋላ ፍራሼ ላይ ጋደም አልኩ...
እህቴ ከሕይወቷ እያስወጣችኝ ነው? ቆይ ምን አደረኩ? ለእሷ ብዬ ነበርኮ የታሰርኩት...
ለእራስህ የምትከፍለው ዋጋ ምናልባት ለሰዎችም ሲተርፍ ታይ ይሆናል... ለሰዎች የምትከፍለው ዋጋ ግን ለአንተ እዳ ብቻ ነው የሚያተርፍልህ...
እቺን የስናፍጭ ቅንጣት ታክል ትምህርት ለመማር አምስት አመት ወህኒ ማቅቄያለሁ!
ተበሳጨሁ በጣም ተበሳጨሁ... እህቴ በዚህ ልክ እኔን መግፋቷ አናደደኝ ያን ሁሉ አመታት መታ አለመጠየቋ ያስቆጣኝ አሁን ነው....
በነጋታው ስትመጣ ምንም አላነሳሁባትም... ስራውን ነገ መጥቼ እንድጀምር ተስማማን አምስት ሺህ ብር ለዚህ ወር ለአንዳንድ ነገር ይሁንህ ብላ ሰታኝ ሄደች እኔ ግን ተከታተልኳት... ወደ ሆነ ሕንፃ ሄደች... እስክትወጣ ጠበኳት
ባየሁት ነገር ግን በጣም ነው የደነገጥኩት... እህቴ ከሰማሁላት በላይ ከባሏ ጋር ስትሆን ደስተኛ ናት... ምንም ሳታፍር በየመንገዱ ከንፈሩን ስትስመውና ሲስማት ሲሳሳቁ ላያቸው ትኩስ ፍቅር እንጂ ልጆች የወለዱ ባለትዳር አይመስሉም!
እህቴ ምን እየሆነች እንደሆነ አልገባህ አለኝ! የእናቴ መሞት የእኔ አምስት አመት በከንቱ መታሰር... እያንዳንዱ ነገር በእህቴ ጥፋት መሆኑ ገባኝ...
ተከተልኳቸው... ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት ሄደው አይተዋቸው ወደቤት ተመለሱ.... ልክ የቤታቸውን የውጩን በር ከፍተው ሊገቡ ሲሉ....
"ፓ👏👏 ጎበዟ እህቴ... ለዚህ ነበር እስር ቤት የማቀኩት? ለዚህ ነበር እናቴ በሠርግሽ ቀን የሞተችብኝ?
አጠገብሽ ከቆመው ሰይጣን በላይ ቤተሰብሽን እምሽክ አድርገሽ የበላሽ አውሬ ነሽ!" ትቻት ሄድኩ...
"ወንድሜ በቃኝ እኔ ደክሞኛል እንዴት እንደማስረዳህ አላውቅም!" ማልቀሷን ጀመረች
"እያየሁት እኮ ነው ምን ታስረጂኛለሽ? እ! እኔ ምስኪኑ እህቴ ክብሯ ተነካ ተደፈረችብኝ ብዬ አምስት አመት ስማቅቅ አንቺ ከደፈረሽ ወንድ ጋር ተጋብተሽ በየመንገዱ ከንፈር ትላላሺልኛለሽ?
ከደፈረሽ ሰው ጋር! ቱ! አውሬ አውሬ ነሽ! ሁለተኛ ዓይኔን አታይውም... እዛ ቤት የኮትሽውንም መተሽ ውሰጂ ስራውንም ቢሆን ከፈለግሽ እራስሽ ስሪበት ያንቺ እገዛ አያስፈልገኝም! ቆሻሻ!" ብያት ትቻት ሄድኩኝ...
እሷ ከሰጠኝኝ ውስጥ ለመመለስ ፍቃደኛ ያልሆንኩት አምስት ሺህ ብሩን ብቻ ነበር!
መጠጥ ቤት ገብቼ እየጠጣሁ እያለ ወደ 3 ስአት ተኩል አከባቢ ይሆናል መኪና ጠባቂዎቹ ወደመጠጥ ቤቱ ገብተው ሰው እየጠራኝ እንደሆነ ነገሩኝ...
እህቴ ትሆናለች ብዬ እንዴት በጥፊ እንደማልሳት እያሰብኩ የሸሚዜን እጅጌ እየሰበሰብኩ ወጣሁ... ስወጣ ወደሆነ መኪና ጠቆመኝ ... ሄድኩኝ...
ደፋሪዋ የእህቴ ባል ነበር ዓይኑ ደም መስሎ መንታ መንታውን እያነባ በእልህ ይተነፍሳል...
መቼም ዓይኑን ታሞ እንጂ ሰይጣንማ ለምን ብሎ ያለቅሳል እያልኩ አስቤ ሳልጨርስ... የእልህ ሳግ በተናነቀው ድምፅ..
"ቀጥ ብለህ መኪናውስጥ ግባ ካልሆነ በዚህ ሽጉጥ አናትህን ነው የምበትንልህ!" አለኝ
መጠጡ ይሆን ፈሪ ያደረኝ? ወይስ ምን ያመጣል ብዬ ነው መኪና ውስጥ የገባሁት? አላውቅም ብቻ በንዴት መሪውን እየደበደበ... በደቤቱ ይዞኝ ሄደና በቀኝ እጁ ሽጉጡን እንደያዘ በግራ እጁ ኮሌታዬን ጠፍንጎ ይዞ... እየጎተተ ወደመኝታ ቤታቸው ይዞኝ ገባ...
ባየሁት ነገር ደነገጥኩ...
"አንተ ውሻ ምናባህ ነው ያደረከው? እገድልሀለሁ እህቴን ምን አድርገሀት ነው?" ኡኡ ማለት አማረኝ ግን ሀይል አጠረኝ...
"እኔ አይደለሁም ይህንን ደብዳቤ እንድሰጥህና እንድታነበው አደራ ብላኝ ነው እጄ ላይ የሞተችብኝ!
ሦስተኛ ልጄንኮ በሆዷ ይዛልኝ ነበር! እኔንስ እሺ ግን ሆዷ ውስጥ ያለው ልጇ ምን አድርጓት ጨከነችበት? (ንፍጡንም እንባውንም በእጅጌው ጠራረገና) ልጄ ላይና እራሷ ላይ እንዲህ በቢላ እንድትጨክን ያደረካት አንተ ነህ ደስተኛ ነበረች በቅፅበት መጣህና ሕይወቷን በጠበጥከው... እራሷ ላይ አስጨከንካት...
ፍቅሬ አደራ ስላለችኝ የፃፈችልህን እንድታነበው እፈቅድልሀለሁ ከዛ ግን እመነኝ አንድ ሰከንድ አልሰጥህም እዚሁ እደፋሀለሁ!" አለኝ
ወረቀቱን ገላልጬ ማንበብ ስጀምር... "ድምፅህን ከፍ አድርገህ ለእኔም አንብብልኝ የውዷ ሚስቴን የመጨረሻዎቹ ቃላቶቿን መስማት እፈልጋለሁ" አለኝ
ማንበብ ጀመርኩ... "ለእናን ብዬ ነበርኮ!... አዎ መንገድ ለመንገድ እንዳልከው ስላላስ አይተኸኝ ይሆናል... አንዴ በጉልበቱ ክብሬን ከነጠቀኝ ወዲያ ምን ክብር አለኝ ብዬ ልሰብሰብ?
እንደዛስ የምሆንለት የእውነት በፍቅር አብጄለት ነበር የመሰለህ?
ለአንተና ለእናቴ ብዬ ነበርኮ! ሙቷል የሚል ወረቀት ከሆስፒታል አፅፌ ወንድምሽን እድሜ ልክ ከማስፈርድበት አግቢኝ ሲለኝ ነው ያገባሁትኮ!
እናቴን ያሳክምልኛል ብዬ ነበርኮ እንዳፈቀርኩት ስሆንለት የነበረው... እናቴ ባጣሁ ማግስት ሁለት መንታ ልጆች በሆዴ እንዳሉ አወኩ... ሌላ እንዳፈቀርኩት የሚያስገድዱኝ ነፍሳት መጡብኝ።
እናቴ ሞተች ላንተና ለልጆቼ ስል ነበር እንደዛ የምሆነው... ቢገባህ ካንተ በላይ እኔ ልገድለው እፈልጋለሁ ግን ልጆቼ ይደጉልኝ ብዬ ቀን ስጠብቅ እንጂ!
አሁን ደግሞ አንተ ተፈታህ ግን አልተረዳኸኝም.... ጭራሽ የእናታችን ገዳይ የአንተም ከሳሽ አደረከኝ ከእንግዲህ ምን ቀረኝ?ልጆቼ? ሀብታም የሆነ አባት አላቸው ጥሩ አድርጎ እንደሚያሳድጋቸው አውቃለሁ...
ልጆቼን አደራ... እናታችንን ሰላም እልልሀለሁ! ቻው ወንድሜ ይሄኛው ቸው ላለመመለስ ነው እወድሀለሁ"ይላል...
"እያስመሰለች ነበር? አትወደኝም ነበር ማለት ነው? እኔኮ የእውነት ነበር ያፈቀርኳት ደስታዬኮ የምር ነበር!"
እያለ ያላዝናል እኔ ግንእንዳቀረቀርኩ እንባዎቼ ይጎርፉ ነበር...
የተኩስ ድምፅ ሰማሁ....
1 350
ለእራስህ የምትከፍለው ዋጋ ምናልባት ለሰዎችም ሲተርፍ ታይ ይሆናል... ለሰዎች የምትከፍለው ዋጋ ግን ለአንተ እዳ ብቻ ነው የሚያተርፍልህ... እቺን የስናፍጭ ቅንጣት ታክል ትምህርት ለመማር አምስት አመት ወህኒ ማቅቄያለሁ!ሕይወትና እጣ ፈንታ! እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ስንቸገር ችግር በላይ በላይ የሚደራረብብን... ስናገኝ ደግሞ ቁንጣን እስኪያሯሩጠን በቃኝ የማንል ኩሩ ድሆች ነን! እናቴ እያመማትም ጉሊት ትቸረችራለች... እህቴ ደግሞ የቤቱን ትወጠውጣለች... እኔ ያው እንደሚታወቀው ስራ አጥ.. በመንደር ስሜ ደግሞ ዲንጋይ አሟቂ ዱርዬ ነኝ! እህቴ እቤት ስራ ስለሚበዛባት ትምህርቷን አቋርጣ የማታ መማር ጀምራለች... እኔ እቤት መቀመጥ አልወድም.. እህቴ የሆነ ቀን... "ወንድሜ አውቃለሁ ስራ አተህ እንጂ ሰንፈህ እንዳልሆነ ግን እስክታገኝ የቤቱን ስራ ብታግዘኝኮ ቢያንስ እኔ ትምህርቴን እቀጥል ነበር ታውቃለህ ጎበዝ ተማሪ እንደሆንኩ!" አለችኝ ዝም ብዬ አየኋትና እንባዬ እንደመጣብኝ ሳውቅ ላለማሳየት ተቆጥቼያት ትቻት ወጣሁ... ድድ ማስጫዬ ላይ ቁጭ ብዬ ግን አለቀስኩ... ገና ድሮ ነበርኮ የቤቱን ስራ ላግዛት የምፈልገው ግን.... ያንን የድህነት አኗኗራችንን ማየት ያቅተኛል... መጥ ለመስራት ግማሽ ሽንኩርትና ብረት ድስት ሙሉ ውሃ ሲሰራ እያየሁ መቻል ያቅተኛል... ሙሉ ሽንኩርት እንኳን እንዲከተፍ ማድረግ ባለመቻሌ እራሴን መውቀሱ እቤት አያስቀምጠኝም! እናቴ እያቃሰተች "ተይው እሱ ትቢተኛ ነው! እዛም እዚህም ይለቃቅማል... የኛ ሽሮ እንዴት ይጣፍጠዋል? አንቺ ብዪልኝ ልጄ!" ትላለች እበሳጫለሁ በልቼኮ አልነበረም! እቢ የምለው... የእነሱን ግማሽ ሽንኩርት ላለመሻማት ነበር...እናቴ ግን ቤቷን እንደናቅኩኝ ተሰማት... ይህ ደግሞ በጣም ያበሳጨኝና የድሀ ቆርቆሮ በራችንን አንኳጉቼው እወጣለሁ። ይሰማኛል እናቴ "ጉረኛ ሙቼልህ ተገላገላታለህ!" ስትለኝ ማን የተባረከ ሰው እንደሆነ አላውቅም መቀመጫ ዲንጋዬ ላይ ቁጭ ብሎ ሲጋራ ሲያጨስ ቆይቶ... ማንን ፈርቶ ይሁን ወይም ጥጋበኛ ሁኖ ግማሽ ላይ ሲደርስ ጥሎት ሄዷል... አንስቼ አገላበጥኩት ሽታው የሆነ በቃ ጭንቅላቴ ላይ ካለው ሸክም የሚገላግለኝ መስሎ ሸተተኝ... ፊት ለፊት ሱቅ ሄጄ ክብሪት ተበደርኩትና ያቺን ግማሽ ሲጋራ በሳል ታጅቤ ተጫጫስኳት... አለ አይደል እናቴ ያልተረዳችኝን ፀፀቴን... እህቴ ያላየችልኝም በራስ ማፈሬን ሲጋራዬ የምትጋራኝ ይመስለኛል... ሳጨሳት በቃ የውስጤን እህ... ብዬ የምነግራት ያክል ይቀለኝ ነበር... ደግሞ በሲጋራዬ መጡብኝ... በጣቶቼ መሀል ሲጋራ ሲያዩ ደርሰው መካሪ ሆኑ.... ከሲጋራው በፊትኮ ቀርቦ ሊያወራኝ የሞከረ አልነበረም... ከማጨሴ በፊትኮ ቆሽሼ አይተውኝ ነበር ታጠብ ብለው ውሃና ሳሙና አልሰጡኝም... በተቀደደ ልብስ አይተውኝም ነበር ሌላው ቀርቶ መርፌና ክር እንኳን እናውስህ አላሉኝም ነበር... ዛሬ ነው መኖሬ የታያችው? የቤተሰቤ ችግርና የእናቴ የቃሏ ጦር ሲያሰቃየኝ የምፈወስባትን ማስታገሻዬን ከጣቶቼ ሊያስጥሉኝ.. ጡጦ እንደማስጣል ቀላል መስሏቸው ከአፌ ሊነጥቁኝ ዳዳቸው... እህቴ ማታ ማታ ከትምህርት ቤት ስትመለስ ፊቷ ላይ ፍርሃት ማየት ጀመርኩ... ትቅበዘበዛለች መረጋጋት የለባትም... "ምን ሁነሽ ነው?" "የሆነ ልጅ እያስቸገረኝ ነው..." የተቀደደ ሹራቤን አንስቼ ወጣሁ... "ና ተመለስ አንተ ወገኛ ሁሉም እንደኛ ዝም የሚልህ መሰለህ ጥርስህን ብለውልህ ብኋላ..." እናቴ ታወራለች ትቻት ወጣሁ ትምህርት ቤቷ ድረስ ሄድኩኝ ግን ከሴትና ከሽማግሌዎች በቀር ወጣት ወንድ አላገኘሁም... በቀጣዩ ቀን ማታ በመውጫዋ ስአት ጠብቄ ተከታተልኳት... ቢንጎ አገኘሁት እስኪተዋትና ወደቤቷ እስክተገባ ጠብቄ የልጁ ደረት ላይ ቢላ ደቅኜ... "ከዚህ ብኋላ እህቴን ጫፏን አይደለም በዓይንህ ብታያት ወደድኳት የሚለው ልብህኝ አውጥቼ ለድመት ነው የምሰጥልህ!" አልኩት ፈርቶ እየሮጠ ሄደ በቀጣዬ ቀን ግን እህቴ አልተመለሰችም ነበር... እኔቴ ልታብድ ደረሰች እኔም ስፈልጋት አድሬ ጠዋት አስራ ሁለት ስአት አከባቢ በደም ተጨማልቃ ሰዎች ደጋግፈው አመጧት... "ያ ውሻ ነው? እሱ ነው አይደል እንደዚህ ያደረገሽ?" ስልኳን ከቦርሳዋ አውጥቼ የሴት ጓደኞቿ ጋር ደወልኩና ስለልጁ ጠየኳቸው ሰፈሩን ነገሩኝ... ስከታተለው ቆይቼ... ሲመሻሽልኝ ጠብቄ ልጁን ሦስት ጊዜ ደረቱን ወጋሁት.... ተዝለፍልፎ ሲወድቅ ሞቷል ብዬ በደም የተጨማለቀ ቢላ ይዤ ወደቤቴ እሮጥኩኝ... "እህቴ አየሽ... አየሽ ያንቺ ደም ብቻ አልፈሰሰም ገድዬልሻለሁ... ከዚህ ብኋላ የሚደፍርሽ የሚያስፈራራሽ የለም ገድዬዋለሁ..." አልኳት እናቴ ሰው የሞተባት ያክል ኡኡ አለች... ፖሊሶች ወዳው የሆኑ ወጣቶችን አስከትለው መጡና ከነደሜ ከነቢላው አፋፍሰው ወሰዱኝ... ፖሊስ ጣቢያ እያለሁ "ወንድሜ ለምን? ዓይንሽን እንደማላየው ለወንድምሽ ንገሪው አስጠልተሽኛል ብሎኝ ነበርኮ! ደግሞ አያስፈራራኝም አይደፍረኝም ነበርኮ! ለምን?" ብላ በህመሟ ስቅስቅ ብላ አልቅሳብኝ ነበር... የፍርድ ቀን ግን የገዛ እህቴ በኩራትና ጭካኔ በተሞላበት ቆራጥ ንግግር " የደፈረኝ እሱ አይደለም ወንድሜ ከልጁ ጋር የግል ፀብ ስለነበራቸው ምክንያት ስላገኘ ይሆናል የወጋው" አለች ደነገጥኩ... እሷን ሲያስቸግራት እንጂኮ ከዛ ውጪ አላውቀውም ነበር... ልጁም ተጠጋግኖ በዊልቸር መቶ ተመሳሳይ ነገር መሰከረብኝና ስምንት አመት ተፈረደብኝ... ሞቷል ብዬ ነበርኮ... በህይወት ሳየው ካልጨረስኩት ብዬ አንዱ የፖሊስ ዱርዬ ነው በሰደፍ ጀርባዬን ነርቶ ያረጋጋኝ! እህቴን አልተቀየምኳትም አስፈራርቷት ሊሆን እንደሚችል አሰብኩኝ... እናቴም ከዚህ ሁሉ ጉድ ብኋላ ታማ የፍርድ ቀኔ እንኳን መገኘት አልቻለችም ነበር... እህቴ ብዙ ጊዜ እየመጣች ትጠይቀኛለች... የሆነ ቀን ልታገባ እንደሆነና ሰውዬውም ጥሩ እንደሆነ እናታችንን እንደሚያሳክምልን ነገረችኝ.. ደስ አለኝ ሀብታም በመሆኑ ደስ አለኝ.. እኔ ያልሰጠኋቸውን ሽንኩርት የሚሞላላቸው ተገኘ... በእህቴ ሠርግ ቀን ጠዋት እህቴ በቬሎ ከድግሱ ምግብ ለታሳሪው ሁሉ አምጥታ እስር ቤቱ ውስጥ እራሱ በእህቴ ስም ሰርግ ነበር በሉት.... ሃይሎጋ ሃይሎጋ ሆ ስንል ነበር የዋልነው... እህቴን የባሏን ፎቶ እንድታሳየኝ አጥብቄ ብጠይቃትም ስትፈታ ታየዋለህ ከማለት ውጪ ፍቃደኛ አልነበረችም! የሰርጉ ቀን ማታ... እህቴ አስጠራችኝ... ሰርጉን ምን አድርጋው ነው የመጣችው እያልኩኝ ስሄድ ገና በመስኮቱ ሳያት ልቤ ተሸበረብኝ ያቺ የጥዋቷ ቆንጅዬዋ ሙሽራ አልመስልህ አለችኝ... አይኗ ቀልቶ ነጭ ቬሎዋ በጥቁር ሙሉ ቀሚስና ሻርፕ ተተክቷል... ወደመስኮቱ እሩጬ ተስገብግቤ ምን እንደሆነች ጠየኳት "እናታችን! ወንድሜ እናታችንኮ ሞተችብን..." እዬዬዋን ለቀቀችው... ጨካኝ ሁኜ ነው አንዲት የእንባ ዘለላ እንኳን አልወረደችኝም ነበር! ግን ድንጋጤዬ ከኖጥ ሚስት በላይ ሀውልት ሳያደርገኝ አይቀርም! ማን እና እንዴት እንደወሰዱኝ.. እንዴትስ እንቅልፍ እንደወሰደኝ... እህቴም እንደቴ ሁና እንደተለያየን ሳላውቅ ነው ጠዋት ከእንቅልፌ የነቃሁት። ቀሉን በሀይሎጋ ሲቦርቅ የነበረው እስረኛ ሁሉ ተሰብስቦ... ቆሎ በስሀን አድርጎ ሀዘን ተቀምጦ እስክነሳ ይጠብቁኝ ነበር... ከእንቅልፌ ተነስቼኳን እናቴ እንደሞተች ያስታወስኩት ዘግይቼ ነው...
1 350
ለእራስህ የምትከፍለው ዋጋ ምናልባት ለሰዎችም ሲተርፍ ታይ ይሆናል... ለሰዎች የምትከፍለው ዋጋ ግን ለአንተ እዳ ብቻ ነው የሚያተርፍልህ...
እቺን የስናፍጭ ቅንጣት ታክል ትምህርት ለመማር አምስት አመት ወህኒ ማቅቄያለሁ!....loading
1 350
ሲባል እሰማለሁ
"ህይወትን አሸንፍ"
መኖር አይበልጥም ወይ
ከመወዳደር ጽንፍ?
እንደሆን ነው እንጂ
የልቡን መቃብር በሳቅ የከለለ
ህይወት ስትሸነፍ ያየ ሰው የት አለ?
ምንድነው መሸነፍ?
ማንን ነው ማሸነፍ ?
ለይመሰል ነው እንጂ እንዲያው ተዘክሮ
መች ይወዳደራል ነዋሪና ኑሮ?
ወዴት ነው መድረሻ የት ነው መነሻዬ?
:
መኖር አይደለም ወይ የመኖር ድርሻዬ?
ሀገሬው መረሬው
"ቀንህን ብለጠው" ብሎ ይለፍፋል
እውነት በሰው አቅም ህይወት ይሸነፋል?
@lewi_derest
1 350
"አንዳንዴ መልስ... አንዳንዴ አለማግኘት.. አንዳንዴ ደግሞ የዘገየ መልስ... ይሄ እኮ የትኛውንም ሰው ሊያጋጥመው የሚችለው የሕይወት አዙሪት ነው... ከፈጣሪ ጋር ምን አገናኘው?
አንድ በፈጣሪ የማያምን ሰውስ ከእነዚህ ሦስት ነገሮች ውጪ ሌላ ምን ያጋጥመዋል? ይህ የሕይወት ጉዳይ እንጂ የእግዜር ጉዳይ አይደለም!
እሱን ፃዲቅና ፍፁም ለማድረግ ስትሉ ሁሉንም የኛ ጥፋት አታድርጉት!
ሀ, መልስ ማግኝ ለ, መልስ አለማግኘት ሐ, ከጥያቄው ያረፈደ መልስ ማግኘት... ከእነዚህ አንዱ በሆነ ሰው ሕይወት ለማጋጠም የእግዜርን አዋቂነት አይገይቅም!
እንዴት አንቺ ኳን ጭንቅላትሽ አያወራሽም?
እግዜር አዋቂም ሆነ አልሆነ ከሦስቱ አንዱ ይፈጠራል ታዲያ እዚህ ጋር እግዜርን ምን አመጣው?" እያየኋት የምናቤም ሴት ትጠፋለች እኔ ግን ለብቻዬ ወሬዬን እቀጥላለሁ...
ለዚህ ነው ከሰው መራቅ የምፈልገው... ሁሉ ነገራችሁ የደመነፍ እንጂ የሰወኛ አይደለም...
ሰው ደመነፍሱን ብቻ ሲሆንኮ እንስሳ ይሆናል ያውም የቤት ብቻ አይደለም የዱርም አውሬ ጭምር እንጂ!
የሰውዬው የእንስሳነት መልክ ደግሞ የስሜቱ ውጤት ነው!
እሳትና ስሜትን አላምናቸውም! እሳት ውስጥ ሁሌም መቃጠል መብሰልና ማረር አለ! ውሃ ውስጥ ግን ሁሌም ተመሳሳይ ነው...
ሎሚ ወይ ቲማቲምን እሳት ውስጥና ውሃ ውስጥ አድርጊው እስኪ... እሳቱ ከደቂቃዎች ብኋላ የሁለቱንም ማንነት ጥቅምና መኖርን ሙሉ በሙሉ ወደተቃራኒው ይቀይራቸዋል .... ውሃ ግን እንዳውም እነሱነታቸውን ይጠብቅላቸዋል... ለዛ ነው ከሀዘን ወይም ከደስታ እሳትነት ይልቅ ከሁለቱም ውጪ ቀዝቃዛነትን የምመርጠው!
"እኔ ካንተ የተሻልኩ ነኝ ማለት ነዋ! ፍልስፍናኮ ሊናገሩት እንጂ ሊኖሩት የማይችሉት ሀሳብ ብቻ ነው!" ደግሞ ከጠፋችበት ትመጣለች ያቺ የምናቤ ሴት
"ካልኖርሽውማ ምኑን ፍልስፍና ሆነ? አብዛኛው ሰው ልክ እንዳንቺ ሳይኮሎጂን ይወዳሉ ፍልስፍናን ግን ያጠላሉ.. ግን ያልተረዳችሁት ነገር የሁለቱም መጨረሻ አንድ መሆን ነው!
የሳይኮሎጂም መጨረሻው ምን መሆን ነው? ሰዎችን ወዴት ለማብቃት ነው ብለሽ ብትጠይቂ ወደ አልኬሚነት ነው! ተመሳሳይ ጥያቄ ለፍልስፍናው ብታቀርቤ መጨረሻው አልኬሚነት ነው!
አልኬሚስት ደግሞ ቀማሚ ነው... አይከፋኝም ማለት ሳይሆን.. መከፋቴ የሚቆጣጠርብኝ ነገር የለውም ማለቴ ነው!
እስኪ ለምሳሌ አንቺ የከፋሽ ቀን ከሌላው ቀንሽ የሚቀየሩ ነገሮችሽን ንገሪኝ?" መልሳ ትጠፋለች!
በቃ እናንተ ለራሳችሁ መልሱት...
✍️ሌዊhttps://t.me/lewi_derest
1 350
ሕይወት ላይ ልክ እንደሰው ያለ ቂም አለብኝ... የምበቀላትም በመኖር ነው!ሰው አስከፍቶኝ ያውቃል.. ከሕይወት ግን አይበልጥም! እንድትስቅልኝ አልጠየኳትም ነበር! ለመተዋወቅ...አብሬያት ለመጫወት... ጓደኛዋ ለመሆን አልጠየኳትም ነበርኮ! ወንድሜ ስልክ ይደወልለታል... ከዛ ከጫማዎቹ አንዱን ጫማ አንስቶ "እንካ ይሄንን ጫማ ለሳሚ ስጠው" አለኝ እኔ እንደታናሽነቴ ጫማውን ይዤ ተንጦልጡዬ በራቸውን አንኳኳሁ... በር ስር ተጥዳ ማንን እንደምትጠብቅ አይገባኝም! እቺማ ማንኳኳቴን ሰምታ አይደለም ገና ጥላዬን በበሮቹ ስር አይታ ነው የከፈተችው! በሚያስብል ፍጥነት ያንኳኳሁበት እረ ሳይወርድ በሩን ከፍታ ከፊቴ ተደነቀረች። "ሳሚ አለ? ይሄን ስጪልኝ!" "የለም ብልህስ? መጀመሪያ ለጥያቄህ መልስ አጠብቅም" አለችኝ እየሳቀች። ጓደኞቼ ብዙ ነገር አካብደው ሲያወሩ ሰምቻለሁ... አጎታቸው ቤት ስላለው ቲቪ.. እነእንትና ሰፈር ስላለችዋ ልጅ... ምናምን ስለሳሚ እህት ግን እንቅጯን ነው የተናገሩት! ምናልባት ለማጋነንም ቃል አተውላት ይሆን? ለመጀመሪያ ጊዜ ከራሴ ጋር አወራሁ! አይገርምም አእምሮዬ እራሴን የጠየቀኝ የመጀመሪያው ጥያቄና ንግግሩ ነበር! "ለማጋነን ቃል አተውላት ይሆን?" "ፅጌሬዳ እባላለሁ ፅጌ አበባ ብትለኝ ደስ ይለኛል" ብላ እጄን ካለበት ጎትታ ጨበጠችኝ "ብስራት.." አልኳት በቀዘቀዘ ድምፅ "የሳሚ እህት ነኝ ግባና ስጠው ጠዋት ስላናደደኝ እኔ አልወስድለትም" አለችኝበሩን ክፍት ትታው እየሄደች... ተከትያት ገባሁ... ከየት መጣ ያላልኩት.. ጓደኞቼ ስለፅጌ አበባ ሲያወሩ የዘነጉት ያላወሩለት ውሻ እያንቧረቀ መጣብኝ እቺማ አውቃ ነው የፈታችው... ሌላው ቢቀር ውሻ እንዳለቸው አትናገርም! ስታስጠላ! አልኩኝ በውስጤ! አአህ ለመጀመሪያ ጊዜ በውስጤ ያልኩትን ደግሜ ሳስበውና ልክእንዳልሆንኩ ለእራሴ ስነግረው "አታስጠላም ግን በቃ..." ምናምን እያልኩ ስታገል ከውሻው አምልጬ ሳሎናቸው መሃል እራሴን አገኘሁት። ሳሚ ጫማውን ተቀበለኝና "ቁጭ በል ቆይ እኔ አስወጣሀለሁ" አለኝ... የምግብ ጠረጴዛው ላይ ቁጭ አልኩ.. ፅጌ ሶፋው ላይ ቁጭ ብላ የቤት ስራ እየሰራች ነው አጠገቤ ስለሆነች በደንብ ይታየኛል... ለሁለተኛ ጊዜ በውስጤ ስጠይቅና የጠየኩትን ሳስተውል.. "ቆይ የቤት ስራዋን እዚህ ዘርግታ በር ስር ምን እየሰራች ነበር?" ምናልባት ጫማውን እንድትቀበልለት ሳሚ ልኳት ይሆናል ብዬ የምትፅፈውን ማንበብ ጀመርኩ... "ኧረ.. እ. እሱ ጋርኮ..." "እዚህ ጋር ምን?" "መልሱ እንደሱ አይደለም..." "ቀለሜ ነሽ እንዴ.. ናና አንተን አይደል እንዴ የምፈልገው" እያለች አጠገቧ እንድቀመጥ በእጇ ሶፋውን እየተመተመች... "እንዳትሰራላት.. እሱ የሚፈተንልሽ መሰለሽ? ደደብ" አለ ሳሚ "አትሳደብ ላባዬ ነው የምናገርልህ!" "ዝበይ ባክሽ ዲንጋይ ራስ.. ባይገባትም አስረዳት እስኪ..." ብሎ ትቶን ወጣ.. ከእሱ ጋር ለመውጣት ስነሳ እጄን ጎትታ አስቀመጠችኝና "እቺን ሳትሰራማ ንቅንቅ የለም!" አለችኝ ቆይ እነጎራው የቤት ልጅ ናት አላሉም እንዴ? የቤት ልጆች ጭዋ እንደሆኑ ነበር የማቀው ምን ያቅለበልባታል? ነው ወይስ በየቤቱ እየዞርን ስለማናያቸው እንጂ የቤት ልጆች እንደዚህ ናቸው? እያልኩ በውስጤ ሰራሁላት... ከዛን ቀን ጀምሮ ጥናት በሚሉት ስበብ እነ ፅጌ አበባ ቤት በየጊዜው እመላለስ ጀመር.... ከንፈሬን እንድትስመኝ አልጠየኳትም ነበር! "Maths እኮ ደፈንኩ" ብላ ካልጠፋ ቦታ ከንፈሬን ሳመችኝ... አንድም ቀን ስለፍቅር ሳናወራ የከንፈር ወዳጆች ሆንን.. የእኔ እነሱ ቤት መመላለስ ብቻ ሳይሆን መሳሳማችንም እለት በእለት ሆነ... ቤተሰቦቿ ከእኔ ጋር ስትሆን ይፈቅዱላታል.. አብራኝ ሱቅ ትወጣለች.. በቃ ተመቸኝ ነው የምላችሁ ጓደኞቼ ላይ እጎርርባቸው ነበር.. እንዳውም ከንፈሯን እንደምስማት ስነግራቸው አላምን ብለውኝ እነሱ ፊት ስማኝ ታውቃለች... ሁሌም እንደምታፈቅረኝ ይሰማኝ ነበር ለዛ ነው እኔም ያለስስት ልቤን እሷን ሲያይ ማሰብ ከጀመረው አእምሮዬ ጋር እነሆኝ ያልኳት። ልጅነታችኝ እየተገፈፈ.. እኛም እየጎረመስን ፍቅራችንም እየጎረመሰ ሁሉም ጥሩና ደስ ይል ነበር ግን... ማደግ የሚያስጠላው ለዚህ ነው! የልጅነት ዓይንኮ አንድ ብቻ ነበር አደግንና ዓይኖቻችን አማተሩ... ነግራኝ ቢሆን ባልከፋ ነበር ግን... ጠዋት ከንፈሬን ስማ ከሰአት የማውቀውን ጎረምሳ ስትስም አየኋት... የሌለብኝን ከትምህርት ቤት ባጥር ዘልዬ የወጣሁትኮ ናፍቃኝ ላያት ነበር እሷ ግን.... ልቤ ብቻ አልነበረም አእምሮዬም ተሰበረ! ከፅጌ አበባ በላይ ግን ሕይወት አስከፍታኛለች! እናቱ "ዛሬ አስቤዛ ግዴታ ይዘህ መምጣት አለብህ የሚላስ የሚቀመስ የለንም!" ስትለው አሳዝኖኝ አትክልት ተራ አብሬው ስሸከም ቆይቼ አንዲት ሳንቲም እንኳን ሳልቀበለው አስቤዛ እንዲገዛ ትቼለት ነበርኮ... ጓደኞቼ ለጨዋታ ቡድን ሲሰሩኳን እንደሚያገሉት ስለማውቅ ቀድሜ ከእሱ ጋር ቡድን እሆን ነበር እንዳይከፋው ብዬ.. ስለፅጌ አበባኳን ከነጎራው በላይኮ ጓደኛዬ እሱ ነው ብዬ ለእሱ ነበር ብዙውን የነገርኩት... ደሞኮ ጠዋት "እናቴ ብር ያስፈልጋታል ክሃስ አልገባም ሲለኝ... ለምሳ የተሰጠኝን ብር ሰጥቼው ነበር ክላስ የገባው.... እሱ ግን ከኔ ቀድሞ በእኔ ምሳ እሷን ቸኮሌት ጋበዛት እኔ ስለእሷ ስነግረው እሱ ለካ ልቡ ውስጥ ቤት ሲሰራላት ነበር... ጓደኛዬ ብዬ ያቀረብኩት ሰው ሕይወቴ ናት ብዬ ከነገርኩት ሴት ጋር ምንም ሳይራራልኝ ከንፈሯን ሲመጥጥ አየሁት! ይህም አስከፍቶኛል ግን ከሕይወት አይበልጥም... ሕይወት ላይ ልክ እንደሰው ያለ ቂም አለብኝ... የምበቀላትም በመኖር ነው! በወንድም በሴትም... በአንድ ጊዜ በተመሳሳይ ቅርበት... በመከዳቴና በመከፋቴ.. ወንድነቴም ሴትነቴም ሞተብኝ formless ሆንኩኝ!... ሕይወት ግን የበለጠ አስከፋችኝ... እፈልግ የነበረውኮ ለሰዎች ሁሉ ማብራሪያ አለመስጠት ነበር... ግድ በማልሰጣቸውና ግድ በማይሰጡኝ ሰዎች መሀል ነበር መኖር የምፈልገው... ከሰዎች ጋር መግባባት... መቧቸር.. ያደክመኛል... ሕይወት ግን ይህን እንዳደርግ ደጋግማ አስገደደችኝ... ነገሮች ተሳኩልኝ በቃ አሁን ይህንን እንዲህ አድርጌ... ምናምን ስል የሆነ ጎዶሎ ይመጣብኛል የተመኘሁትን አይነት የብቻ የራስ ዓለም ኑሮ እንዳልኖር ሕይወት ደጋግማ እንቅፋት እየሆነችብኝ አስከፋችኝ። "ከሰው ለመራቅ መሞከሬ ስህተት ነበር? እስኪ ንገሪኝ..." አልኳት የምናቤን ሴት "ከሰው ተርቆ እንዴት ይኖራል?" "ከሰው ቀርበንስ መቼ ኖርን? እሷን ስለሰጠኸኝ... ብዬ ምስጋና አጉድዬበት አላውቅም ነበርኮ.. እሱንም እንዳረዳው እግዜርን ለምኜው ነበርኮ! እንኳን ሰው ከእግዜርም ቀርበን መኖር አልቻልንም" "እግዜር አዋቂ ነው.. አንዳንዴ ይመልስልናል.. አንዳንዴ እንቢ ይለናል... አንዳንዴ ደግሞ የጠየቅንበት ጊዜ ስህተት ይሆንና አቆይቶ በጊዜው ይሰጠናል..." "አየሽ ልክ ነበርኩ... ከፅጌ አበባና ከጓደኛዬ በላይ በሕይወት መከፋቴ ልክ ነበር ከሰው መራቄም ልክ ነበር... አንቺ እንኳን በደመነፍስ አወራሽ እንጂ ስላወራሽው ነገር ምንም ግድ አልሰጠሽምኮ!" "እንዴት?"
1 350
💞ልእልት
ጥሎብኝ ቆንጆ ሴት እወዳለሁ ( የሰው መንገዱ ከቆንጆ ጋር... እንዲል መፅሐፉ )..... ማን ይጠላል ልትሉኝ ትችላላችሁ..... ማንም!! ሴቶቹ እንኳን ከቆንጆ ሴት ጋር ነው ሚሆኑት::
ግን ደሞ ጭንቅላቷ እንደ መልኳ ካልሆነ አብርያት ጊዜ ማሳለፍ ያሰለቸኛል::
"አይምሮ የሌላት ቆንጆ ሴት በእርያ(በአሳማ ) አፍንጫ ላይ እንዳለ ወርቅ ናት"( አንዳንዴ እንደ ቄስም ያረገኛል 😁 ቻሉት እንግዲህ )
ይታያችሁ!! ይህን ያለው አንድ ተራ ሰው አይደለም..... የአንድ ሺህ ሚስቶች ባል የነበረው ሰለሞን ነው::
እናማ አንዲት ቆንጆ ሴት ባይኔ ውል ትል ጀመር.... ከሰውነቷ ሁሉ ሚገዝፈው ፀጉሯ ነበር.... ከዛ ውጪ ከትንንሽ
ነገሮች የተሰራች ትንሽዬ ፍጥረት ናት::
የኔ ሚጢጥ ጉረኛ ቢጤ ነች..... ቆንጆ መሆኗን ሰለምታቅ ለኔ እና መሰል ወዳጆቿ የማትበላ ወፍ ነበረች ::
በዛ ውብ ፈገግታዋ እና ከላባ በለሰለሰ ድምፅዋ ስታወራ.... የቱ ተባዕት ነው ልቡ ያልሸፈተ?
እንደው ተሳክቶልኝ የራሴ ባረጋት ራሱ ከስንቱ አስጥላታለው?... ጠላት መሰብሰብ ነው ትርፉ......
ያም ለኔ ያም ለኔ
እኔም ለኔ ስላት (×2)
ከሷ ወድያ ቆንጆ
የሌለ መሰላት (×2)
እያልኩ እያንጎራጎርኩ እንደሷ ባይሆንም ደስ የምትለዋን ግዋደኛዋን ጠበስኩ....
ውይ ሴቶች ግን አትገቡኝም እኮ እውነት! ያኔ ለሰላምታ እንኳን ደጅ ምታስጠናኝ ልጅ አሁን ጓደኛዋን ሰበብ እያረገች እኔ ጋር ትመጣ ጀመር::
ጭራሽ አቆላምጣ ትጠራኝ ጀመር:: አቤት በሷ አፍ ስሜ ራሱ ይጣፍጣል :: አንድ ቀንማ "እስኪ ያሩ ጋብዘኝ" አትለኝም? ( ያሬድ መቆላመጡ ነው )
አሁን መጀነኑ የኔ ተራ ሆነ ::
እኔም ገና ለገና ፈገግ አለችልኝ ብዬ ከልዕልት( ከግዋደኛዋ) ጋር ያለኝን ነገር ማበላሸት አልፈለኩም ::
ልጅቷ ፍቅር ብሎ ነገር አታውቅም.... ራሷን እንደ ንግስት እንጂ እንደ ፍቅረኛ ማየት አትችልም..... እኔም ንጉስሽን ፈልጊ ብዬ ወደ ልእልቴ..... (ንጉስ ከመሆን ልዑልነት ሳይቀል አይቀርም )
ከዛም የትዳር አማካሪውን ሰለሞን ሰምቼ " ውበት ሐሰት ነው ÷ ደምግባትም ከንቱ ነው" በማለት ቆንጆ ብትሆንም ፈጣሪን አትፈራም ብዬ ከህይወቴ አራኳት::
( ፍቅረኛ እንደ ገንዘብ አልበረክት ብሏል..... ያዝልቅልህ በሉኝ )
በዚታክ
https://t.me/yegtmalem32
1 350
👋ሰላም የ Biography_Teach ቤተሰቦች!
⭕አዲስ ለተቀላቀላችሁንና እስካሁን የለቀቅናቸው የሮበርት ግሪን "The 48 Laws of Power" ሕጎች ላመለጣችሁ፣ ሁሉንም በአንድ ላይ እዚህ አዘጋጅተንላችኋል።
📌ከታች ያሉትን የሕግ ቁጥሮች በመንካት የሕጎቹን ሙሉ ትርጉምና አስገራሚ ታሪካዊ ምሳሌዎችን ማንበብ ትችላላችሁ
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟙 - በላይህ ካለው አካል በላይ ብልጥ መስለህ አትታይ
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟚 - በጓደኞችህ ላይ ከመጠን በላይ አትመካ፤ ጠላቶችህን እንዴት እንደምትጠቀምባቸው እወቅ
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟛 - ዓላማህን ደብቅ፤ ግልጽ መጽሐፍ አትሁን
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟜 - ሁልጊዜ ከሚያስፈልገው ያነሰ ተናገር
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟝 - ስምህን አንደ ህይወትህ ጠብቅ
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟞 - በማንኛውም መንገድ የሰዎችን ትኩረት ስብስብ
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟟 - ሌሎች እንዲሰሩልህ አድርግ፤ ምስጋናውን ግን አንተ ውሰድ
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟠 - ሌሎች ወደ አንተ እንዲመጡ አድርግ፤ አስፈላጊ ከሆነ ማጥመጃ ተጠቀም
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟡 - በክርክር ሳይሆን በድርጊትህ አሸንፍ
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟙𝟘 - ኢንፌክሽን ተጠንቀቅ፦ ካልታደሉና ደስተኛ ካልሆኑ ሰዎች ራቅ
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟙𝟙 - ሰዎች ሁልጊዜ በአንተ ላይ ጥገኞች እንዲሆኑ አድርግ
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟙𝟚 - ተቃዋሚህን ለማለስለስ እውነተኛ ቅንነትና ልግስናን ተጠቀም
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟙𝟛 - እርዳታ ስትጠይቅ በሰዎች ደግነት ላይ ሳይሆን በራሳቸው ጥቅም ላይ ተመስረት
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟙𝟜 - እንደ ወዳጅ በመቅረብ እንደ ሰላይ መረጃ ሰብስብ
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟙𝟝 - ጠላትህን ሙሉ በሙሉ ደምስሰው
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟙𝟞 - ክብርህን ለመጨመር አልፎ አልፎ ራስህን አርቅ
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟙𝟟 - ሰዎችን በስጋት ውስጥ አቆይ፤ ሊገመት የማይችል ድባብ ፍጠር
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟙𝟠 - ለመከላከል ስትል ግንብ አትገንባ፤ መገለል አደገኛ ነው
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟙𝟡 - ማንን እንደምትጋፈጥ እወቅ፤ የማይገባውን ሰው አትቀስቅስ
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟚𝟘 - ለማንም ወገን አትገዛ፤ ነፃነትህን ጠብቅ
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟚𝟙 - ሞኝን ለመያዝ ሞኝ መስለህ ቅረብ
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟚𝟚 - የእጅ መስጠት ስልትን ተጠቀም፦ ድክመትን ወደ ኃይል ቀይር
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟚𝟛 - ኃይልህን በአንድ ላይ አከማች
💥 ℝ𝕦𝕝𝕖 𝕟𝕦𝕞𝕓𝕖𝕣 𝟚𝟜 - ምርጡ ባለሟል ሁን
ᴊᴏɪɴ ʜᴇʀᴇ
👇👇👇
@BIOGRAPHY_TEACH
@BIOGRAPHY_TEACH
1 350
ድካም ድካም... እጅ መስጠት መስጠት ያሰኛችሁ ሰዎች ግን እንደሀሳብ ይህንን መፅሐፍ ብታነቡት!
እኔ በጣም የወደድኩትና የሰዎችን ሳይኮሎጂ ከግምት ሳያስገቡ ከተፃፉ እንደ The power of now ካሉ መፅሐፎች እጅግ የሚለይ ሳይኮሎጂን የሚያውቅ የself-help መፅሐፍ ነው!
ከፈለጋችሁ ልጨርሰውና ስለመፅሐፉ ያሉኝን እይታዎች ከሳይኮሎጂ አንፃር በፅሁፍ ወይም በvoice እሰራላችኋላሁ
1 350
ሲሳይ እኔ አብሬው ከሌለሁ ለብቻው ወይም ከሌሎች ሰዎች ጋር ማምሸት ምቾት ስለማይሰጠው.. እንዳመመኝና እቤቴ ሂጄ ማረፍ እንደምፈልግ ስነግረው የማምሸት እገ
ቅዱን ትቶት ሊያገኘው የነበረውን ሰው አግኝቶት ብቻ ወደቤቱ እንደሚሄድና እኔ እንድሄድ ነግሮኝ ተለያየን...
እኔ ግን አዚ ጋር ሂጄ ነገሮችን በጥንቃቄ ካደረግን ብኋላ ሲሳይ ሲመጣ ተደበኩ... ሁሉም ነገር በእቅዳችን መሠረት ነበር የሆነው...
ሲሳይን በውድቅት ለሊት አርቀን ቀበርነው!
እንደቀልድ የሲሳይን ቦታ ተክቼ መስራት ጀመርኩ... ለሞባይል ባንኪንጉ ኮዱ እንኳን የማይጠነቀቅ ደደብ ስለሆነ ኮዱን አቀዋለሁ... ለነገሩ ባላቀውም መገመት አይከብደኝም ነበር የሕፃን ጭንቅላት ይዞ...
አሁን ማን ይሙት... የሲም ካር ፒውኬ ይመስል ኮዱን 0000 ያደርጋል?
ደግሞኮ እንደትልቅ ነገር.. "እኔ ብዙ የሚያስጨንቁኝ ነገሮች አሉ ደግሞ ስለኮድ ልጨነቅ? ዋናው ስልኩ ነው ኮድ ባይኖረውስ? ማናባቱ ደፋር ስልኬን ይወስዳል!" ይላል
ሀብቱን ወሰድኩ... ቤቱና መኪናው በስሙ ቢሆንም ጠያቂ እንደሌለ ስለማቅ እሱን የእኔ ለማድረግ አልደክምም ጠያቂ ቢመጣም ሳልከራከር እሰጠዋለሁ... አሁን ያለኝ ሀብት በስሜ ብዙ ነገር የሚያስደርገኝ ነዋ...
አዜብ እንደምኞቷ ልጅ ወለደች ያውም መንታ ልጅ!... እኔ ለባልነቴ ግድ ባይሰጠኝም ግን አባትነቴ ግድ ይሰጠኝ ስለነበር አዜብ ብዙም አልደበራትም... የወለደች ሰሞን የአክስት ልጅ ነኝ ባይ ካላረስኩሽ ብላት እቤታችን ከረመች...
አዜብም የሲሳይ ቢጤ መሆኗ የገባኝ... ሁለተኛ ዙር ብትወልድ እንኳን የመታረሻ ጊዜዊዋ የሚያበቃበትን ያክል ጊዜ የአክስቷ ልጅ ቤታችን ላርስሽ በሚል ስበብ እኔን ለማማለል ስትሞክር አንዲትም ቀን አለመጠርጠሯን ሳይ ነው!
አስቤዛ ለመግዛት "እኔ አብሬው እሄዳለሁ አንቺ አትድከሚ" ስትላት አዝናላት ይመስላታል... የባሏ መኪና ውስጥ ከንፈር ልትቃመስ እንደሆነ ማን በነገራት!
በጊዜ ሂደት የአዜብ የአክስት ልጅ ተብዬ እየተመቸችኝ መጣች... ከእሷ ጋር ለመኖር ተስማማን... ለአዜብ ልጆቹን እንድታሳድግበትና ለተባበረችኝ ወንጀል.. በገንዘብ ደረጃ ግማሹን... በንብረት ደግሞ መኪናውንና የምንኖርበትን ቤት ከአንድ ድርጅት ጋር እንደተውኩላት የተቀሩትን ሁለት ድርጅቶችና የገዛናቸውን አንድ ቤት ከሁለት መኪና ጋር ደግሞ እኔ እንደወሰድኳቸው ነግሪያት... ከአክስቷ ልጅ ጋር የምንጋባበትን የጥሪ ወረቀት ሰጥቻት ልብሴን ይዤ ወጣሁ...
__
ለካ ሲመክሩን የነበሩት ሰዎች ለራሳቸው ሕይወት አልገባቻቸውም ነበር!
ስለመልካምነት... ስለደግነት.. ስለጭዋነት... ምናምን የሚደሰኩሩን ለካ ሕይወት አሳብዳቸው እየዘባረቁ ነበር!
በታፈረና በተከበረ ቤተሰብ ውስጥ አድጌ ድንቄም መታፈር! ይሄው የሰዎች መጫወቻ ሁኜ አረፍኩት!
አባቴ የቃል አምላኪ ነበር! ቃሌንማ እጠብቃለሁ.. እኔኮ ጀነራል ምናምን እያለ ነው መዳን እየቻለ ለክብሬ ቅብርጥሴ ብሎ ክንችር ብሎ የሞተው!
የአባቴ መሞት.. ወንድሜ ከሰሮ ቤቱን አስይዞ የተበደረውን ብር መክፈል ባለመቻሉ ቤታችን ሲወሰድ.. እናቴ ባሌን ዳግም አጣሁት ብላ በደም ግፊት ይሁን በልብ ድካም እሷም ስትሞት.... አወንድምዬውም.. እናቴን ገደልኳት.. ተው አትበደር እያለችኝ.. ብሎ እራሱን ሰቅሎ ሲሞት...
እኔ ሦስቱንም ለመሆን ስንደፋደፍ... እንደአባቴ ቃሌን የማከብር.. እንደእናቴ ለሰዎች የምሞት.. እንደወንድሜ ላለመክሰር የምጠነቀቅ ሰው ነበርኩ...
እነሱን እኖራለሁ ስል ሳይገባኝ ለካ የሰዎች መጫወቻ ሁኜ ነበር...
ከአብርሽ እንደሰማሁት ሲሳይ ያገባኝ ለሀብታም ጓደኞቹ ብሎ እምጂ እኔን ብሎ እንዳልነበር ገባኝ...
አብርሽ ሲሳይን እንድንገድለው ሲያስማማኝ ለካ ለእራሱ ሀብት ለመውረስ እንጂ ለእኔ አዝኖ እንዳልነበር ተረዳሁ...
ሜሮንም ዝምድና ይዟት ሳይሆን ባሌን አጥምዳ ሀብታም የማግባት የልጅነት ሕልሟን ልታሳካ እንደሆነ አወኩ...
ግን ምን ያደርጋል ሁሉም ማወቅ ከረፈደ ሆነና ነገሮችን አበላሽቼ ማስተካከል ጀመርኩ...
ቤታቸው ሆን ብዬ ሰራተኛ አስቀጠርኩ.. በሰራተኛዋ በኩል እራሱ አብርሽ የሰጠኝን አይነት መድሐኒት ሰጠኋቸው...
መጀመሪያም ሙሉ ሀብቱ ለኔ ነበር የሚገባው... ሜሮን ፊቴን እያየችው ብትሞት ተመኝቼ ነበር ግን.. እራሴን ነፃ ማድረግ ነበረብኝ...
ሰራተኛዋ ቃል በገባሁላት መሠረት ወደ ሀረብ ሀገር ላኳት...
በስተመጨረሻም ሰውን ሁሉ አንድ የሚያደርገው ሞት ነው!
ከሞት ብኋላ የሚያስተናንሰንም የሚያበላልጠንም ጉዳይ የለም... ምክንያቱም ከሞት ብኋላ ሥጋና ነፍስ ለየቅል ናቸው!
ሁላችንም ብንሆን እስከማበድ እስከመክነፍ የወደድናቸውን ሰዎች ሥጋቸውን እንጂ ነፍሳቸውን አናውቃትም!
እስከሚገባኝ ደግሞ ነፍስ የሕያው እስትንፋስ እንጂ መልካም ወይም ክፉ አይደለችም!
ላለው ይጨመርለታል በሆነ ዓለም ውስጥ... "ተሸንፌ ላሸንፍ.." ቅዠት እንጂ ድል የለውም!
የሌለው ያለው እኳን በሚወሰድበት ዓለም ውስጥ... "በዝቅታ" የምናጣው እንጂ የምናገኘው ክብር የለም!
እናንተ ሞኞች ክርስቶስን እንኳን አታዩም! በዛ ልክ ዝቅ አለ! ግን በዝቅታው ልክ ከበረ ወይ? ከምራቁና ጥፊው በላይ የዘመናችን ስብከት አላዋረደውም ትላላችሁ?
ታዲያ አንተ ማነህ ዝቅ ብለህ የምትከብረው! ከእንግዲህ እኔ ከፍ ብቻ ነው የምለው.. ከአብርሽ በላይ ነኝ ከተጠቀሙብኝ ሁሉ በላይ ነኝ እኔ ዛሬ ተጠቃሚ ነኝ!
ይህ ማንነቴ በሽታ ሊሆን ይችላል... ግን ከጤንነቴ የተሻለ ከሆነ ለምን ከበሽታዬ ጋር አልኖርም?
ልክ የምንሆንላቸውን ሰዎች ማወቅ አለብን! ልክ ላልሆኑ ሰዎች ልክ ለመሆን ስንሞክር ነው በሽተኞች የሆነው... ልክ አለመሆናችን ልክ ላልሆኑ ሰዎች ሚዛናዊ ነው!
✍️ሌዊhttps://t.me/lewi_derest
1 350
እቤቴ ስመጣ ሌላ የማስመስልበት ሕይወት እንዲጠብቀኝ አልፈልግም!ጥቅም! የሀብታሞች ስርዓት ሱፋቸው ላይ ነው! ለመጀመሪያ ጊዜ ከሀብታሞች ጋር ምሳ ግብዣ ካለብህ ፈጥነህ አግባ.. ይህ አንዱ የሀብታሞች የሱፍ ሕጋቸው ነው! ግርማ ካለው ሱፋቸው ላይ እንደካባ ጣል የሚያደርጉት ሞገሳቸው ትዳራቸው ነው.. ከዛ ብኋላ ነው ግርማ ሞገስ ያላቸው ሰው የሚሆኑት። ለዛ ነበር አዜብን ያገባኋት... ከሀብታሞች ጋር መስራት ስጀምር... ቁም ነገረኛ ልመስላቸው ዘንድ ትዳር አስፈለገኝ... አዜብን በሠላሣ ሦስት አመቷ አገባኋት... አፍቅሬያት ወይም ለእሷ ስሜት ኑሮኝ ምናምን አልነበረም... ከገንዘብ ዓይን ለመግባት እንጂ.... ባለሀብቶች ትዳራቸው ክብርን ለመሸመት የሚደርቡት ካባ እንጂ የእውነት መጎናፀፊያቸው አልነበረም! ለሚስቴ ግድ ባይሰጠኝም ቤቴ ግን ነፃነቴ እንዲሆን እፈልጋለሁ... ምክንያቱም ሀብታም የሆንኩት እያስመሰልኩ ነው! ልክ እንደሀብታሞቹ ስርዓቴን በሱፌ ላይ ታጥቄ ጭዋና ትሁት ሁኜ እሰራለሁ... አከብራለሁ እከበራለሁ... እቤቴ ስመጣ ሌላ የማስመስልበት ሕይወት እንዲጠብቀኝ አልፈልግም! ቀኑን ሙሉ ስመስልና ሳስመስል ውሄ ትወናዬን አሽቀንጥሬ የምጥልበት ገንዳ ቤቴ ነው! ያ በማስመሰል ጭንብል ታፍኖ የዋለው ማንነቴ እቤቱ ሲገባ ተቆጥቶ አውሬ ይሆናል! ይህ ማንነቴ በሆነ ሀብታም ሰውዬ ተበሳጭቶ በግድ እንዳልተበሳጨ እንዲመስል ጭራሽ ጎርነንና ደመቅ ያለ የሀብታም ሳቅ እንዲስቅ ሳስጨንቀው ውሄ እቤት ነፃነት ስሰጠው አውሬ ይሆናል! አውሬነቱን አልከለክለውም! ምክንያቱም ቤቱ ነው! ለማን ብሎ በቤቱ ይታፈናል! ይህንን አውሬነት አዜብ ትጋፈጠዋለች! አንዳንዴ ግራ ትገባኛለች... ቆይ እንዴት ጥላኝ አልሄደችም? እላለሁ... ቤት ውስጥ እንደሚስት ሲያደርጋትና እንደባል ባለመሆኔ ልትወቅሰኝ ስትሞክር "በማረጫ እድሜሽ አግብቼ ወግ ባሳየሁሽ.. ምን ልትሆኚ አማረሽ?" አንገቷን ትደፋለች! ይገባኛል እሷ ስለማረጥ ብላ እንዳላገባችኝ... ቁማ ብትቀር እራሱ ግድ እንደማይሰጣትም አውቅ ነበር! ታዲያ አሁን እንዴት ታገሰችኝ እላለሁ! አንዳንዴ ማንነቴ ያልኩት መልኬ ነፃነቱ በዝቶበት ነው መሰለኝ ከቁጥጥሬም ውጭ ይሆንብኛል... ማታ በሰላም ተኝተን አድረን ጠዋት ስነሳ በድንገት ፊቷ ወደዛ ዙሮ ወይም ጀርባዋን ሰታኝ ተኝታ ከነቃሁ... "ሰው ባረኩሽ ንቀሽኝ ነው?" በጥፊ ወይም በተኛችበት በርግጫ ብዬ እቀሰቅሳታለሁ... ልክ ከእንቅልፏ ስትነቃ የምትደነግጠው ድንጋጤ... አለ አይደል በቃ የሆነ ዱብዳ ድንገት ፍጥፍጥ ሲልባት አይነት ድንጋጤ ሳይ ውስጥ የሆነች ደስ የምትል ስሜት ትሰማኛለች! "አብሬሽ ብተኛ ጀርባሽን ትሰጪኛለሽ?" እጮህባታለሁ.. "ኧረ ሲስ ተኝቼ ስገላበጥ እንጂ..." "ዝበይ!" ሌላ ጥፊ ወይ እርግጫ ይታከልበታል! በዝበል ያደኩ ልጅ አይደለሁ.. ከአባቴ ኮርጄ የእቃቃ ልጄን የተቆጣሁትን መቆጣት አይነት እቆጣታለሁ.. በሰቀቀን ዝም ትለኛለች! ሰባት አመት ሙሉ.... እሷን የምቀጠቅጥበትና እሷም ተስፋ የማትቆርጥበት ጉዳይ ልጅ ነው.... እንደእኔ ትርጉም ዱላ ሲያምራት ልጅ ካልወለድን ብላ ነገር ትፈልገኛለች... እንደሷ ትርጉም ግን አይገባኝም ወይም አላውቅም.. ብቻ ልጅ ስለመውለድ ማሰብ አልፈልግም! ከሰባት አመታት በአንዱ ቀን ወደነፃነቴ ተከትቼ እያመናጨኳት እራት እንድታቀርብልኝ ጠየኳት... ብዙ ጊዜ ስላችሁ በጣም ብዙ ጊዜ አዜብ እራት ወይም ቁርስ ስበላ እንዳጎርሳት ስትፈልግ በዓይኖቿ አይቻለሁ... ዛሬ ግን ተስፋ የቆረጠች መሰለኝ.. አቅርባለኝ ፈጥና ከፊቴ ዞር አለች.. በስሱ ፈገግ አልኩ.. ቀድሞውኑ የተሸነፈችን ሴት ለምን የማሸነፍ ስሜት እንደተሰማኝ አልገባኝም ብቻ ደስ አለኝ... ከሁለት ወይም ከሦስት ጉርሻ ብኋላ ከምላሴ ጀምሮ ጉሮሮዬን ምግቡ የወረደበት በጠቅላላ እስከጨጓራዬ ድረስ ተቃጠልኩ... የመዋኛ ገንዳው ውሃ እራሱ የሚያረሰርሰኝ አልመስልህ አለኝ... አዜብ ከምግቡ ጋር ያቀረበችልኝ ብርጭቆን ተስገብግቤ ላነሳት ጣቶቼ ጯፏን ከመንካታቸው የሆነ እጅ አስጎምጅቶ ነጠቀኝ... አዜብ እንደምትሆን አሰብኩ... ዓይኖቼን መግለጥ እየከበደኝ ነው... በሚጨፈኑት አይኖቼ ብርጭቆውን የጨበጠውን እጅ አሰብኩት... የወንድ ነው! ስአቱ አዎ እጁ ላይ ያለው ስአት! ሀብታም ለመሆን በማሴራቸው ሴራዎቼ እንደቀኝ እጅም እንደጓደኛም ሁኖ አብሮኝ የቆየ.. ከሀብታሞች ጋር ስሆን ጭዋነቴን ከሚስቴ ጋር ስሆን ብልግናዬን ያየ ግን በልክነት ውስጥ የሚተወኝ ጓደኛዬ... ለልደቱ የገዛሁለት ስአት... አይሆንም! አይሆንም! አይሆንም... "አ.. አ.. አብ..አብር..ሽ!"..... ____ ሁሌም ችግር ውስጥ ሲሆን እኔ ጋር ነው እሩጦ የሚመጣው... ደግሞኮ የሚገርመኝ መፍትሄ የሰጠሁት እኔ ሁኜ ሳለሁ ነገሩ ከተሳካ ብኋላ የደስ ደስ ልጋብዝህ ይለኝና... ልክ መፍትሄውን እሱ እንዳሰበው ሁላ.. "ተሳካኮ አብርሽ.. እንደኔ ጭንቅላት ቢኖርህ የት በደረስክ!" ይለኛል በራሴው መፍትሄ ተመፃድቆ እኔኑ ይሰድበኛል... ከሆነ ጊዜ ብኋላ እኔም እንደሱ ማሰብ ጀመርኩ.. ነገሩ ቢዝነስና ቢዝነስ ብቻ ነው እራሴን እንደጓደኛው ሳይሆን እንደሰራተኛው ማየት ጀመርኩ.. እሰማዋለሁ አማክረዋለሁ... ብር እቀፍለዋለሁ! መጀመሪያ ሰሞን አዜብ ታሳዝነኝ ነበር.. አቀራረቧና ሰላምታዋ ግን ወንድነቴን ፈተነው... ለመጀመሪያ ጊዜ የሲሳይን ነገር የኔ ስለማድረግ ተመኝሁ.. አቤት የሴት ሀይል ግን ሀብቱን የኔ ስለማድረግ ከማሰብ ይልቅ ከሀብቱ ላይ መቀፈልን ነበርኮ ያሰብኩት.. ለሴት ሲሆን ግን የእሱን የብቻዬ ስለማድረግ ተመኘሁ... እየቆየ ሲገባኝ ግን በሴት የተጀመረው ምኞቴ አዚ ብቻ ሳትሆን ሀብቱም የኔ የሚሆንበት መንገድ እየታየኝ መጣ... አሲሳይ ቤተኛ አይደለሁ የአዚን ደካማ ጎን አወኩት... ልጅ! አዎ ልጅ ትፈልጋለች እሷን ለማሳመን ብዙ አስቸካሪ አልነበረችም! "አዚ ልጅ እንደምትፈልጊ አውቃለሁ... ከዚህ በላይ ደግሞ ሲስ ልጅ ምን ያክል እንደሚጠላ አውቃለሁ! አስቢው ሳይፈልግ ብትወልጂለት እራሱ ልጅሽ ምን አይነት ሲኦል ውስጥ ሊያድግ እንደሚችል! እኔም ልጅ መውለድ እፈልጋለሁ ግን ሲሳይ ሴት የምተዋወቅበትን ጊዜኳን አልሰጥህ አለኝ! ሁሉም ቦታ እንደጭራው እንድከተለው ይፈልጋል... አሁን ያወራሁሽን አስቢበትና ቀጣይ ዋና ሀሳቤን እነግርሻለሁ..." ብዬ ማሳሰቢያ ቢጤ አእምሮዋ ውጥ ጣል አደረኩ... በቀጣዩ ቀን "አብረን እንጥፋ?" አለችኝ! "ከዛስ? ከሲሳይ የባሰ ድህነት የሚባል ሲኦል ውስጥ ልጃችን ይደግ?" አልኳት "አስጨነከኝኮ አብርሽ? እሺ ምንድነው ያንተ ሀሳብ?" አለችኝ ስጠብቀው የነበረው ይሄንኑ ነበር! "የሲሳይን ሀብት በሙሉ መውሰድ!" አልኳት ማንም እንደሌለ ባውቅም ለምን እንደሆነ እጃ ወደሷ ጠጋ ብዬና ድምፄን ቀነስ አድርጌ! "እንዴት?" "አዚ እኔ ሲሳይን አውቀዋለሁ ደደብ ቢጤ ነው.. እኔ ነኝ እስካሁንም ሀብቱን ያተረፍኩለት! ነገሮችን አገናዝቦ መገመት አይችልም... ስለዚህ እሱን ማስወገድ በጣም ቀላል ነው!" "ማስወገድ!" ደንገጥ ብላ "አማራጭ አለን? አዚ ከዚህ የተሻለ ነገር የለንም እናድርገው" አልኳት ብዙም አላቅማማችም መዳኒቱን ተቀበለችኝ... ስለሲሳይ መጥፋት ማንም ግድ እንደማይሰጠው አውቃለሁ.. በጨዋታ መሀል ለሚነሳው ስሙ ደግሞ ወደውጭ ሄዶኮ ተመቸው መሰል! ማለት በቂ ነው የዛን ያክል ነው ከሰው ልብ ውስጥ የሌለው!
